ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 305 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 758,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 550 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 305 名订阅者。
根据 15 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 88,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 352 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 15 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 307
订阅者
+224 小时
+297 天
+8830 天
帖子存档
13 307
የባቱ - አርሲ ነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀቁ
ቡልቡላ ፣ የካቲት 26፣ 2018 (ኢመአ)፦ የአዲስ አበባ - ሞያሌ - ናይሮቢ - ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ - ሐዋሳ ክፍል 3፡ ባቱ - አርሲ ነገሌ 57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀቁ።
የፍጥነት መንገዱ በ90 ሜትር የመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ የጎን ስፋቱ የመንገድ አካፍይን ጨምሮ 31 ነጥብ 6 ሜትር ነው።
መንገዱ ሙሉ በሙሉ ከከተማ ውጪ የሚያልፍና ከከተማዎች ጋር የሚያስተሳስሩ አገናኝ መንገዶች ያሉት ሲሆን አገናኝ መንገዶቹ በገጠር 10 ሜትር፣ በከተማ ደግሞ 22 ነጥብ 5 ሜትር የጎን ስፋት አላቸው።
ግንባታውን ለማከናወን የዋለው 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተሸፈነ ነው።
የግንባታ ሥራውን ዓለም አቀፉ የሥራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ሲያከናውነው፤ ኩንሃ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር፣ እንዲሁም ሀገር በቀሉ ንዑስ አማካሪ ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ኩባንያ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ በጋራ ሰርተውታል።
መንገዱ የአዲስ አበባ - ሞጆ - ሞያሌ - ላሙ - ሞምባሳ ትራንስ ኢንተርናሽናል ሐይዌይ እንዲሁም 10,000 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ኮሪደር (ኬፕታውን ትራንስ አፍሪካን ሐይዌይ) አካል በመሆኑ፣ የጎረቤት ሀገራትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ የላቀ ሚና ይጫወታል።
የፕሮጀክቱ የ ITS intelligent Transport system ተከላ ተጠናቅቆ መንገዱ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ እና የቱሪዝም ፍሰት ለማቀላጠፍ የሚያስችል ይሆናል።
የመንገድ ኮሪደሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ እና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የሚገኙትን የባቱ ከተማን፣ የአዳሚ ቱሉ እና አርሲ ነገሌ ወረዳዎችን ጨምሮ ከ17 በላይ ቀበሌዎችን ያስተሳስራል።
በተጨማሪም የእርሻና ኢንዱስትሪ ማዕከላትን እንዲሁም የቱሪስት መስህቦችን ለማገናኘት የሚያስችል ሲሆን፤ በተለይም የሀሮ ደምበል፣ ላንጋኖ፣ አብያታ እና ሻላ ሐይቆችን እንዲሁም ሐዋሳን ለመጎብኘት ለሚሄዱ የሀገር ውስጥና ለውጭ ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ፕሮጀክቱ ከሞጆ - ሐዋሳ የነበረውን የ4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ በማድረግ፣ ለመንገዱ ተጠቃሚዎች ደህንነቱ የተጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል።
ከዚህም ባሻገር እንደ ስንዴ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ፓፓያ እና ድንች ያሉ የግብርና ውጤቶች ሳይዘገዩ በፍጥነት ለገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 307
የቡታጅራ - ሆሳዕና - መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው
ቡታጅራ፣ የካቲት 26/2018 (ኢ መ አ):- የቡታጅራ - ሆሳዕና አስፋልት መንገድ በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ መደበኛ ጥገና እየተደረገለት ነው።
የመንገድ ጥገናው 96 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ-ኅይል በማከናወን ላይ ይገኛል።
መንገዱ ከ19 ዓመት በላይ ያገለገለ ሲኾን፣ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና የዲዛይን ዕድሜውን በመጨረሱ ነው መደበኛ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው።
አሁን ላይ የውኃ ማፋሰሻ ጥገና፣ በመንገድ ላይ የተቆፋፈሩ ጉድጓዶችን በአስፋልት የመሙላት፣ የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት፣ የቤዝኮርስ ማስተካከል፣ የመንገድ ትከሻ እንደዚሁም የመንገድ ዳር ምልክቶች እና የመንገድ ደኅንነት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው።
በአሁኑ ወቅት የጥገና ሥራው 80 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ እስከ ሰኔ ወር 2018 ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል።
