es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 391 suscriptores, ocupando la posición 5 586 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 200 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 391 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 22, y en las últimas 24 horas de -7, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 21.30%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.19% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 278 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 569 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 17.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 391
Suscriptores
-724 horas
+227 días
+2230 días
Archivo de publicaciones
ቅዳሜና እሑድ እስር ቤት እንዲያድሩ፤ ሆን ተብሎ ዓርብ የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው ቅዳሜና እሑድ አስተዳዳራው ሲያሳድናቸው ውሏል

የአስተዳደር አስራር ገፍቶዋቸው ከቤ/ ክ የራቁ ብዙ ሰዉች እናውቃለን :: ሃይማኖትም የቀየሩ በረካታ ምዕመናን እናውቃለን ::

ምዕመናን ፣ ሰ. ት.ቤት እና ፖሊሶች እንዲጋጩ ሆን ተብሎ ስራ እንደሚሰራ እናውቃለን :: 👉መጥሪያ ሳይደርሰው ማንም በፖሊስ መታደን አይችልም፡

ይህንን ማስፈንጠርያ ይጠቀሙ https://www.youtube.com/channel/UC9HCZKEuvymsChwLuR2lTsw ዛሬ ከ2:00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሚኖረንን ቆይታ ከታች ያለውን
ይህንን ማስፈንጠርያ ይጠቀሙ https://www.youtube.com/channel/UC9HCZKEuvymsChwLuR2lTsw ዛሬ ከ2:00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሚኖረንን ቆይታ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይከታተሉ። እንዳያመልጦት! #ስለ ታሰሩ አባላት፣ ለምን ታሰሩ? #ወቅታዊ ጉዳዮች

