en
Feedback
አቡ ሱሀይል

አቡ ሱሀይል

Open in Telegram

ﺑِﺴْﻢِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦِ ﺍﻟﺮَّﺣِﻴﻢِ "ﺍﻗْﺮَﺃْ ﺑِﺎﺳْﻢِ ﺭَﺑِّﻚَ ﺍﻟَّﺬِﻱ ﺧَﻠَﻖَ" "አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታ ስም" አል ዐለቅ ምእራፍ/1 በዚህ ገፅ ላይ የተለያዩ ኢስላማዊ መልእክቶችና፣በተለያየ ዘርፍ የሚሰጡ ት/ቶችን በድምፅና በቪዲዮ ያገኙበታል።

Show more
3 227
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+13230 days
Posts Archive
اللهم صَلِّ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ كَمَا أَمَرْتَنَا أَنْ نُصَلِّيَ عَلَيهِ. اللهم صَلِّ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ كَمَا هُوَ أَهْلُهُ. اللهم صَلِّ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ كَمَا تُحِبُّ وَتَرْضَى لَهُ. اللهم صَلِّ عَلَى رُوحِ سَیِّدِنَا مُحَمَّدٍ فِي الأَرْوَاحِ. اللهم صَلِّ عَلَى جَسَدِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ فِي الأَجْسَادِ. اللهم صَلِّ عَلَى قبر سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ فِي القُبُورِ. اللهم بَلِّغْ رُوحَ سَیِّدِنَا مُحَمَّدٍ مِنِّي تَحِيَّةً وَسَلاًما.

ለሚቀጥለዉ ጉዞ ምዝገባ ጀምረናል ✅ ሙሉ የዑምራ ፓኬጅ በፈለጉት አማራጭ ከዙመራና ዳና ትራቭል ኤጀንት *3ቀን በመዲና 7ቀን በመካ ያለ ኡስታዝ 129 ሺ ብር *3ቀን በመዲና 7ቀን በመካ ከኡስታዞች ጋር 149 ሺ ብር *5ቀን በመዲና 6ቀን በመካ ከ ታላላቅ ኡስታዞች ጋር 179 ሺ ብር *VIP 5ቀን በመዲና 6ቀን በመካ አንድ ሩም ለብቻ 195 ሺ ብር *3ቀን በመዲና 5 በመካ 2 ቀን በጅዳ ሆቴሎች መካ አንጁም ሆቴል በመዲና ሂልተን ሆቴል 229 ሺ ብር በፈለጉት አማራጭ ይደዉሉ 0913961132 0912894173 ዙመራና ዳና ትራቭል ኤጀንት የ ሁልጊዜ ምርጫ

በሃይማኖት ስም የልጆቻችሁን አእምሮ በጽንፈኝነት፣ ድንበር ባለፈ አክራሪነት፣ ሙስሊሞችን በማክፈር ( በክህደት ፍረጃ)፣ በቂም፣ በጥላቻና እና በባህሪ ብልሹነት እየሞሉላቹ ነው ። ይህም በስነ-ምግባራ
በሃይማኖት ስም የልጆቻችሁን አእምሮ በጽንፈኝነት፣ ድንበር ባለፈ አክራሪነት፣ ሙስሊሞችን በማክፈር ( በክህደት ፍረጃ)፣ በቂም፣ በጥላቻና እና በባህሪ ብልሹነት እየሞሉላቹ ነው ። ይህም በስነ-ምግባራቸው ላይ በግልጽ ተንፀባርቋል ። በፍጹም ተጠንቀቁ! አላህ ሆይ! መልእክቴን አድርሻለሁ፤ አላህ ሆይ! ምስክር ሁን ።" ✒️ ሸይኽ ዐብዱል ፈታሕ ቁደይሽ

