es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 307 suscriptores, ocupando la posición 1 759 en la categoría Transporte y el puesto 2 546 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 307 suscriptores.

Según los últimos datos del 15 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 88, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 40.23%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.41% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 352 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 050 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 17.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 16 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 307
Suscriptores
+224 horas
+297 días
+8830 días
Archivo de publicaciones
የባቱ - አርሲ ነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀቁ ቡልቡላ ፣ የካቲት 26፣ 2018 (ኢመአ)፦ የአዲስ አበባ - ሞያሌ - ናይሮቢ - ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ - ሐዋሳ ክፍል 3፡ ባቱ - አርሲ ነገሌ 57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀቁ። የፍጥነት መንገዱ በ90 ሜትር የመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ የጎን ስፋቱ የመንገድ አካፍይን ጨምሮ 31 ነጥብ 6 ሜትር ነው። መንገዱ ሙሉ በሙሉ ከከተማ ውጪ የሚያልፍና ከከተማዎች ጋር የሚያስተሳስሩ አገናኝ መንገዶች ያሉት ሲሆን አገናኝ መንገዶቹ በገጠር 10 ሜትር፣ በከተማ ደግሞ 22 ነጥብ 5 ሜትር የጎን ስፋት አላቸው። ግንባታውን ለማከናወን የዋለው 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተሸፈነ ነው። የግንባታ ሥራውን ዓለም አቀፉ የሥራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ሲያከናውነው፤ ኩንሃ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር፣ እንዲሁም ሀገር በቀሉ ንዑስ አማካሪ ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ኩባንያ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ በጋራ ሰርተውታል። መንገዱ የአዲስ አበባ - ሞጆ - ሞያሌ - ላሙ - ሞምባሳ ትራንስ ኢንተርናሽናል ሐይዌይ እንዲሁም 10,000 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ኮሪደር (ኬፕታውን ትራንስ አፍሪካን ሐይዌይ) አካል በመሆኑ፣ የጎረቤት ሀገራትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ የላቀ ሚና ይጫወታል። የፕሮጀክቱ የ ITS intelligent Transport system ተከላ ተጠናቅቆ መንገዱ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ እና የቱሪዝም ፍሰት ለማቀላጠፍ የሚያስችል ይሆናል። የመንገድ ኮሪደሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ እና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የሚገኙትን የባቱ ከተማን፣ የአዳሚ ቱሉ እና አርሲ ነገሌ ወረዳዎችን ጨምሮ ከ17 በላይ ቀበሌዎችን ያስተሳስራል። በተጨማሪም የእርሻና ኢንዱስትሪ ማዕከላትን እንዲሁም የቱሪስት መስህቦችን ለማገናኘት የሚያስችል ሲሆን፤ በተለይም የሀሮ ደምበል፣ ላንጋኖ፣ አብያታ እና ሻላ ሐይቆችን እንዲሁም ሐዋሳን ለመጎብኘት ለሚሄዱ የሀገር ውስጥና ለውጭ ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ፕሮጀክቱ ከሞጆ - ሐዋሳ የነበረውን የ4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ በማድረግ፣ ለመንገዱ ተጠቃሚዎች ደህንነቱ የተጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል። ከዚህም ባሻገር እንደ ስንዴ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ፓፓያ እና ድንች ያሉ የግብርና ውጤቶች ሳይዘገዩ በፍጥነት ለገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቡታጅራ - ሆሳዕና - መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው ቡታጅራ፣ የካቲት 26/2018 (ኢ መ አ):- የቡታጅራ - ሆሳዕና አስፋልት መንገድ በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ መደበኛ ጥገና እየተደረገለት ነው። የመንገድ ጥገናው 96 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ-ኅይል በማከናወን ላይ ይገኛል። መንገዱ ከ19 ዓመት በላይ ያገለገለ ሲኾን፣ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና የዲዛይን ዕድሜውን በመጨረሱ ነው መደበኛ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው። አሁን ላይ የውኃ ማፋሰሻ ጥገና፣ በመንገድ ላይ የተቆፋፈሩ ጉድጓዶችን በአስፋልት የመሙላት፣ የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት፣ የቤዝኮርስ ማስተካከል፣ የመንገድ ትከሻ እንደዚሁም የመንገድ ዳር ምልክቶች እና የመንገድ ደኅንነት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት የጥገና ሥራው 80 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ እስከ ሰኔ ወር 2018 ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል። የመንገዱ መጠገን ምቹ እና የተሻለ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር አስችሏል። ለመኪና መለዋወጫ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎች እንዲቀንስ አስችሏል። የኅብረተሰቡን ድካም እና እንግልትም አስቀርቷል። በተመሳሳይ ከሆሳዕና - አረካ - ወላይታ ሶዶ ያለው መንገድ በቅርቡ ጥገናው ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በቀጣይም መንገዱን በዘላቂነት መልሶ ለመገንባት የዲዛይን ሥራው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ በአሁኑ ወቅት በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል። ተቋማችን ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቡታጅራ - ሆሳዕና - መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው ቡታጅራ፣ የካቲት 26/2018 (ኢ መ አ):- የቡታጅራ - ሆሳዕና አስፋልት መንገድ በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ መደበኛ ጥገና እየተደረገለት ነው። የመንገድ ጥገናው 96 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ-ኅይል በማከናወን ላይ ይገኛል። መንገዱ ከ19 ዓመት በላይ ያገለገለ ሲኾን፣ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና የዲዛይን ዕድሜውን በመጨረሱ ነው መደበኛ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው። አሁን ላይ የውኃ ማፋሰሻ ጥገና፣ በመንገድ ላይ የተቆፋፈሩ ጉድጓዶችን በአስፋልት የመሙላት፣ የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት፣ የቤዝኮርስ ማስተካከል፣ የመንገድ ትከሻ እንደዚሁም የመንገድ ዳር ምልክቶች እና የመንገድ ደኅንነት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት የጥገና ሥራው 80 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ እስከ ሰኔ ወር 2018 ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል። የመንገዱ መጠገን ምቹ እና የተሻለ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር አስችሏል። ለመኪና መለዋወጫ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎች እንዲቀንስ አስችሏል። የኅብረተሰቡን ድካም እና እንግልትም አስቀርቷል። በተመሳሳይ ከሆሳዕና - አረካ - ወላይታ ሶዶ ያለው መንገድ በቅርቡ ጥገናው ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በቀጣይም መንገዱን በዘላቂነት መልሶ ለመገንባት የዲዛይን ሥራው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ በአሁኑ ወቅት በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል። ተቋማችን ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Facebook Ethiopian Roads Administration Published by Ethiopian Roads Authority(tooltip)Only people who manage this Page can see who published · dsoporSntehl120t4122fc38h0a4f13i43ffa4ci307m8cma6at98ufmhhll · የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና የኮንስትራክሽን ሣምንት በሚያዚያ ወር ይካሄዳል… See more

የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና የኮንስትራክሽን ሣምንት በሚያዚያ ወር ይካሄዳል አዲስ አበባ፣ የካቲት 25/ 2018 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና የኮንስትራክሽን ሣምንት "ኢትዮጵያ ትገነባለች!" በሚል መሪ ቃል ከሚያዚያ 9-12 በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ይካሄዳል። ጉዳዩን አስመልክቶ በከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር ዋ/መሥሪያ ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል። የሀገር በቀል አቅምን በማሳደግና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ጫልቱ ሳኒ አስታውቀዋል ። ፍትሐዊ የመሠረተ-ልማት ስርጭትን ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ የመንገድ ዘርፍ ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ ወደ 40 ሺ ኪ.ሜ የሚጠጋ አዳዲስ መንገዶችን በመገንባት እና የመንገድ ርዝመትን ከ144 ሺ ወደ 182 ሺህ ኪ.ሜ ማሳደግ ተችሏል። የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በሰጡት መግለጫ ሳምንቱ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለሕዝብና ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ የተገኙ ተሞክሮዎችን ለመተንተንና የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማመላከት ያለመ ነው ብለዋል። የኢንዱስትሪውን የሀገር ውስጥ ምርት አቅም ለማሳደግ፣ የተቋማትን ቅንጅታዊ አሠራር ለማሳለጥና አዳዲስ የግንባታ ዘዴዎችን ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት። በመርሐ ግብሩ በዘርፉ ላይ የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋራጮች፣ አማካሪዎችና አስፈጻሚ ተቋማት ዕውቅና የሚያገኙ ሲሆን÷ መድረኩ የኮንስትራክሽን ዘርፉን በማነቃቃት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረውም አመልክተዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቡልቡላ - አላጌ - ባራ - ሚቶ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ። ቡልቡላ፣ የካቲት 23/2018 (ኢ መ አ):- የምሥራቅ ሸዋ፣ ስልጤ እና ሀላባ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የቡልቡላ - አላጌ - ባራ - ሚቶ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ወደ ባራ - ሚቶ የሚወስደውን አገናኝ መንገድ ጨምሮ አጠቃላይ 38 ነጥብ 8 ኪሎሜትር ይሸፍናል። የፕሮጀክቱ ጠቅላላ በጀት ስምንት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አስራአራት ሺ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት (878,514,732) ብር ሲሆን፤ በፌደራል መንግስት ተሸፍኗል፡፡ የመንገዱ ነባር ገጽታ 29.1ኪ.ሜትሩ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን፥ ቀሪው 9.7ኪ.ሜትር ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት አልነበረውም። አሁን ላይ የመንገዱ አጠቃላይ ስፋት በወረዳ 21ሜትር ሆኖ፤ 7 ሜትር በግራና ቀኝ ለተሽከርካሪ፣ 2 ሜትር አካፋይ እንዲሁም 2.5 ሜትር በግራና ቀኝ የእግረኛ መንገድ ሲሆን፣ በገጠር 11 ሜትር ስፋት ያለው ነው። የመንገድ ግንባታው ያከናወነው ሀገር በቀሉ ኪቢሽ ኮንስትራክሽን ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ አከናውኖታል። በመንገድ ግንባታው ከመንገድ ደኅንነት እና የእግረኛ መሄጃ ጋር የተያያዙ ጥቂት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የመንገዱ መገንባት ከዚህ ቀደም የነበረውን አስቸጋሪ የመንገዱ ሁኔታ በማሻሻል ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ አሳጥሮ በዙሪያው ያሉትን የወረዳ ከተሞች እና አጎራባች ቀበሌዎች በ30 ደቂቃ ማገናኘት አስችሏል። በተጨማሪም አካባቢው ብዛት ያለው ህዝብ በመኖሩ ለብዙሃኑ የኑሮ መሻሻል፣ የትምህርት እና የህክምና እንዲሁም አጎራባች ክልሎችን ከፈጣን መንገድ ጋር በማገናኘት አይነተኛ ድርሻ ይኖረዋል። አከባቢው እንደ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ቦሎቄ እና በርበሬ አብቃይ በመሆኑ፤ እነዚህን የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢተያ - ሮቤ - ሴሩ መንገድ የአስፓልት ስራ ተጠናቀቀ ። አራት ወረዳዎችን የሚያገናኘውና 75.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ኢተያ-ሮቤ- ሴሩ ሎት 1 ኢተያ ሮቤ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፓልት ስራው ተጠናቋል ። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 ኢንጅነሪግ ግሩፕ የተሰኘው አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚሰራው ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጅነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት ዘርፍ ነው፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አንፃር ደረጃውን ጠብቆ ከአንድ ቢሊየን ሶስት መቶሀያ አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳአራት ሺህ አምስት መቶ አስር ብር (1,324,234,510.32) በላይ በሆነ ወጪ የኢትዮጵያ መንግስት ሸፍኖ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጓል ፡፡ የመንገድ ስራው ያካተተው የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድሬኔጅ ፣ ስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣የቤዝ ኮርስ እንዲሁም ሙሉ የአስፋልት ንጣፍ የተከናወነ ሲሆን ቀሪ ስራዎች ማለትም የቀለም ቅብ፣ የዲች ክዳን እና የመንገድ ትከሻ ና የእግረኛ መሄጃዎች ተጠቃሽ ነው ። የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳና በከተማ ከ 19 – 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 15 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡ የመንገዱ መገንባት በአርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሄጦሣ፣ የሎዴ ሄጦሳ፣ የዲክሲስ እና ሮቤ ወረዳዎችን እና ቦሩ ሌንጫ፤ጎበያ፤አርብ ገበያ፤እድገት ፋና፤ቡላላ ቀበሌዎችን አስተሳስሮ ከዚህ በፊት ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአራት ሰአት አሳጥሮ ምቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር አስችሏል ፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ላይ የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን ስንዴ፤ገብስ እና ከአትክልቶችም እንደ ሽንኩርት፤ድንች እና ቲማቲም በአካባቢው ላይ ስለሚመረቱ በቀላሉ ወደ መሃል አገር እንዲቀርብ በማድረግ የአምራች ገበሬዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጋል ተብሎ ይታሰባል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢተያ - ሮቤ - ሴሩ መንገድ የአስፓልት ስራ ተጠናቀቀ ። አራት ወረዳዎችን የሚያገናኘውና 75.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ኢተያ-ሮቤ- ሴሩ ሎት 1 ኢተያ ሮቤ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፓልት ስራው ተጠናቋል ። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 ኢንጅነሪግ ግሩፕ የተሰኘው አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚሰራው ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጅነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት ዘርፍ ነው፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አንፃር ደረጃውን ጠብቆ ከአንድ ቢሊየን ሶስት መቶሀያ አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳአራት ሺህ አምስት መቶ አስር ብር (1,324,234,510.32) በላይ በሆነ ወጪ የኢትዮጵያ መንግስት ሸፍኖ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጓል ፡፡ የመንገድ ስራው ያካተተው የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድሬኔጅ ፣ ስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣የቤዝ ኮርስ እንዲሁም ሙሉ የአስፋልት ንጣፍ የተከናወነ ሲሆን ቀሪ ስራዎች ማለትም የቀለም ቅብ፣ የዲች ክዳን እና የመንገድ ትከሻ ና የእግረኛ መሄጃዎች ተጠቃሽ ነው ። የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳና በከተማ ከ 19 – 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 15 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡ የመንገዱ መገንባት በአርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሄጦሣ፣ የሎዴ ሄጦሳ፣ የዲክሲስ እና ሮቤ ወረዳዎችን እና ቦሩ ሌንጫ፤ጎበያ፤አርብ ገበያ፤እድገት ፋና፤ቡላላ ቀበሌዎችን አስተሳስሮ ከዚህ በፊት ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአራት ሰአት አሳጥሮ ምቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር አስችሏል ፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ላይ የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን ስንዴ፤ገብስ እና ከአትክልቶችም እንደ ሽንኩርት፤ድንች እና ቲማቲም በአካባቢው ላይ ስለሚመረቱ በቀላሉ ወደ መሃል አገር እንዲቀርብ በማድረግ የአምራች ገበሬዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጋል ተብሎ ይታሰባል ።

የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ ጅግጅጋ፣ የካቲት 22/2018 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ የትራፊክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አጠቃላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ 6 ነጥብ 93 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፣ 30 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ተገንብቷል። መነሻውን ጅግጅጋ ከተማ መግቢያ አድርጎ ቶጎ-ጫሌ አደባባይ ላይ ያበቃው ይህ ፕሮጀክት ዋና ዋና ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን፣ የትራፊክ ምልክቶች ተከላ  እና ሌሎች ጥቃቅን ስራዎች እየተከናወኑ ነው። በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ  ግንባታ ተካቷል። ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ግንባታውን ያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤልዳ አማካሪ ድርጅት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር  በጋራ ሰርተውታል። ለግንባታው ማስፈጸሚያ የዋለውን 672,098,730.28 (ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊየን ዘጠና ስምንት ሺህ ብር ሰባት መቶ ሰላሳ ብር ከሃያ ስምንት) ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ተሸፍኗል። የተለዋጭ መንገድ ግንባታው መጠናቀቅ በጅግጅጋ ከተማ ውስጥ እንዲሁም መግቢያ እና መውጫ  ላይ የሚታየውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያቃልላል። ከቶጎ ጫሌ  እንዲሁም ከደገሀቡር የሚመጡ የከባድም ሆነ ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች ጅግጅጋ ከተማን ሳያቋርጡ ለማለፍ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት እና ውበት በማሳለጥ በኩል ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads