es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 369 suscriptores, ocupando la posición 5 619 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 193 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 369 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -18, y en las últimas 24 horas de 1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 23.10%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 8.16% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 551 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 254 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 369
Suscriptores
+124 horas
+477 días
-1830 días
Archivo de publicaciones
"እነ ወንድም አካለወልድ ያደረጉት ተግባር ልብስ የማልበስ ተግባር እንጂ ሢመተ ጵጵስና አይደለም ፤ ምክንያቱም ሕገወጥ ፣ ሐዋርያዊ አንብሮተ ዕድ የተቋረጠበት እና ተቀባይነት የሌለው ነው ! "ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)

ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው የነበሩት ክቡር መልዐከ ሠላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ ፣ የየም እና የኮንታ አኅጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከሹፌራቸው ጋራ ተፈተዋል።

ክቡር መልአከ ሰላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ ፣ የየም እና የኮንታ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዛሬ ጥር 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጠዋት 12:30 ላይ ዲፖ ከሚገኘው የኮንዶሚንየም መኖርያ ቤታ
ክቡር መልአከ ሰላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ ፣ የየም እና የኮንታ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዛሬ ጥር 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጠዋት 12:30 ላይ ዲፖ ከሚገኘው የኮንዶሚንየም መኖርያ ቤታቸው በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ታፍነው ተወስደዋል። ወደየት እንደወሰዷቸው እስከ አሁን የታወቀ ነገር የለም። ©eotc mk

ቅዱስነታቸው በዛሬ ጥር 21 ቀን ዕለት የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ። ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ለሚመለከተው ሁሉ እሁድ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በሦስት ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት በተፈጸመው የሕግ ጥሰት 26 ኤጲስ ቆጶሳት በመሾማቸው፣ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ቋሚ ሲኖዶስ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ላሉት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሊቃነ ጳጳሳት አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፏል፡፡ ጥሪ የተደረገላቸው አባቶችም በቅጽበት ደርሰው ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አድርገው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት ከላይ በተጠቀሰው ኢሕጋዊ ድርጊት ላይ ውሳኔ ማሳለፋቸው በዚያው ዕለት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም በተላለፈው የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ በሰፊው ተገልጿል፡፡ መግለጫውን ያዳመጡ በውስጥም በውጭም ያሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ሁሉ ብርቱ ድጋፋቸውን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም የዓለም አብያተ ክርስቲያናት እና መንፈሳውያን ተቋማት ድጋፋቸው ከመግለጻቸው በላይ የታሪካዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ኅብረት ተጠብቆ እንዲኖርም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡ እኛም ድጋፋቸውንና መልካም ምኞታቸውን ስለገለጹልን የላቀ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፤ ምስጋናችን በያሉበት ይድረሳቸው፡፡ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂዎች የክርስትናና የእስልምና መሪዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ድንገተኛ ክስተት ተደናግጠውና ተጨንቀው መጥተው የችግራችን ተካፋይ መሆናቸውን በመንፈሳዊ ስሜት ገልጸውልናልና ምስጋናችን ይድረሳቸው፤ እግዚአብሔርም ያክብራቸው እንላለን። አሁንም በድጋሚ ለመንግሥትና ለሰፊው ሕዝባችን የምናስተላልፈው የአደራ መልእክት አለን፤ እሱም፡- 1. የታሪካዊቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት (ቀኖና) እንዲከበርልን፤ 2. ጸጥታ እንዳይደፈርስና የንጹሐን ክርስቲያን ደም እንዳይፈስ ከወዲሁ ብርቱ ጥንቃቄ የተመላበት ጥበቃ እንዲደረግ በእግዚአብሔር ስም በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን። አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥር 21 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

በወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ አል ዐይን አማርኛ ካነጋገራቸው የሕግ ባለሞያዎች የተወሰዱ አንዳንድ ነጥቦች - የመንግስት የመጀመሪያው ኃላፊነት በሃይማኖት እና በመንግሥት መካከል የተሰመረውን ቀይ መስመር ማክበር ነው። መንግስት በየትኛውም ሃይማኖት ጣልቃ አይገባም፣ ሃይማኖትም በመንግስት ሥራዎች ላይ ጣልቃ አይገባም በሚል በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት ላይ በጉልህ ተጽፏል። መንግሥት ይሄንን ጉልህ ሕግ ካላከበረ ዜጎችን የሕግ የበላይነትን አክብሩ የማለት መብቱን ሊያጣ ይችላል። - መንግስት ሕጋዊ ሰውነት ላላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ንብረቶች፣ አገልግሎት እና ሌሎች በሕግ የተመዘገቡ ሃብቶችን እና ተቋማትን ከጉዳት እንዲጠበቁ የማድረግ ኃላፊነት አለበት። ማንኛውም ግለሰብ የፈለገውን ሀይማኖት የመከተል መብት አለው ነገር ግን በአንድ ሃያማኖት መካከል መከፋፈል ሲፈጠር ተቋሙ በራሱ ችግሩን እንዲፈታ መተው አንዱ መፍትሔ ቢሆንም፤ አለመስማማቱ ከቀጠለ ግን ሕጋዊ ሰውነት ላለው ተቋም ሕጋዊ ከለላ መስጠት፣ ንብረቶችን ከዘራፊዎች መጠበቅ የመንግስት ግዴታ ነው። - የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች የአሁኑ ሰላም ሚኒስቴር የሚያስፈጽመው በ2012 ዓ.ም መመሪያ ቁጥር 19/2012ትን ማክበር እንዳለበት አሳስበዋል። ትይዩ ጵጵስና የሰጡ ግለሰቦች በቀጣይ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎቶችን እንስጥ፣ የባንክ አካውንቶችን እናንቀሳቅስ፣ ንብረቶችን እንጠቀም ሊሉ እንደሚችሉ ይጠበቃል። ይህ ግን ከሕግ አንጻር ትክክል አይሆንም፣ የመንግስትም ዋና ኃላፊነት የሚሆነው ሕጋዊ ሰውነት ላለው ተቋም ሕጋዊ ከለላ እና ጥበቃ ማድረግ ይሆናል። በመመሪያ ቁጥር 19/2012 መሠረትም የሃይማኖት አባቶች ወንጀል እንዲፈጸም ማነሳሳት፣ ሕጋዊ ሰውነት ያለው እና የሌላን የሃይማኖት ተቋም አርማ፣ ንብረት፣ አልባሳት እና ሌሎች ንብረቶችን እንዳይጠቀሙ ይደነግጋል። በዚህ መመሪያ መሰረትም እነዚህ የትይዩ "ጵጵስና ሹመት" የሰጡ የቀድሞ የቤተ ክርስቲያኗ አገልጋዮች አዲስ የሀይማኖት ተቋም የመመሥረት እንጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ንብረቶች እና ሀብቶችን የመጠቀም ምንም ዓይነት ሕጋዊ መብት እንደሌላቸው፣ እንጠቀም ካሉም ግጭት ሊከሰት ስለሚችል እና ግጭቱ እንዳይከሰት መንግሥት የቤተ ክርስቲያኗን ውሳኔዎች የማክበር እና የማስከበር ግዴታ አለበት። - በቅርቡ በተወሰኑ የቀድሞ የቤተ ክርስቲያኗ አገልጋዮች አማካኝነት የተፈጸመው ድርጊት የሃይማኖቱን ተከታዮች ሊከፋፍል እና ግጭት እንዲከሰቱ ሊያደርጉ ይችላሉ። ከእንግዲህ ትልቁን ሥራ የሚወስደው በብቸኝነት ሕግን የማስከበር ሥልጣን ያለው መንግስት ነው። መረጃው የተሚማ ነው።

ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጅማ መቆየት አይችሉም ተብለው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርጓል። © ማኅበረ ቅዱሳን

ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጂማ ከተማ በፀጥታ አካላት ተወስደዋል። በነገው ዕለት አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በጂማ ከተማ ለማስመረቅ የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመምሪያ ኃላፊዎች ጋራ ዛሬ ጠዋት ለመሄድ አዲስ አበባ አየር መንገድ ተገኝተው ነበር። ከእነዚህም መካከል ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ፣ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሲገኙ ሌሎች እንግዶች ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ንቡረ ዕድ ኤልያስ፣ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን፣ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ፣ ሊቀ ትጉሃን እስክንድር ገ/ክርስቶስ ይገኙበታል። አየር መንገድ ሲደርሱም የሀገረ ስብከቱ አባት ይበቃሉ በማለት ቀሲስ ታጋይ አብረው እንዲሄዱ በመፍቀድ ሌሎች አባቶችና እንግዶችን ከጉዞ መልሰዋቸዋል። ጂማ ከተማ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በፀጥታ አካላት የተያዙ ሲሆን የያዟቸው አካላትም ከክልል የደረሰን አቅጣጫ ነው ማለታቸው ተሰምቷል። በተመሳሳይ ዜና ሕገ ወጡን ሹመት ትተው ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱት መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል። ©ማኅበረ ቅዱሳን

እንኳን አደረሳቹሁ #ጥር21_አስተርእዮ_ማርያም_ ( #በዓለ_ዕረፍታ_ለማርያም_(ለሶልያና ) #እመቤታችን_በ64_ዓመቷ_ጥር_21_በ49ዓም_ያረፈችበት_ዕለት_መታሰቢያ_ክብረ_በዓል_ነው፡፡ #ተናገራ_ዕዝራ_ተናገራ_ዳዊት_ዘመራ፤ #ዕዝራ_በመሰንቆ_ዳዊት_በበገና_እያጫወቷት፤ #ሳታውቀው_አለፈች_ያንን_መራራ_ሞት፡፡ ፠ ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ከገባላት በኋላ፤ ቅድስት ነፍሷን ከክብርት ሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት፥ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት ደመና ጠቅሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ በአጎበር አድርገው እናትና አባቷ ወደተቀበሩበት ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲወስዷት አይሁድ አይተው፤ ልጇ ተነሳ፥ አረገ እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳች፥ አረገች እያለ ሉያውኩን አይደለምን? ንዑ ናዓውያ ሥጋሃ ለማርያም /ኑ ሥጋዋን እናቃጥልባቸው/ ብለው ተነሱ፤ ለዚሁም ከመካከላቸውም ታውፊኒያ የተባለውን የጎበዝ አለቃ መረጡ፤ እርሱም የአልጋዋን ሸንኮር ሊያቃጥል ሲይዝ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘምበል አድርጋ ቅዱስ ጴጥሮስን እንደነበረው አድርግለት ብላ አዘዘችው፤ እርሱም እጁን አድኖለታል፡፡ ከዚህ በኋላ ጌታችን ከመካከላቸው ነጥቆ ከገነት ከዕፀ ሕይወት ስር አኑሯታል፡፡ ….. ሐዋርያት የቀበሯት ግን ከ6 ወር በኋላ በነሐሴ 14 ነው ----›እርሱን እዚህ ያንብቡ ----›https://t.me/medihanaelem/6840፤ ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር እንዲሉ፡፡››ረፍታ ለሶልያና(ለማርያም) ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ፡፡ #ሶልያና_የእመቤታችን_የማርያም_ሌላ_ስሟ_ነው፡፡ *የእመቤታችንን ዕረፍት ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ‹‹ሞትሰ ለመዊት ይደሉ፥ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኵሉ፡፡ /ሞት ለሚሞት ሰው ሁለ የተገባ ነው፥ የማርያም ሞት ግን ሁለን ያስደንቃል፡፡›› በማለት አደንቆ ጽፏል፡፡ *እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ የላይ ቤት (የግምጃ ቤት ማርያም) አብነትና የታች ቤት(የበዓታ) አብነትን ሁለቱንም አዘጋጅተንላችኋል፡፡ መልካም ክብረ በዓል፡፡ **ክብረ በዓሉ በሃገራችንና በዓለማችን ክፍሎች ባሉ የእመቤታችን አብያተ ክርስቲያናት የሚከብሩ ቢሆንም ግን፤ በልዩ ሁኔታ እንደ ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ግን እንደ ጥምቀት በዓል፤ ከዋይዜማው ጀምሮ ወደ ጥምቀተ ተወርዶ በማደር ክብረ በዓሉ በልዩ ሁኔታ መከበሩን ልብ ይሏል:: /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ቅዱሳን #Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts #Our_mother_Virgin_mary #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw...

“ወይናችን አብቦአልና የወይናችንን ቦታ የሚያጠፉትን ቀበሮች፥ ጥቃቅኑን ቀበሮች አጥምዳችሁ ያዙልን።” — መኃልየ. 2፥15 ሰበር ዜና ቅዱስ ሲኖዶስ በቀድሞ ስማቸው "አባ"ሳዊሮስ ፣ "አባ" ኤዎስጣቴዎስና ፣ "አባ" ዜና ማርቆስን ከዲቁና - ጵጵስና ያላቸውን ሥልጣነ ክህነት ሙሉ በሙሉ በመሻር በቀድሞ የዓለም ስማቸው "አቶ" ተብለው እንዲጠሩና ከቅዱስ ሲኖዶስ አባልነት እንዲለዩ ወሰነ !