es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 365 suscriptores, ocupando la posición 1 754 en la categoría Transporte y el puesto 2 531 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 365 suscriptores.

Según los últimos datos del 19 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 119, y en las últimas 24 horas de 19, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 40.59%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 423 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 060 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 20 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 361
Suscriptores
+1924 horas
+677 días
+11930 días
Archivo de publicaciones
የሁምቦ - ፋርቾ - አባያ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጸጸም ላይ ይገኛል ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ አካባቢ ኮንስትራክሽን ጽ / ቤት ከሚቆጣጠራቸው 11 የመንገድ ስራ ፕሮጀክቶች አንዱ ሲሆን በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኝቷል ። የ 25 . 3 ኪ .ሜ ርዝመት ያለው ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት የ 45 ከመቶ አፈጻጸም ላይ ደርሷል። በዚህም የዲዛይን የአፈር ቆረጣ ፣ ሰብ ቤዝ እንዲሁም የ7 ስላብ ካለቨርት ስራዎች ተከናውነዋል ፡፡ በቀጣይም የሁለት ድልድዮች የግንባታ ስራን ለማከናወን እየተሰራ ነው። የቤዝ ኮርስና አስፋልት ንጣፍ ስራዎችን ለመፈጸም የዝግጅት ስራዎች ተጀምረዋል። የግንባታ ፕሮጀክቱን ይበልጥ ለማፋጠን ከወሰን ማስከበር ጋር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትኩረት እየተሰራ ነው ፡፡ ፕሮጀክቱ ከትራንስፖርት ማሳለጥ ባሻገር የብላቴ ወንዝንና የአባያ ሐይቅን ተፈጥሯዊ ስጦታን በመጠቀም ሰፊ የልማት እርሻ ችሮታዎችን ይበልጥ እውን ለማድረግ ሀገራዊ ፍይዳው የጎላ ነው። ግንባታውን ሀገር በቀሉ ክሮስላንድ ኮንስተራክሽን የስራ ተቋራጭ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው ፡፡ መንገድ ፕሮጀክትን በአማካሪነት የያዘው ደግሞ አርትስ ቴክ ኮንሰልታንት ነው ፡፡ ከወላይታ አርባምንጭ የሚወስደውን ዋና መንገድ የሚገናኘው ይህ ፕሮጀክት ለግንባታው ስድስት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሚሊዮን ( 699 000 000 ) ብር ከኢትዮጵያ መንግስት ተመድቦለታል ፡፡

የደብረ ብርሃን አንኮበር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተሰራ ነው:: ደብረ ብርሃን ፣ መስከረም 27 ቀን2015 ዓ.ም (ኢመአ)፡- በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው የደብረ ብርሃን አንኮበር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው ይህ መንገድ በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ ላለፉት በርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ግን ከአገልግሎት ብዛት አኳያ በመጎዳቱ እና የቦታው ተፈጥሮአዊ አቀማመጥ በጠጠር ደረጃ ለነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ ባለመሆኑ ምክንያት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ በመንግስት ተወስኖ ጥቅምት 13 ቀን 2011 ዓ.ም ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በተገኙበት ግንባታው በይፋ ሊጀመር ችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት 42 ኪሎ ሜትር ከሚረዝመው አጠቃላይ የመንገድ ግንባታ ውስጥ 30 ኪሎ ሜትር አስፋልት የማንጠፍ ስራ ወይም ከአጠቃለይ ስራው ውስጥ የፕሮጀክቱ 72 በመቶው ስራ ተጠናቋል፡፡ ፕሮጀክቱን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው 1,623,194,217.85(አንድ ቢልዮን ስድስት መቶ ሃያ ሶስት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አራት ሺህ ሁለት መቶ አስራ ሰባት ብር ከሰማንያ አምስት ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራው ደግሞ በኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ አማካኝነት በመካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በቀበሌ 10 ሜትር ፣ በወረዳ ከተማ 17 ሜትር እንዲሁም በዞን ከተማ ደግሞ 30 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከዚህ ቀደም በአካባቢው የነበረው የፀጥታ ችግር ፣ የመሬት ናዳ እና በህብረተሰቡ ጥያቄ መሰረት የተካሄደው የዲዛይን ለውጥ በግንባታ ሂደቱ ላይ በተወሰነ ደረጃ መዘግየትን ፈጥሯል፡፡ ከዚህም ባሻገር ያለፈው የክረምት ወራት በግንባታ ሂደቱ ላይ ተጨማሪ ተፅዕኖ ፈጥሮ የነበረ ሲሆን ፣ አስተዳደር መስሪያ ቤቱ በቀጣይ የበጋ ወራቶች በፕሮጀክቱ ላይ የነበሩ ክፍተቶችን በአፋጣኝ በመቅረፍ ፕሮጀክቱን በተገቢው የጥራት ደረጃ በፍጥነት ለማጠናቀቅ ጥብቅ ክትትል እና ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ አንኮበር በ17ኛው መቶ ክፍለዘመን በሸዋው ነጋሲ በመርድ አዝማች አብዬ የተመሠረተችና በአልጋ ወራሹ መርድ አዝማች አምኀኢየሱስ የተስፋፋች የሸዋ ከተማ ስትሆን ከደብረብርሃን 42 ኪ.ሜ በምስራቃዊ አቅጣጫ የስምጥ ሸለቆ አፋፍ ላይ ትገኛለች። በአንኮበር ከተማ ውስጥ የተለያዩ ታሪካዊ ቅርሶችን በውስጡ የያዘው የአጼ ምኒሊክ ቤተመንግስት የሚገኝ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት የአካባቢው የቱሪስት መስህብነት እንዲጨምር ከማድረግ አንፃር የሚኖረው ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በማቃለል አርሶአደሮች ምርታቸውን በቀላሉ ወደ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ከአንኮበር-ዱለቻ-አዋሽ መንገድ ጋር የሚያስተሳስር በመሆኑ ከዚህ ቀድም ወደ አፋር ለመሄድ ይወስድ የነበረውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ ለማስቀረት እንደ አማራጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡

የሞርካ - ጊርቻ - ጬንቻ መንገድ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተደረገ አርባምንጭ፣ መስከረም 26/ 2015 ዓ.ም(ኢመአ)፡ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሶዶ አካባቢ የመንገድ ፕሮከክቶች ማስተባበሪያ ጽ / ቤት ስር ቁጥጥርና ክትትል ከሚደረግላቸው የመንገድ ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የሞርካ - ጊርቻ - ጬንቻ መንገድ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተደረገ፡፡ በጎብኝቱ ወቅት ከአፈፃፀም አኳያ የታዩ ክፍተቶችን በዝርዝር የተነሱ ሲሆን የተቋራጭ አቅም ውስንነት ፣ የግብአት አቅርቦት እና የመንገድ ወሰን ማስከበር ችግሮች ይገኙበታል ። ከጉብኝቱ በኋላ በተካሄደ ውይይት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር እንጂነር ሃብታሙ ተገኝ የወሰን ማስከበር ክፍያን ተንተርሶ ለተነሳው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ ገልጸው በቀጣይም የስራ ተቋራጩ Bei n Urban Construction Group Co. ( BUCG ) ግንባታውን በግዜ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ እና ሊሰመርባቸው የሚገባቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል ። የኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ም / ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ መንገድ ለአገር እድገት ያለውን ጠቀሜታ ለውይይት መድረኩ ገልፀው፣ ሥራው በከፍተኛ ትኩረት እንዲጠናቀቅ አሳስበዋል ። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ በበኩላቸው በዞኑ ውስጥ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣሉ ከሚባሉ መንገዶች አንዱ በሆነው በዚህ መስመር ላይ የነበራቸውን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል ። በተያያዘም የጋሞ ህዝብን በመወከል የአካባቢው ሽማግሌዎችም የውይይቱ አካል የነበሩ ሲሆን ይህ እጅግ ጠቃሚ የሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ማህበረሰቡን በማስተባበር ረገድ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልፀዋል ። የስራ ተቋራጩ የአፈር ቆረጣ ፣ ሰብ ቤዝ ፣ ሰብ ኮርስና የአስፋልት ንጣፍ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል ። ፕሮጀክቱ በታለመለት ጊዜ እንዲጠናቅቅ ተጨማሪ የሰው ሃይልና ግብአት መሟላት አስፈላጊ እንደሆነም አቅጣጫ ተቀምጧል ። የሶዶ አካባቢ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ / ቤት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአዲሱ መዋቅር መሠረት ከተቋቋሙ የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች አንዱ ነው፡፡

የጅግጅጋ-ገላልሼ-ደገሕመደው-ሰገግ አስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ። ጅግጅጋ፣ መስከረም 24/2015 ዓም (ኢመአ) ፡ በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ-ገላልሼ-ደገሕመደው-ሰገግ ሎት 2እና3 110 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ አስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ፡፡ በአሁኑ ወቅት 2 ኪሎ ሜትር ያህሉን አስፋልት ማልበስ የተቻለ ሲሆን፥ ከመንገዱ አጠቃላይ ግንባታም 41 በመቶው ተጠናቅቋል፡፡ ይህም በእቅዱ መሠረት እየተካሄደ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ፥ የፕሮጀክቱን ሎት ሁለት፥ በሚቀጥሉት አራት ወራት ውስጥ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግም በትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ በእሰከአሁኑ የግንባታ ሥራ፤ የአፈር ቆረጣ፣ ድልድይ ግንባታ፣ የግንባታ ግብአቶች ማምረትና ዝግጅት የውኃ መፋሰሻ ቱቦዎች ማምረት ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታውን፥ የፌደራል መንግስት በመደበው 1,828,264,182 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊዮን ኹለት መቶ ስልሳ አራት ሺህ) ብር ወጪ፣ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ሲ-ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እየሠራ ነው፡፡ በክልሉ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ የተፈጠረው የውኃ እጥረት በግንባታው ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ ለመቅረፍ በሥራ ተቋራጩ በኩል አስራ አንድ የውኃ ማጠራቀሚያ ኩሬዎች አጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ፡፡ ኩሬው ከግንባታው አልፎም የአካባቢውን ማኅበረሰብ እየጠቀመ ይገኛል፡፡ መንገዱ ሲጠናቀቅ፥ ቀድሞ ወደ ደገሕመደው ከተማ ለመሄድ፣ በደገሐቡር በኩል ይወስድ የነበረውን የ240 ኪ.ሜ ርቀት ወደ 195 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡ የፋፈን እና ደገሐቡር ዞኖችን በቅርበት በማገናኝት፥ በአካባቢው የሚገኙ አርብቶ-አደሮች እና በእንስሳት ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችንም ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ ፕሮጀክቱ ለአንድ ሺህ ያህል ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ የዚሁ ፕሮጀክት አካል የሆነው ሎት-1 ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ሎት-4 ደግሞ በግንባታ ላይ ይገኛል፡፡

አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ
+6
አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ

በባህርዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ በቀጣይ 3 ወራት ውስጥ የድልድዩ ዋነኛ አካል የሆነው (Grider) ሙሉ ለሙሉ ለመግጠም በትኩረት እየተሰራ ነው። የድልድዩን ዋና ዋና ስራዎች በእቅዱ መሰረት ለማከናወን አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ በመፍጠን ላይ ይገኛል። አጠቃላይ የግንባታ አፈፃፀሙ 76 በመቶ ደርሷል። በእስካሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ ከ760 ሜትር (Girder) ርዝማኔ ውስጥ (በሁለትም መስመር) 511 ሚትር የድልድይ (Grider) ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። በግንባታው ፕሮጀክት ላይ በዋነኛነት የድልድይ ተሸካሚ ምሰሶዎች (piers and Abutments) እንዲሁም ከመሬት በታች የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች (Piers piles, Abutment piles and ramp piles) ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል ። ለድልድዩ የሚያስፈልጉ 8 ቋሚ ተሸካሚ መሶሶዎች ( pylons/towers) ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል: ድልዲዩን ወጥሮ ለመያዝ ከሚያግዙ 72 (Stay cables) አምሳው የተጠናቀቀ ሲሆን የተቀሩትን በቅርብ ለመጨረስ እየተሰር ነው። በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 1.4 ቢሊዮን ብር ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ የተባለው ተቋራጭ ነው። የማማከር እና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ ቦቴክ ቦስፈረስ ኮንሰልቲንግ ከስታዲያ ኢንጅነሪንግ ጋራ በጣምራ እየሰሩት ይገኛሉ። አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልዲይ በባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው እየተገነባ ያለው። ይህ ዘመናዊ ድልድይ ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ጎን ለጎን ምቹ የሆነ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር ያደርጋል። በተጨማሪም ባህር-ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት እንድትላበስ ይረዳታል። ድልድዩ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በግራና በቀኝ በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ ይችላል፣ በተጨማሪም 5 ሜትር የእግረኛ መንገድ እንዲሁም የብስክሌት ተጠቃሚዎችን መስመር ባካተተ መልኩ ነው እየተገነባ የሚገኘው ፡፡

Call for Project Managers and Resident Engineers Training
Call for Project Managers and Resident Engineers Training

[Forwarded from Abrham Era] የጎዴ - ቀላፎ - ፌርፌር ሎት1 ጎዴ -ቀላፎ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ይገኛል፡፡ መስከረም 3 ቀን 2015 (ኢመአ)- በሶማሌ ክልል ሸበሌ ዞን ውስጥ የሚገኘው ይህ መንገድ በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ ላለፉት በርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ግን ከአገልግሎት ብዛት አኳያ በመጎዳቱ እና ለትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ ባለመሆኑ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ በመንግስት ተወስኖ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ግንባታው በይፋ ሊጀመር ችሏል፡፡ 94.8 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን ፕሮጀክት ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው 1,530,000,000.00(አንድ ቢልዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን ብር)ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ(China Railway Seventh Group Co. Ltd) የተባለ የቻይና አለም አቀፍ ድርጅት ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ ስታድያ የምህንድስና ሥራዎች አማካሪ ኃላ/የተ/ የግል ማህበር ከንዑስ አማካሪ ጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ኃላ/የተ/ የግል ማህበር ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የጠጠር መፍጫ ማሽን በመትከል ለግንባታ ግብዓትነት የሚውል ምርት የማምረት ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የአነስተኛ የውሃ መተላለፊያ ቱቦዎችና የድልድይ ግንባታዎች ስራዎች በመካሔድ ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ ከተማ 19 ሜትር እና በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጥራት ደረጃ እና የጊዜ ገደብ መስከረም 5 ቀን 2016 ዓ.ም ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደቱ ወቅት የታዩ ውስንነቶችን በመለየት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ ይገኛል፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የጎዴ እና ቀላፎ ከተሞችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ የሚያስተሳስር ከመሆኑም ባሻገር በአካባቢው ለሚገኙ ትንንሽ ከተሞች እድገትም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከዚህም ባሻገር በዚህ አካባቢ ፍየል ፣ ግመል ፣ ሽንኩርት እንዲሁም ሌሎች አትክልት እና ፍራፍሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ የሚገኙ በመሆናቸው አርሶ እና አርብቶ አደሮች ምርቶቻቸውን እና የቁም እንስሶቻቸውን ካለምንም ውጣ ውረድ በአፋጣኝ ወደ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ በተጨማሪም የጤና ፣ የትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል።

አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ----------------------------------------------------------------------------------- ጋምቤላ፣ ነሐሴ 30፣ 2014 (ኢመአ) በጋምቤላ ክልል ግንባታው እየተከናወነ ያለውና የጋምቤላ ክልልን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ከኦሮሚያ ክልሎች ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው (የጋምቤላ አቦቦ-ጎግ ዲማ) አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ፡፡ ሰማኒያ ሁለት ኪሜ ( 82ኪሜ) የሚረዝመው ይህ መንገድ በአሁኑ ወቅት የዲዛይን ስራን ጨምሮ የምንጣሮ ስራ፣የአፈር ጠረጋ፣ ድልዳሎ እና ሙሌት፣ ተጨማሪ የጠጠር መፍጫ ማሽነሪ ተከላ ስራዎች እየተከናወኑለት ይገኛል። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ NKH Construction Plc ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ በለስ ኮንሰልት Plc እየከወነ ይገኛል:: አጠቃላይ የግንባታ መዋለንዋይ ብር 1,574,746,965.24 ሲሆን የግንባታ ውጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረና ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ በመሆኑ ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት፣ አሽከርካሪዎችን ለጊዜ ወጪ እና ብክነት የዳረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ካለው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አንፃር መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ወደ ደቡብ ሱዳን ከሚወስደው ዋና አውራ ጎዳና (Trunk Road) ጋራ ያገናኘዋል፡፡ በተጨማሪም ዲማ ወረዳን ከጎግ ወረዳ ጋራ በማገናኘት ወደ ጋምቤላ የሚደረገውን ጉዞ የግዜና ገንዘብ ብክነት በእጥፍ ይቀንሰዋል። የመንገዱ መግንባት የኢሉአባቦር እና የሸካ ዞኖችን ከአኙዎክ ዞን ጋራ በቅርበት ያስተሳስራል። አካባቢው በርካታ ማዕድናት (ወርቅ) እና ሰፋፊ የእርሻ መሬት የሚገኝበት በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው። በመንገዱ ኮሪደርና በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የማር፥ ቡና፥ ቅመማቅመም እንዲሁም የሻይ ተክል ምርቶች በተገቢው ፍጥነት ወደ መሃል ገበያ ለማድረስ ያስችላል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ከማሳለጡም ባሻገር፣ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማሕበራዊ አገልግሎት ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል። ነባሩ መንገድ የጎን ስፋት ከ (3) ሶስት ሜትር የማይበልጥ ሲሆን አሁን እየተገነባ የሚገኘው በከተማ 17 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ያለው።

አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ----------------------------------------------------------------------------------- ጋምቤላ፣ ነሐሴ 30፣ 2014 (ኢመአ) በጋምቤላ ክልል ግንባታው እየተከናወነ ያለውና የጋምቤላ ክልልን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ከኦሮሚያ ክልሎች ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው (የጋምቤላ አቦቦ-ጎግ ዲማ) አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ፡፡ ሰማኒያ ሁለት ኪሜ ( 82ኪሜ) የሚረዝመው ይህ መንገድ በአሁኑ ወቅት የዲዛይን ስራን ጨምሮ የምንጣሮ ስራ፣የአፈር ጠረጋ፣ ድልዳሎ እና ሙሌት፣ ተጨማሪ የጠጠር መፍጫ ማሽነሪ ተከላ ስራዎች እየተከናወኑለት ይገኛል። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ NKH Construction Plc ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ በለስ ኮንሰልት Plc እየከወነ ይገኛል:: አጠቃላይ የግንባታ መዋለንዋይ ብር 1,574,746,965.24 ሲሆን የግንባታ ውጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረና ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ በመሆኑ ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት፣ አሽከርካሪዎችን ለጊዜ ወጪ እና ብክነት የዳረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ካለው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አንፃር መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ወደ ደቡብ ሱዳን ከሚወስደው ዋና አውራ ጎዳና (Trunk Road) ጋራ ያገናኘዋል፡፡ በተጨማሪም ዲማ ወረዳን ከጎግ ወረዳ ጋራ በማገናኘት ወደ ጋምቤላ የሚደረገውን ጉዞ የግዜና ገንዘብ ብክነት በእጥፍ ይቀንሰዋል። የመንገዱ መግንባት የኢሉአባቦር እና የሸካ ዞኖችን ከአኙዎክ ዞን ጋራ በቅርበት ያስተሳስራል። አካባቢው በርካታ ማዕድናት (ወርቅ) እና ሰፋፊ የእርሻ መሬት የሚገኝበት በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው። በመንገዱ ኮሪደርና በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የማር፥ ቡና፥ ቅመማቅመም እንዲሁም የሻይ ተክል ምርቶች በተገቢው ፍጥነት ወደ መሃል ገበያ ለማድረስ ያስችላል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ከማሳለጡም ባሻገር፣ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማሕበራዊ አገልግሎት ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል። ነባሩ መንገድ የጎን ስፋት ከ (3) ሶስት ሜትር የማይበልጥ ሲሆን አሁን እየተገነባ የሚገኘው በከተማ 17 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ያለው።

የጅግጅጋ ከተማ ባይፓስ(Bypass) መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ ነው። ጅግጅጋ ፣ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም. ፦ የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅ የሚያስቀረው የጅግጅጋ ባይፓስ (Bypass) መ
+4
የጅግጅጋ ከተማ ባይፓስ(Bypass) መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ ነው። ጅግጅጋ ፣ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም. ፦ የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅ የሚያስቀረው የጅግጅጋ ባይፓስ (Bypass) መንገድ ግንባታ ሥራ እየተካሄደ ነው። ሰባት (7) ኪ.ሜ የሚረዝመው የመንገድ ፕሮጀክቱ የፌደራል መንግስት በመደበው 672 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው። 'ባይፓስ' መንገድ አንድ ዋና ማሳለጫ ባላቸው ከተሞች በውጭ የሚገነባና ተሽከርካሪዎች ከተማ ውስጥ መግባት ሳያስፈልጋቸው አልፈው እንዲሄዱ የሚያገለግል ነው። መንገዱ የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ ለመቅረፍ ታልሞ ነው የሚገነባው። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ይርጋለም ኮንስትራክሽን ሲሆን በእስካሁኑ የግንባታ ሂደት የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የሰብቤዝ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራና የ94 ሜትር ድልድይ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። አስፋልት ለማንጠፍ የሚረዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችም እየተሠሩ ነው። የመንገድ ግንባታው ዋነኛ ግብዓት የሆነው የሲሚንቶ ዕጥረት ለስራው ፈተና እንደሆነበትም ታውቋል። ችግሩን ለመቅረፍ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ። የማማከሩን ስራ እያከናወነ የሚገኘው ደግሞ ኤልዳ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንትሲ ሲሆን የድጋፍና ክትትል ሥራውን እያከናወነ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው በትላልቅ ከተሞች የመንገድ ደረጃ በኮንክሪት አስፋልት እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፥ የእግረኛ እና የብስክሌት መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ በፕሮጅክቱ ተካትተውበታል። የጅግጅጋ ባይባስ ግንባታ ሲጠናቀቅ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በማሳለጥ፤ ለከተማዋ ዕድገት ምቹ ዕድል ይፈጥራል። በክልሉ ለሚደረጉ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችም የጎላ ሚና አለው። መንገዱ 30 ሜትር የጎን ስፋት አለው።