es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 369 suscriptores, ocupando la posición 1 753 en la categoría Transporte y el puesto 2 530 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 369 suscriptores.

Según los últimos datos del 20 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 129, y en las últimas 24 horas de 8, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 38.47%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.24% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 143 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 037 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 21 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 369
Suscriptores
+824 horas
+697 días
+12930 días
Archivo de publicaciones
ኢትዮጵያን ከኤርትራ የአሰብ ወደብ ጋር የሚያስተሳስረው የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ የመንግድ ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ተጀመረ። በዚሁ መርሃ ግብር ግንባታው የተጠናቀቀው የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ _ኤሊዳር _በልሆ የሲሚንቶ ኮንክሪት መንገድም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። የተጠናቀቀውን መረቀው የሚሰራውን ያስጀመሩት የትራንስፖርት ሚንስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሀጂ አወል አርባ፣ የትራንስፖርት ሚንስቴር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ እንዲሁም ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የስራ ሀላፊዎች በታደሙበት ነው። የፕሮጀክቱ መገንባት የአሰብ ወደብ መዳረሻ የሆነው የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ መንገድ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለሚኖረው የንግድ ትስስር መጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ አለው ብለዋል ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ። ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽን የሚያበረክት መንገድ ከመሆኑም በላይ ማህበራዊ መስተጋብሩን የሚያዋህድ ነውም ብለዋል ። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ በበኩላቸው መንግስት በክልሉ ብሎም በሀገራችን ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በመመደብ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ በተሻለ ጥራትና ብቃት እያካሄደ በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። በተለይም በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያን ከተቀረው አለም ጋር ለሚኖራት የወጩ ገቢ ንግድ ተጨማሪ የአሰብን እና የታጁራ ወደብን ለመጠቀም የሚያስችላትን እድል መፍጠር የተቻለበት ታሪካዊ እለት ነው ሲሉም ገልጸዋል። አቶ አወል የመንገድ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ በተለይም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ችግር እንዳያጋጥም ጥብቅ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በበኩላቸው የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ ፕሮጀክት 71.65 ኪ.ሜትር እርዝመት ያለውና በመንግሥት በተመደበ 2 ነጥብ 08 ቢሊዮን ብር በአስፋልት እና በሲሚንቶ ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። ይህ እውን እንዲሆን የመንገድ ፕሮጀክቱ በውሉ መሰረት በ3 ዓመት ከ6 ወር ውስጥ ለማጠናቀቅ የባለስልጣኑ መ/ቤት አስፈላጊውን ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል ። ዛሬ የተመረቀውን የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ _ኤሊዳር _በልሆ የሲሚንቶ ኮንክሪት መንገድን የገነባው የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ነው። የተቋሙ ሀላፊ ኢንጂነር ደቦ ቱንካ ይህ ለግንባታ እጅግ አስቸጋሪ ሞቃታማ ቦታ ላይ የተገነባው እና በሀገራችን የመንገድ ምህንድስና ሙያ በአይነትም ሆነ በቴክኖሎጂ ትልቅ የእውቀት ሽግግር የተደረገበት እንደ ተቋምም ተጨማሪ አቅም የገነባንበት ነው ብለዋል። የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ ዲዛይና ግንባታ ፕሮጀክት የሚገነባው ሻንዶንግ ሊኪኖ ግሩፕ በተሰኘ የቻይና አለማቀፍ ድርጅት ነው። የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ስሜክ ኢንተርናሽናል እንዲሁም ቫሊዩ ኢንጅነሪንግ በንዑስ ተቋራጭነት ይሳተፋሉ፡፡ መንገዱን በጥራት ገንብቶ በተባለው ጊዜ ለማስረከብም የተቋራጩ የስራ ሀላፊ ተወካይ ቃል ገብተዋል ። #### ስለ ፕሮጀክቶቹ ተጨማሪ መረጃ #### ስራው የተጀመረው መንገድ ካለው 71.65 ኪ.ሜትር ውስጥ ከፕሮጀክቱ መጀመሪያ ከሜሎዶኒ መገንጠያ እስከ 12.5 ኪ .ሜትር ድረስ በሲሚንቶ ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ነው፡፡ የተቀረው ከኪሜ 12 .5 እስከ ፕሮጀክቱ ማብቂያ ቡሬ ድረስ የሚዘልቀው መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ይሰራል ። የመንገዱ ስፋት ትከሻን ጨምሮ በከተማ 19 ሜትር እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር ስፋተና ደረጃውን ጠብቆ ይግነባል ፡፡ ወደ አሰብ ወደብ የሚዘልቀው የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ መንገድ ሲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ የተሻለ የወጪ ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ መሳለጥ አይነተኛ ሚናውን ይጫወታል፡፡ በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለአመታት ተቋርጦ የነበረውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ዳግም በመጀመሩ መስመሩን ለሚጠቀሙ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ 78 ኪ.ሜ የሚረዝመው የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ የሲሚንቶ ኮንክሪት መንገድ አዲሱን የታጁራ ወደብ በአማራጭነት ለመጠቀም የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር በነባሩ ጅቡቲ ወደብ ይፈጠር የነበረውን የትራንስፖርት ጫና እና መጨናነቅ እንደሚያቃልለው ይጠበቃል። መንገዱን ለመገንባት ከ2.4 ቢሊዮን ብር በላይ የጠየቀ ሲሆን የመንግስት ልማት ድርጅት በሆነው በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ተገንብቷል። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድርና ከሲም አማካሪ መሃንዲስ በጥምረት ተሳትፈውበታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም የመንገድ ግንባታውን ለማካሄድ የዋለውን ወጪ ሙሉ በሙሉ ሸፍኗል፡፡ አካባቢው ባለው ከፍተኛ ሙቀት ሳቢያ ግንባታው በሲሚንቶ ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ሲሆን ይህም የአየር ጸባዩን የመቋቋም እና የግልጋሎት ዘመኑ ከፍ እንዲል ያደርጋል ።

የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ የመንገድ ገጽታ
+5
የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ የመንገድ ገጽታ

የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ መንገድ

ኢትዮጵያን ከኤርትራ የአሰብ ወደብ ጋር የሚያስተሳስረው የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ የመንግድ ግንባታ ፕሮጀክት ሊገነባ ነው። በነገው ዕለትም ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት ፕሮጀክቱን በይፋ የማስጀመር መርሃ ግብር ያካሂዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። በዕለቱ በሚኖረው መርሃ -ግብርም ግንባታው የተጠናቀቀው የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ የሲሚንቶ ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትም ይመረቃል። የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ መንገድ ሲጠናቀቅ ወደ አሰብ ወደብ የሚዘልቅ መንገድ እንደመሆኑ ለኢትዮጵያ የተሻለ የወጪ ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ መሳለጥ አይነተኛ ሚናውን ይጫወታል፡፡ 71.65 ኪ. ሜ የሚረዝመውን ይህን ፕሮጀክት በብር 2,085,985,162.6 በሆነ ወጪ ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን የሚያከናውነው ሻንዶንግ ሊኪኖ ግሩፕ የተባለ የወጭ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የግንባታውን የማማከርና የቁጥጥር ስራ ደግሞ ስሜክ ኢንተርናሽናል እንዲሁም ቫሊዩ ኢንጅነሪንግ በንዑስ ተቋራጭነት ይሳተፋል ። ለፕሮጀክቱ ግንባታ ማስፈጸሚያ ወጪም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ በአገልግሎት ሳቢያ የተጎዳ የአስፋልት መንገድና ከ6 ሜትር ያልበለጠ ስፋት የነበረውን በቀጣይ ከተሞች ላይ 19 ሜትር እንዲሁም በገጠር ደግሞ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 1ዐ ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ የሚገነባ ይሆናል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለአመታት ተቋርጦ የነበረውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ዳግም በመጀመሩ መስመሩን ለሚጠቀሙ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በተያያዘ ዜናም 78 ኪ.ሜ የሚረዝመው የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ የሲሚንቶ ኮንክሪት መንገድ ግንባታው የተጠናቀቀ ሲሆን ፕሮጀክት በነገው ዕለትም በይፋ ይመረቃል። መንገዱን ለመገንባት ከ2.4 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታ ያካሄደው የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የተባለ የመንግስት ልማት ድርጅት ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድርና ከሲም አማካሪ መሃንዲስ በጥምረት ተሳትፈውበታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም የመንገድ ግንባታውን ለማካሄድ የዋለውን ወጪ ሙሉ በሙሉ ሸፍኖታል፡፡ አካባቢው ባለው ከፍተኛ ሙቀት ሳቢያ ግንባታው በሲሚንቶ ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ሲሆን ይህም የአየር ጸባዩን የመቋቋም እና የግልጋሎት ዘመኑ እንዲጨምር ያደርጋል ። የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ መንገድ መገንባት አዲሱን የታጁራ ወደብ በአማራጭነት ለመጠቀም የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር በነባሩ ጅቡቲ ወደብ ይፈጠር የነበረውን የትራንስፖርት ጫና እና መጨናነቅ እንደሚያቃልለው ይጠበቃል። ፕሮጀክቱ የአገሪቷ የወጪ ገቢ ንግድ የሚካሄድበት ኮሪደር እንደመሆኑ መስመሩን የሚጠቀሙ ብዙ ቁጥር ያላቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች ክብደት የመሸከም አቅም እንዲኖራቸው ታሳቢ ያደረገ ነው ፡፡