📌 ሰው ላይ ከመፍረድ እንቆጠብ ማንም ፍፁም አይደለም፦ ሁላችንም የራሳችን ድክመት፣ስህተት እና ፍፁም ያልሆኑ ጎኖች አሉን።እኛ ራሳችን ሁልጊዜ ትክክል መሆን እንደማንችል ሁሉ፣ ሌሎችም ሰዎች ላይ ፍፁምነትን መጠበቅ ለብስጭትና ለቅሬታ ይዳርጋል። የሰዎችን ድክመት በቅንነት እና በርህራሄ መመልከት የሚጀምረው ይህንን እውነት በመቀበል ነው። ​ሰው ላይ ከመፍረድ መቆጠብ፦ የአንድን ሰው ሙሉ ታሪክ፣ የሚያልፍበትን ፈተና፣ የውስጥ ጭንቀቱንና የደረሰበትን ስቃይ ሳናውቅ በውጫዊ ድርጊቱ ብቻ መፍረድ ይጎዳል። በፍርድ ምትክ ለመረዳት መሞከር፣ ማዳመጥ እና ድልድይ መሆን ለራሳችንም ቢሆን የአእምሮ ሰላም ይሰጠናል። መልካም ምሽት

መውላና ሸይኽ ሙሐመድ ኢልያስ አል-ከንዳህላዊ (ረሒመሁልላህ) እንዲህ ይላሉ :- ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዑለሞችን በአራት ኒያዎች (ዓላማዎች) ሊያገለግላቸው (ሊኻድማቸው) ይገባል፦ 1. ከእስልምና ወንድማ
መውላና ሸይኽ ሙሐመድ ኢልያስ አል-ከንዳህላዊ (ረሒመሁልላህ) እንዲህ ይላሉ :- ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዑለሞችን በአራት ኒያዎች (ዓላማዎች) ሊያገለግላቸው (ሊኻድማቸው) ይገባል፦ 1. ከእስልምና ወንድማማችነት አንጻር፦ አንድ ሙስሊም ሙስሊም ወንድሙን ለአላህ ብሎ መጠየቁ (መጎብኘቱ) ትልቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው። በዚያም ሰባ ሺህ መላእክት ያጅቡታል፤ ምሕረትም ይለምኑለታል። የአንድ ተራ ሙስሊም ጉብኝት ይህን ያህል ትልቅ ደረጃና ምንዳ ካለው፣ የዓሊም (የሊቅ) ደረጃ ደግሞ ከሱ የላቀና፣ ዚያራውም ይበልጥ የጠበቀ ነው። 2. ልቦቻቸውና አካላቶቻቸው ነቢያዊ ﷺ ዕውቀቶችን የተሸከሙ በመሆናቸው፦ ከዚህ አንጻር እነዚህ ዑለማዎች ማክበር፣ ማላቅና ማገልገል ከማንኛውም ሰው በላይ ተገቢ ይሆናል። 3. ስለ ሃይማኖታችን ጉዳዮች ኃላፊዎች (ተጠያቂዎች) በመሆናቸው። 4. ፍላጎቶቻቸውንና ችግሮቻቸውን ለመከታተል፦ ምክንያቱም ሰዎች የዑለማዎችን ዓለማዊ ክፍተቶች ከተከታተሉላቸውና የሀብት ባልተቤቶች ካሟሉላቸው፣ ዑለማዎች በነዚያ ነገሮች ላይ ጊዜያቸውን ከመጨረስ ይድናሉ። በዚህም ያ የሚያተርፉት ጊዜ በሐይማኖትና በዕውቀት አገልግሎት ላይ ይውላል ። በዚህም ባለሀብቶች (የዑለማዎችን ፍላጎት በማሟላታቸው) ዑለማዎች ከሚያገኙት ምንዳ ጋር እኩል የሆነ ምንዳ ያገኛሉ።”

