es
Feedback
አቡ ሱሀይል

አቡ ሱሀይል

Ir al canal en Telegram

ﺑِﺴْﻢِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦِ ﺍﻟﺮَّﺣِﻴﻢِ "ﺍﻗْﺮَﺃْ ﺑِﺎﺳْﻢِ ﺭَﺑِّﻚَ ﺍﻟَّﺬِﻱ ﺧَﻠَﻖَ" "አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታ ስም" አል ዐለቅ ምእራፍ/1 በዚህ ገፅ ላይ የተለያዩ ኢስላማዊ መልእክቶችና፣በተለያየ ዘርፍ የሚሰጡ ት/ቶችን በድምፅና በቪዲዮ ያገኙበታል።

Mostrar más
3 043
Suscriptores
-124 horas
+257 días
+8330 días
Archivo de publicaciones

☞እምነት ፍፁም የሆነ እርግጠኝነት ነው!! ☞እምነት ተስፋ በማይሰጡ ሁኔታዎች ወቅት ብሩህ ተስፋን ማንገብ ነው! ☞እምነት በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ብርሃንን የሚያመጣ ጌታ እንዳለህ ማሰብ ነው! ☞እምነት ማለት ልክ እንደ ሰዪዳችን ﷺ ማን ነው ከኔ የሚያድንህ ብሎ ለጠየቃቸው ጠላት አላህ ማለት መቻል ነው!!! ☞እምነት ማለት ልክ እንደ ነቢዩላህ ዩኑስ በሶስት ጨለማዎች ውስጥ ሁኖ አላህን ተስፋ ማድረግ ነው! ☞እምነት ማለት ልክ እንደ ነቢዩላህ ኢብራሂም እሳት ውስጥ እየገቡ አላህ በቂዬ ነው ምን ያምር መጠጊያ ነው ብሎ በሱ ብቻ መመካት ነው! ☞እምነት ማለት ልክ እንደ ነቢዩላህ ሙሳ ከበስተፊታቸው ሰፊ ባህር ከበስተኋላቸው የጠላት መንጋ ከቧቸው ጌታዬ ከኔ ጋር ነው ብሎ ልብን ማፅናት ነው! ====== ባጠቃላይ ትክክለኛ አማኝ ማለት አላህ እንደገለፀው በሚታየው ሳይሆን በማይታየው የአላህ ሀይል ማመን ነው!!!! አማኝ እምነቱ የሚበጠረው በፈተናዎች ወንፊት ነው!!! ___

