HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 277
Suscriptores
-124 horas
+107 días
+3530 días
Archivo de publicaciones
የመምህር ግርማ የእስር ቤት ገጠመኝና የመናፍስቱ ሴራ!! ብዙዎቻችን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ተወልደናል!! ቀያይ ልብስና ጥለቶችን የሚወዱ የዛር አጋንንቶች!! 😱💥😭 https://youtu.be/kKhI5vAOrtw
++ ከሰኞ ወዳሴ አምላክ ++
"የተባረኩ ደቀ መዛሙርትህን ዐይኖች እንደ ከፈትህ፣ የተቀደሱ መጻሕፍትንም እንዳወቁ፣ አምላካዊ የኾነ የቃሉን ትርጒምም እንደ ተረዱ ወደምታስደንቅና አምላካዊ ወደ ኾነ ዕውቀትም እንደ ተመለሱ። አቤቱ የተቀደሱ መጻሕፍትን ትርጓሜያቸውንም እረዳ ዘንድ፣ ትእዛዝህንና ፍቃድህን አደርግ ዘንድ የዕውሩን ዐይን እንዳበራህ ሥጋዊና መንፈሳዊ ብርሃንንም እንደ ሰጠኸው ለእኔም እንዲህ ዓይነት ጸጋን ስጠኝ፤ አቤቱ እውነተኛ ብርሃንን አይ ዘንድ የሚያስደስትህንም አደርግ ዘንድ የልቤን ዐይኖች ክፈትልኝ።" (ተስፋ ሚካኤል ታከለ (መ/ር ወተርጓሚ)፣ ውዳሴ አምላክ ዘሰኑይ ቍጥር 22)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
+2
የበረከት ሥራ ፡ ለሙዳይ የበጎ አድራጎት ማዕከል
ውድ ቤተሰቦቼ እንኳን ለዐብይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ። ዛሬ ለሁላችንም የሚጠቅም በረከት የምናገኝበት የበረከት ሥራ ይዠላችኋለሁ። አቅማችን በፈቀደው መንገድ እንሳተፍ ሁላችንም።
=> አንደኛ ቦታው ድረስ መሄድ የምትችሉ ቤተሰቦቼ ቦታ ድረስ በመሄድ በመጎብኘት ማገዝ በምትፈልጉት መንገድ ማገዝ ትችላላችሁ።
=> ሁለተኛው ደግሞ ካላችሁበት ሆናችሁ ባላችሁ ነገር እንደ አቅማቸሁ ይሄንን የበረከት ሥራ ማገዝ በገንዘብ፣ በሀሳብ በሌሎችም ነገር ማገዝ መልካም ነው። ከታች በመስቀምጠው ስልክ ደውላችሁ ማነጋገርና ማገዝ ትችላላችሁ።
=> ሦስተኛው ደግሞ እኔ እንዳደርስላችሁ የምትፈልጉና በዚህ የበረከት ሥራ ላይ አብራችሁን መሳተፍ የምትፈልጉ በዚህ ስልክ ደውላችሁ ልታናግሩን ትችላላችሁ 0939241162 ሌላው በአካውን በማስገባትም በዚህ የበረከት ሥራ መሳተፍ ትችላላችሁ። በቀጥታ ወደ አካውንት በማስገባትም እኛ እንድናደርስላችሁ ከፈለጋችሁ በመደወል ልታናግሩን ትችላላችሁ።
ውድ ቤተሰቦቼ ይሄንን የዐብይ ጾም በዚህ አይነት አገልግሎት በናሳልፍና የበረከቱ ተካፋይ ብንሆን መልካም ነው።
እግዚአብሔር ሁላችንንም ይርዳን ያግዘን። እንበርታ እንጠንክር።
ኪዳነ ምሕረት (16)
+++ በድንቅ ጥበቡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ያደነው እጅጉን መሐሪ ስለሆነ ነው፡፡ የቀደሙት የብሉይ ኪዳን ኪዳናት ሕዝቡን ከሲኦል መታደግ አልቻሉም ነበር፡፡ ፍጹም የሆነው ኪዳን የተደረገው በሰባተኛው ኪዳን ይህም ለሰው ዘር ምሕረትን ባስገኝች በንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ነው፡፡
