Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 369 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 619,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 193 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 369 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -18,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 23.10%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.16% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 551 次浏览,首日通常累积 1 254 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 22。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 369
订阅者
+124 小时
+477 天
-1830 天
帖子存档
"እነ ወንድም አካለወልድ ያደረጉት ተግባር ልብስ የማልበስ ተግባር እንጂ ሢመተ ጵጵስና አይደለም ፤ ምክንያቱም ሕገወጥ ፣ ሐዋርያዊ አንብሮተ ዕድ የተቋረጠበት እና ተቀባይነት የሌለው ነው ! "ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)
ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው የነበሩት ክቡር መልዐከ ሠላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ ፣ የየም እና የኮንታ አኅጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከሹፌራቸው ጋራ ተፈተዋል።
ክቡር መልአከ ሰላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ ፣ የየም እና የኮንታ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዛሬ ጥር 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጠዋት 12:30 ላይ ዲፖ ከሚገኘው የኮንዶሚንየም መኖርያ ቤታቸው በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ታፍነው ተወስደዋል።
ወደየት እንደወሰዷቸው እስከ አሁን የታወቀ ነገር የለም።
©eotc mk
ቅዱስነታቸው በዛሬ ጥር 21 ቀን ዕለት የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ።
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ለሚመለከተው ሁሉ
እሁድ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በሦስት ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት በተፈጸመው የሕግ ጥሰት 26 ኤጲስ ቆጶሳት በመሾማቸው፣ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ቋሚ ሲኖዶስ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ላሉት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሊቃነ ጳጳሳት አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
ጥሪ የተደረገላቸው አባቶችም በቅጽበት ደርሰው ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አድርገው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት ከላይ በተጠቀሰው ኢሕጋዊ ድርጊት ላይ ውሳኔ ማሳለፋቸው በዚያው ዕለት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም በተላለፈው የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ በሰፊው ተገልጿል፡፡
መግለጫውን ያዳመጡ በውስጥም በውጭም ያሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ሁሉ ብርቱ ድጋፋቸውን ገልጸዋል፡፡
እንዲሁም የዓለም አብያተ ክርስቲያናት እና መንፈሳውያን ተቋማት ድጋፋቸው ከመግለጻቸው በላይ የታሪካዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ኅብረት ተጠብቆ እንዲኖርም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
እኛም ድጋፋቸውንና መልካም ምኞታቸውን ስለገለጹልን የላቀ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፤ ምስጋናችን በያሉበት ይድረሳቸው፡፡
የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂዎች የክርስትናና የእስልምና መሪዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ድንገተኛ ክስተት ተደናግጠውና ተጨንቀው መጥተው የችግራችን ተካፋይ መሆናቸውን በመንፈሳዊ ስሜት ገልጸውልናልና ምስጋናችን ይድረሳቸው፤ እግዚአብሔርም ያክብራቸው እንላለን።
