es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 271
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+2130 días
Archivo de publicaciones
ጥያቄ 4፦ "መጽሐፈ ቅዳሴን" ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጁት (የደረሱት) አባቶች እነማን ናቸው?
Anonymous voting

ጥያቄ 3፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት "የነቢያት ጾም" (የገና ጾም) ስንት ቀን ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 2፦ "ተዋሕዶ" የሚለው ቃል ትርጉም በነገረ መለኮት ትርጓሜው ምንድነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 8፦ "ተዋሕዶ" የሚለው ቃል ትርጉም በነገረ መለኮት ትርጓሜው ምንድነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 9፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት "የነቢያት ጾም" (የገና ጾም) ስንት ቀን ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 1፦ "አምላክን የወለደች" (ቴዎቶኮስ) የሚለውን ስያሜ ለድንግል ማርያም ያጸደቀው ጉባኤ የትኛው ነው?
Anonymous voting

"በደስታ ጊዜ እግዚአብሔርን አመስግን፤ በመከራ ጊዜም እግዚአብሔርን ፈልግ። በሁሉም ጊዜ እግዚአብሔርን እመን።" አቡነ ሺኖዳ

ብዙዎችን ያስለቀሰ አዶናይ ያጋራን እጅግ የሚገርም ቪዲዮ ተመልከቱ!! በቅዱስ ቁርባን አነደደኝ እረፍት አሳጣኝ!! የቤተሰብ ዛር አጋንንትን በቅዱስ ቁርባን! https://www.youtube.com/watch?v=HkX3yH4Xksk

መናፍስት በሰዎች ዘንድ ስሜን ያጠፉታል ምን በማድረግ ልቆጣጠር እችላለሁ?? 3ቱ የመናፍስት መናበብና ጥፋታቸው በእኛ ህይወት!! #መናፍስት #አጋንንት #ጸሎት https://youtu.be/Zvk4hOjTcQ4

በአራቱ ወንጌላውያን ምስል (ሥዕል) ላይ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ የሚወከለው በምን ዓይነት ምልክት ነው?
Anonymous voting

በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ እጅግ በጣም ብዙ የሆኑ የጸሎትና የነገረ መለኮት መጻሕፍትን (ለምሳሌ፦ መጽሐፈ አርጋኖን፣ ሰዓታት፣ መጽሐፈ ምስጢር) የደረሰውና "የኢትዮጵያ ቄርሎስ" ተብሎ የሚጠራው ሊቅ ማን ነው?
Anonymous voting

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ንጉሥ ሄሮድስ ሕፃኑን ለመግደል በቤተልሔም ያስፈጃቸውና በቤተ ክርስቲያን እንደ መጀመሪያዎቹ ሰማዕታት የሚቆጠሩት ሕፃናት ብዛታቸው ስንት ነው?
Anonymous voting

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ሳለ የሠራው የመጀመሪያው ተአምር የትኛው ነው?
Anonymous voting

እግዚአብሔር በመጀመሪያው ቀን (እሁድ) ከፈጠራቸው ስምንት ፍጥረታት መካከል አንዱ የትኛው ነው?
Anonymous voting

"የእግዚአብሔር ዙፋን" ተብሎ የሚጠራውና እጅግ ከፍታ ያለው ሰባተኛው ሰማይ ስሙ ማን ይባላል?ሀ) ኤረርለ) ኢዮርሐ) አርያምመ) ሰማይ ውዱድ
Anonymous voting

"ያለ ማጉረምረም (ዝም ብለህ) መስቀልህን ተሸከም። ራስህን ከሌሎች የተለየህ አድርገህ አታስብ። ስለ ኀጢአቶችህ እና ስለ ድካሞችህ (ለራስህም ለሌሎችም) ምክንያት አትደርድር። የእውነት አንተ የኾንኸ
"ያለ ማጉረምረም (ዝም ብለህ) መስቀልህን ተሸከም። ራስህን ከሌሎች የተለየህ አድርገህ አታስብ። ስለ ኀጢአቶችህ እና ስለ ድካሞችህ (ለራስህም ለሌሎችም) ምክንያት አትደርድር። የእውነት አንተ የኾንኸውን አድርገህ ራስህን ተመልከት እንጂ።" (ሴራፊም ሮዝ) #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

ጥር ፳፰ /28/ በዚች ቀን የከበረ ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም የሆነ በገላትያ ነገሥት በአርአያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ
ጥር ፳፰ /28/ በዚች ቀን የከበረ ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም የሆነ በገላትያ ነገሥት በአርአያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ አስተማረችው ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው በጾምና በጸሎት መጋደል ጀመረ አገልግሎትንም አበዛ በእሳት የበሰለ ሥጋም ቢሆን አይበላም ነበር። እንደ ሠልስቱ ደቂቅ ጥሬ ባቄላ የሚመገብ ሆነ እንጂ፤ ዲቁናም ተሾመ ጥበብና እውቀትም ተጨመረለት። ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ በተሰማ ጊዜ ለጣዖት እንዲሰዋ በብዙ ቢያባብሉው እሺ አላላቸውም በዚህም በብዙ አሰቃዩት እግዚአብሔርም አጸናው። ከዚህም በኋላ ወደ አደገባት ወደ ኪራስ ከተማ መለሱት በዚያም አሠቃዩት ጌታችንም በጤንነት ያለሥቃይ አስነሣው። ዳግመኛም ወደ መክስምያኖስ መለሱት በዚያም ቅዱስ ከልከላዎስንና ብዙ ሰማዕታትን አግኝቶ እርስ በርሳቸው ተጽናኑ የከበረ ቀሌምንጦስንም ጽኑ ሥቃይን አሠቀዩት ጌታችንም እንደቀድሞው አዳነው። ከዚህም በኋላ ወደ መኰንን ሉቅዮስ ወሰዱትና በዚያ አሠቃዩት ጌታችንም አዳነው። በስተመጨረሻም ብዙ ከአሠቃዩት በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡ ሶፍያ የምትባል አማኒት ሴት መጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወስዳ ገንዛ ቀበረችው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

ጥር ፳፰ /28/ በዚች ቀን የከበረ ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም የሆነ በገላትያ ነገሥት በአርአያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ
ጥር ፳፰ /28/
በዚች ቀን የከበረ ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም የሆነ በገላትያ ነገሥት በአርአያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ አስተማረችው ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው በጾምና በጸሎት መጋደል ጀመረ አገልግሎትንም አበዛ በእሳት የበሰለ ሥጋም ቢሆን አይበላም ነበር። እንደ ሠልስቱ ደቂቅ ጥሬ ባቄላ የሚመገብ ሆነ እንጂ፤ ዲቁናም ተሾመ ጥበብና እውቀትም ተጨመረለት።ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ በተሰማ ጊዜ ለጣዖት እንዲሰዋ በብዙ ቢያባብሉው እሺ አላላቸውም በዚህም በብዙ አሰቃዩት እግዚአብሔርም አጸናው። ከዚህም በኋላ ወደ አደገባት ወደ ኪራስ ከተማ መለሱት በዚያም አሠቃዩት ጌታችንም በጤንነት ያለሥቃይ አስነሣው። ዳግመኛ ም ወደ መክስምያኖስ መለሱት በዚያም ቅዱስ ከልከላዎስንና ብዙ ሰማዕታትን አግኝቶ እርስ በርሳቸው ተጽናኑ የከበረ ቀሌምንጦስንም ጽኑ ሥቃይን አሠቀዩት ጌታችንም እንደቀድሞው አዳነው።ከዚህም በኋላ ወደ መኰንን ሉቅዮስ ወሰዱትና በዚያ አሠቃዩት ጌታችንም አዳነው። በስተመጨረሻም ብዙ ከአሠቃዩት በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡ ሶፍያ የምትባል አማኒት ሴት መጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወስዳ ገንዛ ቀበረችው።ለእግዚ አብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜን።ወስብሐ ት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

የአረቡን ዓለም ያንቀጠቀጡ የኢትዮጵያ ጠንቋዮችና መተተኞች!! 17 ዓመት ሰርታ ብኩን ባዶ አደረኳት ምንም የላትም!! የአርቲስቷ ማሪያማዊት ጉዳይ!! #ጸሎት https://youtu.be/jcnlPURTojc?si=xejaj0_nIULef5Lt

የእግዚአብሔር ፍርድ ቢዘገይ እንጅ አይቀርም!! <<ቆሞስ አባ>> ክፍለ ማርያም ይባላል። የባሕር ዳር ዓባይ ማዶ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን 'አስተዳዳሪ' ነው። እሙሃይ ሐመልማል የተ
+1
የእግዚአብሔር ፍርድ ቢዘገይ እንጅ አይቀርም!! <<ቆሞስ አባ>> ክፍለ ማርያም ይባላል። የባሕር ዳር ዓባይ ማዶ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን 'አስተዳዳሪ' ነው። እሙሃይ ሐመልማል የተባለችው የደብሩ ዐቃቢ መነኵሲት በግዳጅ ደፍ*ሮ ወለደ። መነኵሴዋ ደ*ም አነባች። ሕፃኗ ስትወለድ ቍርጥ እሱን መሰለች። ክስ ተመሠረተበት። ክዶ ተከራከረ። DNA ምርመራ ይካሔድ ሲባልም አሻፈረኝ አለ። በሚስኪኗ ላይ ጠበቃ ቀጠረ። የፍርድ ሒደቱ ተጓተተ። ይባስ ብሎ ነገሩ እንዲመቸው ችሎቱ ከዐዲስ አበባ ወደ ባሕር ዳር ተዛወረለት። እንደ ዋዛ ሦስት ዓመታት ነጐዱ። ብዙዎች ድምጽ አሰሙ። ሀገረ ስብከቱም ዝምታን መረጠ። ይባስ ብሎ የክፍሉ አባትም ታቦት አቁመው <<ሁላችንም እንታማለን>> ሲሉ በዐደባባይ አስተባበሉ። አሁን ከሦስት ዓመታት የደኃዋ ለቅሶ በኋላ ክፍሌ ከማንኛውም የክህነት ሥራ መታገዱን ከውስጥ ምንጭ ሰምተናል። እግዚአብሔር ምን ዓይነት ተአምር ያሳየን ይሆን? ገዳም ጥለው፣ ምናኔውን ንቀው፣ ወደ ከተማ ፈርጥጠው፣ በየመዋቅሩ የተሰገ*ሰጉ የገንዘብ መነኰሳት ቤተ ክርስቲያንን አንገት እያስደፏት ነው። የከተማ ምንኵስና ገና ብዙ ጊዜ ይቀ*ብ*ረናል። በዚህን ያሕል ጊዜ በመቅደሱ ሲንፈላሰስ ትንሽ እንኳ ሕሊናው አይፈርድበትም። ድፍረት ግን ምን ዓይነት በ*ሽ*ታ ነው?? ጊዜ ከሰጠን ገና ብዙ እናያለን። እግዚአብሔር ግን ይፈርዳል። አዎ ት ትዕግሥት እያበዛ ቸርነቱ እየከለከለችው እንጅ እግዚአብሔር ይፈርዳል።