የመንገዱ መጠገን ምቹ እና የተሻለ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር አስችሏል። ለመኪና መለዋወጫ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎች እንዲቀንስ አስችሏል። የኅብረተሰቡን ድካም እና እንግልትም አስቀርቷል።
በተመሳሳይ ከሆሳዕና - አረካ - ወላይታ ሶዶ ያለው መንገድ በቅርቡ ጥገናው ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በቀጣይም መንገዱን በዘላቂነት መልሶ ለመገንባት የዲዛይን ሥራው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ በአሁኑ ወቅት በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል።
ተቋማችን ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 307
የቡታጅራ - ሆሳዕና - መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው
ቡታጅራ፣ የካቲት 26/2018 (ኢ መ አ):- የቡታጅራ - ሆሳዕና አስፋልት መንገድ በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ መደበኛ ጥገና እየተደረገለት ነው።
የመንገድ ጥገናው 96 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ-ኅይል በማከናወን ላይ ይገኛል።
መንገዱ ከ19 ዓመት በላይ ያገለገለ ሲኾን፣ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና የዲዛይን ዕድሜውን በመጨረሱ ነው መደበኛ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው።
አሁን ላይ የውኃ ማፋሰሻ ጥገና፣ በመንገድ ላይ የተቆፋፈሩ ጉድጓዶችን በአስፋልት የመሙላት፣ የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት፣ የቤዝኮርስ ማስተካከል፣ የመንገድ ትከሻ እንደዚሁም የመንገድ ዳር ምልክቶች እና የመንገድ ደኅንነት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው።
በአሁኑ ወቅት የጥገና ሥራው 80 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ እስከ ሰኔ ወር 2018 ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል።
የመንገዱ መጠገን ምቹ እና የተሻለ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር አስችሏል። ለመኪና መለዋወጫ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎች እንዲቀንስ አስችሏል። የኅብረተሰቡን ድካም እና እንግልትም አስቀርቷል።
በተመሳሳይ ከሆሳዕና - አረካ - ወላይታ ሶዶ ያለው መንገድ በቅርቡ ጥገናው ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በቀጣይም መንገዱን በዘላቂነት መልሶ ለመገንባት የዲዛይን ሥራው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ በአሁኑ ወቅት በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል።
ተቋማችን ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Facebook
Ethiopian Roads Administration
Published by Ethiopian Roads Authority(tooltip)Only people who manage this Page can see who published · dsoporSntehl120t4122fc38h0a4f13i43ffa4ci307m8cma6at98ufmhhll ·
የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና የኮንስትራክሽን ሣምንት በሚያዚያ ወር ይካሄዳል… See more
13 307
የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና የኮንስትራክሽን ሣምንት በሚያዚያ ወር ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ የካቲት 25/ 2018 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት እና የኮንስትራክሽን ሣምንት "ኢትዮጵያ ትገነባለች!" በሚል መሪ ቃል ከሚያዚያ 9-12 በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ይካሄዳል።
ጉዳዩን አስመልክቶ በከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር ዋ/መሥሪያ ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል።
የሀገር በቀል አቅምን በማሳደግና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ጫልቱ ሳኒ አስታውቀዋል ።
ፍትሐዊ የመሠረተ-ልማት ስርጭትን ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ የመንገድ ዘርፍ ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ ወደ 40 ሺ ኪ.ሜ የሚጠጋ አዳዲስ መንገዶችን በመገንባት እና የመንገድ ርዝመትን ከ144 ሺ ወደ 182 ሺህ ኪ.ሜ ማሳደግ ተችሏል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በሰጡት መግለጫ ሳምንቱ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለሕዝብና ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ የተገኙ ተሞክሮዎችን ለመተንተንና የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማመላከት ያለመ ነው ብለዋል።
የኢንዱስትሪውን የሀገር ውስጥ ምርት አቅም ለማሳደግ፣ የተቋማትን ቅንጅታዊ አሠራር ለማሳለጥና አዳዲስ የግንባታ ዘዴዎችን ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት።
በመርሐ ግብሩ በዘርፉ ላይ የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋራጮች፣ አማካሪዎችና አስፈጻሚ ተቋማት ዕውቅና የሚያገኙ ሲሆን÷ መድረኩ የኮንስትራክሽን ዘርፉን በማነቃቃት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረውም አመልክተዋል። በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 307
የቡልቡላ - አላጌ - ባራ - ሚቶ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ።
ቡልቡላ፣ የካቲት 23/2018 (ኢ መ አ):- የምሥራቅ ሸዋ፣ ስልጤ እና ሀላባ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የቡልቡላ - አላጌ - ባራ - ሚቶ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቋል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ወደ ባራ - ሚቶ የሚወስደውን አገናኝ መንገድ ጨምሮ አጠቃላይ 38 ነጥብ 8 ኪሎሜትር ይሸፍናል።
የፕሮጀክቱ ጠቅላላ በጀት ስምንት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አስራአራት ሺ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት (878,514,732) ብር ሲሆን፤ በፌደራል መንግስት ተሸፍኗል፡፡
የመንገዱ ነባር ገጽታ 29.1ኪ.ሜትሩ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን፥ ቀሪው 9.7ኪ.ሜትር ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት አልነበረውም።
አሁን ላይ የመንገዱ አጠቃላይ ስፋት በወረዳ 21ሜትር ሆኖ፤ 7 ሜትር በግራና ቀኝ ለተሽከርካሪ፣ 2 ሜትር አካፋይ እንዲሁም 2.5 ሜትር በግራና ቀኝ የእግረኛ መንገድ ሲሆን፣ በገጠር 11 ሜትር ስፋት ያለው ነው።
የመንገድ ግንባታው ያከናወነው ሀገር በቀሉ ኪቢሽ ኮንስትራክሽን ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ አከናውኖታል።
በመንገድ ግንባታው ከመንገድ ደኅንነት እና የእግረኛ መሄጃ ጋር የተያያዙ ጥቂት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው።
የመንገዱ መገንባት ከዚህ ቀደም የነበረውን አስቸጋሪ የመንገዱ ሁኔታ በማሻሻል ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ አሳጥሮ በዙሪያው ያሉትን የወረዳ ከተሞች እና አጎራባች ቀበሌዎች በ30 ደቂቃ ማገናኘት አስችሏል።
በተጨማሪም አካባቢው ብዛት ያለው ህዝብ በመኖሩ ለብዙሃኑ የኑሮ መሻሻል፣ የትምህርት እና የህክምና እንዲሁም አጎራባች ክልሎችን ከፈጣን መንገድ ጋር በማገናኘት አይነተኛ ድርሻ ይኖረዋል።
አከባቢው እንደ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ቦሎቄ እና በርበሬ አብቃይ በመሆኑ፤ እነዚህን የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 307
የኢተያ - ሮቤ - ሴሩ መንገድ የአስፓልት ስራ ተጠናቀቀ ።
አራት ወረዳዎችን የሚያገናኘውና 75.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ኢተያ-ሮቤ- ሴሩ ሎት 1
ኢተያ ሮቤ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፓልት ስራው ተጠናቋል ።
ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 ኢንጅነሪግ ግሩፕ የተሰኘው አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚሰራው ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጅነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት ዘርፍ ነው፡፡
መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አንፃር ደረጃውን ጠብቆ ከአንድ ቢሊየን ሶስት መቶሀያ አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳአራት ሺህ አምስት መቶ አስር ብር (1,324,234,510.32) በላይ በሆነ ወጪ የኢትዮጵያ መንግስት ሸፍኖ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጓል ፡፡
የመንገድ ስራው ያካተተው የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድሬኔጅ ፣ ስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣የቤዝ ኮርስ እንዲሁም ሙሉ የአስፋልት ንጣፍ የተከናወነ ሲሆን ቀሪ ስራዎች ማለትም የቀለም ቅብ፣ የዲች ክዳን እና የመንገድ ትከሻ ና የእግረኛ መሄጃዎች ተጠቃሽ ነው ።
የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳና በከተማ ከ 19 – 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 15 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡
የመንገዱ መገንባት በአርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሄጦሣ፣ የሎዴ ሄጦሳ፣ የዲክሲስ እና ሮቤ ወረዳዎችን እና ቦሩ ሌንጫ፤ጎበያ፤አርብ ገበያ፤እድገት ፋና፤ቡላላ ቀበሌዎችን አስተሳስሮ ከዚህ በፊት ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአራት ሰአት አሳጥሮ ምቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር አስችሏል ፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው ላይ የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን ስንዴ፤ገብስ እና ከአትክልቶችም እንደ ሽንኩርት፤ድንች እና ቲማቲም በአካባቢው ላይ ስለሚመረቱ በቀላሉ ወደ መሃል አገር እንዲቀርብ በማድረግ የአምራች ገበሬዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጋል ተብሎ ይታሰባል ። በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 307
የኢተያ - ሮቤ - ሴሩ መንገድ የአስፓልት ስራ ተጠናቀቀ ።
አራት ወረዳዎችን የሚያገናኘውና 75.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ኢተያ-ሮቤ- ሴሩ ሎት 1
ኢተያ ሮቤ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፓልት ስራው ተጠናቋል ።
ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 ኢንጅነሪግ ግሩፕ የተሰኘው አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚሰራው ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጅነሪግ ኮርፖሬሽን የትራንስፖርት ዘርፍ ነው፡፡
መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አንፃር ደረጃውን ጠብቆ ከአንድ ቢሊየን ሶስት መቶሀያ አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳአራት ሺህ አምስት መቶ አስር ብር (1,324,234,510.32) በላይ በሆነ ወጪ የኢትዮጵያ መንግስት ሸፍኖ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጓል ፡፡
የመንገድ ስራው ያካተተው የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድሬኔጅ ፣ ስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣የቤዝ ኮርስ እንዲሁም ሙሉ የአስፋልት ንጣፍ የተከናወነ ሲሆን ቀሪ ስራዎች ማለትም የቀለም ቅብ፣ የዲች ክዳን እና የመንገድ ትከሻ ና የእግረኛ መሄጃዎች ተጠቃሽ ነው ።
የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳና በከተማ ከ 19 – 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 15 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡
የመንገዱ መገንባት በአርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሄጦሣ፣ የሎዴ ሄጦሳ፣ የዲክሲስ እና ሮቤ ወረዳዎችን እና ቦሩ ሌንጫ፤ጎበያ፤አርብ ገበያ፤እድገት ፋና፤ቡላላ ቀበሌዎችን አስተሳስሮ ከዚህ በፊት ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአራት ሰአት አሳጥሮ ምቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር አስችሏል ፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው ላይ የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን ስንዴ፤ገብስ እና ከአትክልቶችም እንደ ሽንኩርት፤ድንች እና ቲማቲም በአካባቢው ላይ ስለሚመረቱ በቀላሉ ወደ መሃል አገር እንዲቀርብ በማድረግ የአምራች ገበሬዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጋል ተብሎ ይታሰባል ።
13 307
የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ
ጅግጅጋ፣ የካቲት 22/2018 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ የትራፊክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
አጠቃላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ 6 ነጥብ 93 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፣ 30 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ተገንብቷል።
መነሻውን ጅግጅጋ ከተማ መግቢያ አድርጎ ቶጎ-ጫሌ አደባባይ ላይ ያበቃው ይህ ፕሮጀክት ዋና ዋና ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን፣ የትራፊክ ምልክቶች ተከላ እና ሌሎች ጥቃቅን ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ ግንባታ ተካቷል።
ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ግንባታውን ያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤልዳ አማካሪ ድርጅት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በጋራ ሰርተውታል።
ለግንባታው ማስፈጸሚያ የዋለውን 672,098,730.28 (ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊየን ዘጠና ስምንት ሺህ ብር ሰባት መቶ ሰላሳ ብር ከሃያ ስምንት) ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ተሸፍኗል።
የተለዋጭ መንገድ ግንባታው መጠናቀቅ በጅግጅጋ ከተማ ውስጥ እንዲሁም መግቢያ እና መውጫ ላይ የሚታየውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያቃልላል።
ከቶጎ ጫሌ እንዲሁም ከደገሀቡር የሚመጡ የከባድም ሆነ ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች ጅግጅጋ ከተማን ሳያቋርጡ ለማለፍ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል።
ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት እና ውበት በማሳለጥ በኩል ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