photo content
+1

የዓሹራእ ቀን ቤተሰብንና ሚስኪኖችን በወጪ ማንበሽበሽና ማስፋፋት በዐሹራ ቀን በቤተሰብና በዘመዶች ላይ ማስፋፋትና ማንበሽበሽ ነቢየዊ ሱና ነው። ይህ ተግባር በሐዲስ ሊቃውንት ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ፣ በታላላቅ የሐዲስ ሊቃውንት (ሑፋዝ) የተጠናከረ እና በየአገራቱ በሚገኙ የፊቅህ ሊቃውንት ተግባራዊ የተደረገ ነው። 1. ከዐብዱላህ እንደተዘገበው ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ عن عبد الله بن مسعود رضي الله عنه، عن النبي ﷺ قال: «مَنْ وَسَّعَ عَلَى عِيَالِهِ يَوْمَ عَاشُورَاءَ، وَسَّعَ اللهُ عَلَيْهِ سَائِرَ سَنَتِهِ» ከዐብደላህ (ኢብኑ መስዑድ) እንደተዘገበው ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «በዓሹራእ ቀን በቤተሰቡ ላይ ያስፋፋ (ያንበሸበሸ) ሰው፣ አላህ በቀረው የዓመቱ ክፍል በሙሉ (በሲሳይና በበረከት) ያሰፋለታል።» ​ይህ ሐዲስ በበርካታ የሐዲስ ሊቃውንት ተዘግቧል፦ ​ኢብኑ አቢዱንያ በ«አል-ነፈቃ አላ አል-ዒያል» መጽሐፋቸው ላይ። ​ጠበራኒ በ«አል-ሙዕጀም አል-ከቢር» ላይ። ​አል-በይሃቂ በ«ሹዐቡል ኢማን» ላይ። 2. የሐዲስ ሊቃውንት ምልከታ፡ አል-ሀይሰሚ በ«መጅሙዕ አል-ዘዋኢድ» ላይ እንደገለጹት፤ ይህን ሐዲስ ጠበራኒ በ«አል-አውሰጥ» ዘግበውታል። በዘገባው ሰንሰለት ውስጥ ሙሐመድ ቢን ኢስማኢል አል-ጃዕፈሪ የተባለ ሰው አለ። አቡ ሐቲም ስለ እሱ ሲናገሩ "ሐዲሱ ሙንከር (ደካማ) ነው" ብለውታል። ነገር ግን – ተላቁ ሰሓቢይ ጃቢር (ረ.ዐ) ይህንን ተመልክተው "ሞክረነው እውነት ሆኖ አግኝተነዋል" ብለዋል። – ሱፍያን ቢን ዑየይናም በበኩላቸው "ሃምሳ ወይም ስልሳ ዓመት ያህል ሞክረነዋል" በማለት የቀኑን በረከት መስክረዋል። 3. የፊቅህ ሊቃውንት አስተያየት (መዝሀቦች)፦ ¹ _ አል-ሷዊ (ማሊኪይ): በ«ሸርህ አል-ሰጚር» መጽሐፋቸው ላይ በዓሹራእ ቀን በቤተሰብና በዘመዶች ላይ ማስፋፋትና ማንበሽበሽ የተወደደ (ሙስተሐብ) መሆኑን ገልጸዋል። ² _ ሱለይማን አል-ጀመል (ሻፊዒይ): በ«ፈትህ አል-ወሃብ» ማብራሪያቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦ "በዓሹራእ ቀን በቤተሰብና በዘመዶች ላይ ማስፋፋት፣ ለድሆችና ለችግረኞች ምጽዋት መስጠት ይወደዳል። ነገር ግን ከችሎታ በላይ (ያለ ጫና) መሆን አለበት። ምንም ነገር ማግኘት ካልቻለ ግን መልካም ስነ-ምግባሩን ያስፋ ፣ ከበደልም ይቆጠብ።" ³ _ አል-በሁቲ (ሐንበሊይ):** በ«ሸርሕ ሙንተሃ አል-ኢራዳት» ላይ በዐሹራእ ቀን በቤተሰብ ላይ ማስፋፋት እንደሚገባ ይናገራሉ። ⁴ _ ኢብኑ ዓቢዲን (ሐነፊይ): በ«ረድ አል-ሙሕታር» መጽሐፋቸው ላይ፣ ታላቁ ሊቅ አል-ሱዩጢ በ«አል-ዱረር» ላይ እንደገለጹት ይህ የልግስና (ማንበሽበሽ) ሐዲስ የተረጋገጠ (ሰሂህ) ነው። በመሆኑም በሐዲሱ የመጣውን በረከት በማሰብ ቢደረግ ምንም ችግር የለውም። ማጠቃለያ፡ በአሹራ ቀን ቤተሰብንና አቅመ ደካሞችን በችሎታ መጠን ማንበሽበሽና ማስፋፋት የተወደደ ነው። አቅም የሌለው ሰው ደግሞ በምግብ ብቻ ሳይሆን በመልካም ስነ-ምግባር በማስደሰትና ከበደል በመቆጠብ የበረከቱ ተካፋይ መሆን ይችላል።

هدية_الصغراء_بتصحيح_حديث_التوسعة_على_العيال_في_عاشوراء.pdf5.99 KB

photo content

📍የዓሹራእ ቀን፡ የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም በዓሹራእ ቀን ለቤተሰብ ለየት ባለ መልኩ ሰፋ አድርጎ ማውጣት፣ ማንበሽበሽና እነሱን ማስደሰት፣ እንዲሁም ቀኑን መጾም በአራቱም የፊቅህ መዝሐቦች ሊቃውንት ስምምነት የተወደደ (ሙስተሐብ) ሱና ነው። ይህ የደስታ መገለጫ ነው እንጂ የሐዘን ምልክት፣ የለቅሶ ወይም የሐዘን መድረክ አይደለም። የዓሹራእ ቀን የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም! የነቢዩ (ﷺ) ፈለግ በስሜት የሚነቃነቅ ወይም በሐዘን የሚፈርስ አይደለም። ነቢዩን (ﷺ) የሚያስደስታቸው ነገር ቤተሰባቸውንም ያስደስታቸዋል፤ እንዲያውም እነርሱ የእርሳቸውን ሱና በመጠበቅና ሕያው በማድረግ ረገድ ከማንም በላይ ተገቢዎችና ከፍተኛ ትኩረት ሰጪዎች ናቸው። በሰይዳችን ኢማም ሑሰይን (ረዐ) ላይ የደረሰው ታላቅ በደልና አስከፊ ወንጀል፣ በእያንዳንዱ እውነተኛ አማኝ ልብ ውስጥ ጥልቅ ሐዘን የፈጠረ ነው። ይህ ሐዘንም በህይወት እስካለ ድረስ ከልቡ አይለይም። የሰይዳችን ሑሰይንን መገደል ያላሳዘነውና በደረሰበት መከራ ልቡ ያልተነካ ሰው፣ ልቡ የታመመ፣ ድርቀት ያለበትና ሊሰወር የማይችል የጥላቻ በሽታ ያደረበት ነው። ይሁን እንጂ ይህ እውነተኛ ሐዘን እንደ ቋሚ መፈክር መወሰድ የለበትም፤ እንዲሁም እንደ አንዳንድ አንጃዎችአ በየዓመቱ የሚታደስ የሐዘን ስርዓት ሊሆን አይገባውም። ሃይማኖታችን ደስታን የምናድስበት እንጂ ለቅሶንና ዋይታን የምናከርርበት አይደለም። በሸሪዓ የተፈቀደው ሐዘን ቦታው ልብ እንጂ ውጫዊ መድረኮች አይደሉም። መገለጫውም ክብር እንጂ ሁከትና ግርግር አይደለም ። ሰዪዱና አል-ሑሰይንን በእውነት የወደደ ሰው የአያቱን (የነቢዩን ﷺ) ሱና ይጠብቃል። እውነተኛ የመከራ መፅናኛና የልብ መድኃኒትም ያለው በዚህ ውስጥ ነው። 👉 የዓሹራእ ቀን፡ የደስታ እንጂ የሐዘን ቀን አይደለም። 👉 ዓሹራእ፡ በለጋስነት የምንታደስበት፣ በሱና የምንጽናናበት ቀን። 👉 የዓሹራእ እውነት፦ ከሐዘን ግርግር ይልቅ በሱና መጽናናት።

1: የዓሹራእ ቀን መቼ ነው? የዓሹራእ ቀን የሙሐረም ወር 10 ኛው ቀን ነው [አን-ነወዊይ፡ ሸርህ ሰሒህ ሙስሊም፣ 8/18]። እሱም (ሙሐረም) የሂጅራ ዓመት መጀመሪያ ወር ሲሆን፣ ታላቅ ትሩፋትና ቀዳማይ ክብር አለው። ጾሙም በነቢያት (عليهم السلام) ዘንድ የታወቀ ነበር። ነቢዩላህ ኑህ እና ነቢዩላህ ሙሳ (عليهما السلام) አላህን ለማመስገን ሲሉ ጾመውታል። [ኢብን ረጀብ አል-ሐንበሊ፣ ለጣኢፍ አል-መዓሪፍ፣ ገጽ 55]። 2: የዓሹራእ ቀን የመጾም ትሩፋት ስለ ዓሹራእ ቀን ጾም ትሩፋት ከነቢዩ ﷺ የተላለፉ ሐዲሶች አሉ። ከእነሱም ውስጥ፡- «إِنِّي أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ تَعَالَى أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ»، «ያለፈውን ዓመት ወንጀል እንደሚያስምር በአላህ ዘንድ እጠብቃለሁ (ተስፋ አደርጋለው)» የሚለው ይገኝበታል። ከአቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) በተላለፈው ሐዲስም እንዲህ ብለዋል፦ "مَرَّ النَّبِيُّ ﷺ بِأُنَاسٍ مِنَ الْيَهُودِ قَدْ صَامُوا يَوْمَ عَاشُورَاءَ، فَقَالَ: «مَا هَذَا مِنَ الصَّوْمِ؟» قَالُوا: "هَذَا الْيَوْمُ الَّذِي نَجَّى اللهُ مُوسَى وَبَنِي إِسْرَائِيلَ مِنَ الْغَرَقِ، وَغَرِقَ فِيهِ فِرْعَوْنُ"، فَقَالَ النَّبِيُّ ﷺ: «أَنَا أَحَقُّ بِمُوسَى، وَأَحَقُّ بِصَوْمِ هَذَا الْيَوْمِ»، فَصَامَهُ وَأَمَرَ أَصْحَابَهُ بِالصَّوْمِ" "ነቢዩ ﷺ መዲና ሲመጡ አይሁዶች የዓሹራን ቀን እየፆሙ አገኟቸው ። 『ይህ ምንድን ነው የምትጾሙት?』 ብለውም ጠየቁ። እነሱም፡ 『ይህ አላህ ሙሳንና የእስራኤልን ልጆች ከስጥመት ያዳነበት፣ ፈርዖንን ደግሞ ያሰጠመበት ቀን ነው』 አሉ። ነቢዩም ﷺ፡ 『እኔ ለሙሳ ከእናንተ ይበልጥ የቀረብኩኝና ይህን ቀንም በመጾምም ይበልጥ የተገባሁ ነኝ』 አሉ፤ ጾሙትም፣ ባልደረቦቻቸውም እንዲጾሙት አዘዙ" [አህመድ፡ አል-ሙስነድ፣ 8717]። 3 : የታሱዓእ (9ኛውን) ቀን ከዓሹራእ ጋር የመጾም ትሩፋት የነቢዩ (ﷺ) ሱና ይህንን ቀን (አሹራን) ለመጾም ሶስት ደረጃዎችን ተቀምጧል። እጅግ የተሟላው፣ በላጩ እና አይሁዶችን ከመመሳሰል የራቀው ከእሱ በፊት አንድ ቀን እና ከእሱ በኋላ አንድ ቀን መጾም ነው። የጾሙ ደረጃዎች ሶስት ናቸው፦ የመጀመሪያውና የተሟላው ፡- ከእሱ በፊት አንድ ቀን እና ከእሱ በኋላ አንድ ቀን መጾም። ሁለተኛው፡- ዘጠነኛውንና አስረኛውን መጾም (አብዛኛዎቹ ሐዲሶች በዚህ ላይ ያተኩራሉ)። ሶስተኛው፡ አስረኛውን ቀን ብቻ ነጥሎ መጾም። ይህን ካልቻለ ግን ዘጠነኛውን ቀን ብቻ ነጥሎ መጾም ባይበረታታም ችግር የለውም። ኢማም አህመድ ከኢብን አባስ (ረ.ዐ) ባስተላለፉት ዘገባ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «صُومُوا يَوْمَ عَاشُورَاءَ، وَخَالِفُوا الْيَهُودَ، صُومُوا يَوْمًا قَبْلَهُ وَيَوْمًا بَعْدَهُ» «የአሹራን ቀን ጹሙ፣ አይሁዶችንም ተቃረኑ፤ ከእሱ በፊት አንድ ቀን እና ከእሱ በኋላ አንድ ቀን ጹሙ» [አህመድ ኢብን ሀንበል፣ አል-ሙስነድ (2154) ስለዚህ የተሟላው ከአህለል ኪታብ ለመለየት ዘጠነኛውንና አስረኛውን አብሮ መጾም ነው። ቀጥሎ አስረኛውን ብቻ መጾም ነው። አንዳንዶቹ ሊቃውንት፡ 9ኛውን፣ 10ኛውን እና 11ኛውን ቀን መጾም ነው ይላሉ። 10ኛውን ብቻ የጾመም ሰው፣ ይህንን የሚከለክል ማስረጃ ስለሌለ ምንም ችግር የለበትም። ኢማም ሙስሊም ከኢብን አባስ (ረ.ዐ) ባስተላለፉት፡ የአላህ መልክተኛ ﷺ የአሹራን ቀን በጾሙና እንዲጾም ባዘዙ ጊዜ፣ ሰሃባዎች፡ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህ ቀን እኮ አይሁዶችና ክርስቲያኖች የሚያከብሩት ቀን ነው" አሉ። ነቢዩም ﷺ፡ «لَئِنْ بَقِيتُ إِلَى قَابِلٍ لَأَصُومَنَّ التَّاسِعَ»، «እስከሚቀጥለው ዓመት በህይወት ከቆየሁ፣ ዘጠነኛውን ቀን (ጨምሬ) እጾማለሁ» አሉ። ነገር ግን የሚቀጥለው ዓመት ከመምጣቱ በፊት የአላህ መልክተኛ ﷺ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ [ሰሒህ ሙስሊም 1134]። 4: ማጠቃለያ የዓሹራእ ቀን የሙሃረም ወር አስረኛው ቀን ነው። ነቢዩ ﷺ ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ከመስጠም መዳናቸውን ምክንያት በማድረግ አላህን ለማመስገን ጾመውታል። እሱን መጾም ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል የሚያሰርዝ የጠበቀ ሱና (ሱና ሙአከዳ) ነው። አይሁዶችን ለመቃረን ሲባል ከ10ኛው ቀን ጋር 9 ኛውን ቀን አብሮ መጾም የተወደደ ነው።

photo content

photo content
+3

መኻሪጅ ወሲፋት.pdf12.50 MB

[አንድ ባሪያ በእስትንፋሱ ልክ በሳቸው ﷺ ላይ ሶለዋት ቢያወርድ ሀቃቸውን ፈፅሞ አይወጣም] __ 🖊ኢብኑል ቀዩም(ረ.ዐ) 📚ጀላኡል አፍሃም–344 ===== በውዱ አፍቃሪያችሁ ሳትፈጠሩ በናፋቃችሁ በ
[አንድ ባሪያ በእስትንፋሱ ልክ በሳቸው ﷺ ላይ ሶለዋት ቢያወርድ ሀቃቸውን ፈፅሞ አይወጣም] __ 🖊ኢብኑል ቀዩም(ረ.ዐ) 📚ጀላኡል አፍሃም–344 ===== በውዱ አፍቃሪያችሁ ሳትፈጠሩ በናፋቃችሁ በዚያ ቀን በሚያማልዳችሁ ውዱ የውዱ ወዳጅ ተወዳጅ ላይ ሶለዋትን አብዙ! ======= አላሁምመ ሶልሊ ዐላ ሰይዪዲና ሙሀመድﷺ አላሁምመ ሶልሊ ዐላ ሰይዪዲና ሙሀመድﷺ አላሁምመ ሶልሊ ዐላ ሰይዪዲና ሙሀመድﷺ አላሁምመ ሶልሊ ዐላ ሰይዪዲና ሙሀመድﷺ አላሁምመ ሶልሊ ዐላ ሰይዪዲና ሙሀመድﷺ =_=__= 💚💚💚 ⇩⇩⇩ t.me/hamidabuhamid

photo content

እንኳን ለ1448 ኛው የሒጅራ አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! ይህ አዲስ ዓመት የሰላም፣ የጤና እና የደስታ ዓመት እንዲሆንልን እመኛለሁ።

የአመቱ መጀመሪያ ላይ የሚከናወን ፡– ሙሀረም ታላቅ ወር ነው። ትሩፋቱም እጅግ ብዙ ነው። ከረመዳን በኋላ ለጾም በላጩ ወር እርሱ ነው። በመቀጠል ረጀብ፣ ከዚያም ዘልሒጃ፣ ከዚያም ዘልቀዕዳ፣ በመቀጠልም ሸዕባን ይከተላሉ። ስለዚህ ሙሀረም ከተከበሩት ወራት (አል-አሽሁር አል-ሁሩም) ሁሉ በላጩ ነው። ተከታታይ ከሆኑት ሶስት የተከበሩ ወራትም ሶስተኛው ሲሆን፣ አራተኛው ደግሞ ረጀብ ነው። ሐፊዝ ኢብኑ ሀጀር (አላህ ይዘንላቸው) እንደዘገቡት፡ ከሐፍሳ (ረዲየላሁ አንሃ) በተላለፈው መሰረት፣ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- "የዙልሒጃን የመጨረሻ ቀን እና የሙሀረምን የመጀመሪያ ቀን የጾመ ሰው፣ አላህ የሃምሳ (50) ዓመት ወንጀል ማበሻ ያደርግለታል። የሙሀረም አንድ ቀን መጾም የሰላሳ ቀን ጾም ምንዳ አለው" ። በሙሀረም ወር የሚደረገው ዱዓ መሰረት ያለው፣ በረከቱም የተሟላ ነው። ከነሱም መሀከል ይህን አግኝቻለው ፡ ከማንኛውም ዱዓ በፊት መጀመሪያ የሚከተለውን ያነባል፡ አያተል ኩርሲን ከቢስሚላህ ጋር በየአንቀጹ መጀመሪያ እያለ ሶስት መቶ ስልሳ (360) ጊዜ ያነባል። ሲጨርስም የሚከተለውን ዱዓእ ይላል ​«اللَّهُمَّ يَا مُحَوِّلَ الْأَحْوَالِ؛ حَوِّلْ حَالِي إِلَى أَحْسَنِ الْأَحْوَالِ، بِحَوْلِكَ وَقُوَّتِكَ يَا عَزِيزُ يَا مُتَعَالِ، وَصَلَّى اللَّهُ تَعَالَى عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِهِ وَصَحْبِهِ وَسَلَّمَ» "አሏሁመ ያ ሙሐውዊለል አሕዋል፣ ሐውዊል ሐሊ ኢላ አሕሰኒል አሕዋል፣ ቢሐውሊከ ወቁወቲከ ያ ዓዚዙ ያ ሙተዓል፣ ወሰለሏሁ ተዓላ ዓላ ሰይዪዲና ሙሐመዲን ወዓላ ኣሊሂ ወሰህቢሂ ወሰለም።" ትርጉም:– ​«አላህ ሆይ! ሁኔታዎችን ቀያሪ የሆንክ ጌታ ሆይ! ​ሁኔታዬን ወደ ወደ ተሻሉ ሁኔታዎች ለውጥልኝ፤ ​በኃይልህ እና በጉልበትህ ይሁንብህ፣ አንተ አሸናፊ፣ አንተ የላቅክ ጌታ ሆይ! ​አላህም በአለቃችን በሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው እና በባልደረቦቻቸው ላይ እዝነትን እና ሰላምን ያውርድ።» የዚህ ዱዓ ፋይዳ ትልቅ ነው። ሼኻችን ሰዪድ አህመድ ቢን ዘይኒ ደህላን (አላህ ይዘንላቸው) በ"ሰፊናቸው" ላይ ከፃፉት እንደወሰድኩት ይህን አስፍረዋል ፡- " በሙሐረም መጀመሪያ ቀን አያተል ኩርሲን ሶስት መቶ ስልሳ (360) ጊዜ በየአንቀጹ መጀመሪያ ቢስሚላህ እያሉ መቅራት፣ በዚያ አመት ውስጥ ከተረገመው ሰይጣን የሚከላከል ምሽግ ነው። በውስጡም ቁጥር የሌለው ፋይዳ አለው። ሼኻችን ሼኽ ዑስማን አል-ዲምያጢ (አላህ ይዘንላቸው) ይህንን አዘውትረው ያደርጉት ነበር፣ ከዱዓው በፊት መደረግ አለበት። ብለዋል ሼኽ ሐሰን አል-ዐደዊም በ"አንፈሓቱል ነበዊያህ ፊል ፈዳኢሊል ዓሹሪያህ" ላይ፣ ሼኽ አቡል የሰር አል-ቀጣን የሼኽ ከሪም አል-ኸልወቲ ተማሪ፣ ከሼኽ ዲሚርዳሽ እንደዘገቡት፡- "በሙሐረም መጀመሪያ ቀን አያተል ኩርሲን ሶስት መቶ ስልሳ (360) ጊዜ የቀራ ሰው፣ በሁሉም መጀመሪያ ላይ ቢስሚላህ ብሎ፣ ሲጨርስም የሚከተለውን ይላል ፡- ​«اللَّهُمَّ يَا مُحَوِّلَ الْأَحْوَالِ؛ حَوِّلْ حَالِي إِلَى أَحْسَنِ الْأَحْوَالِ، بِحَوْلِكَ وَقُوَّتِكَ يَا عَزِيزُ يَا مُتَعَالِ، وَصَلَّى اللَّهُ تَعَالَى عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِهِ وَصَحْبِهِ وَسَلَّمَ» "አሏሁመ ያ ሙሐውዊለል አሕዋል፣ ሐውዊል ሐሊ ኢላ አሕሰኒል አሕዋል፣ ቢሐውሊከ ወቁወቲከ ያ ዓዚዙ ያ ሙተዓል፣ ወሰለሏሁ ተዓላ ዓላ ሰይዪዲና ሙሐመዲን ወዓላ ኣሊሂ ወሰህቢሂ ወሰለም።" ትርጉም:– ​«አላህ ሆይ! ሁኔታዎችን ቀያሪ የሆንክ ጌታ ሆይ! ​ሁኔታዬን ወደ ወደ ተሻሉ ሁኔታዎች ለውጥልኝ፤ ​በኃይልህ እና በጉልበትህ ይሁንብህ፣ አንተ አሸናፊ፣ አንተ የላቅክ ጌታ ሆይ! ​አላህም በአለቃችን በሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው እና በባልደረቦቻቸው ላይ እዝነትን እና ሰላምን ያውርድ።» ይህንን ያደረገ ሰው በአመቱ ውስጥ ከሚጠላው ነገር ሁሉ ይጠበቃል ።

ይህ ታላቅ ዱዓእ ኢማም አል-ሐቢብ አብደላህ ቢን ዓለዊ አል-ሐዳድ (አላህ ይዘንላቸውና) ለተማሪያቸው ለሰዪድ አህመድ ቢን ዘይን አል-ሐበሺ (አላህ ይዘንላቸው) ያስተማሩት ነው። *بسم الله الرحمن الرحيم* *الحمد لله رب العالمين، اللهم صل علـــى* *سيدنا محمد وعلى آله وصحبه وســـــلم* *اللهم يا من ختمــت النبــــوة والرسالــــة* *بسيدنا محمد صلى الله عليه وآله وسلم،* *أختم يومي بخير، وشهري بخير، وسنتي* *بخير، وعمري بخير، إنك على كل شـــيء* *قدير،وصلى الله على سيدنا محمد وعلى* *آله وصحبه وسلم* (ትርጉም) በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው። አላህ በአለቃችን በሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው እና በባልደረቦቻቸው ላይ እዝነት እና ሰላምታ አውርድ። አላህ ሆይ! አንተ ነቢይነትን እና መልእክተኝነትን በአለቃችን በሙሐመድ (ሶለላሁ ዓለይሂ ወዓሊሂ ወሰለም) የደመደምክ አምላክ ሆይ! ቀኔን በመልካም ጨርስልኝ፤ ወሬንም በመልካም፣ ዓመቴንም በመልካም እና ዕድሜዬን በመልከም ጨርስልኝ። አንተ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነህ። አላህ በአለቃችን በሙሐመድ በቤተሰቦቻቸው እና በባልደረቦቻቸው ላይ እዝነትና ሰላምታን ያውርድ።

photo content