አሁንም በድጋሚ ለመንግሥትና ለሰፊው ሕዝባችን የምናስተላልፈው የአደራ መልእክት አለን፤ እሱም፡-
1. የታሪካዊቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት (ቀኖና) እንዲከበርልን፤
2. ጸጥታ እንዳይደፈርስና የንጹሐን ክርስቲያን ደም እንዳይፈስ ከወዲሁ ብርቱ ጥንቃቄ የተመላበት ጥበቃ እንዲደረግ በእግዚአብሔር ስም በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥር 21 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
በወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ አል ዐይን አማርኛ ካነጋገራቸው የሕግ ባለሞያዎች የተወሰዱ አንዳንድ ነጥቦች
- የመንግስት የመጀመሪያው ኃላፊነት በሃይማኖት እና በመንግሥት መካከል የተሰመረውን ቀይ መስመር ማክበር ነው።
መንግስት በየትኛውም ሃይማኖት ጣልቃ አይገባም፣ ሃይማኖትም በመንግስት ሥራዎች ላይ ጣልቃ አይገባም በሚል በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት ላይ በጉልህ ተጽፏል። መንግሥት ይሄንን ጉልህ ሕግ ካላከበረ ዜጎችን የሕግ የበላይነትን አክብሩ የማለት መብቱን ሊያጣ ይችላል።
- መንግስት ሕጋዊ ሰውነት ላላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ንብረቶች፣ አገልግሎት እና ሌሎች በሕግ የተመዘገቡ ሃብቶችን እና ተቋማትን ከጉዳት እንዲጠበቁ የማድረግ ኃላፊነት አለበት።
ማንኛውም ግለሰብ የፈለገውን ሀይማኖት የመከተል መብት አለው ነገር ግን በአንድ ሃያማኖት መካከል መከፋፈል ሲፈጠር ተቋሙ በራሱ ችግሩን እንዲፈታ መተው አንዱ መፍትሔ ቢሆንም፤ አለመስማማቱ ከቀጠለ ግን ሕጋዊ ሰውነት ላለው ተቋም ሕጋዊ ከለላ መስጠት፣ ንብረቶችን ከዘራፊዎች መጠበቅ የመንግስት ግዴታ ነው።
- የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች የአሁኑ ሰላም ሚኒስቴር የሚያስፈጽመው በ2012 ዓ.ም መመሪያ ቁጥር 19/2012ትን ማክበር እንዳለበት አሳስበዋል።
ትይዩ ጵጵስና የሰጡ ግለሰቦች በቀጣይ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎቶችን እንስጥ፣ የባንክ አካውንቶችን እናንቀሳቅስ፣ ንብረቶችን እንጠቀም ሊሉ እንደሚችሉ ይጠበቃል። ይህ ግን ከሕግ አንጻር ትክክል አይሆንም፣ የመንግስትም ዋና ኃላፊነት የሚሆነው ሕጋዊ ሰውነት ላለው ተቋም ሕጋዊ ከለላ እና ጥበቃ ማድረግ ይሆናል።
በመመሪያ ቁጥር 19/2012 መሠረትም የሃይማኖት አባቶች ወንጀል እንዲፈጸም ማነሳሳት፣ ሕጋዊ ሰውነት ያለው እና የሌላን የሃይማኖት ተቋም አርማ፣ ንብረት፣ አልባሳት እና ሌሎች ንብረቶችን እንዳይጠቀሙ ይደነግጋል።
በዚህ መመሪያ መሰረትም እነዚህ የትይዩ "ጵጵስና ሹመት" የሰጡ የቀድሞ የቤተ ክርስቲያኗ አገልጋዮች አዲስ የሀይማኖት ተቋም የመመሥረት እንጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ንብረቶች እና ሀብቶችን የመጠቀም ምንም ዓይነት ሕጋዊ መብት እንደሌላቸው፣ እንጠቀም ካሉም ግጭት ሊከሰት ስለሚችል እና ግጭቱ እንዳይከሰት መንግሥት የቤተ ክርስቲያኗን ውሳኔዎች የማክበር እና የማስከበር ግዴታ አለበት።
- በቅርቡ በተወሰኑ የቀድሞ የቤተ ክርስቲያኗ አገልጋዮች አማካኝነት የተፈጸመው ድርጊት የሃይማኖቱን ተከታዮች ሊከፋፍል እና ግጭት እንዲከሰቱ ሊያደርጉ ይችላሉ። ከእንግዲህ ትልቁን ሥራ የሚወስደው በብቸኝነት ሕግን የማስከበር ሥልጣን ያለው መንግስት ነው። መረጃው የተሚማ ነው።
#Orthodox_Quotes
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጅማ መቆየት አይችሉም ተብለው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርጓል።
© ማኅበረ ቅዱሳን
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጂማ ከተማ በፀጥታ አካላት ተወስደዋል።
በነገው ዕለት አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በጂማ ከተማ ለማስመረቅ የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመምሪያ ኃላፊዎች ጋራ ዛሬ ጠዋት ለመሄድ አዲስ አበባ አየር መንገድ ተገኝተው ነበር።
ከእነዚህም መካከል ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ፣ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሲገኙ ሌሎች እንግዶች ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ንቡረ ዕድ ኤልያስ፣ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን፣ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ፣ ሊቀ ትጉሃን እስክንድር ገ/ክርስቶስ ይገኙበታል።
