es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 382 suscriptores, ocupando la posición 5 588 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 193 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 382 suscriptores.

Según los últimos datos del 10 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 43, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 23.36%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 592 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 449 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 11 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 382
Suscriptores
-324 horas
-27 días
+4330 días
Archivo de publicaciones
አዋጅ፥ አዋጅ፥ አዋጅ፡፡ የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፡፡ *** እንደ አምለከ አበው መድኀኔ ዓለም ፈቃድ #ለመስከረም_፬/ ፳፻፲፪ ዓ.ም. #የሚካሄደውን_ሰልፍ_በተመለከተ_የወጣ_መርሐ_ግብር_፤ *** ሰልፉ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት መስከረም ፬ በአደባባዮች ይካሄዳል፡፡ *** በዕለቱም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ይገኛሉ፡፡ ሰልፉን ሁሉም ምዕመን በኀላፊነት የሚያስተባብረው ሲሆን፤ በግንባር ቀደምትነት ግን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት፤ የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችን ምሩቃን፤ በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን፤ የወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት፤ የሠለስቱ ምዕት ማኅበራት ኅብረት፤ የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ተናሥኦት ኅብረት፤ የጽዋ ማኅበራት ሙሴና ደርገ ሙሴዎች ናቸው፡፡ *** መስከረም 4 ጠዋት 2.30-3፡30 ሰዐት ቅዳሴ እንዳበቃ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ እስከ ተመደበላቸው መሰባሰቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ (ለምሳሌ የሰሜን አቅጣጫ እኛን ጨምሮ ገነተ ጽጌ ላይ ነው የምንገናኘው)፤ በሚከተለው ሁኔታ ጕዞ ይካሄዳል፡፡ ፠ ባለ መለከቶችና ባለ ጥሩንባዎች ድምፅ እያሰሙ ባንዲራን እያውለበለቡ ከፊት ይመራሉ፤ ፠ በመከተልም የበገና ዝማሬ የሚያቀርቡ ይከተላሉ፡፡ ፠ ማዕጠንት የያዙ ካህናት እያጠኑ ይመራሉ፤ ፠ የየሰንበት ትምህርት ቤት መለያ ልብስ(ዩኒፎርም)ና ጥንግ ድርብ የለበሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና ተማሪዎች በዝማሬ ጭምር ይከተላሉ፤ /የሰ/ትቤቶች አመራር ያስተባብራሉ/ ፠ የጽዋ ማኅበራት በነጭ ልብስ (በማኅበራቸው መለያ ልብስ) ይከተላሉ /የየማኅበሩ ሙሴና ደርገ ሙሴ ያስተባብራሉ/ ፠ ጥንግ ድርብ የለበሱ መዘምራን ማኅሌታውያን ይከተላሉ /አጋፊሪና መጨኔ ያስተባብራሉ/ ፠ መስቀል የያዙ ዲያቆናትና ካህናት፤ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ፥ ጥላና ድባብ የያዙ ካህናት ይከተላሉ፤ /ሊቀ ዲያቆንና ቄሰ ገበዝ ያስተባብራሉ/ ፠ ምዕመናን ነጭ ልብስ፣ ነጠላ (ቲሸርት) በመልበስ ይከተላሉ፡፡ /የሰባካ ጕባኤ አባላት ያስተባብራሉ/ * ** በተመደበልን ቤተ ክርስቲያን ከተገኘን በኋላ ጠዋት ከ3፡30-4፡30 በሊቃነ ጳጳሳት እየተመራን ወደ መስቀል አደባበይ ጕዞ ይካሄዳል፤ *** ከ4፡30-7፡30 በመስቀል አደባባይ ሰልፉ ይካሄዳል፡፡ *** የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችና ምሩቃን /አስተባባሪዎች ያስተባብራሉ/ *** የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ተማሪዎችንም /የተመደቡላቸው አስተባባሪዎች ያስተባብራሉ፡፡/ ስለ ጽዮን ዝም አንልም፠ * ልዩ ማስታወሻ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተቃውሟቸውን ድጋሚ መስከረም 16 በደመራ ዕለት በትርዒቶቻቸው እንደ የሁኔታው ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ * ተጨማሪ የሰልፉን ማብራሪያዎች በተመለከተ ነገ ይጠብቁ፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። #ሩፋኤል_ሊቀ_መላእክት_ወመልከጼዴቅ_ካህን_ርኅወተ_ሰማይ_:: #እንኳን_ለቅዱስ_ሩፋኤል_በዓለ_ሢመትና_ለቅዳሴ_ቤቱ_በ4ኛው_መቶ_ክ_ዘመን_በቅዱስ_ቴዎፍሎስ_ዘእስክንድርያ_አማካኝነት_በሚደንቅ_ተዓምራት_በአሣ_አንበሪ_ጀርባ_ደሴት_ላይ_ለታነጸው_ቅዳሴ_ቤት_እንዲሁም_ለካህኑ_መልከጼዴቅ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_በሰላምና_በጤና_አደረሳችሁ_አደረሰን_፡፡ ✠ ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው። ሣልሳይ ሊቀ መላእክት ነው። (“ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ” እናዳለ /ጦቢ ፲፪፥፲፭/፡፡ ✤ ሄኖክም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ይለዋል (መጽሐፈ ሄኖክ 6፥3):: ✤ ለሄኖክ ወልደ ያሬድ 6 ዓመት በእግረ ገነት ወድቆ ሳለ ኅበዓቱን ክሡታቱን አሳይቶታል። መ.