+++ የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠችውን እናታችንንም ‹‹ኪዳነ ምሕረት›› እያልን የምንማጸናት ለዚህ ነው፡፡ ለአዳም የተገባለት የምሕረት ቃል በእርሷ ተፈጽሟልና፡፡ እመቤታችን አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ወልዳዋለችና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራን ተቀብሎ እንዲሁም በመስቀል ተሰቅሎ ዓለምን ያዳነው ከእርሷ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነውና፡፡
+++ በነገረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት በኋላ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ መቃብር ቦታ ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ስለ ነበር በየካቲት ፲፮ ቀን በጸለየችው ጸሎት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ጸሎቷም እንዲህ የሚል ነበር፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ፥ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡››
+++ ጌታችንም ምን ሊያደርግላት እንደምትሻ ሲጠይቃት በስሟ ለሚማጸኑ፣ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን፣ ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጨምራ ጠየቀችው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በየካቲት ፲፮ ዕለት የገባላትን ቃል ኪዳን እንዲህ በማለት በመሐላ አጽንቶታል፡፡ ‹‹መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ፡፡››
የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠበት ይህ ዕለት ታላቅ ነውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቅት ታከብረዋለች፡፡ ቀድሞ ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነውና፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡
+++ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ የሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና ችግረኛ መርዳት ይገባናል፡፡
+++ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
የጠንቋይና የደብተራ ልጆችን ውጭ ሀገር ውስደው የሚያሰለጥኑ ፈረንጆች!! ገጠመኝ እያልክ ለምን ታሾፍብናለህ ይሉኛል!! የፈረንጆቹን ጉድና ሴራ ተመልከቱ!! https://youtu.be/65hctlj6fSo?si=U905jHV6xF5Pp9bM
+1
+++ ሰላም ሰላም እንዴት ናችሁ ሁሉ መልካም ነው። እንኳን ለኪዳነ ምህረት አመታዊ ክብረበዓል የዋዜማው ዕለት በሰላም አደረሳችሁ። ሰሞኑን በጣም ከገረሙኝ ነገሮች አንዱ፤ የእኛን ቻናሎች የማዘጋትና ቻናሉን የማስቆም ሥራዎችን በብዛት በስም የምናውቃቸው ብዙ ተከታይ ያላቸው ቻናሎች ያውም ደግሞ መንፈሳዊ ቻናሎች፤ የእኛ ቻናል ለየት ብሎ የዲያብሎስን ሴራ በማጋለጡ ቻናላችንን ለማዘጋት በሚገርም ሁኔታ ርፖርት እያደረጉ ይገኛሉ እና ይኼ ድርጊታቸው ከዚህ በፍትም እንዲሁ ክ37ሺህ በላይ ቤተሰብ የነበረኝን ቻናል ለማዘጋት እንዲሁ አድርገው ነበር ነገር ግን እነሱ የፈለጉትን መንገድ ይጓዙ እኛም ጠላታችንን ማዋረዳችንን እንቀጥላለን። አሁን ደግሞ ትላንት የወንድማችንን ፍቅረ ገብርኤልን @user-eneho-tube የዩቱብ ቻናል በአባ ገብረኪዳን ላይ በሰራው ቪዲዮ በሚገርም ሁኔታ ቻናሉን ለማዘጋት እንቅስዋሴ ላይ ናቸው። ይኼ በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው በእውነት ሰልዚህ ውድ ቤተሰቦቼ ሁላችንም አሁንም በደንብ መንቃት ያለብን ጊዜ ነው። ስለዚህ ሁላችንም ወደ ቻናሎቻችን በመግባት ቤተሰብ ይሁን ለብዙ ሰዎች እንዲዳረስ ሸር እናድርግ። መልካም ቀን ይሁንልን።
የፍቅረ ገብርኤል የዩትብ ቻናል፡ @user-eneho-tube @estifo2239 @haileG2239
+++ የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል። ከእግዚአብሔርና ከትዕዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ።
+++ ንስሐ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው። ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውንም ዓይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ሁለም ተባበር። እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ጉዳችን! በተዋቡና ባማሩ ቤቶች ውስጥ እየኖሩ ውስጣቸው ግን ባዶ! በዲያቆን ሄኖክ የተነገረ አስገራሚ መልዕክት! ወንጌል የምንማረው ለጠቅላላ ዕውቀት አይደለም! https://youtu.be/Ap22EBJKY-A
=> የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት፣ ቃልኪዳናቸው ይደርብን በእውነት። የጻድቁ አባታችን አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን። እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ ስለ ጻድቁ አቡነ አረጋዊ ብለህ ማረን ይቅር በለን። ሀገራችንን ኢትዮጵያንም ሰላም አድርግልን። አሜን
+++ ብዙዎች በሰርጋቸው ቀን "የአገራችን ባሕል ነው" የዘፈን ድግስን ያዘጋጃሉ። ወይም ደግሞ "ቤተሰብ እሺ አይልም" በማለት እንደሚቸገሩ ይናገራሉ። ነገር ግን ይህን የቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ ቃል ማስታወስ ይገባል።
=> "አስተውሉ! ጋብቻ ዝሙትን የምናጠፋበት መድኃኒት ነው። ስለዚህ በዲያብሎስ ስራ (በዘፈን) ጋብቻን አናቃልል። ከዚህ ይልቅ አሁን የሚያገቡ ሰዎች በቃና ዘገሊላ እንደ ኾነው ያድርጉ። በመካከላቸው ጌታችን ክርስቶስ እንዲኖር ያድርጉ። "እንዴት ይህን ማድረግ ይችላሉ? ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል። ካህናትን በመጥራት! 'እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል' ይላልና (ማቴ 10:40)። ስለዚህ ዲያብሎስን አርቁት። የሴሰኝነት ዘፈኖችን፣ የርኵሰት ዜማዎችን፣ ሥርዓት የለሽ ጭፈራዎችን፣ የሚያሳፍሩ ቃሎችን፣ ዲያብሎሳዊ ትርኢቶችን፣ ሁከቶችን፣ቅጥ ያጡ ሳቆችን፣ ሌሎች እነዚህን የመሰሉ አግባብ ያይደሉ ነገሮችንም አስወግዱ። በእነዚህ ፈንታም የጌታችን ክርስቶስ ቅዱሳን አገልጋዮችን ጥሩ ፣ በእነርሱም በእውነት ያለ ሐሰት ከእናቱና ከወንድሞቹ ጋር በሰርጋችሁ ላይ ይገኛል። " በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነው" ብሏልና (ማቴ 12:50)።
=> አንዳንድ ሰዎች እንደዚህ ያሉ ተግሣጻትን ስለምናገርና የጥንት ባሕሎችን ስለማስቀር አሰልቺና አስቸጋሪ እንደ ኾንኩ አድርገው እንደሚያስቡ ዐውቃለው። ነገር ግን እነርሱ ስለ ተቃወሙኝ በፍጹም አልጨነቅም። እኔ የምፈልገው በእናንተ ዘንድ ተቀባይነትን ማግኝት ሳይኾን የእናንተን ጥቅም ነውና። ከዚህ ጥበብ ጥቅምን እንድታገኙ እንጂ እንድታመሰግኑኝ አልፈልግምና። ስለዚህ "ይህ ባሕል ነው" ብሎ አንድ ሰውስ እንኳ አይንገረኝ። ኀጢአት በድፍረት የሚፈፀምበት እስከ ኾነ ድረስ ባሕሉን እርሱት። ክፉ ሣራ የሚሰራባቸው እስከ ኾኑ ድረስ ባህሎቹ የቱንም ያህል ጥንታውያን ቢሆኑ ከእናንተ አስወግዷቸው። ክፉ ስራ የማይሰራባቸው ከኾኑ ግን ያልተለመዱ እንኳን ቢሆኑ ተቀበሏቸው።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
“ላገቡት” የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
=> ባልና ሚስት አንድ መኾናቸውን ብዙ ጊዜ ስለ ተማራችሁት እርሱን አልደግምላችሁም፡፡ ከዚህ ተነሥቼ ግን ጥያቄ ልጠይቃችሁ፦ ከሰውነታችሁ ውስጥ አንዱ ሕዋስ ቢታመም ቆርጣችሁ ትጥሉታላችሁን? ከሕመሙ ይፈወስ ዘንድ የምትጥሩ አይደላችሁምን? ለትዳር አጋራችሁም እንደዚህ መኾን አለባችሁ፡፡ እንደዉም'ኮ፥ ከሰውነታችሁ ሕዋስ ውስጥ ያለው በሽታ አንዳንዴ ላይድን ይችላል፡፡ የትዳር አጋራችሁ ግን፥ ምንም ክፉ ቢኾንም ሊለወጥ ይችላል፡፡ በሰውነታችን ላይ የሚኖረው አንዳንዱ ችግር ለምሳሌ ልምሾ እጅ ወይም እግር ሥራ መሥራትን ሊከለክለን፣ በሌላዉ የሰውነታችን ክፍል ላይ ጫና ሊያሳድርብን ይችላል፤ ነገር ግን ይበልጥ እንክብካቤ እናደርግለታለን እንጂ ቆርጠን አንጥለዉም፡፡ ታዲያ መዳን ለማይችለው ሰውነታችን ይህን ያህል እንብካቤ እያደረግንለት ሳለ፥ የመዳን (የመለወጥ) ዕድል ያለው አካላችንን (ባለ ትዳራችንን) መቁረጥ (መፍታት) እንደ አማራጭ ማስቀመጣችን እንዴት ብናብድ ነው? ታዲያ ሁላችንም ልናስብበት የሚገባ ወሳኝ ተግሳጽና ምክር ነው ቤተሰቦቼ!!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የቤት አከራዮችና ተከራዮች የመናፍስት ፈተና!! የቤታዮ እህታችን አስገራሚው ጥያቄ!! ጸሎትና ስግደት ጀምሮ ማቆም ያለው ፈተና!! #ethiopia #ጸሎት #ንቁ https://youtu.be/OnYN7dmSvO0
አንድ ክርስቲያን ልሰራው የምችለው ትልቁ ኃጢአት ተስፋ መቁረጥ ነው!!! #ethiopia #abelbirhanuየወይኗልጅ #አባ_ገብረኪዳን_ግርማ #habesha https://youtu.be/OKJITRxkD8k
የምትፈዙ፣ የምትደነዝዙ፣ የሚጨላልምባችሁ ከሆን ይኼንን አዳምጡ!! መናፍስት በዙሪያችን ሲያደቡ ምን እናድርግ?? እራስህን አጥፋ አጥፋ ይለኛል ምን ላድርግ?? https://youtu.be/J8zm7ntq7So
++ ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤል ዘታህሳስ ም.2:24 እንዲህ ይላል፦ "ማሪያምን ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ በማይመረመር ንጽሕና ክብር በእውነት አነጻት አከበራት እንጂ። ወልደ እግዚአብሔርም ሰው በሆነ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባት ጽንስዋ ያለዘርዐ ብእሲ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ይሆን ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ለአንድ ሰዓት ለዓይን ጥቅሻ ያህል እንኳን ከእሷ አልተለየም። ለዘለዓለሙ ከእሷ ጋር ባለመለየት ይኖራል የእግዚአብሔር እናት ትሆን ዘንድ የልዑል ኃይል ጠበቃት።"
+++ ሃይማኖተ አበው ዘአባ ገብርኤል ም.94 ክ.2 ቁ.11 እንዲህ ይላል፦ "ሁል ጊዜ ንጽሕት ድንግል በምትሆን በደንግል ማህጸን እንደ አደረ ከአብርሃም ከተገኘ በድንግልና ከጸና ባሕሪይዋ የምታውቅ የምትናገር ነፍስ ያለችው፤ የእኛን የሚመስል የአዳምን ሥጋ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ሊዋሐደው እንደፈጠረ አምናለሁ፤ እንዲህ ቃል ሥጋ ሆነ፤ በባሕሪይ በአካል ተዋሕዶ ከሥጋችን ሥጋን ከነፍሳችን ነፍስን ነስቶ ስለ እኛ ሰው ሆነ ያለመለወጥ ያለማጥፋትም እኛን መምሰልን ገንዘብ አድርጎ ያለመለወጥ ያለመቀላቀል በባሕርዩ ጸንቶ ኖረ።"
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አክርስቶዶሎስ ምዕራፍ 112 ክፍል 2 ቁ.19 ላይ እንዲህ ይላል፦ "ለእኛ ፈጽሞ እንደተገለጠልን እግዚአብሔር ቃል ነፍስን ሥጋን ነስቶ እንዲህ ሰው ሆነ፤ እሷም በእውነት ወላዲተ አምላክ ናት፤ አምላክን የወለደች ናት፤ ከወለደችውም በኋላ ድንግል ናት፤ ማህተመ ድንግልናዋ አልተለወጠም፤ ፈጽሞ አደፍ ጉድፍ የለባትም፤ ስለዚህም ከእሷ የተወለደው እሱ እግዚአብሔር ነው እንጂ ዕሩቅ ብእሲ አይደለም፤ ከእመቤታችን ከማሪያም የተወለደው ዕሩቅ ብእሲ ነው የሚሉ ግን ይህን ከንቱ ነገር በመናገራቸው ድኅንታችንን ይቃወማሉ፤ እግዚአብሔር ቃል ሰው ሆኖ የሠራውን ሥራም ይክዳሉ።"
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ሳዊሮስ ም.87፡11 ላይ እንዲህ ይላል፦ "አሁንም የአብ ኅይሉ ቀዳማዊ እግዚአብሔር ቃል እርሱ ድንግልን «ጠበቃት» ሐሰት የሌለበት ወንጌል እንደ አስተማረን የማይመረመር መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በእርሷ በማደሩ ነፍስ ያለችው፤ የሚናገር ሥጋን አንድ አካል በመሆን ከእርሱ ጋር እንዲዋሐድ አደረገው፤ ይህም የተናገርሁት ተዋህዶ መለኮት ከትስብእት ጋር የተዋሐደው ተዋህዶ ነው።"
አርጋኖን ዘእሁድ ምዕራፍ 1፡ 18 ላይ እንዲህ ይላል፦ "እንዳትበድል ድንግል ማሪያምን ከእናቷ ሆድ ጀምሮ የጠበቃት መንፈስ ቅዱስ፥ እንዳትረክስም ያነጻት፣ ለወልድ ዋህድም ማደሪያ ያደረጋት እርሱ ነው። አብ ወደዳት ወልድ ከእርሷ ሥጋን ለበሰ መንፈስ ቅዱስም ጋረዳት።"
ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ቀናችሁን መልካም ያድርግላችሁ። መሻታችሁን ይሙላላችሁ። ዕቅዳችሁን አላማችሁን ሙሉ ያድርግላችሁ። መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን። በርቱ!