photo content

photo content
+9

Repost from Tofik Bahiru
🔺የሰዎችን ምስጢር መከታተል — ክህደት ነው! 🔺ሳያስፈቅዱ የስልክ ጥሪዎችን መቅረጽ — ክህደት ነው። 🔺ሰዎችን ሳያውቁ ፎቶ ማንሳት — ክህደት ነው። 🔺ከሰው ጋር ሆነው ሳለ በስልክ ሲያወሩ ድምፁን በስፒከር መክፈት — ክህደት ነው። 🔺ልጆችን በማታለል ስለ ቤተሰቦቻቸው እንዲናገሩ ማድረግ — ክህደት ነው። : የአላህ ነቢይ [ﷺ] የፈተና ዘመናትን ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል፦ «حين لا يأمنُ الجليسُ جليسَه» «አብሮ የተቀመጠ ሰው ከአብሮ ተቀማጩ ደህንነት ማጣት የሚጀምርበት ጊዜ ነው።…» : ስለዚህ የስብሰባዎችንና የውይይትን ሐቅ እንጠብቅ፤ ከክህደትም እንጠንቀቅ። አንድ ሰው በምስጢርና በአማና ጉዳዩን ሊነግርህ ይችላል፤ ሌላ ሰው እንዲሰማበት አይሻም። አንተም ምስጢር ነው ብለህ ለሌላ ሰው ከመንገር ተቆጠብ። አደራን መጠበቅ የእምነት ክፍል ነው!

​« መልካም ነገር ቢሆን ኖሮ (ሰሓቦች) በቀደሙን ነበር ! በሚል ሰሓቦች ያላደረጉት ነገር ሁሉ እርም (ሐራም) ነው አይባልም ! ​ከብቁ ኢማሞችና ግንዛቤና አረዳድ አንዱን እንመልከት፡- <<<<<<<>>>>>>>> ሓፊዝ አል-ዘሀቢ ‘ሙዕጀም አል-ሹዩኽ አል-ከቢር’ በሚለው መጽሐፋቸው (1/73) ላይ እንዲህ ይላሉ ፡- ………………… ታዲያ ​«የተከበረውን (የነቢዩን ﷺ ) ቀብር መዳበስ » ሰሓቦች ለምን ይህንን አላደረጉም?! ከተባለ… እንዲህ በማለት ይመለሳል: – እነሱማ እርሳቸውን በሕይወት እያሉ አይተዋል፤ በእርሳቸው ተደስተዋል፤ እጃቸውንም ስመዋል። በውዱእ ውኃቸው ላይ ሊጣሉ ምንም አልቀራቸውም፤ በታላቁ የሐጅ ቀን ( 10 ዙልሒጃ ) ፅዱ ጠጉራቸውን ተካፍለዋል። በሚተፉ ጊዜ ምራቃቸው የአንዱ ሰው እጅ ላይ እንጂ አይወድቅም ነበር፤ ከዛም በሱ ፊቱን ያብስ ነበር። እኛ ግን እንዲህ ያለው ታላቅ ዕድል ስላላገኘን፣ በክብር፣ ለመያዝና/ለማቀፍ፣ ለመዳሰስ እና ለመሳም ወደ ቀብራቸው ተጠጋን ። ታቢዒዩ ሳቢት አል-ቡናኒ ያደረገውን አታይምን? የአነስ ኢብኑ ማሊክን እጅ ይስም ነበር፤ በፊቱም ላይ ያደርገውና ፡- «የአላህ መልእክተኛን ﷺ እጅ የነካች እጅ!» ይል ነበር። እነዚህን ነገሮች ለማድረግ አንድን ሙስሊም የሚቀሰቅሰው ለነቢዩ ﷺ ያለው ከባድ ፍቅር እንጂ ሌላ አይደለም። ምክንያቱም እርሱ አላህንና መልእክተኛውን ከነፍሱ፣ ከልጁ፣ ከሰው ሁሉ፣ ከሃብቱ፣ ከጀነትና ከሁረል ዒን በላይ አብልጦ እንዲወድ ታዟል ። እንደውም ከሙዕሚኖች መካከል አቡ በክርንና ዑመርን ከነፍሳቸው በላይ የሚወዱ ፍጥረታት አሉ። ጁንዳር እንደነገረን፡- በበቃዕ ተራራ ላይ በነበረበት ወቅት አንድ ሰው አቡ በክርን ሲሰድብ ሰማ፤ ሰይፉንም መዞ አንገቱን ቆረጠው ። እራሱን ወይም አባቱን ሲሰድብ ቢሰማ ኖሮ ደሙን የተፈቀደ ባላደረገው ነበር። ሶሃቦች ለነቢዩ ﷺ ካላቸው ከባድ ፍቅር የተነሳ፡- « ልንሰግድልህ አይገባም ወይ?» ማለታቸውን አልሰማህምን? እርሳቸውም፡- «አይሆንም» አሉ። ፈቃድ ቢሰጣቸው ኖሮ የዩሱፍ (ዐ.ሰ) ወንድሞች ለዩሱፍ እንደሰገዱት- ለአምልኮ ሳይሆን– የማላቅና የክብር ስግደት ያደርጉለት ነበር ። እንዲሁም አንድ ሙስሊም ነቢዩን ﷺ ለማክበርና ለማላቅ ብሎ ቀብራቸው ገር የሚያደርገው ሱጁድ በፍጹም ከኢስላም መንገድ አያስወጣውም (ካፊር አያደርገውም)፤ ይልቁንም ሐራም የሰራ ወንጀለኛ/አመጸኛ ይሆናል። ይህ የተከለከለ መሆኑ ይታወቅ። ወደ ቀብር መስገድም ልክ እንዲሁ ነው ።» -- ኢማም ሸምሱዲን አል-ዘሀቢ (ረሒመሁላህ) [ معجم الشيوخ الكبير للذهبي ,1/73]