ሄኖክ 8፡5  ቅዱስ ሩፋኤል ሰማያውያን መዛግብትን በእጁ የሚጠበቁ በመሆናቸው "ዐቃቤ ኖኅቱ ለአምላክ" ይባላል፡፡ እግዘአብሔር እንዳዘዘው የሚዘጋቸው የሚከፍታችው እርሱ ነው፡፡ ✤✤✤ ቅዱስ ሩፋኤል ሰውን በመርዳት ሲኖር የነበረውን የጦቢትን ዓይን ያበራና፤ ሣራ ወለተ ራጕኤልን ተቆራኝቷት ከነበረው አስማንድዮስ ጋኔን (ያገባችውን ባል የሚገድል) አላቅቆ የጦቢት ልጅ ጦብያ እንዲያገባት ያደረገ በመኾኑ “ፈታሔ ማሕፀን (መወልድ/አዋላጅ፥ ምጥን የሚያቀል) ይባላል:: ” ና ‹‹መልአከ ከብካብ›› ተብሏል (ዛሬም ድረስ የእናቶች ሐኪም ነው)፤ በኋላም ወደ ጦቢት በመኼድ ረዥም ዘመን የታወረ ዐይኑን አብርቶለት ቤቱንም በበረከት ሞልቶታል፤ በዚህም ፈዋሴ ቊስል (ድውያን)፥ ዐቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ) ተብሎ ይጠራል፡፡  ጦቢት ልጁን ወደ ሜዶን ክፍል ወደ ምትሆነውና ራጌስ ወደ ምትባለው ሀገር ወደ ገባኤል ቤት ሲልከው መንገዱን የመራው አዛርያስ /ቅዱስ ሩፋኤል/ ነው፤ በዚህም ቅዱስ ሩፋኤል ‹መራኄ ፍኖት› /መንገድ መሪ/ ይባላል፡፡  ቅዱስ ሩፋኤል በራማ ሰማይ ሁለተኛ ክፍል ላይ የሰፈሩትንና መናብርት በመባል የሚጠሩትን 10ሩን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ነው፤ በዚህም ‹‹ሊቀ መናብርት›› ተብሎ ይጠራል፤ መናብርት የሚባሉት መላእክት ረቂቅ የኾነ የመብረቅ ጋሻ፥ የእሳት ጦር ይዘው፤ ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲኾኑ፤ ከእነዚኽ 10ር ነገደ መላእክት 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡  #በብዙኃን_ዘንድ_ለሚነሱ_ጥያቄዎች_መልስ_፡፡ #መልከ ጼዴቅ ማነው? #አባትና እናትስ የሉትምን!?፤ #የሰው ዘር አይደለምን!!?፤ #እውን መልከ ጼዴቅ ክርስቶስ ነውን?!!!! ✤✤ #መልከ_ጼዴቅ_ማነው_? መልከ ጼዴቅ በዘመነ አብርሃም የነበረ የሳሌም ንጉሥ እንዲሁም የልዑል እግዚአብሔር ካህን ነው /ዘፍጥ.14፤ ዕብ. 7/፡፡ ይህ ሰው አብርሃም ጠላቶቹን ነገሥተ ኮሎዶጎሞርን ድል አድርጎ ዮርዳኖስን ተሻግሮ በተመለሰ ጊዜ አብርሃምን ሊቀበለውና ሊባርከው ኅብስትና የወይን ጠጅ ይዞ ወጣ ባረከውም አብርሃምም ደግሞ ለመልከ ጼዴቅ ከምርኮው ዐሥራት አወጣ፡፡ (ኅብስትና ወይኑ የቅዱስ ቊርባን፣ መልከ ጼዴቅ የካህናት፣ አብርሃም የምእመናን፣ ዮርዳኖስ የጥምቀት ምሳሌዎች ናቸው)፡፡ ካህኑ መልከ ጼዴቅን ‎ቅዱስ ዻውሎስ "የትውልድ ቊጥር የለውም፤ ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም" ብሎ ያስቀመጠው /ዕብ.7፥3/፤ ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱ ከነገደ ‎ካም ነው፡፡ ወላጆቹም ‹‹ሚልኪና ሰሊማ ›› ይባላሉ፡፡ በፋሬስ ደግሞ፤ ፋሬስ የኦሪት ዛራ ደግሞ የወንጌል ምሳሌዎች ናቸው፤ ዛራ እጁን አውጥቶ መመለሱ ወንጌል በመልከ ጼዴቅ ታይታ የመጥፋቷ ምሳሌ፤ ፋሬስ ጥሶ እንደወጣ በመሀል ኦሪት ተሠርታለች፤ ዛራ ሁለተኛ እንደመወለዱ ወንጌልም ቆይታ ተሠርታለች፡፡  #መልከ ጼዴቅ ክርስቶስን በአራት ነገሮች ይመስለዋል፤ ✤1. መልከ ጼዴቅ ማለት የጽድቅ ንጉሥ የሰላም ንጉሥ ማለት ነው፤ ክርስቶስም ደግሞ አምላከ ጽድቅ አምላከ ሰላም ነው፣ ✤2. መልከ ጼዴቅ በኅብስትና በወይን ያስታኵት /ያመሰግን/ ነበር፤ ክርስቶስም ሥጋና ደሙን በኅብስትና በወይን ሰጥቶናል፣ ✤3. መልከ ጼዴቅ በመጽሐፍ ቅዱስ እናቱና አባቱ አልተጠቀሱም ክርስቶስ ደግሞ ለሰማያዊ ልደቱ እናት ለምድራዊ ልደቱ አባት የለውም፣ ✤4. መልከ ጼዴቅ ለዘመኑ ጥንት ለሕይወቱ ፍጻሜ የለውም፣ ለክርስቶስም በመጀመሪያ ቃል ነበር ቃልም ሥጋ ሆነ ሲባል ለልደቱ ጥንት የለውም አምላክነቱም ዘላለማዊ ነው፡ ✤ መልከ ጼዴቅ ለክርስቶስ ምሳሌ እንጂ ክርስቶስ አይደለም፤ ለዚህም መልከ ጼዴቅ ከጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ከሚለዩባቸው ነገሮች ዋናዎቹ፤ 1.መልከ ጼዴቅ ከካም ዘር ተወልዶ ክህነትን ከልዑል እግዚአብሔር አገኘ፤ ክርስቶስ ደግሞ ከይሁዳ ወገን ቢወለድም ቅሉ ክህነትና ከሌዊ ሳይሆን ከራሱ አገኘ (ክህነቱ የባሕርዩ ናትና፤ ራሱ ሊቀ ካህናት ነውና)፣ 2.የመልከ ጼዴቅ ክህነቱ ዘለዓለማዊት ብትሆንም ቅሉ ‹‹እስከ አለው›› (መነሻ ያለውና ሞት ይገድበዋልና)፤ የክርሰቶስ ክህነት ግን ‹‹እስከ እንደ ፍጡር የሌለበት ዘለዓለማዊት ናት፡፡›› 3.የመልከ ጼዴቅ ክህነት ፍጹም አልነበረችም /ምሳሌ ነበረችና/ (ምንም እንኳን ከሌዋውያን ክህነት ቢበልጥም በአንፃረ ክርስቶስ ግን ያንሳልና ፍፁም አልነበረም)፤ የክርስቶስ ክህነት ግን ፍጹም ናት (ፍፁም ድኀነትን የምታሰጥ በመሆኗ የአዳምን ጥንተ አብሶ በማስወገድ ወደ ጥንተ ክብሩ መልሳዋለችና)፤ 4.የመልከ ጼዴቅ መሥዋዕት ምንም እንኳን የሚሞቱ እንስሳት ባይኾኑም ቅሉ አማናዊ አልነበረም ምሳሌ እንጂ፤ የክርስቶስ መሥዋዕት ግን ራሱን አማናዊውን ሥጋ ወደሙን ሰጥቶናልና ከመልከጼዴቅ ምሳሌያዊ ቊርባን ትለያለች 5. ወንጌል በመልከ ጼዴቅ ምሳሌዋ ታይታ ጠፍታ ቆየች፤ በመድኀኔዓለም ክርስቶስ ግን ወንጌል ተሰበከች ጸንታም እስካሁን ኖረች ለወደፊትም ትኖራለች፡፡ ✠ ‹‹#ርኅወተ_ሰማይ_/ሰማይ የሚከፍትባት እለት››፤  የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግበት፥  አራተኛው መጋቤ ኮከብ (ሕልመልመሌክ) የሚያልፍባት፤  ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት  ሰማይ የሚከፈትባት ቀን፤ በቅዱስ ሩፋኤል መሪነት ጸሎት የሚያርግባት፤ በዚህም ‹‹መዝገበ ጸሎት›› /የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው/ ይባላል፡፡  የጌታችን ዳግም ምጽአት የሚታሰብባት ዕለት፤ ✤ በዚህም ምክንያ አባቶቻችን በዚህች እለት 365 አቡነ ዘበሰማያት ሲጸልዩ ያድራሉ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፥ ወለ ወላዲቱ ድንግል፥ ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን። /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

 ፎቶ 1) በዓለማችን በመልክ ጼዴቅ ስም የተሰየመው ብቸኛው ቤተ ክርስቲያን፡፡ ደብረ ዘይት ሂዲ መልከጼዴቅ፡፡  በኢትዮጵያ በቅዱስ ሩፋኤል ስም ከተሰየሙት ቤተ ክርስቲያን መካከል፤ ፎተ 2) ጎ
+4
 ፎቶ 1) በዓለማችን በመልክ ጼዴቅ ስም የተሰየመው ብቸኛው ቤተ ክርስቲያን፡፡ ደብረ ዘይት ሂዲ መልከጼዴቅ፡፡  በኢትዮጵያ በቅዱስ ሩፋኤል ስም ከተሰየሙት ቤተ ክርስቲያን መካከል፤ ፎተ 2) ጎንደር ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሩፋኤል ወአቡነ ሐራ ድንግል ወቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን (ጐንደር)፤ በአፄ በካፋ የተመሠረተና ዚቅ እንደተጀመረባቸው ከሚነገርላቸው ቦታዎች አንዱና ታላቁ ደብር፡፡ ፎቶ 3) አዲስ አበባ ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል፤ በ1878 ዓ.ም. በዳግማዊ አፄ ምኒልክ የተመሠረተና ባላ አንድ ጣሪያ ያለው ቀደምት የአዲስ አበባ ደብር፡፡ ፎቶ 4) ደብረ ዘይት (አየር ኃይል) ቅዱስ ሩፋኤል ቤ.ክ. ፎቶ 5) ወላይታ ዳሞት ፑላስ ቅዱስ ሩፋኤል ቤ.ክ.

#እንደ_አምላከ_አበው_መድኀኔ_ዓለም_ፈቃድ_የመስከረም_4_2012_ዓ.ም. ሰላማዊ ሰልፋችንን ለመንግሥት አካላት ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ አይጠበቅብንም፤ #ከሃገራችንም_አልፎ_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚደረ
+1
#እንደ_አምላከ_አበው_መድኀኔ_ዓለም_ፈቃድ_የመስከረም_4_2012_ዓ.ም. ሰላማዊ ሰልፋችንን ለመንግሥት አካላት ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ አይጠበቅብንም፤ #ከሃገራችንም_አልፎ_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚደረግ_ሰልፍ_ነው_፡፡ #የሰልፉ_አስተባባሪና_አዘጋጅ_በሃገራችንና_በመላው_ዓለም_የሚኖር_ሁሉም_ሕዝበ_ክርስቲያን_ነው_፡፡ በሃገራችንና በዓለም ክፍሎች ላይ ያላችሁ ሁሉ ከአሁኑ ቀጠሯችሁን ለመስከረም 4 ያዙ!!፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከምትቃጠል እኛ ቀድመን እንቃጠል ብለው አባቶቻችንና እናቶቻችን ሰማዕት ሆነው ያስረከቡንን ቤተ ክርስቲያን በኛ ዘመን ስትቃጠል ዝም ብለን አናይም!!! /ጽዋው ሞልቶ ተርፏል ከ40 በላይ አብያተ ክርስቲያናትና ንዋያተ ቅድሳት ተቃጥለዋልና/ መስከረም ፬/፳፻፲፪ዓ.ም. መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ የቀጠሮ ሰው ይበለን፡፡ /#ላልሰሙ_አሰሙ ፥ #ላልደረሳቸው_አድርሱ_፡፡/

ከዚህ በኋላ ወደ ራጕኤል ቤት እንደ ደረሱ ሣራ በደስታ ተቀበለቻቸው፤ የሣራ አባትም ጦብያን ገና እንዳየው ሚስቱ አድናን ‹ይህ ልጅ የእኔ ዘመድ ጦቢትን ይመስላል› አላት ከዚያም ጋር አያይዞ ‹ልጆች ከየት ሀገር መጣችሁ?› አላቸው፡፡ እነሱም ‹ከነነዌ ሀገር ነው የመጣን› አሉት፡፡ ‹ከዚያም ሀገር ጦቢት የሚባል ወንድም ነበረኝ ታውቁት ይሆን?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ጦቢያ አባቱን ሲጠራለት ‹እናውቀዋለን፡፡ እኔም ራሴ የጦቢት ልጅ ነኝ› አለው፡፡ ከዚያ በኋላ ራጉኤል ‹የወንድሜ ልጅ ነህን?› ብለ እቅፍ አድርጐ ሳመው፡፡ አድናም ሳመችውና ሁሉም ተያይዘው የናፍቆት ልቅሶ ተላቀሱ፡፡ ከወንድሙ እንደ መጡም ሲገነዘብ በግ አርዶ በጥሩ ሁኔታ ጋበዛቸው፡፡ ከበሉ በኋላ ጦብያ ቅዱስ ሩፋኤል በመንገድ የነገረውን በልቡ ሲያወጣ ሲያወርድ ስለ ዋለ፤ ቅዱስ ሩፋኤልን ያንን በመንገድ የነገርከኝን አሁን ፈጽምልኝ ሲለው ሰምቶ ስለ ልጅቷ መሆኑን ስለ ገባው ራጉኤል ጦብያን ‹ልጄ ይህች ልጅ ላንተ የምትገባ ናት ሰጥቸሃለሁ አይዞህ አትጠራጠር አሁንም ብላ ጠጣ ለዛሬም ደስ ይበልህ አለውና ሣራ ካለችበት የጫጉላ ቤት አግብተው ዘጉት፡፡ ጦብያም ሣራን በይ እኅቴ ኑሯችን እንዲቃናልንና ጋብቻችን እንዲባረክልን አስቀድመን ወደ ፈጣሪያችን ጸሎት እናድርግ› አላትና አብረው ጸሎት ካደረጉ በኋላ ያንን የያዘውንና የዓሣ ጉበትና ሐሞት ከዕጣን ጋር ጨምሮ ቢያጤስበት በሣራ አድሮ ባሎቿን ይገድልባት የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ከሣራ ለቆ ወጥቶ ሄደ ሁለተኛም ሊመለስ አልቻለም፡፡ እነርሱም በሰላምና በጤና አደሩ፡፡ የጦብያንና የሣራን ጋብቻ የባረከ ቅዱስ ሩፋኤል ስለሆነ ‹መልአከ ከብካብ› ይባላል፡፡ ከዚያ በኋላ የጤንነታቸውን ነገር ሲረዱ የሰርጉ ቀን የሚሆን የ14 ቀን በዓል እስኪፈጸም ድረስ ጦብያ ወደ ሀገሬ እሄዳለሁ ብሎ እንዳያውከው በማለት አማለው፡፡ የ14 ቀን በዓለ መርዓ ከተፈጸመ በኋላ ግን ጥሬ ገንዘብና የከብት ስጦታ አድርጐ መርቆ ወደ ሀገሩ ሰደደው፡፡ ወላጆቹ ጦቢትና ሐና ግን በመዘግየቱ ልጃችን ምን አግኝቶት ይሆን? እያሉ ለጊዜው ሳያዝኑ አልቀሩም፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ሚስቱንና ግመሎቹን ይዞ ሲመጣ በክብርና በደስታ ተቀበሉት፡፡ የጦብያ አባት ጦቢትም ልጅህ መጣ ሲሉት ዓይነ ሥውር ስለ ነበር እርሱን እቀበላለሁ ሲል ስለ ወደቀ ወዲያው ጦብያ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ይዞ ስለ ነበር የአባቱን ዓይን ቀባው ወዲያውም ዓይኖቹ ተከፈቱ፡፡ በመጨረሻም ከጦብያ ጋር ሄዶ የነበረው መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልን የድካሙን ዋጋ ገንዘብ ለመስጠት ጠሩት፤ እርሱ ግን ጦቢትንና ጦብያን ‹ፈጣሪያችሁን አመስግኑ እናንተ እስከ ዛሬ ድረስ ከየት እንደመጣሁ ማን እንደ ሆንኩ አላወቃችሁኝም፡፡ የእግዚአብሔር ምሥጢር ግን በክብር ሊገለጥ ይገባል እንጂ ሊሰውሩት ስለማይገባ የእኔን ተፈጥሮና ስም ልነግራችሁ እፈልጋለሁ ተፈጥሮዬ መልአክ ነኝ፣ ሥራዬም የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ› ሲል ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለት፡፡ የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡ /መጽ. ጦቢት/፡፡ ስለዚህ እንግዶችን መቀበል አንርሳ፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንዶች ሳያውቁ የመላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና፡፡ ዕብ. 13፥1-2 ፡፡ ጦቢት ከእህሉ ከፍሎ ለተራበ የሚያበላ ከልብሱ ለተራቆተ ሰው የሚያለብስ እግዚአብሔርን ዘወትር የሚያመሰግን፥ ለወገኖቹ የሚራራ፥ ዐሥራት በኩራት የሚያወጣ፥ የሚቀብረው ያጣ አስከሬንን የሚቀብር ሰው ነበር፡፡ በመሆኑም በሥራው ሁሉ እንዲረዳው በችግሩ ጊዜ እንዲያጸናው ቅዱስ ሩፋኤል ተልኮለታል፡፡ እኛም በሕይወታችን የጐደለብንን ነገር እንዲሞላልን ጐዳናችንን እንዲያስተካክልልን ከክፉ ጋኔን እንዲጠብቀን፤ አምላክ ቅዱስ ሩፋኤል ተለመነን፥ ቅዱስ ሩፋኤልንም አማልደን ማለትን ገንዘብ እናድርግ፡፡ ጳጕሜን የዘመን መሸጋገሪያ እንደ ሆነች ዕለተ ምጽአትም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምንሸጋገርባት ስለሆነች ከወዲሁ የቅዱስ ሩፋኤልን የመታሰቢያ በዓሉን ስናከብር በአማላጅነቱ ከቅዱሳን ኅብረት እንዲደምረን በንስሐ ታጥበን ደጅ ልንጠና ይገባል፡፡ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ምልጃው፣ ጥበቃውና ቃልኪዳኑ ይደረግልን በረከቱ ይደርብን፡፡ አሜን፡፡ ልመናው ከእኛ ከሀገራችንም ከኢትዮጵያ ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር። “ስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘአብጽሐና እስከ ዛቲ ሰዓት” /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

✤✠ #ታሪከ_ቅዱስ_ሩፋኤል_ወጦቢት_ (በመጽሐፍ ቅዱስ በመጽሐፈ ጦቢትና በድርሳነ ሩፋኤል ላይ ሰፊውን ታሪክ ታገኛላችሁ እኛ ግን አሳጥረን አቅርበነዋል፡፡) “እንግዶችን መቀበል አትርሱ፤ በዚህ አንዳንዶች ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” ዕብ.፲፫፡፩፤ እንዲል ሰውን በመርዳት በደግነቱ የታወቀው ጦቢት ከመንገድ ወድቆ የተገኘ በድን(አስከሬንን) ቀብሮ፤ በዚያው ሌሊት ከቅጥሩ አጠገብ ፊቱን ተገልጦ ተኝቶ ሳለ አዕዋፍ ትኩስ ፋንድያ ዐይኑ ላይ ጥለውበት እንደ ብልዝ ያለ ወጥቶበት ዐይኑ ጠፋ፤ ሚስቱም ባለማስተዋል ‹‹በጐነትኽ ምጽዋትኽ ያዳነኽ ወዴት ነው?