80 ኪሎሜትር የሚረዝመው የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አሰፓልት ንጥፍ ስራ ተሸጋገረ ። እስካሁን ባለው አፈጻጸም 26 ኪሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍሎች አስፓልት ለማልበስ እየተሰራ ነው። በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ ና የአፈር ሙሌት ፤ የቤዝ ኮርስ ስራ ፤ የአስፋልት እና ፤ የድልድይ ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ ነው። በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት የኦሮሚያ ክልልን ከአጎራባች የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ጋር የሚያገናኝ ወሳኝ ፐሮጀክት ነው፡፡ ከቡታጂራ አዲስ አበባ ከሚወስደው አውራ መንገድ ጋርም በአቋራጭ ያስተሳስራል ፡፡ የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በጀት ነው፡፡ ግንባታውን የሚያካሂደው ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ የተሰኘ ዓለም ዓቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠርና በማማከር አየሰራ ያለው ደግሞ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነው፡፡ 3 ወረዳዎችን አቋርጦ ኬላ ከተማ የሚደርሰው ይህ መንገድ በአካባቢው በሚገኙ በገብስ ፤ ስንዴ ፤ ባቄላና አተር ምርቶቹ የታወቀ በመሆኑ ምርቶቹን በፍጥነት ወደ ማእከላዊ ገበያ እንዲደርስ ስለሚያስችል ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ያጎለብታል፡፡ የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ አመት ለማጠናቀቅ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ ነው።

የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+6
የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

80 ኪሎሜትር የሚረዝመው የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አሰፓልት ንጥፍ ስራ ተሸጋገረ ። እስካሁን ባለው አፈጻጸም 26 ኪሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍ
+4
80 ኪሎሜትር የሚረዝመው የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አሰፓልት ንጥፍ ስራ ተሸጋገረ ። እስካሁን ባለው አፈጻጸም 26 ኪሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍሎች አስፓልት ለማልበስ እየተሰራ ነው። በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ ና የአፈር ሙሌት ፤ የቤዝ ኮርስ ስራ ፤ የአስፋልት እና ፤ የድልድይ ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ ነው። በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት የኦሮሚያ ክልልን ከአጎራባች የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ጋር የሚያገናኝ ወሳኝ ፐሮጀክት ነው፡፡ ከቡታጂራ አዲስ አበባ ከሚወስደው አውራ መንገድ ጋርም በአቋራጭ ያስተሳስራል ፡፡ የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በጀት ነው፡፡ ግንባታውን የሚያካሂደው ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ የተሰኘ ዓለም ዓቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠርና በማማከር አየሰራ ያለው ደግሞ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነው፡፡ 3 ወረዳዎችን አቋርጦ ኬላ ከተማ የሚደርሰው ይህ መንገድ በአካባቢው በሚገኙ በገብስ ፤ ስንዴ ፤ ባቄላና አተር ምርቶቹ የታወቀ በመሆኑ ምርቶቹን በፍጥነት ወደ ማእከላዊ ገበያ እንዲደርስ ስለሚያስችል ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ያጎለብታል፡፡ የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ አመት ለማጠናቀቅ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ ነው።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል!

የጊቤ ወንዝ - ጅማ መንገድ ከባድ ጥገና እንቅስቃሴ
+6
የጊቤ ወንዝ - ጅማ መንገድ ከባድ ጥገና እንቅስቃሴ

ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰትን በማስተናገድና በአገልግሎት ብዛት ለጉዳት የተዳረገው የጊቤ ወንዝ - ጅማ መንገድ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው። 167 ኪ.ሜትር የሚረዝመው የጊቤ ወንዝ - ጅማ መንገድ በኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በጅማ ዲስትሪክት ነው የከባድ ጥገና ስራውን ማከናወን የጀመረው። የዲስትሪክቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ደመቀ የጊቤ ወንዝ - ጅማ መንገድ ከሚሰጠው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አኳያ ከባድ ጥገና ማድረጉ ወሳኘ በመሆኑ ስራው መጀመሩን ተናግረዋል። በአሁን ወቅትም ከስልሳ ሚልዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት በራስ ሀይል የከባድ ጥገና ስራው በጥሩ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል። አጠቃላይ ጥገናው የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የአገልግሎት ጊዜው ዘላቂ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ብለዋል። በመንገድ ፕሮጀከቱ ውስጥ በእጅጉ የተጎዳውን የመንገድ ክፍል በቅድሚያ ጥገናውን በማከናወን የትራፊክ ፍሰቱን ምቹ እንዲሆን እየተደረገ ነው። የዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የመንገዱ ተጠቃሚ አሽከርካሪዎች በበኩላቸው በመንገዱ የጥገና ስራ መጀመር ደስተኞች መሆናቸውን በመግለጽ ለኢመባ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። ይህም አሁን ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነሱም ባሻገር በመንገዱ ብልሽት ሳቢያ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል ብለዋል። የጊቤ ወንዝ - ጅማ መንገድ የአዲስ አበባ - ጅማ- ቦንጋ ሚዛን የመንገድ አንዱ ክፍል ነው። በየአካባቢዎቹ የሚመረተውን ከፍተኛ የቡና ምርትን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን ወደ መሀል ከተማ በማድረስ አምራችና ሸማችን በሰፊው ተጠቃሚ ያደርጋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጎን ለጎን በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙትን ጉዳት የገጠማቸውን መንገዶች በራስ ሀይልና በኮንትራክትሮች የቀላልና የከባድ ጥገና እያካሄደ ነው ።

የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ
+4
የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ

የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ 74 ኪ .ሜ የመንገድ ፕሮጀክት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ነው ። ፕሮጀከቱ በአሁናዊ አፈጻጻሙ 17 ኪ.ሜ የሚሸፍን የአስፋልት ኮንክሪት ንጣፍ ስራንም አከናውኗል፡፡ የፕሮጀክቱ ቀሪ ክፍሎችንም በአሰፖልት ለማልበስ በትኩረት እየተሰራ ነው። ፕሮጀክቱ አሁን ላይ እስከ 30 ሜትር ከፍታ ያላቸው 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሜትር ኩብ የሚሆን የአፈር ቆረጣ ስራዎች እና የአፈር ጠረጋ እና ድልዳሎ እንዲሁም የድልድይ እና የውሀ ማፍሰሻ ቦዮችን የመገንባት ስራ በተመሳሳይ እየተከናወነ ነው፡፡ የሲዳማ እና የኦሮሚያ ክልሎችን በአቋራጭ የሚያስተሳስረው ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ ቀሪ የመንገዱን ክፍሎች አስፋልት የማልበስ ስራዎችን ለማካሄድ ይረዳ ዘንድ ከወዲሁ የመሬት ዝግጅት እና የጠጠር መፍጨት ስራዎች ተመቻችተዋል ። የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 68 ቢሊዮን ብር በጀት ነው። ግንባታውን የሚያካሂደው ቻይና ውይ ሊሚትድ የተባለ አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር የሚሳተፈው ሲቪል ወርክስ ኮንሰልትግ እንጂነርስ የተባለ አገር በቀል አማካሪ ድርጅት ነው፡፡ መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በቀጣይ በሀዋሳ አድርጎ ወደ ሞያሌ የሚሄደውን ዋና መንገድ ከሻሸመኔ ወደ ባሌ ጎባ ከሚወስደው ሌላ ዋና አውራ መንገድ ጋር በአቋራጭ ያስተሳስራል፡፡ ከዛም ባለፈ አካባቢው በከፍተኛ ደረጃ በቡና እና በፍራፍሬ ምርቱ የታወቀ በመሆኑ ምርቶቹን በፍጥነት ወደ ማእከላዊ ገበያ እንዲቀርብ ስለሚያስችል ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ያጎለብታል በአሁን ሰአት 73 ኪሎ ሜትሩን የጠጠር መንገድ በተሸከርካሪ ለመጓዝ ከግማሽ ቀናት በላይ ሲወስድ በክረምት ወቅት ደግሞ ግልጋሎት የሚሰጥ አልነበረም፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአንድ ሰአት ተኩል ጊዜ ውስጥ መጓዝ ስለሚያስችችል በከፍተኛ ደረጃ የትራንስፖርት ጊዜን እና ወጪን ይቀንሳል። በመንገዱ አስቸጋሪነት ሳቢያ መስመሩ ላይ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ባለመኖራቸው ነዋሪው የትራንስፖርት ግልጋሎት በአማራጭነት ይጠቀም የነበረው በሞተር ሳይክል ፣ በበቅሎ አልያም በእግር መጓዝ የነበረውን በቀጣይ በመፍታት በቂ የትራንስፖርት አማራጮችን ያስፋፋል፤ የዳዬ - ጭሪ - ናንሴቦ መንገድ ስራ የሚገኝበት አካባቢ ዝናባማ በመሆኑ በአመት ውስጥ አራት ደረቅ ወራትን ብቻ ነው ተቋራጩ ለመንገድ ግንባታ እየተጠቀመ ያለው በተጨማሪም መልክአ ምድራዊ አቀማመጡ ውሃ አዘል መሬት መሆኑ ተደጋጋሚ የመሬት መንሸራተት እና ናዳ ማስከተሉ የፕሮጀክቱ ተግዳሮቶች ናቸው። ይህን ተግዳሮት ከመቅረፍ አንጻር የግንባታ ስራ ተቋራጩ ባለው ደረቃማ ወቅት ቀሪ ስራዎችን በአፋጣኝ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ጊዜን በመመደብ ምሽትን ጨምሮ ግንባታ እያካሄደ ይገኛል።

88 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአንድሆዴ-አጋምሳ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ በያዝነው በጀት አመት መጨረሻ ድረስ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል ውስጥ 71 ኪ.ሜትሩ አስፋልት የማንጠፍ ስራው ሙሉ ለሙሉ ተከናውኗል ፡፡ ቀሪ የመንገዱን ክፍሎች ለማጠናቀቅም በትኩረት እየተሰራ ነው የመንገዱን ግንባታ በ 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ወጪ በማከናወን ላይ የሚገኘው ጄ.ኤም.ሲ(JMC ) የተባለው የሕንድ አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው ፕሮጀክቱን ለመገንባት የሚውለውን መዋዕለ-ነዋይ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት እና ከአለም ባንክ በተገኘ ብድር ነው፡፡ ለግንባታ አመቺነት ሲባል በሶስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚገነባው የነቀምት-ቡሬ የመንገድ ደረጃ የማሳደግ ስራ ፕሮጀክት አካል ነው። በዚህ የኮንትራት ሒደት የሥራ ተቋራጩ የመንገዱን ዲዛይን እና ግንባታ ካጠናቀቀ በኋላ የጥገናና እንክብካቤ ወይም የማስተዳደር ሥራውን እንዲያከናውን የሚያስገድደው የስምምነት አይነት ነው፡፡ በተጨማሪም የመንገድ ኔትወርኩን በወቅቱና ቀድሞ በመጠገን የአገልግሎት ጊዜውን የተራዘመ ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ይጠበቃል፡፡ በተያያዘ ዜናም የዚሁ የነቀምት - ቡሬ የመንገድ ፕሮጀክት ትስስር አካል የሆኑት ነቀምት-አንድሆዴ ክፍል አንድ ፤ እንዲሁም አጋምሳ-ቡሬ ክፍል ሶስት በአጠቃላይ 180 ኪ .ሜ መንገድ ግንባታ ስራ ከዚህ ቀድም ሲያከናውኑ የነበሩ ተቋራጮች በገቡት ውል መሰረት ስራውን ለማከናውን ባለመቻላቸው ውላቸው እንዲቋራጥ ተደርጎ አዲስ ጨረታ እንዲወጣ መደረጉ ይታወሳል፡፡ የጨረታ አሸናፊው የቻይናው ቾንግኪንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በአሁን ሰአት የግንባታ ስራ ጀምሯል፡፡ የነቀምት - ቡሬ የመንገድ ፕሮጀክት በምሥራቅ ወለጋ ዞን ከምትገኘው ነቀምቴ ከተማ ተነስቶ ደብረ ማርቆስ ባህር ዳር ዋና መንገድ ላይ ከምትገኘው ቡሬ ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ ነው፡፡ በመሆኑም የአገሪቱን የሰሜንና የምዕራብ ክፍሎች ደረጃውን በጠበቀ የመንገድ መሠረተ ልማት በአቋራጭ ከማገናኘት አንጻር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚያበረክት መንገድ ነው ፡፡ ፕሮጀከቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገድብ እንዲጠናቀቁ መላው ባለድርሻ አካላት የጎላ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ኢመባ ያሳስባል ።