تنبيه الأنام في بيان علو مقام نبينا محمد عليه أفضل الصلاة وأزكى السلام @MuhammedNessim

دلائل_الخيرات_طبعة_فاخره_جدا_.pdf6.50 MB

#ደላኢለል_ኸይራት** «ደላኢለል ኸይራት» ተራ ኪታብ አይደለም፤ ይልቁንም በሁሉም ዘመናት፣ በየትኛውም የሕይወት ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ሰዎች ሁሉ የሚሆን ድንቅና ወሳኝ መጽሐፍ ነው። ከቅዱስ ቁርኣን ቀጥሎ ስንት ጊዜ እንደታተመ፣ በተለያዩ የጠሪቃና የተርቢያ ማእከሎች ስንት አንባቢዎች በዜማ እንደቃኙት በቁጥር የማይታወቅ ብቸኛው የዓረብኛ መጽሐፍ ሳይሆን አይቀርም። አንዳንድ ተመራማሪዎች ከቅዱስ ቁርኣን ቀጥሎ በኢስላሙ ዓለም ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት በማግኘት፣ በስፋት በመሰራጨትና በመቀራት ሁለተኛው መጽሐፍ አድርገው ይቆጥሩታል። ቀደምትም ሆኑ የዘመኑ ሸይኾችና ሙሪዶቻቸው ትልቅ ትኩረት ሰጥተውታል፤ አድናቆታቸውን ገልጸውለታል፣ ማብራሪያዎችን ፅፈውለታል፣ እንዲሁም በየሳምንቱ አንዴ አንብቦ ለመጨረስ እንዲመች በሰባት ክፍሎች ከፍለውታል። ይህን የተባረከ «ደላኢለል ኸይራት» አጥብቆ መያዝ፣ ለማንበብ መጓጓትና እንደ ሰውየው አቅምና ፍላጎት በሳምንት፣ በቀን ወይም በሌሊት የዘወትር ተግባር (ዊርድ) ማድረግ ትልቅ የችግር መውጫ በር ነው፤ እንዲሁም ፀጋና በረከቶችን፣ ደስታና ፍስሐን ለመሳብ አስተማማኝ ድልድይ ነው። ምክንያቱም ረሱለላህ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡ “አንድ ጉዳይ የጠናበት ሰው በእኔ ላይ ሶለዋት ማውረድን ያብዛ፤ እሷ ጭንቀቶችን፣ ሀዘኖችንና መከራዎችን ታስወግዳለች፤ ሲሳይን ታበዛለች፣ ፍላጎቶችንም ታሟላለች።” በዚክር መጅሊሶችና፣ በሚታደመው ሰው ላይ ደስታና ፍስሐ ሲያካባቸው ብዙ ጊዜ እንመለከታለን። በሰይዳችን ሙሐመድ ﷺ ላይ ሶለዋትና ሰላም ማውረድን በሚያበዙ ሰዎች ላይ ደግሞ ጸጋዎችና ልዩ መለኮታዊ ስጦታዎቹ ይጨምራሉ። ይህም ከታላቁ ሶሓቢይ ሰዪዱና ኡበይ ኢብኑ ከዕብ (رضي الله) ዘንድ የተረጋገጠው ሶሒሕ ሐዲሥ የሚያመላክተው ነው ። «የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሆይ! በእርሶ ላይ ሶለዋት ማውረድ እወድዳለሁ፤ ከዱዓዬ ላይ ለእርሶ ምን ያህሉን ላድርግ ?» አሏቸው። እርሳቸውም፦ “የፈለግከውን ያህል” አሉ። «ሩብ ያህሉን?» አላቸው። እርሳቸውም፦ “የፈለግከውን ያህል፣ ብትጨምር ግን ይበልጥ መልካም ነው” አሉ። «ግማሹን?» አላቸው። እርሳቸውም፦ “የፈለግከውን ያህል፣ ብትጨምር ግን ይበልጥ መልካም ነው” አሉ። «ሁለት ሦስተኛውን?» አላቸው። እርሳቸውም፦ “የፈለግከውን ያህል፣ ብትጨምር ግን ይበልጥ መልካም ነው” አሉ። «ዱዓዬን በሙሉ በእርሶ ላይ ሰለዋት ብቻ ማውረድ ላድርገው?» አላቸው። እርሳቸውም፦ “እንዲያ ካደረግክ ጭንቅህ ይወገድልሃል፤ ወንጀልህም ይማርልሃል” አሉት። ከዚህ በመነሳት በሰይዳችንና የዓይናችን ማረፊያ በሆኑት በነቢያችን ሙሐመድ ﷺ ላይ ሶለዋትና ሰላም ማውረድን የሚያበዙ ሰዎችን የማይለያቸው የውስጥ እርካታ፣ ደስታ፣ ፍስሐና ሰኪና ምስጢሩ ምን እንደሆነ መረዳት እንችላለን።

photo content

photo content

photo content

photo content

​የ'ደላኢሉል ኸይራት'ን ሶላዋቶች በጥልቀት ካስተዋልክ፤ በሙሐመዳዊ ብርሃናት ውስጥ ለረዥም ጊዜ የተመላለሰ ልብ መንፈሳዊ ስጦታዎችና ፍሰቶች መሆናቸውን በእርግጠኝነት ትረዳለህ ።
​የ'ደላኢሉል ኸይራት'ን ሶላዋቶች በጥልቀት ካስተዋልክ፤ በሙሐመዳዊ ብርሃናት ውስጥ ለረዥም ጊዜ የተመላለሰ ልብ መንፈሳዊ ስጦታዎችና ፍሰቶች መሆናቸውን በእርግጠኝነት ትረዳለህ ።

#ለይለቱል መውሊድ #በለጯ ሌሊት ____ ሰዪዳችን ﷺ የተወለዱባት ሌሊት ከለይለተል ቀድር በላጭ ሌሊት ናት:– የውልደታቸው ክስተት የተከወነው በሌሊሉ ክ/ጊዜ ነው። እና የትኛቸው ነው በደረጃ የሚልቀው? የሚል ጥያቄ ካነሳህ! መልሱ ይኸውልህ የውልደታቸው ሌሊት ከመወሰኛዪቷ ሌሊት ከ3 ምልከታ አንፃር በላጭ ነች ። 1:የውልደታቸው ሌሊት የተገለጡበት(ብቅ ያሉበት)ሌሊት ሲሆን፣ ለይለተል ቀድር ግን ለሳቸው የተሰጠች ሌሊት ነች። የተከበረው አካል ማንነት እንዲገለጥባት በማድረግ የተላቀው ሌሊት ለተላቀው አካል እንደ ስጦታ ከተቸረው ሌሊት ይበልጣል። ይህ ምንም ተቃርኖ የለበትም። በዚህ አንፃር ለይለተል መውሊድ በላጭ ነው። 2:ለይለተል ቀድር በውስጧ መላአክቶች በመገለጣቸው ስትከበር፣ ለይለተል ቀድር ደግሞ በሳቸው መገለጥ ተልቃለች። ለይለተል ቀድር ከተላቀችበት አካል በላይ ለይለተል መውሊድ የተላቀችበቱ በላጭ ነው። ስለዚህ በጠንካራውና በተመራጩ አቋም ለይለቱል መውሊድ በላጭ ነው። 3:ለይለተል ቀድር ስጦታ የተቸረባት ለነቢያችን ኡመት ከሆነ፣ ለይለተል መውሊድ ደግሞ ለተቀረው ፍጡር ባጠቃላይ ስጦታ የተበረከተባት ሌሊት ነች። አላህ ለአለማት እዝነት አድርጎ የላካቸው ነቢይ ናቸው። ስጦታነታቸው ሁሉንም ፍጡር አጠቃልሏል። ስለዚህ የለይለቱል መውሊድ ጥቅም ጠቀሜታ ሰፋ ያለ ስለሚሆን እሱ በላጭ ነው። ____ ኢማም አል ሓፊዝ አል ቁስጠላኒ(رحمة الله عليه) المواهب اللدنية بالمنح المحمدية =====____====== ታላቁ የሐነፊይ መዝሀብ ሊቅ ኢማም አቡ ጀዕፈር አጥ ጠሓዊይ(رحمة الله عليه)ከተወሰኑ የሻፊዒይ ሊቃውንቶች አንስተው፣ከሌሊቶች ሁላ በላጭ ብለው እንደሚከተለው አስፍረዋል 1:ሰዪዳችን ﷺ የተወለዱባት ሌሊት 2:ከዛ ለይለቱል ቀድር 3:ከዛ የኢስራእና ሚዕራጅ ጉዞ የተከሰተባት 4:ከዛ የዐረፋ ሌሊት 5:ከዛ የጂሙዐህ ሌሊት 6:ከዛ የሸዕባን ወር አጋማሽ ሌሊት 7:ከዛ የዒድ ለይል ነው። __ حاشية ابن عابدين رحمه الله ======_======= ኢማም አዝ’ዘርቃኒይ(رحمة الله عليه) በ"አል መዋሂብ"ኪታብ ትንታኔያቸው ላይ ውልደታቸው የተከሰተው በቀኑ ክፍለ ጊዜ ውስጥ ነው ካልን፣ በላጩ የውልደታቸው ቀን ነው ወይስ የተላኩበት ቀን ነው? ቅርቡ ብይን (ሸይኻችን እንዳሉት)የውልደታቸው ቀን አላህ ለአለማት ውለታ የዋለበት በመሆኑ በላጩ እሱ ነው። የሱ መገኘት መላካቸውን በውስጡ ይዟል። መገኘት መሰረት ሲሆን መላክ ደግሞ በሱ ላይ መጪ(ተከሳች) ነው፤ለዛ ውልደታቸው መሰረት ስለሆነ የሱን በላጭነት ያስፈርዳል … " __//////___ اللهم صل وسلم على سيدنا وحبيبنا وشفيعنا محمدﷺ