አየር መንገድ ሲደርሱም የሀገረ ስብከቱ አባት ይበቃሉ በማለት ቀሲስ ታጋይ አብረው እንዲሄዱ በመፍቀድ ሌሎች አባቶችና እንግዶችን ከጉዞ መልሰዋቸዋል።
ጂማ ከተማ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በፀጥታ አካላት የተያዙ ሲሆን የያዟቸው አካላትም ከክልል የደረሰን አቅጣጫ ነው ማለታቸው ተሰምቷል።
በተመሳሳይ ዜና ሕገ ወጡን ሹመት ትተው ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱት መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል።
©ማኅበረ ቅዱሳን
እንኳን አደረሳቹሁ
#ጥር21_አስተርእዮ_ማርያም_ ( #በዓለ_ዕረፍታ_ለማርያም_(ለሶልያና )
#እመቤታችን_በ64_ዓመቷ_ጥር_21_በ49ዓም_ያረፈችበት_ዕለት_መታሰቢያ_ክብረ_በዓል_ነው፡፡
#ተናገራ_ዕዝራ_ተናገራ_ዳዊት_ዘመራ፤
#ዕዝራ_በመሰንቆ_ዳዊት_በበገና_እያጫወቷት፤
#ሳታውቀው_አለፈች_ያንን_መራራ_ሞት፡፡
፠ ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ከገባላት በኋላ፤ ቅድስት ነፍሷን ከክብርት ሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት፥ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት ደመና ጠቅሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ በአጎበር አድርገው እናትና አባቷ ወደተቀበሩበት ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲወስዷት አይሁድ አይተው፤ ልጇ ተነሳ፥ አረገ እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳች፥ አረገች እያለ ሉያውኩን አይደለምን? ንዑ ናዓውያ ሥጋሃ ለማርያም /ኑ ሥጋዋን እናቃጥልባቸው/ ብለው ተነሱ፤ ለዚሁም ከመካከላቸውም ታውፊኒያ የተባለውን የጎበዝ አለቃ መረጡ፤ እርሱም የአልጋዋን ሸንኮር ሊያቃጥል ሲይዝ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘምበል አድርጋ ቅዱስ ጴጥሮስን እንደነበረው አድርግለት ብላ አዘዘችው፤ እርሱም እጁን አድኖለታል፡፡ ከዚህ በኋላ ጌታችን ከመካከላቸው ነጥቆ ከገነት ከዕፀ ሕይወት ስር አኑሯታል፡፡ ….. ሐዋርያት የቀበሯት ግን ከ6 ወር በኋላ በነሐሴ 14 ነው ----›እርሱን እዚህ ያንብቡ ----›https://t.me/medihanaelem/6840፤ ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር እንዲሉ፡፡››ረፍታ ለሶልያና(ለማርያም)
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ፡፡
#ሶልያና_የእመቤታችን_የማርያም_ሌላ_ስሟ_ነው፡፡
*የእመቤታችንን ዕረፍት ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ‹‹ሞትሰ ለመዊት ይደሉ፥ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኵሉ፡፡ /ሞት ለሚሞት ሰው ሁለ የተገባ ነው፥ የማርያም ሞት ግን ሁለን ያስደንቃል፡፡›› በማለት አደንቆ ጽፏል፡፡
*እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ የላይ ቤት (የግምጃ ቤት ማርያም) አብነትና የታች ቤት(የበዓታ) አብነትን ሁለቱንም አዘጋጅተንላችኋል፡፡ መልካም ክብረ በዓል፡፡
**ክብረ በዓሉ በሃገራችንና በዓለማችን ክፍሎች ባሉ የእመቤታችን አብያተ ክርስቲያናት የሚከብሩ ቢሆንም ግን፤ በልዩ ሁኔታ እንደ ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ግን እንደ ጥምቀት በዓል፤ ከዋይዜማው ጀምሮ ወደ ጥምቀተ ተወርዶ በማደር ክብረ በዓሉ በልዩ ሁኔታ መከበሩን ልብ ይሏል::
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ቅዱሳን #Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts
#Our_mother_Virgin_mary #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም
https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw...
#Orthodox_Quotes
“ወይናችን አብቦአልና የወይናችንን ቦታ የሚያጠፉትን ቀበሮች፥ ጥቃቅኑን ቀበሮች አጥምዳችሁ ያዙልን።”
— መኃልየ. 2፥15
ሰበር ዜና
ቅዱስ ሲኖዶስ በቀድሞ ስማቸው "አባ"ሳዊሮስ ፣ "አባ" ኤዎስጣቴዎስና ፣ "አባ" ዜና ማርቆስን ከዲቁና - ጵጵስና ያላቸውን ሥልጣነ ክህነት ሙሉ በሙሉ በመሻር በቀድሞ የዓለም ስማቸው "አቶ" ተብለው እንዲጠሩና ከቅዱስ ሲኖዶስ አባልነት እንዲለዩ ወሰነ !
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