42 ኪ. ሜትር የሚረዝመ የደብረብርሃን-አንኮበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። በቀጣይ ሶስት ወራት ውስጥም ወደ አስፋልት ንጣፍ ስራ ይሸጋገራል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የአፈር ሙሌትና፣ ድልዳሎ፣የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ የሰብ ቤዝ ስራ እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ማምረት ስራ እየተካሄደ ይገኛል። የደብረብርሃን-አንኮበር የመንገድ ፕሮጀክት ስራ ከ 1 .1 ቢልየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ሲሆን ወጪው በመንግስት የሚሸፈን ነው። ሀገር በቀሉ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ ግንባታውን እያከናወነው ይገኛል። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ/ማ እያካሄደው ይገኛል። የደብረብርሃን-አንኮበር መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረና የጎን ስፋቱ ከ 7 ሜትር ያልበለጠ ለትራንስፖርት ምልልስ አሰቸጋሪ የነበረ ነው። መስመሩ ከሚያሰተናገደው የተሸከርካሪ ብዛት፣ ማህበራዊና ኢኮኖማዊ ፋይዳ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ አድገት ጋር አልሞ በአስፋልት ደረጃ እንዲገነባ እየተደረገ ነው። ይኸው የመንገድ ፕሮጀክት የጎን ስፋት በዞን ከተማ ደብረብርሃን 30 ሜትር ፣በወረዳ አንኮበር 17 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር ሲሆን በገጠር 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተሰራ ነው። በተጨማሪም ግንባታው በውስጡ የመንገድ አካፋይ ፣ እግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ይሆናል ፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ አንድ ድልድይ እና የተለያዩ ፉካዎችና ከልቨርቶችን አካቷል። በአሁን ሰዓት ከደብረብርሃን - አንኮበር 42 ኪ. ሜትሩን መንገድ በተሸከርካሪ ለመጓዝ ከ 2፡00 ሰዓት በላይ የሚጠይቅ ሲሆን ግንባታው በአስፋልት ደረጃ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ጊዜን በአማካኝ ከግማሽ በላይ ያሳጥረዋል። አንኮበር ላይ የቀድሞ የአጼ ሚኒሊክ ቤተ-መንግስት እና የተለያዩ ገዳማት እንዲሁም በርካታ አብያተክርስቲያናት ስለሚገኙ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። በአካባቢው የሚገኘውን ከፍተኛ የሰብል ምርቶች ጤፍ ፣ ገብስ ፣ ስንዴ ፣ባቄላ በተጨማሪም የቀንድ ከብቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል። መስመሩ ከደብረብርሃን- አዋሽ- አርባ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል ። መንገዱ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት እንዲሆን አሁንም ያልተፈቱ የወሰን ማስከበር ችግሮች በመኖራቸው በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት፣ የክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ያሳስባል፡፡