#ሐምሌ_7_ቀን_ቅድስት_ሥላሴ_ለአብርሃም_የተገለጹበት_ነው፡፡ ቅድስት ቀደሰ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣና ትርጕሙም ልዩ ማለት ሲኾን የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ልዩ ስለኾነ (የሥላሴን አንድነትና ሦስትነትን የሚመስል ስለሌለ፤ ቢመስልም ፍጹም ሦስትነት የሌለውና ምሳሌ ዘየኀጽጽ ስለሆነ)፤ ሥላሴን ቅድስት በሚል ቅጽል እንጠራለን፡፡ በዚህች #ሐምሌ_7_ቀን_ቅድስት_ሥላሴ_ለአብርሃም_የተገለጹበት_ነው፡፡ ይኸውም ስለ ፫ት ምክንያቶች ነው፤ #፩ኛ) ለመልካም ነገር /በአብርሃም አንግዳ መቀበል ፀር የኾነ ሰይጣንን ለማሳፈር/ (ሰይጣን በምቀኝነት አብርሃም እንግዳ እንዳይቀበል የውሸቱን ወደ አብርሃም ቤት በሚወስድ መንገድ ላይ ግንባሩን ገምሶ፥ ደሙን አፍስሶ ሰዎች አብርሃም እንዲህ መጥፎ ነውን እንዲሉና እንግዶች ወደ ቤቱ ሂደው እንዳይስተናገዱ አድርጓል፤ አብርሃምም ለ3 ቀናት እንግዳ እየጠበቀ ጾሙን ውሎ ነበር፡፡ ይህን የሰይጣን ክፋት የአብርሃምን እምነትና እንግዳ መቀበል የተመለከቱ ፥ ምግብን የማይመገቡ ሥላሴ በአብርሃም ቤት ገብተው እሳት ቅቤን እንደሚበላ ተስተናግደዋልና ነው፡፡ መስተናገዳቸውንም መምህረ ጋሥጫ የኾነው ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በመልክአ ሕማማት ድርሰቱ እንዲህ በግጥም አስቀምጦታል፤ ለንግሥክሙ ሰገደ አብርሃም በርእሱ፡፡ ቤተ ገብርክሙ እንዘ ይብል ገሐሡ፤ አጋዕዝትየ ዘትሤለሱ ግናይ ለክሙ፡፡ እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባው አምላካችንም ኾነ ቅዱሳን መላእክት ለአብርሃምና ለሌሎችም ቅዱሳን በተለያየ አምሳል መገለጻቸውን ልብ ይሏል፡፡ ለአብነትም፤ ፠ #ለአብርሃም በአምሳለ አረጋዊ፤ ፠ #ለሕዝቅኤል በዘባነ ኪሩብ፤ ፠ #ለዳንኤል በአረጋዊ፣ ፠ #ለዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ በተለያየ አምሳል፤ ፠ #ለደብረ መጕናው (ሞጊና) ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን #አቡነ አብሳዲ ደግሞ ራሱ መድኀኔዓለም ተገልጾላቸውና ተቀብለውት እንደ አብርሃም እግሩን ያጠቡት መኾኑን ልብ ይሏል፡፡ #፪ኛ) ዘርህን እንደ ምድር አሸዋ፥ እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛልሃለሁ ያሉት ሥላሴ ቃሉ የማይታበይ መኾኑን ለማሳየት (ሰማይና ምድር ያልፋል ፥ ቃሌ ግን አያልፍም ብሎ በኋለኛው ዘመን ጌታችንም እንዳረጋገጠው)፤ ለአብርሃምና ለሣራ ልጅ ሊሰጧቸው፡፡ አባታችን አብርሃም 99 ዓመት ፥ እናታችን ሣራ 89 ዓመት መልቷቸውና የመውለጃ ጊዜያቸው ባለፈበት ሰዐት እንደሚወልዱ ለማብሰር፡፡ #፫ኛ) ምግብ ተመግበን ካበቃን በኋላ አምላካችንን ማመሰገን እንደሚገባን ለማስተማር፡፡ (የታረደው ወይፈንም በተዓምራት ተነሥቶ ስብሐት ብሎ አመሰግኗል፤ ይህንንም መምህረ ጋሥጫ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በመልክአ ሕማማት ድርሰቱ በግጥም እንዲህ አስቀምጦታል፤ ድኅረ በላዕክሙ ላሕመ እንበይነ ፍቅረ ሰብእ ፍጹም ፤ ዘበኀይልሙ ሐይወ ላሕም፤ ሥላሴ ክቡራነ ስም፡፡ ግናይ ለክሙ፡፡ SHARE ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com

