es
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Ir al canal en Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Mostrar más
638
Suscriptores
-224 horas
-57 días
-1130 días
Archivo de publicaciones
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሰኔ ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያ_ጻድቅ ለታላቁ አባት በደብረ ዳሞ ገዳም ለ37 ዓመታት ላገለገሉ 3 ታላላቅ ገዳማት በስማቸው ለተሰየመ #ለአቡነ_ሠምረ_አብ_ዘሳይንት_ወዘትግራይ ዓመታዊ ለልደት በዓል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                                                              ✝️ ✝️ ✝️   ❤#አቡነ_ሠምረ_አብ ዘሳይንት ወዘትግራይ፦ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ሲሆኑ የትውልድ ሀገራቸው በወሎ አምሐራ ሳይንት ነው። አቡነ ሠምረ አብ የትውልድ ዕለታቸው ሰኔ 4 ቀን ነው። በብሕትውና ከተረጋገጠላቸውና ከ47ቱ ከታወቁት ሊቃውንት አንዱ ናቸው። ❤ አባ ሠምረ አብ ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ሄደው በዚያ 37 ዓመት ተቀምው፤በኋላም ወደ ገርዓልታ ሄደው በስማቸው የተሰራውን ታላቁን  ገዳም ቆረቆሩ። (ገርዓልታ አቡነ ሠምረ አብ ገዳም)፤በዚህም ምክንያት አቡነ ሠምረ አብ ዘትግራይ ይሏቸዋል። በተጨማሪም አስደናቂ የሆነ ገዳማቸው በጎንደር ደንቀዝ ውስጥ ይገኛል። ❤ በኢትዮጵያ ውስጥ በጻድቁ ስም 3 አብያተ-ክርስቲያናት ተሰርተዋል። የዕረፍት ቀናቸውም ጥር 4 ቀን ነው። ከአባታችን ከአቡነ ሠምረ አብ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን!።  ምንጭ፦ ዜና ቅዱሳን።

❤ ቅዱስ ለውንትዮስም ለሥጋው መልካም ለሠራች ለመስፍኑ ሚስት መልካም ወጋዋን ሊከፍላት ሽቶ በዚያች ሌሊት በወህኒ ቤት ለባልዋ ተገለጠለት በወህኒ ቤቱም ብርሃን ወጣ ለመኰንኑም የራሱ የሆነውን በቤቱ ያለውን የሚያውቀውን የወርቅ ልብስ ለብሶ በጐልማሳ ፈረሰኛ አምሳል ተገለጠለት። ❤ ከዚህም በኋላ እንዲህ አለው "አትዘን አታልቅስም ዛሬ ከዚህ ወጥተህ ከንጉሥ ጋር በማዕዱ ትቀመጣለህና ከዚያም ወደ ቤትህ በሰላም ትሔዳለህ"። የታሠረው መስፍንም ይህን ጐልማሳ ፈረሰኛ ስለ አየው በላዩም ስለ ወጣው ብርሃን የወህኒ ቤቱም ደጅ እንደ ተዘጋና እንደ ተቆለፈ ወደ ርሱ ስለ መግባቱ ደግሞም የራሱ የሆነውን በቤቱ ውስጥ የተወውን የወርቅ ልብስ ለብሶ ስለ ማየቱ በዚህ ሁሉ ሥራ ያደንቅ ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ለውንትዮስ በዚያች ሰዓት ወደ ንጉሡ ሔደ በመኝታውም ተኝቶ ሳለ ረገጠው እጅግም ደነገጠ ለንጉሡም እንዲህ አለው "ንጋት በሆነ ጊዜ መስፍን ዕገሌን ከወህኒ ቤት አውጣው አክብረውም በክፉ አሟሟትም ሙተህ እንዳትጠፉ ወደ ቤቱ ይሔድ ዘንድ ተወው"። ንጉሡም ከግርማው የተነሣ እየተንቀጠቀጠ "እሺ ጌታዬ ያዘዝከኝን ሁሉ አደርጋለሁ" ብሎ መለሰለት። በነጋ ጊዜም ንጉሡ ወደ ወህኒ ቤት ልኮ መስፍኑን አወጣው ታላቅ ክብርንም አከበረው መልካም ልብሶችንም አልብሶ ከእርሱ ጋራ በማዕዱ አስቀመጠው። ፈረሰኛም እንደ ተገለጠለትና ይፈታው ዘንድ እንዳዘዘው ነገረው መስፍኑም አደነቀ። ንጉሡም የሥራይ ሥራ እንደሆነ አድርጎ አሰበ መስፍኑም "እኔ መጠበብንና ሥራይን አላውቅም ከእሊህ ከምትለኝም ነገሮች ማን እንደተገለጠልህ ምንም አላውቅም"። ንጉሥም ከተገለጠለት ራእይ ፍርሀት የተነሣ ክፉ ነገርን ሊናገው አልደፈረም ነገር ግን ወደ አገሩ በታላቅ ክብር ሰደደው። ❤ መስፍኑም በጎዳና ሲጓዝ ሁለተኛ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለት ወደ አገሩ ጠራብሎስም እስኪደርስ እያነጋገረው ያጽናናው ነበር ከዚህም በኋላ ተሠወረው። ወደ ቤቱም በገባ ጊዜ ቤተሰቦቹን ሰላም አላቸው የእርሱን የወርቅ ልብስ የሚመስል ልብስ ለብሶ ፈረሰኛ ጐልማሳ እንደ ተገለጠለትም ነገራቸው ከወህኒ ቤትም እሥራት ያድነው ዘንድ ቃል እንደገባለት ነገራቸው። ሚስቱም ያዳነው ቅዱስ ለውንትዮስ እንደሆነ አውቃ "ብታየው ታውቀዋለህን" አለችው "አዎን" አላት ከዚያም የቅዱስ ለውንትዮስ ሥዕል ወደ አለበት ቦታ አስገባችው አይቶም "የተገለጠልኝ በእውነት ይህ ነው" አለ። ❤ ሁለተኛም የቅዱስ ለውንትዮስ ሥጋ ያለበትን ሣጥን ከፈተች ያንንም የርሱን የወርቅ ልብስ እንደለበሰ አየው። የፊቱንም መሸፈኛ ገለጠ የተገለጠለትና ከእሥራት ያዳነውም እርሱ እንደ ሆነ ተረዳ። መስፍኑም ማን እንደሆነ ስለ እርሱ ሚስቱን ጠየቃት እርሷም የቅዱስ ለውንትዮስን ገድል ነገረችው መስፍኑም ይህን መልካም ሥራ ስለ ሠራች ሚስቱን አመሰገናት መረቃትም የተመሰገነ እግዚአብሔርንም በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ድንቅ ሥራ ስለሚሠራ አመሰገነው። መብራትና ማዕጠንትም እንዳይለየው ሚስቱን አዘዛት ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስን ጌታችን እስከ አጠፋው ድረስ እንዲሁ የምትሠራ ሆነች። ❤ ከዚህም በኋላ መልካም ቤተ ክርስቲያን አንፀው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ በዚች ዕለትም ሰኔ 1 አከበሩዋት ከሥጋውም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ለውንትዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ #የሰኔ_1_ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ ናሁ ዘእንተ ሠራዕከ እሙንቱ ነሠቱ። ወጻድቅሰ ምንተ ገብረ። እግዚአብሔር ውስተ ጽርሐ መቅደሱ። መዝ 10፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥42-ፍ.ም።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወሤሞ መልአከ አሕዛብ። ወረሰዮ እግዚአ ለቤቱ። ወአኰነኖ ላዕለ ኵሉ ጥሪቱ"። መዝ 104፥21-22። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥21-32፣ 1ኛ ጴጥ 4፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥9-23። የሚነበበው ወንጌል 24፥45-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የማርያም ቅዳሴ ነው፡፡ መልካም የቅዱስ ዮሴፍና የሚስቱ የቅድስት አሰኔት የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ዮሴፍ ከታሰረ ከሁለት ዓመት በኋላ ንጉሡ ፈርዖን ሕልም አየ፡፡ በነጋም ጊዜ ነፍሱ ታውካ የግብፅን ሕልም ተርጓሚዎችና ጠቢባንን ሁሉ ሰብስቦ እንዲተረጉሙለት ሕልሙን በዝርዝር ነገራቸው፡፡ ነገር ግን ሊተረጉሙለት አልቻሉም ነበር፡፡ የንጉሡም የጠጅ አሳላፊ አስቀድም ከዮሴፍ ጋር ታስሮ ሳለ እርሱ ያየውን ሕልም ዮሴፍ ተርጉሞለት እንደነገረው ሆኖለት ስለነበር በዚህ ጊዜ የጠጅ አሳላፈው ለንጉሡ ስለ የሴፍ ነገረው፡፡ ፈርዖንም ዮሴፍን አስመጥቶ ሕልሙን ነግሮት ተረጎመለት፡፡ በፈርዖንም ሕልም መሠረት ሰባት ዓመታት ጥጋብ እንደሚሆንና ከዚያም በኋላ ሰባት የርኃብ ዓመታት እንደሚመጡ ነገረው፡፡ ፈርዖንም ዮሴፍን "እኔ በዙፋኔ ብቻ ከአንተ እበልጣለሁ" ብሎ በቤቱና በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ሾመው፡፡ ቀለበቱንም አውጥቶ አሰረለት፡፡ ይህም የሆነው በ30 ዘመኑ ነው፡፡ ዮሴፍ በእናት በባቱ ቤት 17 ዓመት፣ በጲጥፋራ ቤት 10 ዓመት፣ በእስር ቤት ሁለት ዓመት ተቀምጦ ባጠቃላይ ልክ 30 ዓመት ሲሆነው በፈርዖን ፊት ለሹመት ቆመ፡፡ ይኸውም ምሳሌ ነው፡፡ ዮሴፍ በ30 ዘመኑ ለሹመት በፈርዖን ፊት እንደቆመ ሁሉ ጌታችን መድኃኔዓም ክርስቶስም በጲላጦስ ፊት ለፍርድ የቆመው በ30 ዘመኑ ነው፡፡ ❤ ዮሴፍም በግብፅ ምድር ዞሮ የሰባቱን ዓመት እጅግ ብዙ እህል ሰበሰበ፡፡ ሰባቱም የጥጋብ ዘመን ሲያልፍ ሰባቱ የርኃብ ዘመን በጀመረ ጊዜ በሀገሩ ሁሉ ታላቅ ርኃብ ሆነ ነገር ግን በግብፅ ምድር ብቻ እህል ነበር፡፡ ንጉሡም ከየሀገሩ ሁሉ ወደ እርሱ የሚመጡትን ወደ ዮሴፍ እየላካቸው ዮሴፍም እህል ከጎተራ እያወጣ ይሸጥላቸው ነበር፡፡ የዮሴፍ አባት ያዕቆብ በግብፅ እህል እንዳለ በሰማ ጊዜ ልጆቹን እህል እንዲሸምቱ ወደ ግብፅ ላካቸው፡፡ ነገር ግን ክፉ እንዳያገኘው ብሎ የዮሴፍን ወንድም ብንያምን ከእነርሱ ጋር አላከውም ነበር፡፡ ዮሴፍም ዐሥሩ ወንድሞቹ ከሕዝቡ ጋር ገብተው ሲሰግዱለት አይቶ ዐወቃቸው፣ እነርሱ ግን የሰገዱለት የሀገሩ ገዥ ስለነበረ ነው እንጂ ወንድማቸው እንደሆነ ዐላወቁትም ነበር፡፡ ዮሴፍም በልጅነቱ ከእነርሱ ጋር ሳለ ያየውን ሕልም አሰበ፡፡ እነርሱም ስለራሳቸው በነገሩት ጊዜ "እቤት የቀረውን ወንድማችሁን አምጡ" ብሎ ለርኃባቸው እህሉን ሰጥቶ አንዱን (ስምዖንን) ለይቶ አስቀርቶ ዘጠኙን ስንቃቸውን ጭኑ ወደ አባታቸው ቤት ወደ ከነዓን ላካቸው፡፡ ሄደውም የሆነውን ለያዕቆብ ነገሩት፡፡ እርሱም ከወንድማቸው ጋር ድጋሚ ወደ ግብፅ ላካቸውና ድጋሚ በዮሴፍ ፊት ሰግደው ሰላምታ አቅርበው እጅ መንሻን አመጡለት፡፡ ዮሴፍም የእናቱን ልጅ ብንያምን ባየው ጊዜ ወደ ውስጥ ገብቶ አለቀሰ፡፡ ዮሴፍ ቆይቶ ራሱን ገለጠላቸው፡፡ ያደረጉበትንም ነገራቸው፡፡ የርኃቡም ዘመን ገና 5 ዓመት ይቀረው ነበርና ዮሴፍ ወንድሞቹን "ስለሸጣችሁኝ አትዘኑ እነሆ ሕይወታችሁን ለማዳን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከእናንተ በፊት ወደ ግብፅ ልኮኛል" አላቸው፡፡ አባቱንም ወደ እርሱ እንዲያመጡት ላካቸው፡፡ ያዕቆብም ከነቤተሰቡ ንብረቱንም ሁሉ ሰብስቦ ወደ ግብፅ ወረደ፡፡ ልጁን ዮሴፍንም ባየው ጊዜ እያለቀሰ አቅፎ ከሳመው በኋላ ሞቱን ተመኘ፡፡ ❤ በግብፅ የያዕቆብ የልጅ ልጆቹ ቁጥር 66 ሆነ፡፡ ከዮሴፍም ልጆች ጋር አንድ ላይ 70 ሆኑ፡፡ ያዕቆብም ፈርዖንን ገብቶ ከባረከው በኋላ በግብፅ ጌሤም ምድር 17 ዓመት ተቀመጠ፡፡ ዘመኑም 140 በሆነ ጊዜ በሞት ማረፉን ዐውቆ ልጁን ዮሴፍን ጠርቶ በአባቶቹ መቃብር ቤት ውስዶ እንዲቀብረው ነገረው፡፡ የዮሴፍንም ሁለቱን ልጆች ምናሴንና ኤፍሬምን ባረካቸው፡፡ "አባቶቼ አብርሃምና ይስሐቅ በፊቱ የሄዱለት እርሱ እግዚአብሔር፣ ከታናሽነቴ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እኔን የመገበኝ እግዚአብሔር፣ ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ፤ ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅ ስም በእነርሱ ይጠራ፤ በምድርም መካከል ይብዙ" ብሎ ባረካቸው፡፡ ያዕቆብም ልጆቹን ጠርቶ ወደፊት የሚሆነውን ሁሉ ይልቁንም የጌታችንን የመወለዱን ነገር በምሳሌ እያደረገ ነገራቸው፡፡ እያንዳንዳቸውንም እንደ በረከታቸው ባረካቸውና በአብርሃምና በይስሐቅ ሣራም በተቀበረችበት መቃብር ወስደው እንዲቀብሩት ከነገራቸው በኋላ በ137 ዕድሜው እግሮቹን በአልጋው ላይ ሰብስቦ በሰላም ዐረፈ፡፡ የግብፅ ሰዎችም 70 ቀን አለቀሱለት፡፡ ዮሴፍም አባቱን ባዘዘው ቦታ በእነ አብርሃም መቃብር ከቀበረው በኋላ ወደ ግብፅ ተመለሰ፡፡ ❤ የዮሴፍም ወንድሞች አባታቸው እንደ ሞተ ባዩ ጊዜ "ምናልባት ዮሴፍ ይጠላን ይሆናል፣ ባደረግንበትም ክፋት ሁሉ ብድራት ይመልስብን ይሆናል" ብለው ፈርተው ወደ ዮሴፍ መልዕክት ልከው "አባትህ ገና ሳይሞት 'ዮሴፍን እባክህ የወንድሞችህን በደል ኃጢአታቸውንም ይቅር በል፣ እነርሱ በአንተ ከፍተውብሃልና፤ አሁንም እባክህ የአባትህ አምላክ ባሪያዎች የበደሉህን ይቅር በል' ብሎሃል" ብለው ላኩለት፡፡ ወንድሞቹም መጥው በፊቱም ሰግደው "እነሆ እኛ ለአንተ ባሪያዎችህ ነን፣ በአባቶችህ አምላክ ባሮችህን ኃጢአታችንን ይቅር በለን" አሉት፡፡ ዮሴፍም እንዲህ ሲሉት አለቀሰ፡፡ እርሱም "ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ፈቃድ የተደረገ ስለሆነ አይዟችሁ አትፍሩ" እያለ እንዳይፈሩ አጽናናቸው፤ ደስም አሰኛቸው፡፡ ዮሴፍም በግብፅ ተቀምጦ 110 ዓመት ኖረ፡፡ ❤ የኤፍሬምን ልጆች እስከ ሦስት ትውልድ ካየ በኋላ ወንድሞቹን ጠርቶ "እኔ እሞታለሁ፤ እግዚአብሔርም መጎብኘትን ይጎበኛችኋል፣ ከዚህችም ምድር ያወጣችኋል፤ ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም ወደማለላቸው ምድር ያደርሳችኋል፡፡ እግዚአብሔር ሲያስባችሁ አጥንቴን ከዚህ አንሥታችሁ ከእናንተ ጋር ውሰዱ እንጂ ከዚህ አትተውት" ብሎ አማላቸው፡፡ ዮሴፍም በ110 ዕድሜው በሰላም በዚች ቀን ዐረፈ፡፡ በሽቱ አሽተው በግብፅ ምድር በሣጥን ውስጥ አኖሩት፡፡ ዮሴፍም "እግዚአብሔር ሲያስባችሁ አጥንቴን ከዚህ አንሥታችሁ ከእናንተ ጋር ውሰዱ እንጂ ከዚህ አትተውት" ማለቱ አንድም ከግብፅ ምድር እንደሚወጡና የአባቶቻቸውን ርስት ከነዓንን እንደሚወርሱ ሲነግራቸው ነው፡፡ ፍጻሜው ግን ግብፅ የመቃብር ከነዓን የትንሣኤ ምሳሌ ናቸው፡፡ አንድም ግብፅ የገሃነም ከነዓን የመንግሥተ ሰማይ ምሳሌ ናቸው፡፡ ያዕቆብም እንዲሁ ብሏልና ዮሴፍም እንዲህ ያለ ስለምን ነው ቢሉ አባቶቻችን እንዲህ ማለታቸው መውጣታችንን ቢያውቁ ነው ብለው እንዲነቁ፣ እንዲተጉ፣ አንድም ለማጸየፍ ነው፣ "አባቶቻችን አጥንታችን እንኳን ከዚህ አይቅር" ብለዋል ብለው እንውጣ እንዲሉ ነው፡፡ ከቅዱስ ዮሴፍ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎቱም ይማረን!። ምንጭ፦ አትሮንስ ሚድያ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የቅዱስ_ለውንትዮስ_የቤተክርስቲያ_ቅዳሴ ቤት፦ ይኸውም ቅዱስ ለውንትዮስ በሐምሌ ወር በሃያ ሁለተኛው ቀን በሰማዕትነት በዐረፈ ጊዜ ከታላላቅ መኳንንቶች የአንዱ መኰንን ሚስት መጣች ለወታደሮቹም ብዙ ገንዘብ ሰጠች የቅዱሱንም ሥጋ ወሰደች በባሏም ልብስ ገነዘችው በሣጥንም አድርጋ በቤቷ ውስጥ አስቀመጠችው በቀንና በሌሊትም የሚያበራ መብራት በፊቱ አኖረች። እንሆም ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በመኰንኑ ባሏ ላይ በሆነ ሥራ ምክንያት ተቈጣ። በአንጾኪያም ከተማ በወህኒ ቤት አሠረው።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤ ❤ #የተባረከ_የሰኔ_ወር_ቀኑ_ዐሥራ_አምስት_ሰዓት ነው። ከዚህም በኋላ ይጐድላል።                ❤ #ሰኔ ፩ (1) ቀን። ❤ እንኳን #እስራኤል_ለተባለው_ለያዕቆብ ልጅ #ለጻድቁ_ለቅዱስ_ዮሴፍና_ለሚስቱ #ለቅድስት_አሰኔት_ለዕረፍት_ቀን_መታሰቢያ_በዓል፣ ከእርሱ ተአምራት ለተገለጡ #ለሶርያ_ሰው_ለሆነ #ለቅዱስ_ለውንትዮስ_ለቤተ_ክርስቲያኑ_ለቅዳሴ ቤቱ በዓልና ለመስተጋድል ለሰማዕት #ለቅዱስ_ቢፋሞን_ለዕረፍቱ_መታሰቢያና በስሙ ከታነፁ አብያተ ክርስቲያናት የመጀመርያዪቱ ቤተ ክርስቲያን ለቅዳሴ ቤቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ ከላይኛው ግብፅ ከጣሀ አውራጃ ከሆኑ ከባልጀራሞች ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው፣ #ከሰማዕት_ቆዝሞስ_ከዕረፍቱ መታሰቢያና፣ #ከእስክድርያ_ከተማ_ሰማዕታትና #ከሊቀ_ጳጳሳት_ቶማስም_ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_ዮሴፍ፦ አባቱ ያዕቆብ እናቱ ራሄል ይባላሉ፡፡ ለአባቱ 11ኛ ልጅ ነው፡፡ አባቱ ያዕቆብ የወንድሙን የኤሳውን በረከት ከአባቱ ከወሰደ በኋላ ከኤሳው ሸሽቶ ወደ አጎቱ ላባ ዘንድ ተሰዶ 14 ዓመት ለላባ ተገዝቶ ራሄልንና ርብቃን አግብቶ ብዙ ልጆችን ወለደ፡፡ ሀብት ንብረትም ካፈራ ከ21 ዓመት በኋላ ወደ አባቱ አገር ተመልሶ ከወንድሙ ጋር ታረቀ፡፡ ያዕቆብም በምድረ በዳ አቅራቢያ ባለች አብርሃም ይቀመጥባት ከነበረ አገር ከአባቱ ከይስሐቅ ዘንድ ደረሰ፡፡ ይህችውም በከነዓን ያለችው ኬብሮን ናት፡፡ አባቱ ይስሐቅ አብርሃም ይቀመጥባት በነበረችው የወይራ ዛፍ ሥር ተቀምጦ አገኘው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ይስሐቅ አርጅቶ ዘመኑን ጨርሶ ሞተ፡፡ ያዕቆብም አባቱ ይስሐቅ ይኖርባት በነበረች አገር ኖረ፡፡ ያንጊዜም ልጁ ዮሴፍ 17 ዓመት ሆኖት ነበር፡፡ እርሱም ከአባቱ ከያዕቆብ ሚስቶች ከዘለፋ ልጆችና ከባላ ልጆች ጋር የአባቱን በጎች ይጠብቅ ነበር፡፡ ያዕቆብም በእርጅናው ዘመን ወልዶታልና አብልጦ ይወደው ነበር፡፡ ወንድሞቹም በዚህ ምክንያት ጠሉት፡፡ ዮሴፍም ሕልም አልሞ ሕልሙን ለወንድሞቹ ነገራቸው፡፡ ዮሴፍም ያየው ሕልም 11ዱ ወንድሞቹና አባቱም ጭምር ለዮሴፍ እንደሚገዙለትና እንደሚሰግዱለት የሚያሳይ ነበር፡፡ ይህንንም ሕልሙን ሲሰሙ ወንድሞቹ ይበልጥ ጠሉት፡፡ ❤ የዮሴፍም ወንድሞች የአባታቸውን በጎች ይዘው ወደ ሴኬም ጎዳና ሄዱ፡፡ አባቱም ዮሴፍን "ወንድሞችህን አይተሃቸው ና" ብሎ ስንቃቸውን ቋጥሮ ወደ ቆላው ላከው፡፡ ሴኬምም እንደደረሰ አንድ ሰው ወንድሞቹ ያሉበትን አሳይቶት ወደ ዶታይን ወረደ፤ በዶታይንም አገኛቸው፡፡ እነርሱም በሩቅ ሳለ አዩትና ወደ እነርሱ ገና ሳይቀርብ ይገድሉት ዘንድ በእርሱ ላይ ተማከሩ፡፡ "እንግደለውና በአንድ ጕድጓድ ውስጥ እንጣለው፡፡ ክፉ አውሬም በላው እንላለን" ብለው ሲመካከሩ ከእነርሱ ውስጥ ሮቤል ይህን ሲሰማ "ሕይወቱን አናጥፋ፣ ደም አታፍስሱ፤ በዚህች ምድረ በዳ ባለችው ጕድጓድ ጣሉት፣ ነገር ግን እጃችሁን አትጣሉበት" አላቸው፡፡ ሮቤልም እንዲህ ማለቱ ከእጃቸው ሊያድነውና ወደ አባቱ ሊመልሰው ነው፡፡ ❤ ዮሴፍንም ቀሚሱን ገፈው ወስደው ወደ ቀበሮ ጕድጓድ ጣሉት፡፡ ጉድጓዱንም በድንጋይ ገጥመው በላይ ተቀምጠው ዮሴፍ ያመጣላቸውን እንጀራ እየተመገቡ ሳለ የእስማኤላውያን ነገዶች ወደ ግብፅ ለመውረድ ከገለዓድ ሲመጡ አይተው በይሁዳ ምክር ወንድማቸውን ከጕድጓድ አውጥተው ለእስማኤላውያን በሃያ ብር ሸጡት፤ እስማኤላውያንም ዮሴፍን ወደ ግብፅ ወሰዱት፡፡ የፈርዖን ጃንደረባ የዘበኞቹም አለቃ የሚሆን የግብፅ ሰው ጲጥፋራ ዮሴፍን ወደ ግብፅ ካወረዱት ከእስማኤላውያን እጅ ገዛው፡፡ እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር ነበረ፣ ሥራውም የተከናወነለት ሰው ሆነ፡፡ ጌታውም እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንዳለ፣ እርሱ የሚሠራውንም ሁሉ እግዚአብሔር በእጁ እንዲያከናውንለት አየ፡፡ ❤ ዮሴፍም በጌታው ፊት ሞገስን ስላገኘ በቤቱ ላይ ሾመው፣ ያለውንም ሁሉ በእጁ ሰጠው፡፡ በቤቱ ባለውም ሁሉ ላይ ከሾመው በኋላ እግዚአብሔር የግብፃዊውን ቤት ስለ ዮሴፍ ባረከው፤ የእግዚአብሔር በረከት በውጪም በግቢም ባለው ሁሉ ላይ ሆነ፡፡ ጲጥፋራም ያለውን ሁሉ ለዮሴፍ አስረከበ። የዮሴፍም ፊቱ መልከ መልካምና ውብ ነበረ፡፡ ይኸውም ምሳሌ ነው፡፡ ዮሴፍ የጌታችን፣ ወንድሞቹ ደግሞ የአይሁድ ምሳሌ ናቸው፡፡ ዮሴፍ ምግባቸውን ይዞላቸው ቢሄድ ከበው እንደደበደቡት ሁሉ ጌታችንም "እኔ ግን እላችኋለሁ…›" እያለ የነፍሳቸውን ምግብ ቢያስተምራቸው አይሁድ ጠልተውት ገድለውታል፡፡ ዮሴፍ እንዲሸጥ ሀሳብ ያመጣው ይሁዳም ጌታችንን የሸጠው የይሁዳ ምሳሌ ነው፡፡ ዮሴፍ በግብፅ ሕያው በከነዓን ግን ምውት እንደሆነ ሁሉ ጌታችንም በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በትስብእቱ ግን ምውት ሆኗል፡፡ ❤ ወንድሞቹም የዮሴፍን ቀሚስ ወስደው የፍየል አውራም አርደው ቀሚሱን በደም ነክረው ወደ አባታቸው ሄደው "ይህንን አገኘን፣ ይህ የልጅህ ልብስ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ እስኪ እየው" አሉት፡፡ ያቆዕብም "ይህ የልጄ ቀሚስ ነው፤ ክፉ አውሬ በልቶታል" ካለ በኋላ ልብሱን ቀዶ በወገቡም ማቅ ታጥቆ ለልጁ ብዙ ጊዜ አምርሮ ስላለቀሰ ዐይኑ ጠፋ፡፡ ❤ ዮሴፍም ጌታውን በቅንነት እያገለገለ ሲኖር የጌታው ሚስት ባሏ በሌለበት ጠብቃ በዮሴፍ ላይ የዝሙት ዐይኗን ጣለችበትና "ከእኔ ጋር ተኛ" አለችው፡፡ ዮሴፍም "እነሆ ጌታዬ በቤቱ ያለውን ምንም ምን የሚያውቀው የለም፣ ያለውንም ሁሉ ለእኔ አስረክቦኛል፤ ለዚህ ቤት ከእኔ የሚበልጥ ሰው የለም፤ ሚስቱ ስለሆንሽ ከአንቺም በቀር ያልሰጠኝ ነገር የለም፤ እንዴት ይህን ትልቅ ክፉ ነገር አደርጋለሁ? በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ኃጢአትን እሠራለሁ?" አላት፡፡ እርሷ ግን ስለዚህ ነገር በየጊዜው ትጨቀጭቀው ነበር፡፡ አንድ ቀን ወደ ቤቱ በገባ ጊዜ በቤት ውስጥ ከቤት ሰዎች ማንም ስላልነበረ ወደ እርሱ ገብታ ከእኔ ጋር ተኛ ስትል ልብሱን ተጠማጥማ ያዘች፤ እርሱም ልብሱን በእጅዋ ትቶላት ሸሽቶ ወደ ውጭ ወጥቶ ሄደ፡፡ የጲጥፋራ ሚስት ግን የቤቷን ሰዎች ጠርታ "እዩ ዕብራዊው ሰው ከእኔ ጋር ሊተኛ ወደ እኔ ገባ፣ እኔም ድምፄን ከፍ አድርጌ ስጮኽ ቢሰማ ልብሱን በእኔ ዘንድ ጥሎ ሸሸ ወደ ውጭም ወጣ" ብላ በሐሰት ከሰሰችው፡፡ ባሏም ሲመጣ እንዲሁ ብላ ነገረችው፡፡ ባሏም የእርሷን ቃል በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ዮሴፍን ይዞ እስር ቤት ጣለው፡፡ እግዚአብሔርም ከዮሴፍ ጋር ነበረ ምሕረትንም አበዛለት፥ በግዞት ቤቱም አለቃ ፊት ሞገስን ሰጠው፡፡ የሚያደርገውንም ሁሉ እግዚአብሔር ያቀናለት ነበር፡፡ ❤ የጲጥፋራ ሚስት የኃጢአት ምሳሌ ስትሆን ዮሴፍ የንጽሕና ምሳሌ ነው፡፡ ኃጢአት ደርሳ ሥሩኝ ሥሩኝ ስትላችሁ የንጽሕናን የቅድስናን ነገር አስባችሁ ፈጥናችሁ ከእርሷ ተለዩ ሲል ነው፡፡ ንጽሕናችሁን በኃጢአት አታቆሽሹ አለ፡፡ አንድም የጲጥፋራ ሚስት የዚህ ዓለም ዮሴፍ የመናንያን ምሳሌ ነው፡፡ ዮሴፍን የጲጥፋራ ሚስት ሽንገላ ሳያታልለው ጥሏት እንደሸሸ ሁሉ መናንያንም የዚህ ዓለም ሀብት፣ ንብረት፣ ቤት፣ ልጅ፣ ባል፣ ሚስት… ሳያታልላቸው የዓለምን ጣዕም ሸሽተው ገዳም ይገባሉና ነው፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለሐዋርያት_ለሰኔ_ጾም_የመጀመሪያ_ሳምንት ስለ #መንፈስ_ቅዱስ (ጰራቅሊጦስ) ነገር ለሚነገርበት ዕለት እሑድ  እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የታች_ቤት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፪ "#ወረደ_መንፈስ_ቅዱስ ላዕለ ሐዋርያት ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት"። ትርጉም፦ #መንፈስ_ቅዱስ በሐዋርያት ላይ እንደ እሳት ሙላድ (በእሳት አምሳል) ወረደ፤ በሀገሮች ሁሉ ቋንቋ ተናገሩ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_በላይ_ቤት፦ ሃሌ ሉያ ፬ "ዐርገ እምኀቤሆሙ #ጰራቅሊጦስሃ_እፌኑ_ለክሙ ዘይሄሉ ዘልፈ ምስሌክሙ ኢየኀድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ ዘኢይክል ዓለም ነሢኦቶ። ትርጉም፦ ከእነርሱ ወደ ሰማይ ዐረገ እንዲህም አላቸው፤ ዘወትር ጸጋ በረድኤት የማይለያችሁ፣ ከጭንቀት የሚያረጋጋ፣ ከኀዘን የሚያጽናና፣ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ በመከራ ውስጥ የሚያስደስት ኃይል የሚሰ ምሥጢር የሚገልጥ #መንፈስ_ቅዱስን_እልክላችኋለሁ ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች ትኾኑ ዘንድ አልተዋችሁም። ይህን ዓለም ሊቀበለው የማይችል ነው።                                                      ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_ዕለቱ_ምስባክ፦"ዐርገ ውስተ አርያም ፄዊወከ ፄዋ። ወወሀብከ ጸጋከ ለእጓለ እመሕያው። እስመ ይክሕዱ ከመ ይኅድሩ"። መዝ 67፥18-19። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 4፥1-17፣ 1ኛ ዮሐ 2፥1-18 እና የሐዋ ሥራ 2፥1-14። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 14፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮ ቅዳሴ ነው። መልካም ዕለት ሰንበትና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ከዚያም ከመሰቀል ያዳነችው ወጣት ልጅ አባት ቀረበና፣"ልጄ ዐይነ ሥውር ኹኖብኛልና ስለርሱ ለምነሽ አድኝልኝ" አላት። እርሷም ኃጢአቱን እንዲናዘዝ ጠየቀችው። ያም ወጣት መቶ ዲናር ሰጥታ ከመሰቀል ያዳነችውን አንዲት ሴት ፈቃዱን እንድትፈጽም ሲጠይቃት ባይኾንለት በግፍ ለመርከበኞች እንደሸጣትና ከነርሱም ተለይቶ እንደተመለሰ ወዲያውኑ ዐይነ ሥውር እንደኾነ ተናዘዘ። እርሷም "እንዲህ ያለህ ቀጣፊ ነህ፣ ኾኖም አሁን ግን እግዚአብሔር በግልጥ እንድትናገር አድርጎሃል" ብለ ገሠጸችውና በዐይኖቹ ላይ ጸልያ አዳነችው። ግብጻዊውም ከዕብራዊ አገልጋዩ ጋር ቀረበና እንድትፈውሰው ጠየቃት። እርሱም ከመቃብር ውስጥ ያወጣት አርሷ እንደኾነች፡ከቶ አላወቃትም ነበር። እርሷም ዕብራዊው የሠራውን ክፉ በደል ከተናገረ እንደምትፈውሰው ነገረችው። ያም፡ግብጻዊ "ያደረግኸውን ፈጥነህ ተናገር፣ አለዚያ ግን እዚሁ ጥዬህ እመለሳለሁ" አለው። ዕብራዊውም "አንዲት እስራኤላዊት ሴት እኛ ዘንድ መጣች። ከእኔ ጋርም አንድ እንድትኾን ጠይቅኋት፣ አይኾንም ባለችኝም ጊዜ የአንተን ልጅ ከእናቱ ወስጄ በወቅለምት ገደልሁና ከአጠገቧ አደረግሁ፣ ወቅለምቱምንም እጇ ከሚደርስበት ቦታ አኖርሁት፣ ይህንም ማድረጌ ፈቃዴን ስላልፈጸመችልኝ አንተ እንድትገድላት ብዬ ነው" አለው። ከዚህም በኋላ ጸለየችለትና አዳነችው። ❤ ከዚህም በኋላ የዚያች ደሴት ሰዎች ኹሉ የሚሹትን ካገኙ በኋላ ኹላቸውም ኼዱና ቅድስት አርዋ እና ባልዋ ቀሩ። ከዚያም ትጠይቀው ጀመረች። "እንዲህ የምትናገርላት ሚስትህ እኔን ትመስላለችን?" አለችው። እርሱም "አፍንጫዋ ዐይኖቿ ኹሉ አንቺን ይመስላሉ። እርስዋ ካልሞተች አንቺ እርሷ ትኾኝን?" አለ። እርስም መልሳ ሚስቱ አርዋ እንደኾነች ነገረችው። ከዚህም በኋላ የቅድስት አርዋ ባል ወደርሷ ሊደርስ ወደደ። እርሷ ግን "እዚህ አይኾንም፣ ታጥቤ እመጣለሁ ወደ ቤታችን" አለችውና እርሱ ወደ ቤት ኼደ። እርሷም ወደ ዋሻዋ ተመለሰችና ሰውነቷን ታጥባ ንጹሕ ልብስ ከለበሰች በኋላ ከዋሻው ወጣች። ቀድማ ግን ጌታችንን እንዲህ ስትል ተማጸነች። "ጌታዬ አምላኬ ከወደድኸኝ ነፍሴን ተቀበላትና ዳግመኛ ከወንድ ሳልገናኝ ልሙት" በማለት ጸለየች። ወዲያውም ሰገደችና ዐረፈች። ባልዋም መጣና ዐርፋ አገኛት። ወስዶም ቀበራት።  ከእናታችን ከቅድስት አርዋ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን ጸሎቷ ይማረን!። ምንጭ፦Dn Melaku Yifru Zewulude Birhan.                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ሚካኤል፦ ይህም አባት ለአባቶች ሊቃነ ለእስክንድርያ ጳጳሳት ስሳ ስምንተኛ ነው። የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ስለ ተማረ አዋቂ ነበር። በልቡም አጠናቸዌ በቃሉም አጠናቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ንጸሕት ሰውነቱ ከአምላክ በተገኘ የምንኵስና መንገድ በመጋደል ክብር ይግባውና የክርስቶስ ጭፍራ ልትሆን ወደደች። ወደ አስቄጥስ ገዳም ሒዶ በውስጡ ብዙ ዓመታት ኖረ ቅስናም ተሾመ። ❤ ከዚህም በኋላ በግጽ አገር ወደ አለ ወደ ሠንጋር ወጣ በዚያም በዋሻ ውስጥ ራሱን እሥረኛ አደርጎ አርባ ዓመት ኖረ ከዚያም የሚበዛ ኖረ በዚያም ዋሻ ውስጥ ታላቅ ተጋድሎ ተጋደለ። የትሩፋቱ የጽድቁምና የዕውቀቱ ወሬ በተሰማ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ኤጲስቆጶሳት ተስማሙ ወዲያውኑ ይዘው በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። ❤ በተሾመም ጊዜ በጎ አካሔድን ሔደ የዚህን ዓለም ጥሪት ሁሉ ንቆ ተወ። ከሚገባው ከሚአመጡለት ገጸ በረከት አንድ ዲናር ወይም አላድ ጥሪት አድርጎ አላኖረም። ከእርሱ በየጥቂት እየተመገበ የቀረውን ለድኃና ለጦም አዳሪ ይሰጣል ለአብያተ ክርስቲያናትም ለንዋየ ቅዱሳትና ለቅዱሳት መጻሕፍት መግዣ ያደርገዋል። ሕዝቡንም ያስተማራቸዋና ይገሥጻቸው ይመክራቸውም ነበር። አንድ ጊዜ ከመጻሕፍት አንድ ጊዜም ከቃሉ። ❤ መልካም አገልግሎቱንም በፈጸመ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ከዚህ ዓለም ድካም