es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 275
Suscriptores
+124 horas
+117 días
+3230 días
Archivo de publicaciones
ግንቦት ፯ /7/ በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያኛ የሆነ የከበረ አባት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ሐዋርያዊ አትናቴዎስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ሐናፊ ከሚባል የእስላም ነገድና ከአረማውያን ተወላጅ
ግንቦት ፯ /7/
በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያኛ የሆነ የከበረ አባት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ሐዋርያዊ አትናቴዎስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ሐናፊ ከሚባል የእስላም ነገድና ከአረማውያን ተወላጅ ነው ይባላል። እርሱም ከመምህር ከሚማሩ ሕፃናት ጋራ እያለ እርስ በርሳቸው በመጫወት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየሠሩ ከእነርሱ ውስጥ ዲያቆናትን ኤጲስቆጶሳትንም ሲያደርጉ እሊያን የክርስቲያንን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእሳቸው ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት እርሱም ክርስቲያን እሆናለሁ አላቸው እነርሱም ደስ ተሰኙበት። ያን ጊዜም ወስደው በሊቀ ጳጳሳት አምሳል አደረጉት ከበታቹም ወንበር አድርገው ይሰግዱለት ጀመር። በዚያን ጊዜም ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስ በዚያ አለፈ የክርስቲያን ልጆች ሲጫወቱ በአያቸው ጊዜ አብረውት ላሉ ይህ ሕፃን ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች ሹመትን ይሾም ዘንድ አለው አላቸው። አባቱም በሞተ ጊዜ ወደ አባ እለእስክንድሮስ መጣ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቀው። ከዚህም በኋላ 325ዓ.ም በኒቂያ በተደረገው ጉባዔ ላይ ተገኝቷል ስለቀናች ሃይማኖትም ተጋድሎ ከሀገር ተሰዷል። በሚሞትበትም ጊዜ በእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን ባገኝ ይህን የጣዖት ቤት ያፈርስ ዘንድ በፊቱ እኔ እየሰገድኩ እለምነዋለሁ። ይህም አባት ከአረፈ በኋላ ንጉሥ ልኮ ያንን የጣዖት ቤት አስፈረሰው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

=> እስኪ ንገሩኝ! ከእናንተ መካከል ከመዝሙረ ዳዊት ውስጥ አንዲትዋን ምዕራፍ ወይም ከሌላው የቅዱሳት መጻህፍት ክፍል ውስጥ ጥቂት በቃልህ ድገም ቢባል ይህን ማድረግ የሚችል ማን ነው? አንድ ሰውስ እንኳ አይገኝም። የሚያሳዝነው ነገር ግን ይኼ ብቻ አይደለም። ከመንፈሳዊ ነገሮች አንፃር እንደዚህ አእምሮ የጎደላችሁ ኾናችሁ ሳለ ዲያቢሎሳዊ በኾኑ ነገሮች ላይ ግን ከእሳት በላይ ኀያላን ናችሁ። እንዲህም በመኾናችሁ አንድ ሰው መጥቶ ዲያቢሎሳዊ ዘፈኖችንና የዝሙት ዜማዎችን ንገሩኝ ቢላችሁ ከእናንተ መካከል እነዚህን የሚያውቁና ደስ ተሰኝተው የሚደግሟቸው ብዙ ሰዎችን ያገኛል። => ነገር ግን"ለምንድን ነው እንደዚህ የምትኾኑት?" ተብላችሁ ስትጠየቁ የምትመልሱትስ መልስ ምን የሚል ነው? "እኔ ከመነኮሳት አንዱ አይደለሁም። ሚስት አለቺኝ፣ ልጆችም አሉኝ፣ የቤተሰብ መሪ ነኝ" የሚል ምክንያት ታቀርባላችሁ። ለምን እንደዚህ ትላላችሁ? ከመነኮሳቱ ይልቅ ይበልጥ ማንበብ ያለባችሁ እናንተ ኾናችሁ ሳለ ብዙዎች እንዲጠፉ ያደረገው "ቅዱሳት መፃህፍትን ማንበብ ለመነኮሳት ብቻ ነው" የሚለው አመለካከታችሁ ነው። ይበልጥ ብዙ መድኃኒት የሚያስፈልጋቸው በማእከለ ዓለም የሚኖሩትና ዕለት ዕለትም መንፈሳዊ ቁስል የሚያገኛቸው ሰዎች ናቸውና። ስለዚህም ከለማንበባችሁም በላይ" የእኛ ማንበብ ትረፍ ነገር ነው" ብላችሁ ማሰባችሁ በራሱ የዲያብሎስ አሳብ ነው። ወይስ ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ "ዝንቱ ኵሉ ተጽሕፈ ለተግሣጸ ዚአነ - ይህም ኹሉ እኛን ሊገስጸን ተፃፈ"(1ኛ ቆሮ 10:11) ያለውን አላዳመጣችሁምን? ቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በመምህር ግርማ ጉባኤ ላይ መንፈሱ ከታሰረላት በኋላ ከHIV ዳነች! ይኼ የብዙ ነጋደዎች ችግር ነውና ንቁበት! የብዙዎቻችን ኑሮና ሕይወት ጌርጌሴኖንን መስሏል! https://youtu.be/VmLScCFiPdQ