.......#የደብራችን አስተዳደር የከሰሰው አባላችን የዋስ መብት ተከለከለ:: .......#ዛሬ የታሰሩት አባላት አዳራቸው እስር ቤት ነው:: #ለቤተክርስሰቲያን እና ለእውነት የቆመው ወንድማችን በቀለ አሰፋ ዛሬ ጠዋት ጉለሌ ፍርድ ቤት ቀርቦ በ1000 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ቢወሰንለትም መርማሪው ይግባኝ ስለጠየቀ ጉዳዩ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት እንዲዘዋወር ሆኗል፡፡ #ለእውነት መቆም እና ለቤተክርስቲያን መቆርቆር ዋስ የሚያስከለክል ወንጀል ነውን? ቃለ እግዚአብሔር ማስተማር ልደታ ፍርድ ቤት ድርስ ያስከስሳልን ? ጉዳዩ ውስጥ ውስጡን ጠንከር ያለ ይመስላል፡፡ #የቀሩት 10 ወንድም ና እህቶቻችን ዛሬ አዳራቸው ፤ ቅዱስ ጴጥሮስንና ጳውሎስን እየዘከሩ እስር ቤት ይሆናል ፡፡ ነገ ጠዋት ወደ ፍርድ ቤት ይሄዳሉ ፡፡ አሁንም ሐገረ ስብከቱ አይቶ እንዳላየ ሰምቶ እንዳልሰማ ሆኗል :: ደም እስኪፈስ እየጠበቁ ይመስላል፡፡ #አስተዳደሩ ወንጌል #ለማስተጓጎል ፣ #ትውልድ ማፍራያ ተቋም ላማጥፋት ፣ #እውነት ለምን ተወራ ፣ #መማርያ ቦታ ለምን ተጠየቀ ብለው እያደሩጎት ያለው ተግባር እጅግ ስር የሰደደ ነው ይህም አገልጋዩች ቂሊንቶ እንዲወርዱ ነው ፡፡የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ስዩም ወልደ ገብርኤል በዚህ የሚያቆሙ አይመስሉም እጃቸው ረጅም ነው፡፡በአውደ ምሕርት ላይም ለምዕመናን ውሸት መናገረቸው እናዳይዘነጋ፡፡ #ከዚህ በተረፈ ሽብሻቦ በካቴና እንደሚቀጥል ፣ #መልዕክታት ለቀጨኔ ሕዝብ ከእስር ቤት እንደሚላኩ ከዚህም በላይ በዝተን እውነትን መስበካችንን እንደምንቀጥል 11 አገልጋይ ያሳሰሩ ቢሆንም 111 አገልጋይ እንደበዙልን እና ፍትሕ ደግሞ ከእውነት ጋር ስለሆነች እኛ ጋር መምጣቷ የማይቀር መሆኑን እናምናለን፡: ለማንኛውም ቀጣይ ስም ዝርዝሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ሁላችንም እንዘጋጅ ፡፡ የቀጨኔ ምዕመናን ቀጣይ የማን #ልጅ ፣ የማን #ወንድም እንደሚታሰር አይታወቅም የእርሶ ቢሆንስ? የማን #ጓደኛ ፣ የማን #ዘመድ እንደሚታሰር አይተወቅም የእርሶ ቢሆንስ ? ከእነዚህ ምክኒያቶች ሁሉ ለሚበልጠው ምክንያት ‹‹ስለ እውነት እና ስለ ደብራችሁ›› ስትሉ ዛሬውኑ ለምን በሉ! #ታውቋቸው ዘንድ ቀጣይ የሚሆኑትን እንዘረዝራልን ገብርኤል ፍርዱን ይሰጣል

.......#የደብራችን አስተዳደር የከሰሰው አባላችን የዋስ መብት ተከለከለ:: .......#ዛሬ የታሰሩት አባላት አዳራቸው እስር ቤት ነው:: #ለቤተክርስሰቲያን እና ለእውነት የቆመው ወንድማችን በቀለ አሰፋ ዛሬ ጠዋት ጉለሌ ፍርድ ቤት ቀርቦ በ1000 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ቢወሰንለትም መርማሪው ይግባኝ ስለጠየቀ ጉዳዩ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት እንዲዘዋወር ሆኗል፡፡ #ለእውነት መቆም እና ለቤተክርስቲያን ...... ፌስቡክ ገጻችን ላይ መሉውን በማንበብ ሃሳባቹህን በኮሜንት ስጡ + share + like https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

.......#የደብራችን አስተዳደር የከሰሰው አባላችን የዋስ መብት ተከለከለ:: .......#ዛሬ የታሰሩት አባላት አዳራቸው እስር ቤት ነው:: #ለቤተክርስሰቲያን እና ለእውነት የቆመው ወንድማችን በቀለ አሰፋ ዛሬ ጠዋት ጉለሌ ፍርድ ቤት ቀርቦ በ1000 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ቢወሰንለትም መርማሪው ይግባኝ ስለጠየቀ ጉዳዩ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት እንዲዘዋወር ሆኗል፡፡ #ለእውነት መቆም እና ለቤተክርስቲያን ...... ፌስቡክ ገጻችን ላይ መሉውን በማንበብ ሃሳባቹህን በኮሜንት ስጡ + share + like https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