ሊያሳርፈው የሕይወትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ሊሰጠው ወዶ የአንዲት ቀንና የአንዲት ሌሊት ሕማም በላዩ አመጣ። ከቶ አልተናገረም በሚሞትበትም ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችንን አመሰገነው ፊቱንም በመስቀል ምልክት አማተበ። ነፍሱንም ክብር ይግባውና በእግዚአብሔር እጅ ግንቦት30 ቀን ሰጠ መላ ዕድሜውም ዘጠና ዓመት ከስምንት ወር ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ሚካኤል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። የግንቦት ወር ንባብ ተፈጸመ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ለመንግሥተ ሰማያት የተዘጋጀን ያደርገን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የንግቦት30 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለቆሮስ_ለወልደ_ማርያም_ዘተልእኮ። መጠነ ፫ቱ ዓመት በኢያውክኮ። ወእምድ ኅረዝ ዐርገ #ካዕበ_ምስለ_ጳውሎስ ተወሲኮ። እምነ ሥቃይ ዘረከቦ ወእምንዳቤ ዘሆኮ። አመ ፍጻሜ ወርኅ አዕረፈ በሠናይ አምልኮ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_30። ❤ መልካም የቅዱስ ቆሮስ የዕረፍት በዓል፣ የቅድስት ዜና ማርያም የዕረፍት በዐልና የበዐለ ጰራቅሊጦስ ሰሞንና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

መኾንዋን ነገረው። ብዙ ሲፈልጋትም ከቆየ በኋላ በመንገድ አገኛት። ❤ በተመለከታትም ጊዜ ከመልኳ የተነሳ አደነቀ። ከርሱም ጋራ በመኝታ አንድ እንድትኾን በፈለገና መሻቱን በነገራት ጊዜ "እኔ አንተን ከዚህ ዓለም ምድራዊ እሳት ነጻ አደረግሁህ፣ አንተ ግን በሰማዩ እሳት ትጥለኝ ዘንድ እንዲህ ክፉ ምክንር ትመክረኛለህን?" አለችው። እግዚአብሔርንም እንደምትፈራ ባየ ጊዜ ተዋት። በኋላም በመርከብ የሚኼዱ ብዙ ሰዎችን ተመለከተና "በገንዘቤ ኹሉ የገዛኋት አንዲት አመት(አገልጋይ) አለቺኝ፣ ገንዘቤን መልሳችሁ ከሰጣችሁኝ እርሷን እሸጥላችኋለሁ" አላቸው። ከእነርሱም እጅግ ብዙ ወርቅ የነበረው(ይኸውም ማለት አንድ፡መቶ ዲናር የነበረው) አንድ ሰው ነበር። ያም እናታችን አርዋ ከስቅላት ያዳነችው ሰው ለዚያ ሰው በዚህ ገንዘብ ሸጣት። የገዛትም ሰው መርከብ እንድትሳፈር አደረጋት፣ መልኳንም ባየ ጊዜ ወደዳት ከርሷም ጋር ይተኛ ዘንድ ተመኘና እጇን ያዘ። በዚህም ጊዜ ፀሐይ ጨለመች፣ ነፋሳቱም እጅግ በኃይል ነፈሱ፣ ማዕበላቱም ፈጽመው ተነሱና መርከቡንም ሊያሰጥሙት ደረሱ። በዚያም በመርከቡ የነበሩት ኹሊ ወደ እግዚአብሔር፡ማልቀስና መጮህ ጀመሩ። ቅድስት አርዋም "እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፣ እምነቱን በእግዚአብሔር ያደረገ ከቶ አይሞትም፣ በርሱም የሚያምን ከቶም አይጠፋም" በማለት እግዚአብሔርን አመሰገነች። ❤ ወደ እነዚያም ሰዎች ዘወር አለችና "በማይገ'ባ የገዛችሁኝ እናንተ ሰዎች! እናንተም በማይገ'ባ የሸጣችሁኝ ሰዎች! እኔ ከቶ አመት(አገልጋይ) አይደለሁም፣ ነገር ግን እመቤት ነኝ እንጂ። እኔ የምላችሁንም የምታደርጉ ከኾነ ከዚህ መከራ የምትወጢበትን መንገድ እንዲያፈርግላችሁ እጸልያለሁ"። እነርሱም "እናደርገው ዘንድ የምትነግሪንን ኹሉ እናደርጋለን" አሏት። እርሷም "ይህ ሰው የሸጠኝ ከእኔ ጋር የተኛ ዘንድ ስላላሰናበትሁት ነው፥ ይህ ደግሞ እግዚአብሔር ከቶ የማይወደው ምግባር ነው" አለቻቸው። ሰዎቹም ኹሉ ገንዘብ አወጡና ዐሥር ሺህ ዲናር እርሷን ለገዛት ሰው ሰጡት። እርሱም ነጻ አደረጋት። አርዋም ጸለየችና ማዕበሉ ጸጥ አለ፣ ነፋሳቱም ቆሙ። ፈጽሞም ጸጥታ ኾነ። በዚያም የነበሩት ኹሉ ወደድዋትና በርሷም ላይ ሊወድቁ ተመኙና "እኔ እኔ" እየተባባሉ ሲገፋፉ ወዲያውኑ ነፋስ መጣና መርከቡን ሰባበረው። እነርሳቸውም ኹላቸው በባሕሩ ላይ ተበተኑና ሰጠሙ። ገንዘባቸውም ኹሉ ከርሷ ጋር ቀረ። የወንድ መታጠቂያ ሱሪም ሰራችና ራስዋንም መልክዋን ልክ እንደወንድ ተቀብታ በልብሷም ፈጽሞ ተመሳሰለችና በመርከብ ኼደች። ❤ ወደ አንድ ትልቅ ወደኾነ ብዙ ሰዎችም፡ወዳሉበት ደሴት ደረሰችና ወደ ንጉሡ ኼደች። ንጉሡም ባያት ጊዜ ገና ጽሕሙ ያላደገ ወጣት ወንድ መስላዋለች። ኋላም ቀርባ "እነሆ ገንዘቤ እጅግ ብዙ ነው፣ በዚያም ሙሉ ኹኖ የተጫነ መርከብ አለ። የዚያም ባለቤቶቹ የነበሩት በባሕር ሰጥመው ሙተው ጠፍተዋልና እንደምታየው እኔ አንዲት ደካማ ቀርቻለሁ። እኔም እንዳልጠፋ እሰጋለሁና ይህን ለአንተ አደራ እሰጣለሁ። ለሞቱትም ሰዎች ቤተሰብ ለእያንዳንዳቸው የድርሻቸውን ትሰጣቸው፡ዘንድ ደብዳቤ እጽፍልሃለሁ"። ንጉሡም ከሰዎቹ ገንዘብ ምንም ምን እንዳልወሰደች ተመልክቶ አደነቀ። ገንዘቡንም ተቀበለ። ቅድስት አርዋም እግዚአብሔርን በመፍራት ሳለች እግዚአብሔር ልመናዋን ሰማት፣ በጸሎትዋም ብዙ ድውያን ተፈወሱ። ከዚያም ተነስታ ወደ ባሕር ዳርቻ ኼደችና በዚያ በዋሻ ገብታ በገድል ተጸምዳ መኖር ጀመረ። የዚያችም ደሴት ንጉስ በጽኑዕ ታመመና ሰዎች ወደርሱ ተሰበዘቡ። ከዚያም በርሱ ፈንታ ሊነግሥ የሚገባውን ቢጠይቁት "በመርከብ እጅግ ብዙ ገንዘብ አምጥቶ የሰጠኝ አንድ ወጣት አለና እርሱ ከኔ በኋላ ንጉሥ ይኾን ዘንድ መርጫለሁ" አላቸው። እነርሱም በዚህ ነገር አደነቁና እጅግ ደስ ተሰኙ፥ "ከአንተ በኋላም፡ሊነግስ ይገባዋል፣ ይደልዎ" አሉ። ከዚህም፡በኋላ ንጉሡ ሞተ። ቅድስት አርዋንም በነርሱ ላይ አሰለጠንዋት፣ እርስዋም ወጣት ወንድ መስላቸው ነበር። እርሷም በልቧ እንዲህ አለች፥ "ይህ ቤተ መንግሥት ከእግዚአብሔር ያርቀኛል"። ከዚያም ይህን በነርሱ ላይ መሰልጠንን እና ንግሥናውን እንደማትፈልግ መናገር ወደደችና ሕዝቡን ኹሉ ሰብስባ እንዲህ አለች። ❤ "ከእናንተ ዘንድ ሴቶች ልጆችና እኅቶች ያሏችሁ ኹሉ በወርቅና በሐር በንጹሕም ልብስ አስጊጣችሁ ወደ እኔ አምጧቸው፥ ለእኔም ሚስት የምትኾነኝን እመርጣለሁ" አለቻቸው። እነርሱም ካመጡላት በኋላ ቅድስት አርዋ ከነዚያ ሴቶች ጋራ ለብቻዋ ከኾነች በኋላ የተሸፈነችበትን መሸፈኛዋን ኹሉ አውልቃ ተመለከቷት። ከመልከ መልካምነቷም የተነሳ እጅግ አደነቁ። እጅግም የተዋበች እንደኾነች ተመለከቱ። ምንም ወንድ ሳታገባ ብትመራቸውም እጅግ ደስ እንደሚሰኙ ነበሩ። እርሷ ግን በዚህ መቆየትን አልወደደችምና ወደ ዋሻዋ ተመልሳ በዚያ በገድል ተጸምዳ መኖርን ቀጠለች። በጸሎት የመትጋትዋና ድንቆችን የማድረጓ ዜና፣ ድውያንንም በጸሎት ኃይል የመፈወሷ ነገር በአገሩ ኹሉ ተሰማ። ❤ የአርዋም ባል(በዚህ ጊዜ ደክሞና አይነ ሥውርና ሽባ ኹኗል) ከብዙ ጊዜ በኋላ ወደ ቤቱ ተመለሰና። ቅድስቷን ባጣት ጊዜ ወንድሙን ሚስቴን አርዋን ምን አደረግህባት አለው። ወንድሙም መለሰና "ከወንድ ጋር አንድ ስትኾን አገኘናት፣ ከዚያም በድንጋይ ወገርናትና ገድለን ቀበርናት" አለው። የአርዋም ባል ዝም አለና ከብዙ ቀናት በኋላ ድውያንን የመፈወሷንና ሌሎችንም ድንቅ ዜናዎቿን ሰማና ወደ ወንድሙ ሄደና"በደሴቱ የምትኖር በጸሎትዋ የምትፈውስ አንዲት ቅድስት አለችና ወደዚያ ውሰደኝ" አለው። ወንድሙም "እዚያ ድረስ የምትኼድበትን አቅም አለህን" አለው። እርሱም "ተነስተን እንሂድ ምናልባት እግዚአብሔር ቢምረን" እያለ ለመነው። ኹለቱም ሰዎች ተያይዘው ወደርሷ ሲኼዱ በመንገድ ላይ አርዋ በመቶ ዲናር ነጻ ያወጣችውን ወጣት (አሁን ግን አይነ ሥውር ኹኖ ሳለ) እና የዚያን ግብጻዊ ጌታውን ሕጻን ልጅ የገደለውንም ዕብራዊ አይነ ሥውርና ድውይ ኾኖ በጌታው እየተመራ ሲወስደው አገኟቸው። አርዋ በመቶ ዲናር ያዳነችው ወጣት በአባቱ እየተመራ፣ የቅድስት አርዋ ባል ወንድም የቅድስት አርዋን ባል እየመራ፣ ያም ዕብራዊ ደግሞ በግብጻዊ ጌታው እየተመራ ኹላቸውም ከቅድስቲቷ ፊት ቀረቡ። ❤ እርስዋም በተመለከተቻቸው ጊዜ ኹሉንም አወቀቻቸው። እነርሱ ግን ከቶ አላወቋትም ነበር። በኋላም ወደ ዋሻዋ ገባችና ተመልሳ ወደ እነርሱ ወጣች። ባልዋም "አድኝ፣ እነሆም ገንዘብ እሰጥሻለሁ" አላት። እርሷም መልሳ "ከድውያን ገንዘብ አልወስድም፣ ከአንተ ግን እወስደዋለሁ፣ ወንድምህም ሊናገረው የሚገባው ሌላም ኃጢአት አለና የሠራውን ኹሉ ከዚህ ይናገረው እናም እንድትድን እንጸልይልሃለሁ" አለችው። እርሱም "ይህች ሴት በሚገ'ባ ተናግራለችና በል ያደረግኸውን ተናገር" አለው። እርሱም "ሚስትህን ጎበኘኋትና ከኔ ጋር እንድትተኛ ጠየቅኋት፣ አይኾንም ባለችም ጊዜ አራት የሐሰት ምስክር አስመስክሬባት ሕዝቡ በድንጋይ ወግረው እንዲገድሏት አደረግሁ" ብሎ ተናዘዘ። የአርዋም ባል "ሚስቴን እንዲህ በግፍ በመግደልህ እጅግ ክፉ አድርገሃል፣ አንድ አባትና አንድ እናት ነው ያለን፣ ላለፈው ነገር እንግዲህ ምን እናደርጋለን? ይቅር ብዬሃለሁ" አለው። አርዋም በባልዋ ዓይን ላይ ጸለየችና ዐይኑ ተከፈተ፣ እግሮቹም ከሽባነታቸው ፈጽመው ተፈቱ፣ መላው አካሉም ፈጽሞ እንደቀድሞው ደህና ኾነ።