💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Ir al canal en Telegram
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Mostrar más9 033
Suscriptores
-424 horas
-337 días
-13630 días
Archivo de publicaciones
Repost from ስለ ስልካችን
🌸 ችግሩ ሪዝቅን መፈለግ ላይ አይደለም፤ ይልቁንም ፍለጋው ወደ ፍርሃት ተቀይሮ ነፍስን ማድከሙ ላይ ነው።
👤 ሰው በምድር ላይ እንዲጓዝ ታዟል፤ ነገር ግን ልቡ ከምድርና ከሰማያት ጌታ ጋር የተንጠለጠለ መሆን አለበት።
t.me/SleSlkachin
🌸﴿وَلكِن تَعمَى القُلوبُ الَّتي فِي الصُّدورِ﴾
العبد هو الذي يخاف موت قلبه لا موت بدنه
إذ أكثر الخلق يخافون موت أبدانهم
ولا يبالون بموت قلوبهم.
👈 ابن القيم
"👉ባርያ ብሎ ማለት እሱ ያ የልቡ መሞት የሚፈራ እንጂ የአካሉ መሞት አይደለም።
~ሆኖም ግን አብዘሀኛው ሰው ለአካሉ ሞት እንጂ ለልቡ መሞት ምንም ቁብ አይሰጥም።"
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው።
👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው።
💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
✏️ [ ምርጧን ሴት አላህ ይምረጥልህ ]
አንድ ጠቢብ ሰው ስለ ምርጥ ሴቶች ተጠይቆ እንዲህ አለ፡- "ምርጥ ሴት ማለት፡-
1- ጌታዋን የምታስደስት።
2- ለባሏ ፍቅር ያላት።
3- ከቤቷ የማትወጣ።
4- አምስት አውቃት ሶላት የምትሰግድ።
5- ሚስጥሯን የምትጠብቅ።
6- ጫማዋ የማይታይ።
7- ድምጿ የማይሰማ።
8- ባህሪዋ የማይታወቅ።
9- በሕዝቦቿ መካከል የተከበረች።
10- በራሷ ትሑት የሆነች።
11- ለልጇ አፍቃሪ እና አሳቢና ተንከባካቢ የሆነች።
12- ቤቷ ቅርብ ጀነት የሆነ።
13- ከባሏ መልካም ነገር ካየች ታመሰግናለች።
14- ክፉ ነገር ከእሱ ካየች ትታገሳለች።
15- ወደ ክፍሏ ሲገባ ትደሰታለች በፈገግታ ትዋጣለች።
16- ከቤቷ ሲወጣ ታዝናለች ትናፍቃለች።
17- በእሷ ላይ ከተቆጣች ትጸናለች ትታገሳለች።
18- ወደ እሱ ስትቀርብ ታስደስተዋለች።
19- እሱ በማይኖርበት ጊዜ ክብሩን ትጠብቃለች።
20- ጉድለቶቹን ካየች ትሸፍናለች።
21- ይቅርታ ከጠየቃት ይቅርታ ታደርጋለች።
=
የቴሌግራም ቻናል
t.me/AbulbukhariSeid
🥀 ﴿ يدبّر الأمر ﴾
👉ከዚህ ባህሪው ቡኋላ
~መዋለል
~መጨነቅ
~መፍራት የለም! 🌻👌
ይችን አያ እናስተንትናት!
👈(أيهم أحسن عملا)
" የትኞቹ ስራን አሳማሪ እንደሆኑ ለመፈተን ነው ።
የትኞቹ ብዙ ስራ እንደሚሰሩ አላለም።ምክንያቱም ሚፈለገው ስራን ማብዛት ሳይሆን ማሳመር(ለአላህ ብሎ መስራት) ነውና !🔖ከደጋግ ቀደምቶች መንደር ለእህቶች አርኣያ የምትሆን ድንቅ ሴት!!
———
ኢብኑል ጀውዚ (ረሒመሁላህ) እንዲህ አሉ:-
«ሰያር (ረሒመሁላህ) ከሪያህ ረሒመሁላህ እንዲህ ማለቱን ዘገበልኝ:-
ሪያህ:- “አንዲትን እንስት ተጠቆምኩኝ እና አገባሁዋት። ሁሌም የዒሻ ሶላት ሰግዳ እንደጨረሰች ሽቶ ላይዋ ላይ ትነሰንስና፤ ራሷን በእጣን አጥና (ተቆነጃጅታ) ምርጥ ልብሷን ትለብስና ወደኔ በመቅረብ ...
“አንዳች ፍላጎት አለህን?” ብላ ትጠይቀኛለች። መልሴ “አዎን” ከሆነ አብራኝ ትቆያለች “አይ” ከሆነም ምርጡን ልብሷን ትቀይርና እስከ ንጋት ድረስ በሶላት ታሳልፋለች።»
ሪያህ እንዲህ ሲል ይጨምራል:-
"በአላህ ይሁንብኝ! በጣም ነውያስደሰተችኝ!"
[ሲፈቱ ሰፍወህ ገፅ:116]
~
አንቺስ እህቴ በዒባዳሽ ምን ያህል ብርቱ ነሽ?፣ ወይስ ካገባሽ በኋላ ደርስ ትተሽ፣ ከዒባዳሽ ተዘናግተሽ፣ ለዱኒያ መንገብገብሽና ጭንቀትሽ ጨምሯል??፣ ባለ ቤትሽን ከሀራም ለመጠበቅና በአንቺ ድክመት ሰበብ ሌላ እንዳይመኝ ለባለቤትሽ ምን ያህል ትቆነጃጂያለሽ? ሀቁን ጠብቀሽ ምን ያህል ታዝናኚዋለሽ? ወይስ ካገባሽው በኋላ እራስሽን ጥለሽ የቤት እቃሽን ውበት ነው ምትጠብቂው?
አስቢበት!!። ከደጋግ ቀደምቶች መንድር ይህቺን ድንቅ ሴት ከትዳር ጋር ዒባዳን በማጣጣም በዒባዳ ላይ በመበርታትና ድንቅ በሆነው የባል አያያዟ አርኣያ አድርጊያት!!። መልካም ሴት ማለት:- መልእክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሷሊህ ብለው የጠሯትና ሷሊህ የሆኑ ወንዶች የሚደሰቱባት፣በጥሩ የሚዘክሯት ሴት ናት!!
منقول✔ ባጣሽው ነገር አትዘኚ የፈለግሽውን አግኝተሽ ቢሆን ኖሮ የበለጠ ልታዝኚ ትችይ ይሆናል! የአሏህ ውሳኔዎችን ውደጂ ጥበብ የተሞሉ ረቂቅ ሚስጥሮች ናቸው።
#እህቴ_ሆይ
ሂጃብ ሁለት አይነት ነው
☀️አንደኛው ትኩረትን ከመሳብ የሚሸፍን ሂጃብ ሲሆን....
☀️ሌላው ደግሞ ትኩረትን የሚስብ ሂጃብ ነው።
ከነዚህ ሂጃብ ውስጥ የትኛው ነው ሂጃብሽ???
Repost from شـبـاب السـلــفـــيـــيــن
👉ባለቻናሎች ለምን ጨከናችሁ⁉️
«ሁሌም የሱና ቻናሎች ለሙስሊሞች ድምፅ አይሆኑም ለምን ...እንዴ የሙስሊሙ ግፍ አይታያችሁም ነው⁉️
👉ለምንድነው ሰው በክፉ እንድመለከታችሁ የምታደርጉት⁉️
👉ሙስሊሙ ከዚህ በላይ ምን አይነት በደል ይድረስበት ⁉️
«ቢያንስ ሌላው ቢቀር «ኢና ሊላሒ ወኢና ኢለይሒ ራጂዑን»አይባልም ወይ‼️«የሙስሊሞችን ግፍ የሚያስተጋባው ኢብኑ_ሙነወር ብቻ ነው ብሎ ያቀራችሁ ማነው⁉️ ቆይ እንደት ነው የሚያስችላችሁ⁉️ በምን አቅም ነው ወገናችሁ እያለሸ ፀጥ ለማለት የጨከናችሁት⁉️ 🛑እስኪ ከልምዳችሁ ለኔም ንገሩኝ እኔም ዝም ልበል...አላስችል እያለኝ እንጂኮ እኔም እንደናንተ ዝም ብል ...እህህህ ግን አያስችለኝም በቃ‼️ ⭕️ስለ ሙስሊሙ ብትጮሁ ቻናላችሁ ይቀንሳል⁉️ ⭕️ስለሚሞተው ወገናችሁ ድምፅ ብቶኑ #ከሱና ትወጣላችሁ⁉️ 🛑ስለ ሙስሊሞች በደል ብትናገሩ #ከሰለፍያ የሚያባርራችሁ ሰው አለ⁉️ ....በአሏህ ምን ሆናችሁ ነው⁉️ ....ለምንድነው ሳንፈልግ እንድንናገራችሁ የምታደርጉን⁉️ እንወዳችኋለን እናከብራችኋለን ግን ስንሞት ስንገደል ቢያንስ ሀዘናችሁን አሳውቁን በአሏህ⁉️ 👉የሱና ሰዎች አዛኝ እንጂ ጨካኝ አይደሉም 👉የሐቅ ሰውች የተግባር እንጂ የወሬ ሰዎች አይደሉም። 👉ሰለፍዮች ከማንም ላይ ሩህሩህ እንጂ የወገናቸው በደል የማይሰማቸው አይደሉም። 🛑«የሙስሊሙ በደል አይመለከታችሁም ነው⁉️ 🛑«የሙስሊሙ መገ*ደል አያሳዜናችሁም ንገሩን⁉️ ....ፀጥ ማለታችሁ መስለሀው ምንድነው⁉️ የአፄ ዩሀንስ የቦሩ ሜዳ ጭፍጨፋ የአፄ ሚኒሊክ የጨለንቆ ግፍ የሀረር ሙስሊሞች የጂምላ እልቂት በአንዴ የተከሰተ አይደለምኮ .....ለምን ታሪክ አታነቡም⁉️ ልክ እንደ አሁኑ በየትም ቦታ ሙስሊሙን እየመረጡ በዘግናኝ ሁኔታ በመ*ግደል ካስፈራሩ በኋላ በመጨረሻ ሀይላቸውን አሰልፈው ተነጋግረውና ተናበው ቦታና ቀን መርጠው...ግፋቸውን ይፈፅማሉ ....አሁንም ዝግጂት ላይ ናቸው። ⭕️ወላሒ ሀታ በዚህ በስደት እንኳን የተቃወማቸውን #ገዳይ_እስኳድ አላቸው በዚህ ልክ ነው #የተደራጁት ልንገራችሁ። ሙስሊም ባለ ቻናሎች ለምንድነው የሚስሊሙን በደል የማታሰራጩት ምንድነው ያስጨከናችሁ ነገር⁉️ ምን እየጠበቃችሁ ነው⁉️ ምንስ ነው አላማችሁ⁉️ 🛑#ሰለፍይ አያዝንም እንዴ 🛑ሰለፍይ ወጣት የሙስሊም በደል አያመውም እንዴ⁉️ በስም እጠራለሁ ወላሒ ምን ያክል እንደምወዳችሁ ታውቃላችሁ ወላሒ ለሱና ወንድሞቼ ነፍስን እንኳን አልሰስትላችሁም ግን በሙስሊሙ መበደል ላይ እጂግ ችልተኛ ናችሁ ለምን⁉️ 👉ሰለፍያ ሁሌ ስለትዳር መፃፍ ብቻ ነው እንዴ‼️ 👉የሰለፍዮች አላማ ስለ ሴቶች እየፃፉ ቻናላቸውን ማሳደግ ብቻ ነው እንዴ⁉️ ⭕️በዚህ ወቅት ለወገናችሁ ድምፅ ካልሆናችሁ ለመቼ ነው የምትደርሱልን⁉️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi
•የኔ ልባም ሴት🌸👈
» ልባም መሆን ማለት ዝምተኛ መሆን ማለት አይደለም፤ ልባምነት ማለት መቼ መናገርና መቼ ዝም ማለት እንዳለብሽ ማወቅ ነው። የኔ ልባም ሴት፣ አንቺ በዙሪያሽ ላሉት ሰዎች ብርሃን፣ ለቤተሰብሽ መከታ፣ ለራስሽ ደግሞ ኩራት ነሽ።
» ብዙ ፈተናዎች ሊገጥሙሽ ይችላሉ፣ አለም ተስፋ እንድትቆርጪ ሊገፋፋሽ ይችላል። ነገር ግን አንቺ ውስጥ ያለው ያ የማይበገር የልባምነት መንፈስ "ገና ነኝ!" ይልሻል። እራስሽን ውደጂ፣ እውቀትሽን አሳድጊ፣ እናም በምትሄጂበት መንገድ ሁሉ በልበ ሙሉነት ተራመጂ።
» አንቺ የጥበብ ምንጭ፣ የጽናት ተምሳሌት ነሽ።ዛሬ የምታደርጊው ጥቃቅን በጎ ነገር ነገ ትልቅ ታሪክ ሆኖ ይነበባል። በርቺ፣ የኔ ልባም ሴት!
=
t.me/https_Asselefya1
ይህ መልእክት
አሁንም ትኩረት ስጡት በብልግና ቪዲዮ ተታለው ብዙዎች አካውንታቸው እየተጠለፈ ነው። ከዛ በናንተ አካውንት የብልግና ምስል በመላክም ሰዎችን አዛ እያደረጉ ነው።አላህ ይጠብቀን🔖قال ابن عباس رضي الله عنهما:
~የቁርአን ሰዎች ቁርአን ላይ የሚገባውን ሀቅ ቢወጡለትና በአግባቡ ቢይዙት አላህ በወደዳቸው ነበር
~ነገር ግን በቁርአናቸው ዱንያን ፈለጉበትና አላህም ጠላቸው ሰዎች ዘንድም ያነሱ ሆኑ
📙 تفسير القرطبي [٢٠/١]
t.me/https_Asselfya
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