#በድጋሚ አሳዛኝ ዜና #የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር ቅዳሜ ዕለት ለሕጻናት ቃለ እግዚአብሔር አስተምሮ ሲወጣ ያሳሰርው አባላችንን በቀለ አሰፋ ፤ ከሁለት ቀን የእስር ቤት ቆይታ በኃለ ወደ ፍርድ ቤት ሄዷል ፡፡ #አስተዳደሩ የከሰሳቸው እና በዕለተ ሰንበት ከቤተክርስቲያ ግቢ ውስጥ በሲቪል ፖሊሶች ሊታሰሩ ሰፈለጉ የነበሩት 11 አባላት ዛሬ ጠዋት ቃል ሰጥተው ታሰረዋል፡፡ #ስም ዝርዝራችው.. በቀለ አሰፋ ( በአሁኑ ሰዓት ፍርድ ቤት ያለ ) ዲ/ን ታምራት መሉነህ ዲ/ን ፍቅረ ሥላሴ አዳነ ዲ/ን ዮሐንስ መስፍን መ/ር ኪሩቤል ጀቤሣ ዲ/ን ተሻለ አለሙ ይሰሐቅ ወርቅዬ ሰላም ታመነ ፀጋዬ ቶላ እሙዬ ሽታዩ መስታወት ይጥና አሳልፈው ጎረምስ #እነዚህ የሰ.ት.ቤት አገልጋዮች ወንጌል ማስፋፋያ ቦታ ፣ ትውልድ ማፍርያ ቦታ ይሰጠን ብለው እውነት ይዘው ስለጠየቁ ለክስ እና ለእስር ተዳርገዋል፡፡ የደብሩ አስተዳደር አካል ከሃገረ ስብከቱ የመጣለትን ውሳኔ የማይቀበል እና የማይተገብር መሆኑ እና በአውደ ምሕረትም ላይ ለምዕመናኑ ክሴን አንስቻለሁ በሰላም እንፈታዋለን ብሎ ቢናገርም ፤ ንግግር እና ተግባር አንድ ሳይሆን ቀርቶ በየዕለቱ እውነትን የያዙ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋዮች እየተከሰሱ እና እየታሰሩ ነው ያለው ፡፡ #የአዲስ አበባ ሐገረ ስብከትም እንደወትሮ አይቶ እንዳላይ ዝም ብሏል ፡፡ ለቅድስት ቤተክርስቲያናችን ፍትሕ የሚሰጥ አካል እሱ ሆኖ ሳለ ደም ካልፈሰሰ አንነቃም ያሉ ይመስላል፡፡ እውነትን የያዙ አጋልጋዮች እያተሳሩ ሳለ መፍትሔ ባለመስጠት አሁንም ዝም ብሎ ተቀምጧል፡፡ #የቀጨኔ ምዕመናን እስከመቼ ዝምታ ፣ እስከመቼ በአውደ ምሕርት ሌላ መልዕክት ተነግሮዋቹ ሌላ ተግባር የምታዩት ፣ እሰከ መቼ ነው ደብራቹህ ላይ ሰላም የምታጡት ፡፡ የቀጨኔ ምዕመናን ለቤተክርስቲያናቹ ሰላም ዛሬ ነገ ሳትሉ አሁኑኑ ልቶቆሙ ይገባል ፡፡ #በእስር ቤት ያሉት ወንድምና እና እህቶቻች ምን እንደተባሉ እና ፍርድ ቤት የቀረበው ወንድማችን ምን ላይ እንደደረሰ ከሰዓታት ቆይታ ቦኃላ እናሳውቃለን! አስተዳደሩም በቅርቡ ይፋ የምናደርጋቸውን ስሞች በተጨማሪ ለመክሰስ እንዳቀዱ ደርሰንበታል ፡፡ #ቅዱስ_ገብርኤል ፍርዱን ይሰጣል! መድኀኔዓለም ከፊታችን ይምራን ቅዱስ ገብርኤል ከኃላ ይከተለን ፡፡ ተጨማሪውን በፌስቡክ ገጻችን ተመልከቱ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool