HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 269
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+2130 días
Archivo de publicaciones
=> ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (St. John Chrysostom) ናርሲስት ሰዎች ስላላቸው "የምስጋና ጥማት" ሲያስረዳ፦ "ትዕቢተኛ ሰው እንደ ንፋስ ፊኛ ነው፤ በውስጡ ምንም የለውም ነገር ግን በትልቅነቱ ይኩራራል። የሌሎችን ምስጋና ካላገኘ በስተቀር ሕልውና የለውም" ይላል። አባቶች እንደሚመክሩት፣ እንዲህ ያለው ሰው "የሰው ምስጋና መርዝ እንደሆነ" ማሰብ አለበት። ምስጋናን በፈለገ ቁጥር "እኔ አፈር ነኝ" የሚለውን ሐሳብ እንዲያሰላስል ይመከራል።
=> የጋዛው ቅዱስ ዶሮቴዎስ (St. Dorotheos of Gaza) ስለ ትሕትና ሲያስተምር እንዲህ ይላል፦ "ሰላም ማግኘት የምትፈልግ ከሆነ፣ በማንኛውም ነገር ላይ 'እኔ' የሚለውን ሐሳብ አውጣ።" ናርሲስት ሰው ሁሉንም ነገር ወደ ራሱ ያዞራል (Self-referential)። ቅዱስ ዶሮቴዎስ እንደሚለው፣ ፈውሱ የሚጀምረው "ሁልጊዜ እኔ ነኝ ትክክል" የሚለውን ሰይጣናዊ ሐሳብ በመተውና "ወንድሜ ይሻለኛል" በማለት ነው።
=> በናርሲስት ሰዎች ምክንያት ለሚሰቃዩ (ለምሳሌ በትዳር ወይም በሥራ) የቤተክርስቲያን አባቶች የሚከተሉትን ነጥቦች ይመክራሉ፦ 1. መንፈሳዊ ንቃት (Discernment)፦ ናርሲስት ሰዎች ሰይጣናዊ በሆነ መንገድ ሰውን የማሳመን (Manipulation) ተሰጥኦ አላቸው። ቅዱስ እንጦንስ "መለያየትን (Discernment) ተማሩ" ይላል። አንድ ሰው በፍቅር ስም ማንነትህን ሊያጠፋውና ከእግዚአብሔር ሊለይህ ሲሞክር፣ ያ ፍቅር ሳይሆን እስራት መሆኑን ተረድተህ ራስህን መጠበቅ ክርስትና ነው። 2. ትዕግስት እንጂ ተገዢነት አይደለም፦ ክርስትና "የዋህ" እንድንሆን ያዘናል እንጂ "ሞኝ" እንድንሆን አያዝዝም። ቅዱስ ባሲልዮስ እንደሚለው፣ ክፉ ሰው ሕይወትህን እያወደመ ዝም ማለት እርሱን በኃጢአቱ መተባበር ነው። ስለዚህ በጸሎት እየተጋደሉ፣ ራስን ግን ከጥቃት መጠበቅ (Boundaries) መንፈሳዊ ግዴታ ነው። አስተውሉ! "ከእግዚአብሔር ይልቅ ራሱን የሚወድ ሰው፣ በመጨረሻ ራሱንም ያጣል፤ እግዚአብሔርን የሚወድ ግን ራሱንም ያገኛል፣ ሌሎችንም መውደድ ይቻለዋል።"
"ከፍተኛ የትዕቢት ደዌ" Or ናርሲስት (Narcissist)
=> ናርሲስት (Narcissist) የሚለው ሥነ-ልቦናዊ ቃል፣ በመንፈሳዊው ዓለም "ከፍተኛ የትዕቢት ደዌ" ወይም "ራስን የመውደድ (Philautia)" ጣዖት ተብሎ ሊገለጽ ይችላል። በኦርቶዶክሳዊ እይታ፣ አንድ ናርሲስት ሰው በራሱ ማንነት ላይ የቆመ፣ ሌላውን ለማሳነስ የሚጥርና እግዚአብሔር ሊኖርበት በሚገባው የልቡ ዙፋን ላይ "ራሱን" ያስቀመጠ ሰው ነው።
=> በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትምህርት የናርሲዝም መሠረቱ ትዕቢት (Pride) ነው። ትዕቢት ደግሞ የኃጢአት ሁሉ እናትና ሰይጣን የወደቀበት የመጀመሪያው ደዌ ነው። ቅዱሳን አባቶች "የፍላጎቶች ሁሉ እናት ራስን መውደድ ናት" ይላሉ። አንድ ሰው ከእግዚአብሔርና ከባልንጀራው ይልቅ ራሱን ብቻ ማዕከል ሲያደርግ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ይታመማል። ናርሲስት የሆነ ግለሰብ ወይም ሰው ከሰው ምስጋናን እጅጉን ይፈልጋል፤ ይህ ደግሞ በቤተክርስቲያን "ከንቱ ውዳሴ" (Vainglory) ይባላል።
=> አንድ ናርሲስት ሰው እንዴት ሊድን/ሊለወጥ ይችላል?
*** በመንፈሳዊው ዓለም የማይፈወስ ደዌ የለም፤ ነገር ግን ፈውሱ የሚጀምረው ግለሰቡ "ታምሜአለሁ" ብሎ ሲያምን ብቻ ነው። ፈውሱ የሚከተሉትን ደረጃዎች ይጠይቃል፦ እውነተኛ ንስሐ፦ ንስሐ ማለት "ሐሳብን መለወጥ" ማለት ነው። ናርሲስት ሰው ዓለምን የሚያየው በእኔነቱ መነጽር ብቻ ነው። ንስሐ ደግሞ ትኩረቱን ከራሱ ላይ አንስቶ ወደ እግዚአብሔር እንዲያደርግ ይረዳዋል። "እኔ" ከሚለው ቃል ወደ "ጌታ ሆይ ማረኝ" ወደሚለው ቃል መሸጋገር የመጀመሪያው እርምጃ ነው።
*** ትሕትናን መለማመድ (Practicing Humility)፦ ትሕትና የናርሲዝም ቀጥተኛ መድኃኒት ነው። ማንም ሳያየውና ሳይመሰግነው ዝቅ ያሉ ሥራዎችን (ለምሳሌ ቤተክርስቲያን መጥረግ፣ ደካሞችን መርዳት) እንዲያከናውን ይመከራል። ይህም "እኔነቱን" የመስበር ተግባር ነው። ቅዱስ ጳውሎስ "ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ያስብ" (ፊልጵ 2፡3) እንዳለው፣ ሌሎችን ማድነቅና ማክበርን መለማመድ አለበት። የናርሲስት ሰው ትልቁ ችግር "እኔ አውቃለሁ" ባይነት ነው። ስለዚህ ለንስሐ አባት መታዘዝ ትልቅ ፈውስ ነው። የራሱን ፈቃድ ሰብሮ ለአባትየው ምክር መገዛቱ "ራስን የመግዛት" (Self-denial) ትልቅ ልምምድ ነው። ናርሲስት ሰው የሚያደርገው መልካም ነገር ሁሉ ለሰው "ታይታ" እንዲሆን ይፈልጋል። መድኃኒቱ ግን በስውር መስጠት ነው። ቀኝ እጁ ሲሰጥ ግራ እጁ እንዳታውቅ በማድረግ (ማቴ 6፡3) ያንን ለሰው ምስጋና የሚገዛውን ማንነቱን ይገፋዋል። አባቶች እንደሚመክሩት ሞትን ማሰብ ትዕቢትን ያጠፋል። "አፈር ነኝ፣ ወደ አፈርም እመለሳለሁ" ብሎ የሚያስብ ሰው፣ ራሱን ከሌላው በላይ አድርጎ ለመስቀል የሚኖረው ጉልበት ይቀንሳል።
=> በዙሪያህ ያለ ናርሲስት ሰው እንዲለወጥ ስትጸልይ፣ አንተ ራስህ በበሽታው ሰለባ እንዳትሆን መጠንቀቅ አለብህ፦ ወሰን ማበጀት (Boundaries)፦ ክርስትና ማለት ለበደለኛ ሰው "ምንጣፍ" መሆን ማለት አይደለም። በክርስቲያናዊ ጨዋነት ራስህን ከጥቃት መከላከልና "አይሆንም" ማለት ትችላለህ። በትዕግስት መጸለይ፦ ናርሲዝም ጥልቅ የሆነ የስነ-ልቦና እና የመንፈሳዊ ስብራት ውጤት ሊሆን ስለሚችል፣ ግለሰቡን እንደ ጠላት ሳይሆን እንደ ታካሚ አይቶ መጸለይ ይገባል። ምሳሌ መሆን፦ ክርክር ውስጥ ከመግባት ይልቅ በትሕትናህና በፍቅርህ እንዲሸነፍ ማድረግ (በራሱ ላይ ፍም መከመር) የተሻለ መንገድ ነው።
=> ናርሲዝም በአንድ ጀንበር የሚጠፋ ሳይሆን፣ በረጅም ጊዜ ጸሎት፣ በንስሐና በትሕትና ልምምድ የሚፈወስ "የነፍስ ቁስል" ነው። እግዚአብሔር የድንጋዩን ልብ ወደ ሥጋ ልብ የመለወጥ ኃይል አለው (ሕዝ 36፡26)። ዋናው ቁልፍ ግን ግለሰቡ ከራሱ አምላክነት ወርዶ ለእውነተኛው አምላክ ለመገዛት ያለው ፈቃደኝነት ነው።
በክፉ መንፈስ እየቀደሙን እኛ ዘወትር ቁልቁል እንጓዛለን ይማረን በእውነት!! ብዙ ሰዎች በአጋንንት ተደግፈው ኑሯቸውን ጭንቀት አድርገዋል!! https://youtu.be/O8TFiE-ygTU
እግዚአብሔር በ5 መንገድ ሁላችንንም ይፍትነናል ይኼንን በደንብ አዳምጡ!! መከራና ፈተና ሲበዛባችሁ ይኼንን በደንብ አስተውሉ!! https://youtu.be/TjLZChFG7i8
ይኼ ወንድማችን ያልሞከረው የአስማትና የጥንቆላ ተግባር የለም ዛሬ ግን ተለውጧል!! የሚገርሙ የህይወት ገጠመኞች በትንሳኤ እንግዶች! #በመምህር_ተስፋዬ_አበራ https://youtu.be/nEE0YY1J74U?si=TJSHPPqH9_j0wzSD
ከፋሲካ በኋላ ልናደርጋቸው የሚገቡ 6 ወሳኝ ነጥቦች! https://youtu.be/CmZkoMN5sdQ?si=enHcuO4ifAPfPNCr
+ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም በጤና በፍቅር አደረሳችሁ። የትንሳኤው ጌታ ሁላችንንም በበረከት በሰላም በጤና ይሙላን። ውድ ቤተሰቦቼ በያላችሁበት የእግዚአብሔር ፍጹም ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን። በርቱ ጠንክሩ!!
እግዚአብሔር ያክብርልኝ በወጣ ይተካ የትንሳኤው ጌታ ቤታችሁን በበረከት ይሙላ። ብዙ ሰዎች በዚህ የበረከት ሥራ ተሳትፋችኋል ክበሩልኝ። ፈበን እህታችን ደግሞ ይሄንን አስገብታለች።
Hi, Mache Tsenga kidus Michael Bete Christian! I've sent you 200960.1 ETB to your bank account ending in *****9216.
Here's the money transfer PIN: 12518802313 and Order number IT463753909.
You'll see the money deposited in your account when it's available. You can track this transfer directly in the Ria app or at https://ria.mt/en-GB/track/IT463753909
ብዙዎቻችን በዚህ ምክንያት ከሥጋውና ደሙ የራቅን አይመስላችሁም!! ነገሮች አልሳካ ካላችሁና ከተዘጋጋባችሁ ይኼንን ማድረጋችሁን እንዳትረሱ!! https://youtu.be/vTII-hG6qb8
ዛሬ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከ11፡00 ሰዓት በኋላ ሕልሞቻችንና ፍችዎቻቸው በሚል ክፍል 5 ዛሬ እንቀጥላለን። ስለዚህ ሁላችሁም #የዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
https://youtube.com/@haileG2239
ውድ ቤተሰቦቼ እንኳን አደረሳችሁ። ስግደት፣ ጾሙ፣ ሱባኤውና ጸሎቱ እንዴት አለፈ? ዕለተ ስቅለት እንዴት ነበር? ዘወረደ ብለን ጀምረን ለዛሬው ልዩ ቀን በሰላም ያደረሰን አምላክ ለብርሃነ ትንሳኤውም በሰላም ያድርስን። መልካም ምኞታችሁን ሁላችሁም ጻፉ።
መልካም ምሽት!
👉 ጌታዬ ሆይ
"ተፈጸመ" ስትል ራስህን አዘነበልክ፤ እኔን ቀና ለማድረግ።
👉 ያለ በደልህ ተሰቀልክ፤ እኔን ከሞት እስራት ለመፍታት። እኔ በኃጢአት በደለልኩ፣ አንተ ግን በችንካር ተከፈልክ። እኔ ጥፋት አጠራቀምኩ፣ አንተ ግን ደምህን አፈሰስክ።
አምላኬ ሆይ! ያ "ተፈጸመ" ያልከው ቃል ዛሬ የልቤን ክፋት ይፈጽመው።
👉 የኔን ኃጢአት በመስቀልህ ላይ ቅበረው። አንተ ለእኔ ሙተህ እኔ ግን ለአለም መሞት አቅቶኛልና፣ ዛሬ በዚህች ሰዓት ነፍሴን ካንተ ጋር ስቀላት።
ከመስቀልህ ስር በንስሐ ወድቄያለሁ፤ አትለፈኝ። በደሙ ዋጋ የገዛኸኝ ወዳጅህ ነኝና፣ በመንግሥትህ አስበኝ።
አሜን።
👉3960 ብር ለቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ገቢ ሆኗል። እግዚአብሔር ይስጥልን ወንድማችን በወጣ ይተካ። ቅዱስ ሩፋኤል ረድኤት በረከቱ በሁላችን ላይ ይሁን።
+1
👉 64,400 ብር በ21 ንፋስ ቀላቅሎ በዘነበው ዝናብ ለፈረሰው ለቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቼ ይሄው ገቢ አድርገዋል። እግዚአብሔር ይስጥልኝ። ቅዱስ ሚካኤል እቅፍ ድግፍ ያድርጋችሁ።
ይኼንን ማድረግ ካልቻላችሁ እባካችሁ ዝም ብላችሁ አትድከሙ!! በመንገዳችን በኑሯችን ያደፈጠን አጋንንት ለማሸነፍ ይኼው መፍትሔ!! https://youtu.be/ppTrpvjnH-c
መተትና አጋንንት ወደኛ በተላከ ሰዓት ይኼንን በደንብ ማስተዋል ይገባችኋል!! ሁላችሁም ማዳመጥ የሚገባችሁ ሁለት መልዕክቶች!! https://youtu.be/N5KqJkqyBKg
እህታችን ወለተ ሰንበት 1000 ብር አስገብታለች እግዚአብሔር ያክብርልኝ በእውነት። በወጣ ይተካ ቢያለሁ ሌሎቻችሁም በዚህ የበረከት ሥራ ተሳተፉ ይኼ ወቅት ደግሞ የበረከት ሥራ በደንብ የሚሰራበት ነውና ሁላችሁም የቻላችሁትን አስገቡ። መልካም ቀን።
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