›› በማለት በተናገረችው ጊዜ ዐዝኖ ሞትን ተመኘ (ጦቢ ፪፥፲፬)፡፡ እነርሱ ሲሄዱ ውለው ማታ ጤግሮስ ከተባለው ታላቅ ወንዝ ደረሱና ከዚያም ለማደር ወሰኑ፡፡ በዚህ ጊዜ ከድካሙ ጽናት የተነሣ ጦብያ ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረደና ልብሱን አውልቆ መታጠብ ሲጀምር አንድ ዓሣ ሊውጠው ከባሕር ወጣ፡፡ ወዲያውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ያዘው ፤ ዓሣውን እንዳትለቀው አለው ፤ ጦቢያም ከዓሳው ጋር ግብ ግብ ገጥሞ እየጐተተ ወደ የብስ አወጣው ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡ ዓሣውን እረደው ጉበቱንና ሐሞቱን ተጠንቅቀህ ያዘው ሌላውን ግን ጠብሰን እንበላዋለን አለው፡፡ ጦቢት በ፯፻፳ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በፋርስ ንጉሥ በስልምናሶር ዘመን ዐሥሩ ነገደ እስራኤል ሲማረኩ አብሮ የተማረከ ከነገደ ንፍታሌም የተወለደ ጽኑዕ እሥራኤላዊና ጻድቅ ነው፡፡ እግዚአብሔር በስልምናሶር ፊት የመወደድን ግርማና ባለሟልነትን ስለ ሰጠው አለቃ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ ለወገኖቹ ምጽዋት በመስጠት ሕገ ርትዕን በመሥራት የተጋ ሰው ነበር፡፡ ሐና የምትባል ሚስት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዷል፡፡ ስልምናሶር ሞቶ ሰናክሬም በነገሠ ጊዜ ከሹመቱ ስለሻረው ደግሞ ወደ ምድያም መሔድ አልቻለም፡፡ ሣራ ወለተ ራጉኤል ከፍተኛ ችግር ደርሶባት ነበር፡፡ ችግሯም ሕፃናት ወልጄ ቤት ንብረት ይዤ እኖራለሁ በማለት ባል አገባች። ነገር ግን በዚች ሴት አስማንድዮስ የሚባል ጋኔን አድሮ ያገባችውን ሰው ገደለባት ሌላም ባል ብታገባ ሞተባት እንደዚህ እየሆነ በጠቅላላ ሰባት ድረስ ያሉትን ባሎችን ገደለባት፡፡ የራጉኤል ልጅ ሣራ በዚህ ሁኔታ በኀዘን ተውጣ ስትኖር በነበረበት ጊዜ ጦቢት ሸምግሎ ስለ ነበር ልጁ ጦብያን ጠርቶ በዚህ ዓለም እስካለ ድረስ ሊሠራው የሚገባውን መንፈሳዊ ሥራ እንዲሠራ በጥብቅ ከመከረው በኋላ በመጨረሻ ልጄ እኔ ሳልሞት የኑሮ ጓደኛህን ፈልግ፣ ስትፈልግም ዕወቅበት፣ እኛ የአብርሃም የይስሐቅና የያዕቆብ ዘሮች ነን ስለዚህ ከእነርሱ ወገን የሆነችውን እንድታገባ ከዚህም ሌላ ከገባኤል ዘንድ በአደራ ያስቀመጥኩት ገንዘብ አለና እኔ በሕይወት እያለሁ ብታመጣው የተሻለ ነው አለው፡፡ ጦብያም ያባቱን ምክር ሁሉ በጽሞና ካዳመጠ በኋላ ‹አባባ የነገርከኝን ነገር ሁሉ በተቻለኝ መጠን እፈጽማለሁ ግን ከገባኤል ጋር ስላለው ገንዘብ እንዴት ለማምጣት እችላለሁ? ሀገሩን አላውቀውም› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ነገሩ አሳሳቢ ሆኖ ስላገኘው ጦቢት ልጁ ጦብያን ‹አብሮህ የሚሄድ ሰው እስቲ ፈልግ ምናልባት አብሮ የሚሄድ ጓደኛ ታገኝ ይሆናል ደመወዝም ሰጥተን ቢሆን ካንተ ጋር የሚሄድ አንድ ሰው ግድ ያስፈልግሃልና ሂድ ሰው ፈልግ› አለው፡፡ አብሮት የሚሄደው ሰው ለመፈለግም ቢሄድ አንድ መልካም ጐበዝ አገኘ ይኸውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ጦብያ ግን መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል መሆኑን ፈጽሞ አላወቀም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ጦብያ መልአኩን ሰው መስሎ እንዳገኘው ‹የሜዶን ክፍል ወደ ምትሆነውና ራጌስ ወደ ምትባለው ሀገር ከእኔ ጋር ለመሄድ ትችላለህን የድካምህን ዋጋ የጠየቅኸውን ያህል እሰጥሃለሁ› ሲል ጠየቀው ቅዱስ ሩፋኤልም ‹እሺ ካንተ ጋር ለመሄድ ፈቃኛ ነኝ መንገዱንም ሆነ ሀገሩን በሚገባ አውቀዋለሁ ከገባኤል ቤት ብዙ ጊዜ ኑሬአለሁና› አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ጦብያ በል ከአባቴ ጋር ላስተዋውቅህ ብሎ ወደ አባቱ ወስዶ አስተዋወቀው ከእኔ ጋር የሚሄደው ሰው ይህ ነው በማለት ካስተዋወቀው በኋላ ጦቢትም ከወዴት እንደ መጣ ማን ተብሎ እንደሚጠራ ጠየቀው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልም የታላቅ ወንድምህ ወገን ከመሆንም ሌላ ስሜም አዛርያስ ይባላል አለው፡፡ ጦቢ. 5.12 ፡፡ ጦቢትም የወንድሙ ዘመድ መሆኑን ከሰማ በኋላ ‹አንተስ ወንድሜ ነህ በል የልጄ የጦብያን ነገር አደራ ከሀገር ወጥቶ አያውቅምና እንዳይደነግጥ ደኅና አድርገህ እንድትይዝልኝ› ብሎ ስንቃቸውን አስይዞ ሸኛቸው፡፡ አዛርያስ /ቅዱስ ሩፋኤል/ በመንገድ ይመራው ነበር፡፡ በዚህም ቅዱስ ሩፋኤል ‹መራኄ ፍኖት› /መንገድ መሪ/ ይባላል፡፡ እነርሱ ሲሄዱ ውለው ማታ ጤግሮስ ከተባለው ታላቅ ወንዝ ደረሱና ከዚያም ለማደር ወሰኑ፡፡ በዚህ ጊዜ ከድካሙ ጽናት የተነሣ ጦብያ ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረደና ልብሱን አውልቆ መታጠብ ሲጀምር አንድ ዓሣ ሊውጠው ከባሕር ወጣ፡፡ ወዲያውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ያዘው ፤ ዓሣውን እንዳትለቀው አለው ፤ ጦቢያም ከዓሳው ጋር ግብ ግብ ገጥሞ እየጐተተ ወደ የብስ አወጣው ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡ ዓሣውን እረደው ጉበቱንና ሐሞቱን ተጠንቅቀህ ያዘው ሌላውን ግን ጠብሰን እንበላዋለን አለው፡፡ ጦብያም መልአኩ እንዳዘዘው ዓሣውን አርዶ ሐሞቱንና ጉበቱን ያዘ፣ ሌላውን ሥጋውን ግን ጠብሰው ራታቸው አደረጉት፡፡ ጦብያም ያንን የዓሣውን ጉበትና ሐሞት ለምን እንደሚያገለግል ለመረዳት ‹ይህን ያዘው ያልከኝ ለምንድን ነው?› ሲል ጠየቀው ቅዱስ ሩፋኤልም ጋኔን ያደረበት ሰው ሲገኝ ይህንን ከዕጣን ጋር ቢያጤሱበት ጋኔኑ ይለቃል ሲል መለሰለት፣፡ በዚህ ሁኔታ አንድ ባንድ ሲነጋገሩ ከቆዩ በኋላ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ‹ዛሬ ከራጉኤል ቤት እናድራለን፡፡ እርሱ ዘመድህ ነው፡፡ የእርሱም ልጅ ሣራ የምትባል ቆንጆ ልጅ አለችው፡፡ እሷን ለሚስትነት ይሰጥህ ዘንድ ለራጉኤል እነግርልሃለሁ› አለው፡፡ ጦብያም ‹ያች ልጅ ከዚህ በፊት ሰባት ሰዎች እንዳገቧትና ሰባቱም ባገቧት ሌሊት ደርቀው /ሞተው/ እንደሚያድሩ ሰምቻለሁ፡፡ ስለዚህ እኔ ላባቴና ለእናቴ አንድ ልጅ ነኝ እርስዋን አግብቼ ከዚህ በፊት እንዳገቧት ሰዎች እኔም የሞትኩ እንደሆነ አባቴንና እናቴን የሚረዳቸው የለም ቢሞቱም የሚቀብራቸው አያገኙምና እፈራለሁ› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ግን ‹አባትህ ከዘመዶችህ ወገን ካልሆኑ በስተቀር ሌላ ሴት እንዳታገባ ሲል የነገረህን ረሳኸውን? በል ሰባት ባሎቿ ሙተውባታል ስለምትለው እኔ መድኃኒቱን አሳይሃለሁ ፤ አይዞህ አትፍራ አትሞትም የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ለምን መሰለህ ያዘው ያልኩህ ? እንግዲህ ሐሞቱንና ጉበቱን ከዕጣን ጋር ጨምረህ ስታጤስበት በሣራ አድሮ የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ወጥቶ ይሄዳል ፈጽሞም ወደ እርሷ በገባህም ጊዜ ሁለታችሁ ይቅር ባይ ወደ ሆነው እግዚአብሔር ጸልዩ እርሷም የተዘጋጀች ናት፡፡ ከእኛ ጋርም ወደ ሀገርህ ይዘናት እንሄዳለን› አለው፡፡ ጦብያም ይህንን ቃል በሰማ ጊዜ ደስ አለውና ከእርሷ በስተቀር ሌላ እንዳያገባ በሙሉ አሳቡ ወሰነ፡፡

#ዘመነ_በርዮድ_ #ጳጕሜን_ ዓመትን በዘመናት ስንከፋፍለው በ4ት ዘመናት ይከፈላል፤ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ዘመነ ክረምት (ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25) ነው፤ በዘመነ ክረምት ውስጥ ደግሞ ከሚውሉት መካከል ከነሐሴ 28 እስከ ጳጕሜን ፭ት (በሠግር ዓመት ፮ት) ድረስ ያለው #ዘመነ_በርዮድ_ ይባላል፤ ይህም ወደ አዲስ ዘመን የሚያሻግረን ነው፡፡ በቅዱስ ያሬድ ድጓ መሠረትም ጎሕ (ውጋገን)፣ ነግህ (ንጋት)፣ ጽባሕ (ጥዋት)፣ ብርሃን፣ መዓልት (ዕለት)፣ ጌና (ልደት) ይባላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም (ዘመንን ቀንን በቊጥር ሰጣቸው፣ በውስጧም ያለውን ፍጥረት አስገዛቸው፡፡) እንዲል /ሲራክ 17፥2/ ጳጕሜን ማለት ጭማሪ ማለት ነው፤ ይህም በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት በስድስት መቶ ዓመት አንዴ ደግሞ ሰባት ቀን በመሆን የምትመጣ ናት፡፡ ጳጕሜን በአራት ዓመት አንዴ (ማለትም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ ቅበላ ስድስት ቀን ትሆናለች)፤ የዘንድሮውን የ2011 ዓ..ም ወርኀ ጳጕሜን ልብ ይሏል፡፡ በዚህም ሃገራችን ኢትዮጵያ የዐሥራ ሦስት ወራት ጸጋ /Thirty months of sunshine/ በመባል ትታወቃች፡፡ #የጳጕሜን_ጾም_ጾመ_ዮዲት_ በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጕሜን ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም በተጨማሪ ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፤ ጾሙ እንደ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ጾመ ዮዲት የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ /እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡/ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ፥ ድንበር አስፋ፤ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ፥ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ /ዮዲት 2፥2-7/፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ ዮዲት ባሏ ሞቶባት፤ ከወንድ ርቃ፥ ንጽሕናዋን ጠብቃ፥ በጾም፥ በቀኖና፥ በሐዘን ተወስና የምትኖር ነበረችና፤ በተፈጠረው ጥፋት ሕዝቡ ላይ ለመጣው መከራ፤ ማቅ ለብሳ፥ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክን ሕዝቡ የሚድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለጸላት /ዮዲት 8፥2/ ፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡ ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንንና ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን ለመጎናጸፍ ጳጕሜን በፈቃድ እንጾማለን፡፡ #ጳጕሜን_የዕለተ_ምጽአት_መታሰቢያ_ የጳጕሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡ ይህም ጳጕሜን የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ፤ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፥ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡ #ጠበል_በወርኀ_ጳጕሜን_ ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በጳጕሜ ወር ሁሉም ተሰብስበው ከሌሊት ጀምረው በቤተክርስቲያን ተገኝተው ጠበል ይጠመቃሉ፡፡ ይህንን የምናደገውም እግዚአብሔር የተባረከ ዓመት እንዲሰጠን፣ ባሳለፍነው ዓመት የሰራነውን ኃጢአት ይቅር እንዲለን ነው፡፡ የምንጠመቀውም ንስሐ ገብተን ነው፡፡ በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጠበል ደግሞ ከበሽታችን ያድነናል፥ የተቀደስንም ያደርገናል፤ መጪውንም ሕይወታችን የተባረከ ያደርግልናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ ጷጕሜን ይሁንልን፡፡ /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ተመልከት_ዓላማህን_ተከተል_አለቃህን_፨ ቢዘገይም ቢረፍድም ይህ ሊሆን ግን ግድ ነው፤ #ነሐሴ_30_2011_ዓ_ም_ በቅርብ ዐሠርት ዓመታት ወዲህ ቅዱስ ሲኖዶስ ለእንዲህ ዓየነት ሁኔታ አስቸኳይ ምልዓ
+5
#ተመልከት_ዓላማህን_ተከተል_አለቃህን_፨ ቢዘገይም ቢረፍድም ይህ ሊሆን ግን ግድ ነው፤ #ነሐሴ_30_2011_ዓ_ም_ በቅርብ ዐሠርት ዓመታት ወዲህ ቅዱስ ሲኖዶስ ለእንዲህ ዓየነት ሁኔታ አስቸኳይ ምልዓተ ጕባኤ ተጠርቶ አያውቅም፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጕባኤ ስብሰባ በዓመት ሁለቴ ማለትም፤ ፠በጥቅምት 12 (በሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍትና) ፠በርክበ ካህናት (የትንሣኤ በዓል በዋለ በ20ኛው ቀን) ይካሄዳል፡፡ በስብሰባው ትላላቅ የሚባሉ አጀንዳዎችን ይወስናል የቋሚ ሲኖዶስ (ቅዱስ ፓትርያርኩና 6ት ጳጳሳትን የያዘ) በየሳምንቱ 2ቴ/1ዴ/ ወይም እንደያስፈላጊነቱ እየተሰበሰበ ውሳኔዎችን ይወስናል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ከበላይ ሁኖ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ እንደመሆኑ በዋነኛነት ተቀብለን ልንትገብረው የሚገባው የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔንና ቅዱስ ሲኖዶስ ያዋቀራቸውን የቤተ ክርስቲያን መዋቅሮችና ክፍሎች እንጂ በተለያዩ መንገዶችን ሰዎች የሚተላለፉ መልእክቶችን መሆን አይገባውም፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያናችን ሐዋርያዊት ናትና፤ ሐዋርያዊት ከሚያስብሏት ነገሮች አንዱ እንደ ሐዋርያት በቅዱስ ሲኖዶስ መመራቷ ነው፡፡ ምንም እንኳን በአንዳንድ አባቶች ስንፍና፣ ለሥጋ ማደር፣ ለፖለቲካ መወገን፣ ለብሔር መወገን፣ ለገንዘብ መሞት፣ …… ከተሾሙበት አባትነት ውጭ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ ብናይና ብንሰማም ……… ችግር ያለባቸውን አባቶች ለይቶ እንዲስተካከሉ ማደረግ ተገቢ ነው፤ በሌላ ወገን ለተሾሙበት ዓለም እስከ ሞት ድረስ ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ እውነተኛ አባቶች አሉና፤ …… የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን ልንሰማና ልንትገብር ግድ ነው፡፡

በቀሲስ በላይ መኮንን በኦሮሞ ባሕል ማዕከል የተጠራው የዕወጃ መርሐ ግብርን ቤተ ክርስቲያን እንደማታወቀውና ድርጊቱም ሕገ ወጥ መሆኑን ገለጠች፡፡ መርሐ ግብሩ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዕውቅናና ይሁንታ ውጭ
በቀሲስ በላይ መኮንን በኦሮሞ ባሕል ማዕከል የተጠራው የዕወጃ መርሐ ግብርን ቤተ ክርስቲያን እንደማታወቀውና ድርጊቱም ሕገ ወጥ መሆኑን ገለጠች፡፡ መርሐ ግብሩ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዕውቅናና ይሁንታ ውጭ የሚካሔድ በመሆኑ መንግሥት ሕገ ወጥ ድርጊቱን እንዲያስቆም ቤተ ክርስቲያኒቱ አሳስባለች፡፡ የኦሮሞ ቤተ ክሕነት ካስፈለገም እንኳን ፈቃጁ ቅዱስ ሲኖዶስ እንጂ ቀሲስ በላይ አይደለም፨

#ኢይትበሃሉ_አነ_ዘጳውሎስ_ወአነ_ዘኬፋ_(እኔ የጳውሎስ ነን፤ እኔ የኬፋ ነኝ አትበሉ) ፠ሹመት ለማግኘት ሲሉ ፖለቲካዊ አወቃቀርን በቤተ ክርስቲያን ላይ ለመጫን የሚጥሩ፤ ፠በመንፈስ ቅዱስ መንገድ የማ
#ኢይትበሃሉ_አነ_ዘጳውሎስ_ወአነ_ዘኬፋ_(እኔ የጳውሎስ ነን፤ እኔ የኬፋ ነኝ አትበሉ) ፠ሹመት ለማግኘት ሲሉ ፖለቲካዊ አወቃቀርን በቤተ ክርስቲያን ላይ ለመጫን የሚጥሩ፤ ፠በመንፈስ ቅዱስ መንገድ የማይመሩ፤ ፠ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ቀን ከሌት የሚጥሩ፤ ፠ሊቀ አእላፍ የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው በአእላፍ ላይ አለቃ እንዲሆኑ እንጂ የአንድ ወገን አለቃ እንዲሆኑ አልነበረም!!!