ምኞትና የበላይነት! መንፈሳዊ ሰው ምኞቱን፣ ደስታውን መውደዱንና የበለይነቱን አስመልክቶ ራስን መግዛት አለው። በራሱ ዓይኖች ፊት ራሱን አዋቂ አድርጎ ሲያገኝው ወይም በአመለካከቱ ውስጥ ራስን አጽድቆ ሲመለከት ወይም ደግሞ ራሱን ከሚያስበው በላይ ከፍ አድርጎ ሲያስብ ራሱን ለመግዛት ይጥራል። (ሮሜ 12፡3) https://www.youtube.com/watch?v=xtH3LpYTlbM ከዚህ በተጨማሪም እግዚአብሔር ከሰጠው ጸጋ በላይ ራሱን ሊያልቅ አይሞክርም። አስተውሉ! ዲያብሎስ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በልይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ ብሎ በትዕቢት የተነሳውን ራሱን መግዛት ባለመቻሉ ወድቋል። (ኢሳ.14፡14) https://www.youtube.com/watch?v=xtH3LpYTlbM መንፈሳዊ ሰው ራሱን የሚገዛው ውዳሴ ከንቱን አስመልክቶ ብቻ ሳይሆን ስጦታዎችንም በተመለከተ ነው። ወይም ደግሞ ሰውዬው ራሱን ከፍ ከፍ እንዳያደርግ እግዚአብሔር እርሱነቱን የሚገዛበትን መንገድ ያመቻችለታል። ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን አስመልክቶ የተናገረውን ቃል በጭራሽ አትርሱ! "ስለዚህም በመገለጥ ታላቅነት እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ እርሱም የሚጎስመኝ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ፤ ይኼውም እንዳልታበይ ነው።" (2ኛ.ቆሮ.12፡7) https://www.youtube.com/watch?v=xtH3LpYTlbM ወንድሜ ሆይ! አሳብህ ከፍ ከፍ ባለብህ ጊዜ ሁሉ ተቆጣጠረው። ራስህን ከተሰጠህ በለይ አድርገህ አትገምት። አንተነትህን ከሌሎች ጋር አነጻጽረህ ወደምትመለከትበት ደረጃ የሚመሩህ ምኞቶችህን ግታቸው። ራስህን ከፍ ከፍ ብሎ ስታየው ወይም ደግሞ በፊትህ ታላቅ ሆኖ ስታገኘው ታዛዥነትህን፣ ትሕትናህንና ለሌሎች ያለህን ክብር በማጣት ላይ መሆንህን እወቅ። በማንኛውም ጊዜ ከፊት ለፊትህ የሚከተለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አኑር። "ትዕቢት ጥፋትን ኩሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል።" (ምሳ.16፡18) (ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

አቤቱ፥ እስከ መቼ ፈጽመህ ትረሳኛለህ? እስከ መቼስ ፊትህን ከእኔ ትሰውራለህ? እስከ መቼ በነፍሴ እመካከራለሁ? ትካዜስ እስከ መቼ ሁልጊዜ ይሆናል? እስከ መቼ ጠላቴ በላዬ ይጓደዳል? አቤቱ አምላኬ፥ እየኝ ስማኝም፤ ጠላቴ። አሸነፍሁት እንዳይል፥ የሚያስጨንቁኝም እኔ ብናወጥ ደስ እንዳይላቸው፥ ለሞትም እንዳልተኛ ዓይኖቼን አብራ። እኔ ግን በቸርነትህ ታመንሁ፥ ልቤም በመድኃኒትህ ደስ ይለዋል። የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ። (መዝሙረ ዳዊት 13)

የቁራሃን መምህሩ የገጠመው የአጋንንት ፈተናና መከራው!! የተባረከ ልጅ ለማግኘት እንዴት እንጸልይ? ያላገባችሁ ሰዎች ልታዳምጡት የሚገባ ድንቅ ትምህርት!! https://youtu.be/zJcP8XpoNeg?si=POf0AjgdsbGawC87

የብዙዎቻችን ጥያቄ መልስ ያገኘበት አስገራሚው ቪዲዮ ይኼው!! የጸሎት ቤት አስፈላጊነትና የአጋንንት ውጊያ! ባልና ምስቶች ይኼንን በደንብ አዳምጡ! https://youtu.be/QoMlTeF64e0?si=qIsvzuOpgQ8uk4jR

ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤን የሚጫወታት የሙጬ ዘሪጋ የዛር አጋንንትና ምልክቶቹ!! ሰይፉ ፈንታሁንና ኩኩ ሰብስቤን ምን ነካቸ? Haile Gebriel Reacts19 https://youtu.be/RjhJQ-VA0fI?si=VvqEVaRb8iXRuWV0

እንዲህ የምታደርጉ ካህናት እባካችሁ እረፉ!! ሴቶችም ባል ማጬት ይችላሉ ነገር ግን በጥበብ!! ከበሮ በመምታት ብቻ የሚዋረሱት መናፍስትና ሴራዎቹ!! #ጸሎት https://youtu.be/avnuP4i8LWI

ግንቦት ፪ /2/ በዚች ቀን ጻድቅ ኢዮብ አረፈ። ለዚህም ጻድቅ በዘመኑ እንደርሱ ያለ ዕውነተኛ ደግ ሰው እንደ ሌለ በቅዱሳት መጻሕፍትም ስለርሱ እንደተነገረ እግዚአብሔር መሰከረለት። ሰይጣንም ቀንቶበ
ግንቦት ፪ /2/
በዚች ቀን ጻድቅ ኢዮብ አረፈ። ለዚህም ጻድቅ በዘመኑ እንደርሱ ያለ ዕውነተኛ ደግ ሰው እንደ ሌለ በቅዱሳት መጻሕፍትም ስለርሱ እንደተነገረ እግዚአብሔር መሰከረለት። ሰይጣንም ቀንቶበት በገንዘቡና በልጆቹ ላይ ያሠለጥነው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ። የጻድቅ ኢዮብን ትዕግሥት እግዚአብሔር ስለሚያውቅ አሠለጠነው ለመጪ ትውልድም አርአያና ምሳሌ እንዲሆን ፈቀደለት። ስለርሱም ሐዋርያ ያዕቆብ በመልእክቱ እነሆ የጻድቅ ኢዮብን ትዕግሥቱን ሰምታችኋል አለ። ከዚህ በኋላም በአንዲት ቀን ገንዘቡ ሁሉ ጠፋ ሥጋውም በደዌ ሥጋ ከራሱ እስከ እግሩ ድረስ ተመታ። በዚህም በአስጨናቂ ደዌ ውስጥ ኖረ እግዚአብሔርንም አመሰገነው። አንዲት ቃልን እንኳ በፈጠረው እግዚአብሔር ላይ አላጉረመረመም ነገር ግን የተወለደባትን ቀን ረገመ። እንስሶቹና ገንዘቡ ሁሉ በጠፋ ጊዜ እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔርም ነሣ የእግዚአብሔርም ስም የተመሰገነ ይሁን አለ። በዚህ መከራ በነበረበት ዘመናት በተራራ ላይ ተጥሎ ሳለ የወዳጆቹና የሚስቱ ዘለፋ በዝቶበት ነበረ። ሚስቱም አሁን ግን እግዚአብሔርን የማይገባ ቃል ተናግረኸው ሙት አለችው። እርሱም ገሠጻት። እግዚአብሔርም እዮብን ከደዌው ፈወሰው ጥሪቱን ሁሉ ከቀድሞ እጥፍ አደረገለት። ኢዮብም ከደዌው ከተፈወሰ በኋላ መቶ ሰባ ዘመን ኖረ የኖረውም ዘመን ሁሉ ሁለት መቶ አርባ ስምንት ዓመት ነው። በበጎ ሽምግልናም እግዚአብሔርን አገልግሎ በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የተበደረችውን ገንዘብ ላለመክፈል የገዛ ወንድሟን በመተት አፉን አዘጋችው!! Haile Gebriel Reacts19 https://youtu.be/UHFFm_gu9a4

12 ደብተራዎችን የጎበኜውና ለሌብነት መናፍስትን የተዋረሰው ወጣት አስገራሚው ገጠመኝ!! ለሀብትና ለሌብነት ብለው በንቅሳት የሚያስገቡት መንፈስና መዘዙ!! https://youtu.be/8r9BiY0g_0I

✥ዓለም እንዴት ደስ አይለው!✥ የእውነት ብርሃን መግቢያ በር፣ የሕይወት ዝናብ የክርስቶስ እውነተኛ ደመና፣ የጽድቅ ጸሐይ ክርስቶስ መውጫ ምስራቁ፣ የሽቱ ሙዳይ የሕይወት ውኃ መገኛ ድንግል፣ የሊቀ ካ
✥ዓለም እንዴት ደስ አይለው!✥ የእውነት ብርሃን መግቢያ በር፣ የሕይወት ዝናብ የክርስቶስ እውነተኛ ደመና፣ የጽድቅ ጸሐይ ክርስቶስ መውጫ ምስራቁ፣ የሽቱ ሙዳይ የሕይወት ውኃ መገኛ ድንግል፣ የሊቀ ካህናቱ መቅደስ፣ ከኪሩቤልና ከሱራፊ የምትበልጠዋ መንበር፣ የማይደገመው ጸጋ ባለቤት፣ የብቻ ወላዲተ አምላክነት የተሰጣት እናት የብርሃን እናት፣ ፍጹም ለወደደን ስለ ኃጢአታችን ቤዛና ማስተስርያ አድርጎ እራሱን ላቀረበው የዓለም መድኃኒት እናቱ እነሆ የክርስቶስ አያት ለመሆን ከበቁት ከኢያቄምና ከሐና ተወለደች! “ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።” የሉቃስ ወንጌል 1፥14 ለልጇ መንገድ ጠራጊው በዮሐንስ መጥምቅ መወለድ ብዙዎች ደስ ካላቸው ወደ አባቱ መግቢያ በር ወደቀደመ ክብራችን መመለሻ መንገድ የሆነውን መንገድ የሚጠረግለትን ጌታ በወለደች ድንግል መወለድ እንዴት ዓለም ደስ አይለው! እንኳን የቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምን መወለድ ለምናስበብት በዓል አደረሳችሁ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ኃጢአትን ለመተው ከመጣር ይልቅ ይኬንን ዘወትር ለማድረግ ሞክር!! ዘፈን ማቆም አቃተኝ ጨነቀኝ ምን ላድርግ? የአረብ ሀገር መተትና ከባዱ ፈተናው! የለብኝም ብለን የምንደብቀው መንፈስና ፈተናው በኑሯችን! https://youtu.be/O_gRKdXQafA?si=tG2cKN-u715yg-YN

እንዲህ አይነት አስነዋሪ ተግባር ከቄሶች በጭራሽ አይጠበቅም!! የመምህር ተስፋዬ ጥብቅ መልዕክት ለቄሶችና መምህራን ጭምር!! የዝሙትና የጥንቆላ ዜማዎች!! https://youtu.be/ko7GFsZFGwk

ብዙዎችን ለሞትና መከራ ስለዳረገው የጥላ ወጊ መተት ማወቅና መረዳት ያሉብን ነገሮች!! ይኼንን የዲያብሎስ ፈተና የተረዳ ሰው ሁሉ ያሸንፋል!! #ethiopia https://youtu.be/y2oU8vD32J8

=> የአባታችን መምህር ግርማ ወንድሙ ቀጣይ አገልግሎት የፊታችን እሁድ ግንቦት 3/2017 ዓ.ም አያት በቅዱስ ፋኑኤልና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት እና የንግስ አገልግሎት ይከናወ
=> የአባታችን መምህር ግርማ ወንድሙ ቀጣይ አገልግሎት የፊታችን እሁድ ግንቦት 3/2017 ዓ.ም አያት በቅዱስ ፋኑኤልና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት እና የንግስ አገልግሎት ይከናወናል። #አድራሽ፡ ከሁሉም አቅጣጫ መጥተው አያት አደባባይ ሲደርሱ ወይም (ደራርቱ አደባባይ ) ወደ ዞን ስምንት በሚወስደው ተራራው ላይ ቅዱስ ፋኑኤል ቤተ ክርስቲያን ይታያል። ስለ አገልግሎቱ ፈጣን መረጃ እንዲደርሳችሁ ሼር ላይክ በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ ላልነቁ አንቁ! መንፈሳዊነት ይብለጥ። ሸር ይደረግ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በጸሎት ሰዓት ከፍተኛ ማግሳት መተናነቅና መጨናነቅ ካለ ይኼንን አዳምጡ!! በምግብ የገባ መተትና የዛር አጋንንት!! ገንዘብ እከፍላለሁ ጸልዩልኝ የምሉ ሰዎች!! https://youtu.be/2XxI_byLKfo

የጬንጌርና አብዱልቃድር የዛር አጋንንቶች ሴራና ፈተናዎች በኑሯችን!! ደጋግሜ በአንድ ኃጢአት እወድቃለሁ ምን ላድርግ?? በሙዝቃ እራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች!! https://youtu.be/AGdKQqPwPwI