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት_አንዱ_ለሆነው #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ቆሮስ_ለዕረፍት፣ #ተጋዳ_ለሆነች_ፍትወተ_ሥጋን_ድል_ላደረገች በበጎ ሥራዋም እግዚአብሔርን ደስ ላሰነች #ለቅድስት_አርዋ_ለዕረፍት በዓልና ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት #ስሳ_ስምንተኛ_ለሆነ ለእስክድርያ ሊቀ ጳጳስ ለቅዱስ አባት #ለአባ_ሚካኤል ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። ተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰበው፦ #ከሰማዕት_ዲማዲስ_ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ቆሮስ፦ ይህም ቅዱስ ጌታችን በሚያስተምርበት ወራት ሦስት ዓመት አገልግሎታል ከዕረገቱ በኋላም ሐዋርያትን አገልግሏቸዋል ከእርሳቸውም ጋራ መንፈስ ቅዱስን ተቀበለ። ❤ ከዚህም በኋላ ከሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ጋራ በመሆን መልእክቶቹንም ወደ ብዙ አገሮች ተሸክሞ በመውሰድ አገለገለው። ከአይሁድና ከአሕዛብም ብዙዎቹን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትና አጠመቃቸው። ❤ ከዚህም በኋላም በምሥራቅ ወዳሉ አገሮች ሔደ ከምኵራቦችም ብዙ መከራ ደርሶበት ግንቦት 30 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቆሮስ ጸሎት ይማረ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ተጋዳ_የሆነች_ፍትወተ_ሥጋን_ድል_ያደረገች #ቅድስት_አርዋ፦ ይህችውም ቅድስት እስራኤላዊት ናት። ባልዋም እጅግ ብዙ ሀብት ያለው ባዕለ ጸጋ ነው። እርስዋም በውበትዋ በሥነላህይ በዚያ ከነበሩት ማንም ማን የማይተካከላት ሴት ናት። ባልዋም በንግድ ምክንያት ወደ ሩቅ አገር በኼደ ጊዜ ቤቱንና ንብረቱን ኹሉ ለወንድሙ አደራ ሰጥቶ ኼደ። የሚኼድበትም መንገድ ሩቅ ነበርና ለወንድሙ ኹሉንም ነገር አደራ ብሎ ወጣ። የባልዋም ወንድም ከጊዜ በኋላ ወደ እናታችን ይቀርብና "እኔ ባልሽን፡ስለፈራሁ እንጂ አንቺን ከወደድሁሽ ቆይቻለሁ፥ አሁን ግን እርሱ ርቆ ኼዷልና ስለዚህ ከአንቺ ጋር ላድር እወዳለሁ" በማለት ከእርሱ ጋራ አንድ እንድትኾን ይጠይቃታል። እርሷም "ምን እንኳ ባሌ ርቆ የኼደ ቢኾን እግዚአብሔር ሩቅ ነውን? ባሌ ሊያየኝስ ባይችል እግዚአብሔር ከሰማይ ሊያየኝ አይችልምን?" በማለት ገሠጸችው። እርሱም ተዋትና ወጣ። ❤ ከርሷም ወጥቶ በመንገድ ሲኼድ ግን ሰይጣን ከመንገድ ላይ አገኘውና እንዲህ አለው፣ "ፈጥነህ ወደርሷ ተመለስ፣ እኔም የወደድኸውን ኹሉ አደርግልሃለሁ" አለው። እርሱም ተመለሰና እንዲህ አላት፣ "እንግዲህ አሁን አንዱን ምረጭ፣ ከእኔ ጋራ የበመኝታ አንድ የምትኾኝ ከኾነ በሚገባ እንከባከብሻለሁ፣ ነገር ግን ይህን አይኾንም ብትዪኝ እንድትወገሪ አደርግሻለሁ" አላት። ቅድስት አርዋም መለሰችና "ምን ልታደርገኝ ትችላለህ" አለችው። ያም ሰው "ከእሥራኤል የለበሩ ሰዎች መኻከል ምስክሮችን አስነሳብሻለሁ፣ ባልሽ ወደ ሩቅ አገር ሲኼድ ሌላ ሰው አግብተሻልና"። እርሷም "አንተ የባሌ ወንድም ነህ፣ ከአንተም ጋር ከቶ እንዲህ አላደርግም። የወደድኸውን አድርግ፣ ከአንተም እጆች ቸሩ አምላኬ እግዚአብሔር ያድነኛል" አለችው። እርሱም ፈጥኖ ወጣና ወደ አገረ ገዢውና ወደ ሕዝቡ ኼደ። እነርሱም ኹላቸውም ተሰበሰቡ። እርሱም እንዲህ ሲል ቅድስት አርዋን ከሰሳት፣ "የወንድሜ ሚስት ባልዋ ወደ ሩቅ አገር ሲኼድ ሌላ ሰው አግብታለች" በማለት። እንዲህም ባላቸው ጊዜ ቅድስት አርዋን ይዘው አመጧትና ከአገረ ገዢው ፊት አቁመው የሐሰት ምስክር አቆሙባት። እሊያንም አራት የሐሰት ምስክሮች የባልዋ ወንድም "ከሌላ ወንድ ደርሳለችን?" ሲል ቢጠይቃቸው "አዎን ከሌላ ወንድ ደርሳ አይተናታል" ብለው በሐሰት በማያውቁት መሰከሩባት። ❤ አገረ ገዢውም ነገሩን ስንኳ ገና ሳይመረምር በዚህ ፈረደባትና ከከተማው ወደ ውጭ አውጥተው አገረ ገዥውም አብሮ በድንጋይ ወገሯት። ከፊቷም እጅግ ብዙ ደም እንደ ውሃ ፈሰሰና ሞተች። እርስዋም ጅግ መልከ መልካም ነበረችና (እሥራኤል በልማዳቸው በድንጋይ የወገሩትን ሰው የማይቀብሩት ኹነው ሳለ እርስዋን ግን ስለመልኳ ሲሉ) ቆፍረው በዚያው ቀበሯትና ተመለሱ። በኋላም አንድ ግብጻዊ ነጋዴ ከመንገድ አምስት ግመሎቹን ጭኖ በዚያ ሲያልፍ ከቅድስት አርዋ መቃብር አካባቢ ድምጽ ይሰማና ሲመጣ ቢመለከት ቅድስት አርዋን ልክ እንደፀሐይ ስታበራ አገኛት። እጇንም ሰጠችውና ከዚያ እንዲያወጣት ውኃም እንዲያጠጣት ጠየቀችው። እርሱም አወጣትና ውኃ ከሰጣት በኋላ ወደ ቤቱ ወሰዳት። ባለ መድኃኒትም አምጥቶላት ከቀድሞ ይልቅ በእጅጉ ደህና ኹና ተነሳች። ከዚያም በኋላ ይህ ግብጻዊ ቅድስት አርዋ እጅህ መልከ መልካም ነበረችና የርሱ እንድትኾን ተመኘ። ኋላም ከርሱ ጋራ እንድትተኛ ቢጠይቃት እርስዋ ግን "እግዚአብሔርን መትፈራም፣ ስለራስህስ አታዝንምን፣ ስለ ፍርድ ቀንና ስለዓለም ፍጻሜስ አታስብምን ከቶ አታስብምን? ከአንተ ጋር ከቶ እንዲህ አላደርግም፣ ስለምንስ ባሌን እበድለዋለሁ?" አለችው። እርሱም ትቷት ወደ ውጭ ወጣ። ❤ ለዚህም ሰው የሚያገለግለው አንድ ዕብራዊ ሰው ነበር፣ ከዚህም በኋላ እርሱ ወደርሷ ገባና "አንድ እንድንሆን እወዳለሁና ፈቃዴን ፈጽሚልኝ" አላት። "እንደውሻ የኾንህ አንተ ከእኔ ዘወር በል!" በማለት ገሠጸችው። ይህም ሰው ፈቃዱን ስላልፈጸመችለት ቂም አደረገና ለዚያ ግብጻዊ ጌታው ምንም ምትክ የሌለው አንድ ሕጻን ልጅ ነበረውና፣ ያንን ሕጻን ልጅ ከእናቱ አጠገብ ተኝቶ ሳለ ሳታውቅ አንስቶ ወስዶ በወቅለምት ከገደለው በኋላ ከቅድስት አርዋ፡አጠገብ አምጥቶ አስቀመጠው። ወቅለምቱንም እጇ ከሚደርስበት ርቀት አቅርቦ አስቀመጠው። እንዲህም ማድረጉ ያ ግብጻዊ ጌታው በዚህ ተቆጥቶ ቅድስት አርዋን ይገድላት ዘንድ ነው። በኋላም የሕጻኑ እናት ተነስታ ልጇን፡ልታጠባ ብትፈልገው አጣችው። ስትመጣም ከቅድስት አርዋ አጠገብ ሙቶ አገኘችው። እናቲቱም ከበር ወጣችና አሰምታ መራራ ልቅሶን አለቀሰች። ሰዉም ኹሉ ተሰበሰበ። ያም ግብጻዌ ነጋዴ መጥቶ እናታችን አርዋን "ስለምን ስለበጎ ፈንታ እንዲህ ያለ ክፉ ነገር አደረግሽ? ከሞት አዳንሁሽ፣ ከመቃብርስ ያወጣሁሽ አይደለምን?" አላት። እርሷም መልሳ፣ "በሚገ'ባ ጠይቀኸኛል፣ ከመቃብርም ቦታ አውጥተኸኛል። እንግዲህ ታዲያ እንዲህ ስላደረግህልኝ በጎ ነገር ስለምን ብዬ ልጅህን በመግደል በክፉ እመልስልሃለሁ? ከጥቂት ጊዜ በፊት ልታገባኝ ስትጠይቀኝ እኔ በአንተ ላይ የተመኘሁት ምን ክፉ ነገር ከቶ ነበር? እግዚአብሔርን ከመፍራት የተነሳ አይኾንም አልሁ እንጂ። እንግዲህ ከዚህ የሚበልጥ ኃጢአት እሠራ እና ሰው እገድላለሁን? ልጅህን ፈጽሞ አልገደልሁትም" አለችው። ❤ ግብጻዊውም "እንግዲህ ላቆይሽ አልችልምና ከዚህ ኺጂልን"። ለራስዋም እንዲኾናት መቶ ዲናር ሰጣትና "ከዚህ በኋላ ከቶ በዚህ ኹኔታ ልቆይሽ አልችልምና ከዚህ ኺጂ፣ በእኔ ላይ የመጣውን ከቶ አላወቅሁትምና"። እርስዋም ከዚያ ወጥታ በመንገድ ስትኼድ ወደ ከተማው ስትቀርብ አንድን ሰው ከዛፍ ላይ እያሰቃዩ ሲሰቅሉት ተመለከተች። ቀርባም በምን ምክንያት እንደሚሰቅሉት ስትጠይቅ መቶ ዲናር ዕዳውን መክፈል ባለመቻሉ እንደሚሰቅሉት ነገሯት። እርሷም ለራስዋ የያዘችውን መቶ ዲናር ከፈለችና ሰውየውን ነጻ አደረገችው። ያም ሰው አባቱን ማን ነጻ እንዳደረገው ሲጠይቅ አባቱ እርሱ ነጻ፡እንዳላወጣው ነጻ ያወጣችው መልከ መልካም የኾነች አንዲት ሴት

❤ "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ጻድቅ ጌታችን በዕለተ አርብ የጠጣው መራራ ሐሞት በማሰብ በቅል ውስጥ የሚገኘውን መራራ ፍሬ ከኮሶ ጋር በአንድነት #ደርጣ (አዋህዳ) ትመመገብ ለነበረች ለታላቋ እናት #ለቅድስት_ዜና_ማርያም_ለልደት_በዓል፣ #ለቅድስት_ወለተ_ማርያም_ዘጎንደር_የዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ጻድቋ_ቅድስት_ዜና_ማርያም፦ ከአባቷ ከቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ከእናቷ ከቅድስት አመተ ማርያም በ11 መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ ዘመነ መንግሥት በምድ ነጋሲ በጎጃም ምድር ግንቦት 30 ቀን የተወለደች ሲሆን ለአቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜ በንፅህ ድንግልና በምድረ ሂንፍራንስ ጣራ ገዳም አካባቢ በሚገኘው በአቡነ እንድርያስ ዋሻ ለ25 ዓመት በጾም በፀሎት ምንም አይነት የላመ የጣፈጠ እህል ሳትቀምስ በቅል ውስጥ የሚገኘውን መራራ ፍሬ ከኮሶ ጋር በአንድነት ደርጣ (አዋህዳ) በመዘፍዘፍ ከ3 ቀን በኃላ በመመገብ እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ድረስ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ ላይ የቀመሰውን መራራ ሐሞትን በማሰብ ሙሉ ሕይወቶን እየተመገበች ታላቅ ተጋድሎዋን ፈፅማለች፡፡ ከዚህ የተነሳ ሸክላ ማርያም ተብላ ትጠራ የነበረችው ቦታ ስያሜ ተቀይሮ ደሪጣ ዜና ማርያም ዋሻ ተብሎ እስከ አሁን ድረስ በስሞ እየተጠራ ይገኛል፡፡ ❤ ከአቡነ እድርያስ ዋሻ በመቀጠል ከአዲስ አበባ ተነስተን ስንጓዝ አዲስ ዘመን ከተማ በስተቀኝ በኩል ተገንጥለን 15 ኪሜ ያክል የጥርጊያ መንገድ እንደተጓዝን  በስሟ የተሰየመውን ደሪጣ ጻድቋ ቅድስት ዜና ማርያም ገዳም ላይ ቀሪ ሕይወቶን ምንም አይነት ዋሻ ባልነበረበት በከፍተኛ ተራራ ላይ እጅግ አስቸጋሪ ቀዝቃዛ አየር ባለበት ብርዱን፣ ፀሐዩን፣ ቁሩን፣ ረኃቡንና ጥሙን በመቋቋም ራቁቶን በመሆን መራራ ምግቦችን አዋህዳ በመመገብ በጾም በፀሎት በመትጋት አስቸጋሪ የሆነውን ተጋድሎዋን በመፈፀም በዚሁ በተቀደሰ ስፍራ ነሐሴ 30 ቀን በታላቅ ክብር አርፋለች፡፡ ❤ በዚህም ወቅት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከእልፍ አላፋት ቅዱሳ መላዕክት ጋር እንዲሁም ከሐዋርያት ፣ ከሰማዕታት ፣ ከጻድቃን ፣ ከደናግል ጋር በመሆን ከሰማይ በመውረድ በታላቅ ክብር ዕረፍቷን አክብሮላታል ታላቅ ኪዳንም ገብቶላታል፡፡      ❤ በዚሁ በተቀደሰ ስፍራ ላይ ወይንም በአሁኑ ሰዓት መቃብሯ በሚገኝበት ዋሻ ቤተመቅደስ አካባቢ በተጋድሎዋ ጊዜ ራቁቷን በሆነች ሰዓት መላ ገላዋን የሸፈነላት ፀጉር በእየ ዛፎቹ ላይ እስከ አሁን ድረስ አለ፡፡ ይህም የጸጉር አምሳያ ከገዳሙ በመውሰድ ብዙ ሰዎች በቤታቸው በመታጠን ከአስም እንዲሁም ከተለያዩ በሽታዎች እየተፈወሱና እየዳኑ ሲሆን ታላላቅ ታምራትን እያደረገ ይገኛል፡፡ ❤ በዚህ ገዳም ከሌሎች ገዳማት ለየት የሚያደርገው ታሪክ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ በመውረድ ራሱ የባረከው ልዩ ታሪክ ያለው ጠበል የሚገኝ ሲሆን ይህም ጠበል በቦታው ላይ ሆኖ የተጠመቀ ፣ የጠጣ ፣ አልያም በአለበት ቦታ ሆኖ የተጠቀመ እስከ አሁን ድረስ መካን የሆኑ ሰዎች በፍጥነት ልጅ የሚያገኙ ከመሆናቸው ባሻገር ከማንኛውም ከተለያዩ በሽታዎች በመፈወስ  ታላላቅ ታምራትን እየሰራ ይገኛል፡፡ ❤ በ11ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቅዱስ ላሊበላ በጌታችን በአምላካችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ መሰረት ወደዚሁ ታላቅ ስፍራ በመምጣት የጻድቋ ማረፈያ መታሰቢያ ዋሻ ቤተ መቅደስ በመፈልፈል የሰራላት ሲሆን በመቀጠል አፄ ይስሐቅ በ14ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ይህን ገዳም በስሟ በመገደም በዚሁ ዋሻ ውስጥም የጻድቋ የቅድስት ዜና ማርያም መቃብሯ እንዲሁም የመታሰቢያዋ ፅላት የሚገኝ ከመሆኑ አንጻር በአካባቢው ያሉት ሕዝበ ክርስትያን ከካህናት ጋር በመሆን ሥርዓተ አምልኮ በመፈፀም እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ ❤ ይህ ዋሻም አስቀድሞ ሦስቱ ቅዱሳን ማለትም አቡነ እንድርያስ ዘጣራ ገዳም ፣አቡነ ተክለኃይማኖት ዘደብረ ሊባኖስ፣ ጻድቋ ቅድስት ዜናማርያም ዘደሪጣ ውስጥ ለውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት በፀጋ እግዚአብሔር ይገናኙበት የነበረ ሲሆን በአሁን ሰዓትም እግዚአብሔር የመረጣቸው ቅዱሳን ይመላለሱበታል፡፡ ❤ ለጻድቋ ቅድስት ዜና ማርያም የተሰጠ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር አምላክ መርጦና ፈቅዶ በጻድቋ አማላጅነት ካለበት ስፍራ ተነስቶ የጻድቋ ደጃን የረገጠ ለ3 ግመል ጭነት ጤፍ ወይም የሦስት አህያ ጤፍ ያህል ነፍሳትን እምርልሻለሁ፤ ከሲዖልም እሳት ነፍሳትን አወጣልሻለሁ የሚል ቃል ኪዳን ለጻድቋ ቅድስት ዜና ማርያም ተሰቶታል። ከእናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷም ይማረን!። ምንጭ፦ ማኅበረ ዜማ ማርያም ካዘጋጁት በራሪ ወረቀት የተወረደ።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_ወለተ_ማርያም_ዘጎንደር፦ ትውልዷ ጎንደር ሲሆን በዐፄ ወናአግ ሰገድ ዘመን የነበረች ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነች ጻድቅ እናት ናት፡፡ ደብረ ሊባኖስ ሄዳ ከመነኰሰች በኋላ ወደ ጣና ገዳም ገብታ በጣና ባሕር ውስጥ ለ11 ዓመት ቆማ የጸለየች ድንቅ እናት ናት፡፡ ከእናታችን ከቅድስት ወለተ ማርያም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን እኛንም በጸሎቷ ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤          ❤ #ግንቦት ፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን #በድንጋይ_አምድ_ላይ_ለሰባት_ዓመት ለቆሙት #ለአባ_ስምዖን_ዘአምድ_ዘአንጾኪያ ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከጌታችን_ከአምላካችን_ከመድኃኒታችን_ከኢየሱስ_ክርስቶስ_ከልደቱ_ወራዊ_መታሰቢያ፣ #ከመነኰስ_ይስሐቅና #ከፊልጶስ_ልጅ_ከንጉሥ_እስክንድር_ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ስምዖን፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ዮሐንስ የእናቱም ስም ማርታ ነው ስለ ርሱም ድንቆች ተአምራት ሆነ። ይኸውም እናቱ ገና ሳትፀንሰው መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ወደ እርሷ መጥቶ የዚህን ቅዱስ ስምዖንን መወለድ ነገራት እርሱም የሚሆነውን ገለጠላት። ❤ ተወልዶም ሰባት አባት በሆነው ጊዜ በአንጾኪያ ወደአለ ገዳም ሔደ። ራሱንም ወደ ምንኵስና ቀንበር ውስጥ አስገብቶ ታላቅ ገድልን ተጋደለ። መላእክትም አባ ጳኵሚስን እንደ አስተማሩት በሌሊቱ ሁሉ እየተገለጡለት የምንኵስናን ገድል አስተማሩት። የማይጠፋ የምንኵስናንም የገድል አሠራር ገለጡለት። እርሱም አጽንቶ ሥጋ ከለበሱ ሁሉ አብዝቶ ተጋደለ መላእክትም ሁልጊዜ መንፈሳዊ ምግብ ያመጡለት ነበርና። ብዙ ከመጋደል የተነሣ ከደጊያ ምሰሶ ላይ ወጥቶ በላይዋ ሰባት ዓመት ቆመ። ❤ ከዚህም ወደሌላ ተራራ ሒዶ በሠራው ደንጊያ በዓት ውስጥ እስከ ሃያ ዓመት ፍጻሜ ከእርሷ ሳይወጣ ሃያ ዓመት ኖረ። ከዚህ በኋላም ደግሞ ከታላቅ ተራራ ራስ ላይ ወጥቶ በላዩ አርባ አምስት ዓመት ኖረ። መላው ዕድሜውም ሰማንያ ስምንት ዓመታት ነው። ይኸውም በአባቱ ቤት ሰባት በአንጾኪያ ገዳም ዘጠኝ ዓመት በምሰሶ ላይ ሰባት ዓመት በደንጊያ ውስጥ ሃያ ዓመት ደግሞ በተራራ ላይ ቁሞ የኖረበት አርባ አምስት ዓመት በጠቅላላ ሰማንያ ስምንት ነው። ❤ ተአምራቱን ግን መቁጠር የሚችል የለም ከእርሳቸውም በገድሉ አለ። ብዙ የሆኑ ድርሳናትንና ተግሣጽን ደረሰ ይልቁንም ለመነኰሳት ከቤተ ክርስቲያን መጻሕም ብዙዎቹን ተረጐመ። ከዚህም በኋላ ግንቦት 29 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ስምዖን በጸሎቱ ምማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 29 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለስምዖን_ዘተበሥረ_ፅንሱ። በአፈ ዮሐንስ መጥምቅ እንተ ኢይኄሱ። እንዘ ይትለአክዎ ዘልፈ መላእክት ለማኅሠሡ። ፈጸመ ምግባረ እንተ ወጠነ እምንእሱ። እምአመ ተወልደ በዓመት ስሱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_29።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3።የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 2፥1-8።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወተግሣፅከ ውእቱ ዘይሜህረኒ። ወአርኀብከ መከየድየ በመትሕቴየ። ወኢደክመ ሰኰናየ። መዝ 17፥38-39። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥1-12፣ 1ኛ ዮሐ 4፥9-18 የሐዋ ሥራ 12፥7-12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥1-17። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠልስቱ ምዕት ወይም የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ መዝራተ ክርስቶስ፣ የአባ ጉባ፣ የአቡነ ስምዖን የዕረፍት በዓል፣ የአቡነ አፍጼ የስዋሬ በዓልና የበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ከዚኽም በኋላ መዝራዕተ ክርስቶስ ምን ማድረግ እንዳለበት ሲያስብ ቆይቶ ወደ አንዱ ገዳም ጠፍቶ በመሄድ በምንኵስና ለመኖር ወሰነ፡፡ አንድ ቀን አባቱን ተከትሎ ግምጃ ቤት ማርያም ወደምትባለው ቤተ ክርስቲያን ሄዶ ሳለ አጣኙን አባት ባሕታዊ አባ ቴዎድሮስን "አባቴ ከዛሬ ጀምሮ በምንኵስና ለመኖር ወስኛለሁና መርቀህ ላከኝ" አለው፡፡ ባሕታዊውም "አንተ ገና ልጅ ነህ" ቢለው የሚቀበለው አልሆንም፡፡ በመጨረሻም መርቆ አሰናበተው፡፡ ወዲያም ጻድቁ በሌሊት ከጎንደር ከተማ ጠፍቶ ወደ ሰሜን አርማጭሆ ቆላ ሄደ፡፡ በዚያም በያዕቆብ ግሙድ ስም በተገደመው ገዳም ገብቶ ከአባ ስነ ክርስቶስ ጋር ተገናኘ፡፡ ያመነኰሰውም ዘንድ ለመነው፡፡ አባ ስነ ክርስቶስ ማንነቱን ከጠየቀው በኋላ "አንተ ገና ልጅ ስለሆንክ የምንኩስናን ቀንበር መሸከም አይቻልህም" በማለት ወደ አባቱ እንዲመለስ መከረው፡፡ በሌላም በኩል ከንጉሡና ከመሳፍንቱ ጋር ላለመጣላት ፈርቶ ነበር፡፡ መዝራዕተ ክርስቶስ ግን እያለቀሰ "የአንተ አምላክ ጽናት ይሆነኛልና አመንኵሰኝ" በማለት ለመነው፡፡ እርሱም ተግባር ቤት በአርድዕትነት እያገለገለ እንዲቆይ የአመክሮ ጊዜ ሰጠው፡፡ ❤ መዝራዕተ ክርስቶስም አባቱ ጭፍሮቹን ልኮ እንደገና ወደ ዓለም እንዳይወስደው ፈርቶ ቶሎ እንዲያመነኵሱት "ታመምኩ" ብሎ ተኛ፡፡ መነኰሳቱም "ሳይመነኵስ ቢሞት ኵነኔ ይሆንብናል" ብለው አበምኔቱን ለምነው አመነኰሱት፡፡ ከመነኰሰ በኋላ በሳምንቱ አባቱ ልጁ ያለበትን ገዳም ዐውቆ ታናሽ ወንድሙን ከጭፍሮቹ ጋር በመላክ ለአባ ስነ ክርስቶስ "ልጄ መዝራዕተ ክርስቶስ አንተ ጋር እንዳለ ሰምቻለሁና ከመመንኰሱ በፊት በአስቸኳይ እንድትልክልኝ" ብሎ መልእክት ላከበት፡፡ አባ ስነ ክርስቶስም ለመጡት ጭፍሮች መዝራዕተ ክርስቶስ እንደመነኰሰ ነገራቸው፡፡ ጭፍሮቹም ከአባ ስነ ክርስቶስ ጋር ብዙ ስለተጨቃጨቁ መዝራዕተ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር ለመሄድ ተስማማ፡፡ ከእነርሱም ጋር ሳለ ከጭፍሮቹ አንዱና መሪያቸው የሆነውን ሰውም "ተሳልሜ ልምጣ፣ ጋቢህን ስጠኝ" ብሎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በምሥራቅ ባለው በር ወጥቶ ጠፍቶ አርማጭሆ ጫካ ውስጥ ገብቶ ጠፋ፡፡ አጎቱና ጭፍሮቹም ፈልገው ቢያጡት ተስፋ ቆርጠው ተመለሱ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ ወደ አንገረብ ወንዝ ሄዶ በዚያ ከርኵሳን መናፍስት ጋር እየተዋጋ በተጋድሎ በጾም ጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ ተመልሶ ወደገዳም ቢመጣ አባቱና ዘመዶቹ እንደማያስቀምጡት ስላወቀ አባ ስነ ክርስቶስን አስፈቅዶ ወደላይ አርማጭሆ ደብረ ሙጅና አባ አብሳዲ ገባሬ ተአምር ገዳም ሄደ፡፡ በዚያም 7 ዓመት በተጋድሎ ከኖረ በኋላ ወደ ዋልድባ ገዳም ሄደ፡፡ በዚያም ሥዕለ ማርያምን በጎኑ ታቅፎ ሲያዝን ለብዙ መናንያን የተሰወረችው ደብረ ሲና የተባለች በዋልድባ የምትገኝ ቅድስት ቦታ ተገለጠችለት፡፡ በደብረ ሲና ተራራ ላይ ወጥቶ 40 ቀንና 40 ሌሊት ሱባኤ ያዘ፡፡ በዋልድባ 11 ዓመት እንደተቀመጠ የታዘዘ መልአክ መጥቶ "በዚህ ገዳም የምትኖርበት ጊዜ አልቋልና ውጣ" ብሎ አዘዘው፡፡ ከዚያም ከዋልድባ ወጥቶ ወደ ሰሜን ተራራ ሄዶ ከቅዱስ ያሬድ ገዳም ተባርኮ ወደ ትግራይ ገርዓልታ ሄደ፡፡ ቀጥሎም ወደ ጒንዳጒንዲ ማርያም ገዳም ገብቶ በተጋድሎ መኖር እንደጀመረ አንድ የበቃ ባሕታዊ መጥቶ "ክፍልህ በዚህ ገዳም አይደልምና ወደ ሌላ ገዳም ሂድ" አለው፡፡ ❤ ወደ መጠራ መቃብረ ጻድቃን ዘንድ ሄዶ ዐጽመ ቅዱሳንን ሲያጥን "ይህ ገዳም ክፍልህ አይደለም" የሚል ድምጽ ከሰማይ መጣለት፡፡ ተነሥቶም ወደ ደብረ ቢዘን ሲጓዝ ሌሎች መነኰሳትን አገኘና በመረብ ወንዝ ሸለቆ ውስጥ ብዙ መናንያን እንዳሉ ሲነግሩት በሌላ አቅጣጫ ወደ መረብ ወንዝ አቀና፡፡ በዚያም ሸንፋ በተባለ ቦታ ገዳም መሥርቶ ሲቀመጥ መንፈሰ እግዚአብሔር የጠራቸው 12 መነኰሳት መጥተው አርድእት ሆኑለት፡፡ እነርሱም በወባ በሽታ ታመው ስላረፉ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ "ወንድሞቼን አጥቼ በዚህ መኖር ለእኔ አይገባኝም፣ ክፍሌ አይደለም" ብሎ ወጥቶ ወደ ትግራይ ሄደ፡፡ ❤ አድዋ አውራጃ የሐ አቡነ አፍጼ ገዳምን ከተሳለመ በኋላ ገዳሙን ከከበቡት ተራሮች መካከል በአንደኛው ማይ ዱር ወደሚባለው ተራራ ወጥቶ አዲስ ገዳም መሠረተ፡፡ ታቦተ ማርያምን አስገብቶ ሲኖር ከየአቅጣጫው መናንያን መነኰሳት ወደ እርሱ መጡ፡፡ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስም እስከ 93 ዓመቱ ገዳሙን በአበምኔትነት እያስተዳደረ በታላቅ ተጋድሎ ከኖረ በኋላ ግንቦት 29 ቀን ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፈ፡፡ "ማይዱር" በተባለው ገዳሙ ራሱ በሠራት በእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተቀበረ ሲሆን ገዳሙም እስከዛሬ ድረስ "እንዳ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ ገዳም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ከአባታችን ከአቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።

❤ ከዚህም በኋላ በአክሱም ከስምንቱ ጓደኞቻቸው ጋራ ለዐሥራ ሁለት ዓመት በአንድነት አብረው ከኖሩ በኋላ "እርስ በራሳችን እየተያየን ብንኖር ተድላ ደስታ ይሆንብናልና ተለያይተን እንቀመጥ" ብለው ተማከረው በተለያየ በዓት በተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ አቡነ አፍጼም የእርሳቸው እጣ ወደ ሆነው ገዳማቸው የሓ ገነተ ጽባሕ ደብረ ሐመልማል ገዳም ገብተው በዐት ወስነው በብዙ ተጋድሎ የአካባቢውን ሕዝቡ በማስተማራ፣ በመምከር በዚያ መኖር ጀመሩ።.... ❤ በመጨረሻ የፀሐይ ጮራ ማር አቡነ አፍጼ የሚሠወሩበት ጊዜ ሲደርስ በግንቦት 29 ቀን ጌታችን ቅዱሳን መላእክቱን አስከትሎ እመቤታችን ማርያምም ከእነርሱ ጋር መጥታ በቀኙ ተቀመጠች፣ ነቢያትና ሐዋርያት፣ ጻድቃንና ሰማዕታት በየወገኖቻቸው አብረው መጡ ነቢዩ ዳዊትም መሰንቆውን ተሸክሞ "ጻድቅስ እንደ ዘንባባ ያፈራል እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይበዛል እነርሱም በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ የተተከሉ ናቸው" እያለ እየዘመረ ከከበሩ ነገሥታት ሁሉ ጋር መጣ። ❤ ከዚህ በኋላ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ፋና የፀሐይ ጮራ ተአምራትንና ድንቆችን የሚያደርግ ማር አቡነ አፍጼን "የታመንህ የምሻውን የምታደርግ ፈቃዴንም የምትፈጽም ወዳጄ ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ከአንተ ጋር በሰማይና በምድር የሚጸና ቃል ኪዳን ላቆም ከመከራና ከዚህም ዓለም ድካም ከሰይጣን ወጥመድና ከአላፊው ዓለም ውጣ ውረድና ደስታ ላድንህ መጣሁ"አለው። አባ አፍጼም ከጌታችን መለኮታዊ ግርማ የተነሣ ደነገጡ ፈርተውም በምድር ላይ ወደቁ እንደ በድንም ሆኑ። ጌታችንም በእጁ ያዘውና አለውም "የታመንህ ወዳጄ ሆይ አትፍራ ከእኔም የተነሣ አትደንግጥ የወደድኸውን በልብህም የምትሻውን ሁሉ ለምነኝ"። አቡነ አፍጼም "የሚታየውንና የማይታየውን ፍጥረት ሁሉ ፈጥረህ የምትገዛ ጌታዬ... መታሰቢዬን የሚያደርገውን በእኔም ተማምነው ስሜን የሚጠሩትን ኃጥአን ማርልኝ አቤቱ ጌታዬ ሆይ ስለወደድኸው ስለ ቅዱስ አብርሃም ስለ ወዳጅህም ስለ ቅዱስ ይስሐቅ ስለ ቅዱስህም እስራኤል ስለወለደችህ ስለ ማርያም ስላጠመቀህ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ቅዱሳንህም ሁሉ የፈጠርኸውን ሕዝብህን ይቅር በል"። ጌታችንም ለአቡነ አፍጼ መልሱ እንዲህ አለው "የታመንህ ወዳጄ ሆይ እሺ በጎኝ መታሰቢያህን ያደረገውን፣ ስምህን ጠርቶ የጸለየውን፣ በስምህ በተሠራ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም የተሳለውንና የተማለለውን እኔ እስከ 45 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ፤ ሰባቱንም የሰማያት ደጆችም እከፍትለታለሁ የእሳትንም ባሕር አሻግሬ የተከፈተ ገነት አለቆች የማያውቁት የተጎናጸፈ ዕረፍት ወዳለበት አገባዋለሁ፤ ያለምርመራና ያለ ክርክርም ወደ ሰማያዊት መንግሥት እልፍኝ አልፎ ይገባል የሚቃወመው የለም የሚከራከረውም አይኖርም እኔ ከፀሐይና ከጨረቃ ከከዋክብትም ብርሃን ይልቅ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን ማደሪያ እሰጠዋለሁ እንጂ የውስጥ አሠራሯን ከሰማያዊ አባቴ ከማኅየዊ መንፈስ ቅዱስም በቀር የሚያውቅ የለም በሰማያውያን በብርሃናውያን መላእክቴ ፊት ደስ አሰኘዋለሁ።... ❤ ንዑድ ክቡር ማር አባታችን አፍጼ "ጌታዬ አምላኬ ሆይ መታሰቢያዬ የሚያደርገው፣ በዓሌን የሚያከብረው ወዳጄ ልጆች ባይኖሩት ምን ታደርግለታለህ ምንስ ትሰጠዋለህ?" አለው። ጌታችንም መልሶ አለው "መታሰቢያህን የሚያደርገው፣ በዓልህንም የሚያከብረውን ወዳጅህ ልጆች ከሌሉት እኔ ወጋውን የ45 ትውልድ ወጋ አድርጌ እሰጠዋለሁ ከዚህም የሚበልጥና የሚሻል ደስታ የምሥራች እነግርሀለሁ የሞት መልአክ አያስደነግጥህም የሞት ጥላም አያገኝህም አንተ ከሚያስፈራ፣ ከሚያስደነግጥህም የሞት መልአክ ፊት ትሠወራለህ፣ ትሸሸጋለህ እንጂ እኔ ከወዳጆቼ ከነቢያት ከኄኖክና ከኤልያስ ከዕዝራም ጋር አኖርሀለሁ እንጂ ይህችን የተቀደሰች የየሓ ገነተ ጽባሕ ደብረ ሐመልማል ገዳምህም የመቃብሬ እንዳለባት እንደ ኢየሩሳሌም የመንግሥቱ ዙፋን እንደተዘረጋበት እንደ ጽርሐ አርያም የከበረችና ከፍ ከፍ ያለች አደርጋታለሁ። ንዑድ ክቡር ማር አቡነ አፍጼም ይህን ሰምተው ፈጽሞ ደስ ተሰኙ ይህንንም ታላቅ ክብርና ገናናነት ልልናም ስለሰጣቸው ፈጣሪያቸውን ፈጽመው አመሰገኑ። ❤ ከዚህም በኋላ ደቀ መዛሙርቱንና ማኅበሩን "የተወደዳችሁና የተመረጣችሁ ልጆቼ ሆይ ከዛሬ ጀምሮ ወዲያ እንደቀድሞው በዚህ ዓለም በሥጋ አታዩኝም" አሏቸው። ደቀ መዛሙርቱና አርድዕቱም ይህን ነገር ሰምተው ፈጽመው አዘኑ እንዲህም እያሉ አለቀሱ "ወዮልን ወዮልን እናይ ነበር አሁን ታወርን፤ አገኘን መልሰን አጣን፤ በልጽገን ተራቆትን በላን መልሰን ተራብን፤ ደስ ተሰኝተን ነበር አሁን ግን በመሸሸግህ ከእኛም በመሠወርህ ምክንያት አዘንን አባታችን የሁላችን መምህር፤ ጠባቂያችን የዐይናችን መብራት በትምህርትህ ከየሥፍራው የተሰበሰብኸን ተስፋችን ሆይ ከእኛ ወዴት ትሄዳለህ? እኛ አገራችንን አባታችንና እናታችንን፣ ወንድማችንና ባልጀራችንን፣ ንብረታችንን፣ ገንዘባችንን፣ ጥሪታችንን ይህን ሁሉ ትተን ተከተልንህ አሁን ለማን ትተወናለህ? ንዑድ ክቡር ማር አቡነ አፍጼም "እኔ ወደ ክርስቶስ ወደ አምላኬ እሄዳለሁ እናንተንም ለክርስቶስ ለአምላካችሁ አደራ እሰጣችኋለሁ" አሏቸው። ይህንንም ብለው ከሞት መልአክ ፊት ግንቦት 29 ቀን ተሠወሩ። ጌታችንም ከማደሪያውቸው አጠገብ አንሥቶ ወሰዳቸው ወደ ላይም አወጣቸው ወደ ብሔረ ሕያዋንም አድርሶ ከእነ ቅዱሳን ኄኖክ፣ ኤልያስና ዕዝራ ጋር ጨመራቸው እነርሱም በደስታ ተቀበሏቸው። ከአባታችን ከአቡነ አፍጼ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ አፍጼ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_መዝራዕተ_ክርስቶስ፦ አባቱ ለባሴ ክርስቶስ የዐፄ ፋሲል የቅርብ ወዳጅ የነበረ የጦር አዛዥ ደጃዝማች ሲሆን እናቱ ሚላንያ ትባላለች፡፡ ጻድቁ ታኅሣሥ 29 ቀን በጎንደር ተወለዱ፡፡ ወቅቱ ዐፄ ሱስንዮስ የረከሰች የሮም ካቶሊክ እምነትን ተቀብሎ የሀገራችንን ክርስቲያኖች በሰማዕትነት የሚገድልበት ዘመን ስለነበር እናቱ ይዛው ፎገራ ወረዳ ቆራጣ ወለተ ጴጥሮስ ገዳም ገባች፡፡ በዚያም ሕፃን ልጇን ክርትስትና የሚያነሳላት ካህን አጥታ ስታለቅስ ደገኛው አባት አባ ስነ ክርስቶስ በስውር መጥተው አጠመቁትና ስሙን መዝራዕተ ክርስቶስ አሉት፡፡ ❤ የመዝራዕተ ክርስቶስ እናት ብዙም ሳትቆይ ስለሞተች በዚያው የምትኖር መነኵሲት የሆነች አያቱ አሳደገችው፡፡ እንደ አገሩም ባሕል ፈረስ ግልቢያና ጦር ውርወራ እየተማረ ከፎገራ ልጆች ጋር አደገ፡፡ አያቱም ወላጅ እናቱ ትመስለው ነበር፡፡ አንድ ቀን አብሮት የሚጫወተው ልጅ ወላጆቹ ሲያወሩ የሰማውን ወስዶ ለመዝራዕተ ክርስቶስ እናቱ እንዳልሆነች ነገረው፡፡ እርሱም በሰማው ነገር ደንግጦ አያቱን ስለእውነቱ ጠየቆ ተረዳ፡፡ ከዚህም በኋላ ደጃዝማች አባቱ ወደ ዐፄ ፋሲል ቤተ መንግሥት ወሰደው፡፡ መዝራዕተ ክርስቶስ መልከ መልካም ስለነበር ንጉሡ ዐፄ ፋሲል በወጣቱ ደም ግባት ደስ ተሰኝቶ ድምጹን አሰምቶ "ለዚህ ልጅ ሴት ልጄን እድርለታለሁ" ሲል ለመኳንንቱ ሁሉ ተናገረ፡፡ መዝራዕተ ክርስቶስ ግን በልቡ መንኵሶ ስለመኖር የወሰነው በቤተ መንግሥት ይህንን የሰማ ዕለት ነበር፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤         ❤ #ግንቦት_፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ #ለአቡነ_መዝራዕተ_ክርስቶስ_ለዕረፍት_በዓል፣ #ከዘጠኙ_ቅዱሳን መከካከል ለሆኑ #ለአባ_አፍጼ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወሩበት በዓልና #ለአባ_ጉባ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_አፍጼ፦ የልደታቸው ነገር እንደዚህ ነው ከከበሩ ሰዎች በእስያ ተወለዱ የአባታቸው ስም አቡሉዲስ የእናታቸው ስም አቅሌስያ ነው፤ ሁለቱም ደጋግ ጻድቃን እግዚአብሔርንም የሚፈሩ ነበሩ። እኚህ ንዑድ ክቡር ማር አቡነ አፍጼን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላ በ245 ዓመት መጋቢት 29 ቀን ተፀነሱ። የፅንሰታቸው ጊዜ ሲፈጸም ንዑድ ክቡር የዓለም ብርሃን የፀሐይ ጮራ ማር አቡነ አፍጼን ታኅሣሥ 28 ቀን በእኩለ ሌሊት ተወለዱ። በተወለዱበትም ቀን ከፀሐይና ከጨረቃ ከከዋክብትም ብርሃን ሰባት እጅ ይልቅ የሚያበራ ታላቅ ብርሃን ከሰማይ ወረደ፤ ቀንና ሌሊቱም አይለይም ነበር፤ ሰባት ቀንም ያህል ምድር በራች አንፀባረቀችም፤ በልደታቸውም ቀን ተራሮችና ኮረብቶች፣ የዱር እንጨቶችም ሁሉ ስለመወለዳቸው ክብር ደስ አላቸው። ❤ በተወለዱም ጊዜ ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አወደሱት አመሰገኑትም። ዳግመኛም አንዱ አብ ቅዱስ ነው፣ አንዱ ወልድም ቅዱስ ነው፣ መንፈስ ቅዱስም አንድ ነው አሉ። እኒህን ታላላቅና ድንቅ ምስጋናዎች አከናውነው የተናገሩት መንፈስ ቅዱስ ሥላሴ በአካል ሦስት በመለኮት አንድ የመሆናቸውን ምሥጢር ስለገለጸላቸው ነው። ጌታችንም ኢየሱስ ክርስቶስም አቅፎ በአፉ ሳማቸው ከሰው ወገኖችም አልቆ ወደዳቸው ታላቅነትና ከፍ ከፍ ማለትን ከጻድቃንና ከሰማዕታትም ሁሉ ባለሟልነት የበለጠ ፍጹም ባለሟልነትንና ጸጋን ሰጣቸው፤ ሥልጣናቸው በክብር ከፍ ይላልና። ... ❤ የአርባ ቀን የአራስነት ጊዜ ሲፈጸም በሕግ እንደታዘዘው ሥርዓት በክርስቶስ ስም ይጠሩ ዘንድ ሕፃኑን ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት። ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስ ሕፃኑን ተቀብሎ በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስም ስም አንድ አምላክ እያለ በዮርዳኖስ ውኃ አጠመቀው። ሊቀ ጳጳሳቱም ሲያጠምቀው ሳለ ሕፃኑ ለአብ ስግደት ይገባል ለወልድም ስግደት ይገባል ለመንፈስ ቅድስም ስግደት ይገባል ለአብ ምስጋና ይገባል ለወልድም ምስጋና ይገባል ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል እያለ ራሱ በራሱ ሰገደ። ❤ ከዚህም በኋላ ስማቸውን አፍጼ አላቸው። የከበረውን ሜሮን ዘይትንም ቀባቸው። ሊቀ ጳጳሳቱም ስርሳቸው እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "ይህ ሕፃን ለኢትዮጵያውያን ወደ መንግሥት ሰማያት መርቶ የሚያደርስ የጽድቅ መሪ፣ ለዘላለማዊ ሕይወትም የደስታ ብርሃን ይሆናል፤ በረሀብ ዘመን ምግብ እና ጥጋብ፣ በጥምም ዘመን መጠጥ ፣ በመራቆት ጊዜ ልብስ በችግርና በጭንቅ ጊዜም መጠጊያ ይሆናቸዋል" ይንንም ብሎ ሊቀ ጳጳሳት ጢሞቴዎስ ከግርማው ታላቅነት የተነሣ እየፈራና እየራደ ሕፃኑን አንሥቶ በጉያው አቀፈው ፤ በአፉም ሳመውና በትእምርተ መስቀል ባረከው ሕፃኑ በመንፈስ ቅዱስ የተባረከ የከበረ ነውና። ❤ አባታችን አቡነ አፋጼ ሰባት ዓመት ከሞላቸው በኋላ ጢሞቴዎስ የተባለው ሊቀ ጳጳሳት የዳዊት መዝሙርና፣ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን፣ ብሉይና ሐዲስን ሕጋቸውንና ትዕዛዛቸውን፣ ሥርዓታቸውንም ከመጠበቅ ጋር አስተማራቸው፤ በሚማሩበት ጊዜ መንፈስ ቅዱሱ በአንደበታቸው ይናገራል፤ ቀድሞ የተማሯቸው ይመስል ነበር መምህራቸው ያስተማሯቸውን ፈጥነው ያጠኑ ነበር፤ መንፈስ ቅዱስ አድሮባቸዋልና። ❤ ዐሥራ አምስት ዓመት ሲሆናቸው ሊቀ ጳጳሳት አቡነ ጢሞቴዎስ ለንዑድ ማር አቡነ አፍጼ የዲቁናና የቅስና ሹመት ሰጣቸው። ከዚህ በኋላ የብዙኃን መነኰሳት አባት አቡነ መቃርስ ወዳለበት መዳልወ አልባብ ወደተባለች ወደ አስቄጥስ ገዳም ይሄዱ ዘንድ አሰቡ ብርህት ደመናንም በእጃቸው ጠቅሷት መጥታም ከፊታቸው ቀረበች "ደመና ሆይ ጉም አጽፍሽን ዘርጊ" አሏት፤ ደመናም ጉም አጽፏን ዘረጋችው ወደ የአቡነ እንጦንስ ልጅ የአቡነ መቃርዮስ ገዳም ወደ አስቄጥስ አደረሰቻቸው። አቡነ መቃርስም ንዑድ ክቡር ማር አቡነ አፍጼን ባያቸው ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው የእግዚአብሔርም ጸጋ አድሮባቸዋልና ወደዷቸው፤ ራሳቸውንም ሳሟቸው እርስ በርሳቸውም ፍቅርና ሰላም ታላቅ ሞገስም በሞላበት መንፈሳዊ ሰላምታ ሰላም ተባባሉ። አቡነ መቃርዮስ ንዑድ ክቡር ማር አቡነ አፍጼን "ከወዴት አገር ወደዚህ መጣህ ወደእኔስ ያመጣህ ጉዳይ ምንድ ነው?" አላቸው። አቡነ ፍጼም "ቅዱስ አባት ሆይ ወዳንተ የመጣሁት አንተ በበረከት የተሞላህ ነህና ልመነኵስ እንዳንተም መነኵሴ ልሆን ካንተም በረከትን እቀበል ዘንድ ነው አሏቸው። አቡነ መቃርዮስም "ገርና ትሑት ልጄ ሆይ የምንኵስናን ቀንበር ትሸከም ዘንድ ትችላለህ?" አሏቸው። አቡነ አፍጼም "የከበርህ አባቴ ሆይ ይህን የሚያልፍ ዓለም የሚጠፋውንም መንግሥት ተውኹኝ፤ አዎን እግዚአብሔር ቢያስችለኝ የምንኵስናን ቀንበር እሸከም ዘንድ ይቻለኛል፤ ነገር ግን አባቴ ሆይ ስለእኔ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር እየማለድህ ጸልይ"። ከአቡነ መቃርዮስ ከልጁ ከአቡነ አፍጼ ንግግር ይህን ነገር ሰምተው ስለ ምግባራቸው ማማር ስለ ቃላቸውም ሞገስ ስለ አንደበታቸውም መከናዋወን ስለቀና ሃይማኖታቸው አብዝተው ወደዷቸው የምንኵስና ልብስም አለበሷቸው። "በትዕግስቱና ስለጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በመጋደሉ ጠላትን ያቸነፈ የአባቴን የእንጦንስን አስኬማ የባረከ እግዚአብሔር ይባርክህ"። አቡነ አፍጼም ሰባት ዓመት ያህል ወደ ተመሰገነ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩ እየተማለሉና እየማለዱ ከአቡነ መቃርስ ጋር በዚያ ገዳም ኖሩ። ❤ በዚያም ገዳም በብዙ ተጋድሎ እየተጋደሉ ሳለ ስሙ ቅዱስ ገብርኤል የተባ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠላቸው አባ አፍጼንም እንዲህ አላቸው "ከዚህ ሥፍራ ተነሥና ወደ ኢትዮጵያ ሂድ ይህች አገር ለአንተ የተሰጠች ናትና በጸሎትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ" ብሏቸው ወደ ሰማይ ዐረገ። አቡነ አፍጼም በተቀደሰች ዋሻው ውስጥ በጾምና በጸሎት በስግደትና በመትጋት በታላቅ ምሕላም ላይ ሳሉ ወደ አባታቸው ወደ አቡነ መቃርስ ሄደው። "አባቴ ሆይ እኔ ወደ ኢትዮጵያ እሄዳለሁ ከዚህ መሄዴ በዚያችም አገር መኖሬ የተመሰገነ ከፍ ከፍም ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ ነው አባቴ ሆይ በከበረች በእግዚአብሔርም ዘንድ ተቀባይነት ባላት ጸሎትህ አስበኝ የጻድቅ ሰው ጸሎት ግድጃ ታስፈጽም ዘንድ ትችላለችና" ስለዚህም ነገር አዙኑ ተከዙ ስለ መለያየታቸውም እርስ በርሳቸው ተላቀሱ ...። ❤ ከዚህ በኋላ አቡነ አፍጼ ደመናን በእጃቸው ጠቅሷት ደመናም ወደርሳቸው መጣች። "ደመና ሆይ የጉም አጽፍሽን ዘርጊ" አሏት። ደመናም የጉም አጽፋን ዘረጋች እርሱም ታቦቶቹንና የቤተ ክርስቲያን መገልገያዎቹን ሁሉ በእጇቸው እንደ ያዙ ከደቀ መዛሙርታቸው ጋር ከአርድዕታቸም ጋር በላይዋ ተቀምጡ። ከዚህም በኋላ ደመና ተሸክማ ወሰደቻቸው በእግዚአብሔርም ፈቃድ የከተሞች አናት የአብያተ ክርስቲያናትም መብራት ወደሆነችው ወደ አክሱም ከተማ አደረሳቸው ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገቡና ተሳለሙ።