es
Feedback
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

Ir al canal en Telegram

💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።

Mostrar más
9 060
Suscriptores
+624 horas
-97 días
-11130 días
Archivo de publicaciones
👈‏كانت فاطمةُ رضيَ اللهُ عنهَا إذا كانَ يومُ الجمعة، أرسلَت غلامًا لها ينظرُ لها الشّمس، فإذا أخبرَها أنها تدلّت للغُروب، أقبلَت علىٰ الدُّعَاء إلىٰ أن تغِيب. 📕 [ فتح الباري كتاب الجمعة (۱۹۲۲) ] 🔖ፋጢማ አላህ መልካም ስራዋ ይውደድላትና የጅሙአ ቀን ከአሱር በኋላ አንድ ልጅ ታስቀምጥና ፀሀይ እንዲመለከትላት ታዘዋለች። ይህ ሰው ፀሀይ ልትገባ እየተቃረበች መሆኑን ሲነግራት፦ ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርጋ በመተው ፀሀይዋ እስክትጠልቅ ድረስ ወደ ዱአ ትዞር ነበር ~ t.me/https_Asselfya

ለሱና ደዕዋ የእውነት መቆርቆር ያላችሁ ወገኖች! ~ ደዕዋው በጩኸት፣ በግርግር፣ በፍጥጫ፣ በንትርክ እንዲታወቅ አናድርግ። አላህን እንፍራ። እንዲህ አይነት አካሄድ ደዕዋው ላይ ከባድ ጠባሳ ነው የሚጥለው። * እርጋታ፣ ስክነት ይኑረን። በትንሽ በትልቁ ከመጯጯህ እንውጣ። * ለደዕዋው መልካም ስም እንጨነቅ። መልካም ስም ዋጋው ከምናስበው በላይ ዋጋው ትልቅ ነው። ለራሳችን ክብር ስንል ያለፈ ያገደመው ላይ የምንጮህ ከሆነ ደዕዋውን እንጎዳለን። * ወገናችንን ከስር ጀምሮ በስርአት በዒልም መኮትኮት ላይ ቅድሚያ ሰጥተን ተግተን እንስራ። * ክፉ አመላችንን እንግራ። ጀብደኝነት፣ ከዚያም ከዚህም ጋር መላተም ይጎዳናል እንጂ አይጠቅመንም። * በየ አካባቢያችን በተቻለን አቅም ማህበራዊ ተሳትፎ ቢኖረን መልካም ነው። የተቸገረን መርዳትና ማስተባበር፣ የታመመን መጠየቅ፣ ማሳከም፣ መሻይኾችን ማክበር፣ ማገዝ፣ ወዘተ. ተግባር ከንግግር በላይ ይጣራል። የቴሌግራም ቻናል፡- = https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

7,000 እናስገባት የኡስታዛችን ቻናል ሼር 👇👇👇 https://t.me/durusuabihizam https://t.me/durusuabihizam

👉 ሱረት ካህፍ ...! ~ ➴የቻለ ይቅራ ያልቻለ ያድምጥ! ~ የአላህ መልዕክተኛﷺእንዲህ ብለዋል 👉የጁምዓ ቀን ሱረቱል ከህፍን የቀራ ሰው አላህ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል ብርሃን ያበራለታል። = https://t.me/MohamedAliEdris

{ ربنا هب لنا من أزواجنا وذرياتنا قرة أعين }
قال ابن علّان رحمه الله:
بدأ بالزوجة لأن في صلاحها صلاح الذرية [دليل الفالحين ٣٧٦/١]

~ምን ያማረ መልስ ነዉየሰዉ ባል የሰዉ ነዉ። በሰዉ እጅ ላይ ያለን ወርቅ ከመመኘት ፦በራስሸ እጅ ያለዉን መዳብ ማፅዳት ይሻላል። ~

🎀ውድ እህቴ ሆይ! ይህ ጥያቄሽ የብዙ እህቶች እንባ ያለበት፣ የብዙ ቤቶች መፍረስ መነሻ የሆነ እና እጅግ በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው። ልብ ብለሽ አድምጪኝ። 1ኛ―«ሚስቴ አትረዳኝም» የሚለው
🎀ውድ እህቴ ሆይ! ይህ ጥያቄሽ የብዙ እህቶች እንባ ያለበት፣ የብዙ ቤቶች መፍረስ መነሻ የሆነ እና እጅግ በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው። ልብ ብለሽ አድምጪኝ። 1ኛ―«ሚስቴ አትረዳኝም» የሚለው የሰይጣን ማጥመጃ ነው። አንድ ወንድ ላንቺ ብሎ የልጆቹን እናት፣ የቤቱን ንግስት፣ የአምስትና አስር አመት የትዳር አጋሩን እያማ እና እያብጠለጠለ ወደ አንቺ ከመጣ፣ እመኚኝ እሱ ታማኝ ሰው አይደለም። የቤቱን ሚስጥር ላንቺ ያወጣ ወንድ፣ ነገ ደግሞ ያንቺን ሚስጥር ለሌላ ሴት እንደሚያወጣ ጥርጥር የለውም።―ሌላን ሴት እያማ ወደ አንቺ የመጣ ወንድ፣ አንቺን ለማግባት ሳይሆን አንቺን ለመጠቀም እየሞከረ ነው።አንድ አላህን የሚፈራ  ወንድ ችግር እንኳን ቢኖርበት፣ የቤቱን ነውር ሸፍኖ እንጂ አጋልጦ ለሌላ ሴት አሳልፎ አይሰጥም። 2ኛ―በሌላ ሰው እንባ ላይ ደስታ አይገነባም! በሸሪዓችን ሁለተኛ ማግባት መስፈርትን ከማሟላት ጋር የተፈቀደ ሀላል ነው። ነገር ግን ይህ የሚሆነው በሀላል መንገድ፣ በወንድነት እና በኃላፊነት ሲመጣ እንጂ፣ በድብቅ ግንኙነት፣ በሚስት ላይ ሴራ በመሸረብ እና ሌላኛዋን ሴት በማንኳሰስ አይደለም። ሁለተኛ አቅም ካላችሁ አግቡ ግን ስለ መጀመሪያዋ ሚስታችሁ መጥፎን አታውሩ። ደሞ እህቴ…አንቺ ምናልባት «ትዳር ማፍረስ አልፈልግም» ትያለሽ፤ ነገር ግን ከእሱ ጋር የምታደርጊው ስሜታዊ ወሬ፣ እሱ ለሚስቱ የሚሰጠውን ፍቅር፣ ጊዜ እና ትኩረት እየሰረቀ ነው። ይህ በራሱ የሌላን ቤት ማፍረስ ነው። በሌላ ሴት እንባ እና ህመም ላይ የሚገነባ ትዳር በረካ የለውም። 3ኛ―«ወደፊት አገባሻለሁ»የሚለው ቃል የብዙ ወንዶች ማደንዘዣ ነው።ውድ ነገር የሚገኘው በውድ ዋጋ ነው። እውነት እሱ አንቺን የሚፈልግሽ ከሆነ እና ብቁ ወንድ ከሆነ፣ በጓሮ ሳይሆን በበራፍ ይመጣል።«ሚስቴ አትመቸኝም» እያለ ማለቅለቅ ሳይሆን፣ እንደ ወንድ «እፈልግሻለሁ፣ ወይም ሁለተኛ ማግባት አቅሙ አለኝ፣ ቤተሰብሽን ላናግር» ብሎ ይመጣል። ለማንኛውም ቆም ብለሽ እሰቢ። ስሜታዊ አትሁኚ። አሁን የምታይው የእሱን ጣፋጭ ምላስ እና እሞትልሻለሁ የሚለውን ማሽቃበጥ ብቻ ነው። ነገ አብራችሁ መኖር ስትጀምሩ ግን ዛሬ ሚስቱን ያማት አፍ፣ ነገ አንቺንም ሊወቅስበት ይችላል። ስሜት ያልፋል፤ ጸጸት ግን ይቀራል። የሰው ባል የሰው ነው። በሰው እጅ ላይ ያለን ወርቅ ከመመኘት፣ በራስሽ እጅ ያለውን መዳብ ማጽዳት ይሻላል። እሱ እውነት ወንድ ከሆነና ሁለተኛም ማግባት አቅም ካለው በሸሪዓው መንገድ ይምጣ። አላህ የተሻለውን ይተካለሻል! ይቅርታ ወንድሜ ተቆጣሁ መሰለኝ¡ እንድህ ያለ ልፍስ'ፍስ ወንድና ስለ ሚስቱ መጥፎነት የሚያወራ እስስት ባል ስለማልወድ ነው¡¡ t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1

ያፈቀሩትን ለመርሳት - ክፍል ② ▫️ትዝታው እንደ ወጀብ ሲመታህ፣ ናፍቆቱ እንደ እሳት ሲለበልብህ፣ የነበረው ቅርበት ርቆ የቀረው ባዶነት ሲያስተጋባ... በዚህ ሁሉ ህመም መሀል አንድ ብርሃን አለ። ወዳጄ... ልብ በል! አንዳንድ መለያየቶች መጨረሻዎች አይደሉም፤ አዲስ እና የተባረከ ጅምር እንጂ። ዛሬ ልነግርህ የወደድኩት ስለ "መርሳት" ብቻ አይደለም፤ ስለ "መተካት" እንጂ። የዓለማቱ ጌታ አላህ፣ በነቢዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንደበት የላከልን አንድ ልብን የሚያረጋጋ፣ ስብራትን የሚጠግን ታላቅ ቀመር አለ። "مَنْ تَرَكَ شَيْئًا لِلَّهِ عَوَّضَهُ اللَّهُ خَيْرًا مِنْهُ" «አላህን ፈርቶ አንድን ነገር የተወ ሰው፣ አላህ ከዚያ በሚበልጥ ነገር ይተካለታል" የሚለው መለኮታዊ ቃል ኪዳን ነው። ህመሙ ይገባኛል። የለመድከው ድምፅ ሲጠፋ፣ ያመንከው ተስፋ ሲጨልም ልብህ "እንዴት እኖራለሁ?" ብሎ ይሰጋ ይሆናል። ነገር ግን እስኪ ከህመሙ ወዲያ ማዶ ያለውን እውነት እንይ። አንተ ይህንን ሰው፣ ይህንን ግንኙነት፣ ይህንን ስሜት የምትተወው ስለተጠላህ አይደለም፤ ወይም አቅም ስለሌለህ አይደለም። የምትተወው ለአላህ ብለህ ነው።ይህ ግንኙነት ሀላል ስላልሆነ፣ አላህ ስላልወደደው፣ መንገድህ ወደ ኸይር ስላልመራህ... «ጌታዬ ሆይ! ስሜቴን ላንተ ስል አሸነፍኩት፣ የልቤን ምርጫ ላንተ ስል ተውኩት»ብለህ ስትወስን፤ ያኔ አንተ ዝም ብለህ እየተውክ አይደለም፤ ታላቅ ንግድ እየነገድክ ነው። 🎁እጅህ ላይ የያዝከውን አቧራ  ለአላህ ብለህ ስትለቅ፣ አላህ ወርቁን ሊያስጨብጥህ እጁን ዘርግቷል። እስኪ ራስህን ጠይቅ... አላህ ለአንተ መጥፎን ይመኝልሃልን? የከለከለህ ሊነፍግህ ነውን? በፍጹም! አላህ ከእጅህ ላይ የወሰደው፤ እጅህ ነፃ ሆኖ የተሻለውን ስጦታውን እንድትቀበልለት ነው። ለአላህ ብሎ መተው ጣፋጭ የኢማን እርካታን ያወርሳል። ትናንት በሰው ፍቅር ሲባዝን የነበረው ልብህ፣ ዛሬ በፈጣሪ ፍቅር ይረካል። ያጣሁት ሰው ይሻለኝ ነበር ብለህ አትስጋ። ፈጣሪህ የሚሰጥህ "ካሳ" ስሌቱ ረቂቅ ነው። ምናልባት የውጪ ውበቱን ወስዶ የልብ ውበት ያለውን ይተካሃል። ምናልባት ሀብት ያለውን ወስዶ፣ ሀብትም ሰላምም ያለውን ይሰጥሃል። አላህ ሲተካ ሙሉ አድርጎ፣ አሳምሮና አስውቦ ነው። 🩵ወዳጄ ሆይ...ያፈቀርከውን ሰው ለመርሳት ስትታገል፣ ይህንን ስሜትህን እንደ መስዋዕትነት ቁጠረው። ይህ ህመሜ፣ ይህ እንባዬ፣ ይህ ናፍቆቴ ለአላህ ብዬ የምከፍለው ዋጋ ነው በል። አላህ ደግሞ ለቀረበለት መስዋዕትነት ምላሹ ፈጣን ነው። ስለዚህ አሁን... ልክ በዚህ ሰዓት... ልብህን አሳምነው። በሩን ዝጋው። ያንን ምዕራፍ ቋጨው። እጅህን ከአላህ ክልከላ ሰብስበህ ወደ አላህ እዝነት ዘርጋ። እርግጠኛ ሁን! ለአላህ ብሎ የተወን ባሪያ፣ አላህ በፍጹም ባዶውን አይመልሰውም። የተሻለ መምጣቱ፣ የተሻለ መተካቱ፣ የተሻለ መኖሩ አይቀርም! t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1

🔖ከሰዎች ተገለህ ብቻህን መሆን ልመድ! 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 • ሃሜት ውስጥ ከመግባት ትታቀባለህ፡፡ • ወሬን ትተህ ጌታህን ማስታወስ ትጀምራለህ፡፡ • የሰራሃውን ወንጀል ቆም ብለህ ታይበታለህ፡፡ • እራስህን ለመገምገም ይረዳሃል .... = t.me/https_Asselfya

🔖ዚክር እና ዱዓ  ማብዛት የኸይር  ሁሉ መክፈቻ ነው። አቡል ዓባስ ኢብኑ ተይሚያህ 📚 مجموع الفتاوى (٦٦١/١٠)

﴿إِنَّ الَّذينَ يَتلونَ كِتابَ اللَّهِ وَأَقامُوا الصَّلاةَ وَأَنفَقوا مِمّا رَزَقناهُم سِرًّا وَعَلانِيَةً يَرجونَ تِجارَةً لَن تَبورَ﴾

ዝምድናን የሚቆርጥ ሰው ጀነት አይገባም።
ዝምድናን የሚቆርጥ ሰው ጀነት አይገባም።

👂ስማማ ጆሮ ያላህ በሙሉ። የአቶ ሙስጦፋ ሙሀመድ መሸሻን ግፍ በእህቶ ቻችን ላይ። ከግራዝማጂ ኸድር ጊምባ ጋር የነበራቸው ግፍ ሲጋለጥ። አረብ አገር ያሉ እህቶቻችንን ለግዜ ማሳለፊያ የጭን ገረድ ሊያደርጓት ሲያሴሩባት የሚያ ሳይ ድምፅነው። ይሄ ሰው ግን የጁን ያገኘ ይመስለኛል ምክንያቱም ዘሙዬ እያያለ ሲያላግ ጥባቸው ነበር። በርሃብ ሲቆነ ጠጥ ሰበብ የሆኑት እነዛው ሚስኪን የአረብ ሀገር እህቶች ናቸው። እህቶች ተጠን ቀቁ ማፊያ ቡድነው ጩከቱ ከአን ገት በላይነው ሰለፊያ የምትል ታርጋ ለጥፎ!! ውስጡ ከሂዝብይ ነትም በላይ ዘራፊም ጭምርነው የክህደት ካባየለበሰነው። ✅👉https://t.me/abujemila25

~የሙስሊሞች ምሳሌያቸዉ እርስ በርስ ያላቸዉ መዋደድ፦መተዛዘን አንዱ ለሌላዉ መራራት ሁኔታቸዉ ልክ እንደ አካል ነዉ።ከፊሉ ሠዉነት ሲታመም ከፊሉ እንቅልፍ ሠላም ያጣል። ከፊሉ ትኩሳት ይሠማዋል። አንዱ ለሌላዉ መቆርቆር ማሠብ እራሱን የቻለ ኢማን ነዉ። ~የእዉነት ከልብ አንዳችን ለአንዳችን መልካም ነገር የሚያሳስበን  ወይም  የሌላዉ መከፋት የሚያስከፋን ከሆነ እዉነተኛ የሆነ ኢስላማዊ ወንድማማችነት እህትማማችነት  አለ።       t.me/https_Asselfya

🔴በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ፕሮግራማችን ሊጀመር ነው! ⚠️ማስታዎሻ፦የፕሮግራሙ ዓላማ ግልፅ ይሆንላችሁ ዘንድ፤ ከመጀመሪያ ጀምሮ መከታተል ይገባል! https://t.me/AbuSufiyan_Albenan?livestream=5fa0e0798dd3516730

🙁🙁🙁🙁🙁🙁☹️🥳 ⭐️የአል-ኢማም አህመድ ኦንላይን መድረሳ የምዝገባ ማስታወቂያ ☹️🙁🙁🙁☹️🙁🙁🙁 አል-ኢማም አህመድ ኦንላይን መድረሳ በአዲስና በተሻሻለ አቀራረብ አዲስ የሶስት ወር
🙁🙁🙁🙁🙁🙁☹️🥳 ⭐️የአል-ኢማም አህመድ ኦንላይን መድረሳ  የምዝገባ ማስታወቂያ ☹️🙁🙁🙁☹️🙁🙁🙁 አል-ኢማም አህመድ ኦንላይን መድረሳ በአዲስና በተሻሻለ አቀራረብ አዲስ የሶስት ወር ኮርስ ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቋል። ⭐️የምንሰጣቸው ትምህርቶች✅ ✅ዓቂዳህ (የእስልምና እምነት መሰረቶች) ✅ሲራ (የነብዩ ሙሐመድ ﷺ የህይወት ታሪክ) ✅የአረብኛ ቋንቋ 🔺ምዝገባው እስከ ታህሳስ 10, 2018 ዓ.ል ድረስ ብቻ የሚቆይ ሲሆን, ወዲያውኑ መደበኛ ትምህርት ይጀምራል።✔️ ❤️ለመመዝገብ ቀጣዩን የቴሌግራምና የዋሳፕ ሊንክ ይጫኑ የቴሌግራም ሊንክ👇👇 ❤️https://t.me/+EwtXi8ZPpONiNzc0 ✅📞የዋሳፕ ሊንክ👇👇 📗https://chat.whatsapp.com/DUwIsMEnxQpJd9vU8OqdEx

~ለነፍሴ እረፍትን ሰላምን ፈለኩላት እናም የማይመለከተኝን ነገር እደመተው የተሻለ ነገር አላገኘሁም ።   ራስህ ላይ አተኩር....! ~ ✍t.s

🔖መስለማ ቢን አብዱል መሊክ አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል። ~ መልካም ሚስት ለአንድ ሙእሚን ከሁለት አይኑ፣ ከሁለት እጁና ከሁለት እግሩ በላይ አስፈላጊና በላጭ ነች። 📚【 أحسن المحاسن
🔖መስለማ ቢን አብዱል መሊክ አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል። ~ መልካም ሚስት ለአንድ ሙእሚን ከሁለት አይኑ፣ ከሁለት እጁና ከሁለት እግሩ በላይ አስፈላጊና በላጭ ነች። 📚【 أحسن المحاسن للثعالبـﮯ : ٣٦٨

▶️ተጀመረ!✅ ✅ የሙሓደራ ፕሮግራም       ተ🎁              ጀ▶️                   መ ▶️                           ረ▶️ ✅ t.me/tdarna_islam?livestream        t.me/tdarna_islam?livestream