፤ የዛሬውን አያድርገውና አዲሱ ገበያ አካባቢ ነዋሪ እንደመሆናቸው የመንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተ ወዲህ ከበላይ ሆነው እንዲቈጣጠሩ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳወሎስ ተሹመው መልካም ሲሠሩ የቆዩት ‹‹ሊቀ አእላፍ በላይ መኰንን›› በስተመጨረሻው ነገር አምጥተዋል፤ መጨረሻዬን አሳምርልኝ የሚባለው እኮ ….. ፠የቤተ ክሕነት ዝምታስ ምንድን ነው፤ ፠በክልል ደረጃስ የኦሮሚያ ቤተ ክሕነት ማዋቀሩስ ጥቅሙ ምንድን ነው፤ ነገም እንደ ፖለቲካው የትግራይ ፥ የአፋር፥ የአማራ፥ የቤንሻንጉል፥ የሐረሪ፥ የሶማሊያ፥ …. ቤተ ክሕነት እያለ ይቀጥላል፡፡ ፠ስብከተ ወንጌልን ለማስተማር ያልተጉ፤ በሸፍጥ የተሞሉ፤ ለኦሮምያ ሕዝብ የቆምን ነን እያሉ (ፖለቲክን በሃይማኖት ላይ የሚጭኑ) የሚያጨናብሩ አወናባጆች፤ ፠ቤተ ክርስቲያንን ለሚያጠፉ ወገኖች መናጆ የሆኑ፤ አታላይ፡፡ ……. እውነቱን እውነት፤ ሐሰቱን ሐሰት በሉ፡፡ ፠ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ባጎረሰች እጇን ሊነክሱ ተነስተዋልና፤ (ለሊቀ አእላፍ በላይ መኰንንና ግብረ አበሮቹ) የአበው አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ፍርዱን ይስጣቸው፨

#እንኳን_ለቅድስት_ክርስቶስ_ሰምራ_ለአቡነ_ተክለሃይማኖትና_ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ_በዓለ_ዕረፍት_ በሰላምና_በጤና_አደረሰን_አደረሳችሁ_፡፡ #ሥርዐተ_ማኅሌት_ወታሪከ_ቅድስት_ክርስቶስ_ሰምራ_ ✤ ለቡ! (ሥርዐተ ማኅሌቱ ላይ ልዩ ማስታወሻ)፤ በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም የክርስቶስ ሰምራ የአቡነ ተክለሃይማኖትና የቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ በዓለ ዕረፍታቸው በየዓመቱ ነሐሴ 24 ስለሚከበር በሥርዐተ ማኅሌቱ ላይ አስቀድመን በደብራችንና በጣና ክርስቶስ ሰምራ የሚቆመውን የክርስቶስ ሰምራ ማኅሌት እያስቀደመን በመቀጠል ደግሞ የአቡነ ተክለሃይማኖትን ሥርዐተ ማኅሌት አስቀምጠናል፤ (በደብራችን በመጀመሪያ የክርስቶስ ሰምራ ማኅሌት ከተቆመ በኋላ የተክለሃይማኖት ይቀጥላል)፡፡ በሌሎች የአቡነ ተክለሃይማኖት ክብረ በዓል በሚደረግባቸው ገዳማትና አድባራት ደግሞ የክርስቶስ ሰምራ የሚለውን እያለፋችሁ የተክለሃይማኖት የሚለውን እንድትቆሙበት አዘጋጅተነዋል፡፡ የተክለሃይማኖት ዚቁ ላይ ስትደርሱ ዚቅ ዘአባጃሌ ተክለ ሃይማኖትና ዚቅ ዘአደባባይ ተክለሃይማኖት በሚል ያስቀመጥነው በላይ ቤትና በታች ቤት እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት በማሰብ ነው ኹሉንም ያስቀመጥነው፡፡ ✤✣✤ #ክርስቶስ_ሠምራ_ እናታችን ክርስቶስ ሠምራ አባቷ ደርሳኒ እናቷ እሌኒ ይባላሉ። ሀገሩዋም በሸዋ ቡልጋ ልዩ ስሙ ገዬ ይባላል በሕግ በሥርዐት በቤተሰቦቿ ካደገች በኋላ ሰምረ ጊዮርጊስ ለተባለ ክርስቲያን በጋብቻ ተዳረችና ፲፪ ልጆችን ወለደች። በትዳሯ መልካም ሴት በሃይማኖቷም ብርቱ ተጋዳይ ነበረችና፣ ሐሳቧ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ወደ መንፈሳዊ ነገር ያዳላ ነበር ይህቺም እናታችን ሁልጊዜም መንኵሳ ፈጣሪዋን ማስደሰት አካሄዷንም በእግዚአብሔርም መንገድ ማድረግ ትፈልግ ነበርና አብዝታ ትጸልይ ነበር፡፡ «የነገሩትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ» አምላክ ትመነኵስ ዘንድ ፈቀደላት፤ እሱ ባይፈቅድ አትመነኩስም ነበር፤ ምክንያቱም ምንኩስና ለተፈቀደላት ለተመረጠ እንጂ የፈለገ ሁሉ አያገኘውምና እናታችን ክርስቶስሠምራም የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ስታረጋግጥ የመጨረሻ ልጇ ሕፃን ነበርና እሱን ይዛ ወደ ደብረሊባኖስ ገባች። በዚህም ስትሰግድና ስትጸልይ ልጇን ስታጠባ መነኰሳቱ ቢያዩዋት "ይህች ሴት ገዳማችንን ልታረክስብን ነው" ብለው ተነጋገሩባት፡፡ ኋላም ነገሩን ሰምታ ብትጸልይ መልአኩ ልጇን ወስዶ ብሔረ ብፁዓን አስገብቶት አገኘችው እሷም ደነገጠች፡፡ መልአኩም ተገልፆ "አይዞሽ ልጅሽ ከሕፃጻናቱ ጋር ብሔረ ብፁዓን ገብቷል ተክለ ሊባኖስ የነበረው ስሙም ተቀይሮ ዳግማዊ ቂርቆስ ተብሏል" አላት፡፡ እሷም ደስ እያላት ተጋድሎዋን ቀጠለች፤ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ፲፪ ዓመት ከቆየች በኋላ ወደ ሐይቅ ሄዳ ቢዚያ ፫ ዓመት ሥርዐተ ገዳማትን ተማረች፡፡ ተመልሳም ወደ ጣና ሐይቅ በመሄድ በባሕር ውስጥ ቁማ ፲፪ ዓመት በሰውነቷ ውስጥ አሳዎች እየተመላለሱባት ጸለየች፡፡ ተጋዶሎዋን ፈፅማ ያረፈችው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነው፡፡ ይህች እናት ግን ከሁሉ ልዩ የሚያደርጋት በግንቦት ፲፪ ቀን ጌታችን ተገልፆ ምንላደርግልሽ ሲላት የጸለየችው ጸሎት ነው ይኸውም "ሰውን ሁሉ ብትምረው ደስ ይለኛል ነገር ግን ሰው መበደሉ አይቀይርምና በደል ጥፋት ይጠፋ ዘንድ ዲያብሎስን ማርልኝ" ብላ ጸለየች። ጌታችንም "እንደ ወደድሽ ይሁን ፈቃዱ ከሆነ የሚመለስ ከሆነ እሺ" አላት፡፡ ዲያቢሎስ ግን ተመጻዳቂ ነውና "ከእኔ የተሻለ መፍጠር ስላልቻለ ነው እኔ የሱ ተገዢ መሆን አልፈልግም" ብሎ እናታችን ክርስቶስ ሠምራንም ነጥቆ ሊወስዳት ሲል መልአኩ ደርሶ አስጣላት፡፡ ይህ ልመናዋ ሌሎች ከጠየቁት ኹሉ ልዩ በመኾኑ ድንቅ ድንቅ ሲባል ይኖራል፤ ለዲያቢሎስ ሳይቀር ምሕረት የለመነች ያሰኛታል፤ የፃድቋ ምልጃና ጸሎት አይለየን፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ #በአዲስ_አበባ_የቅድስት_ክርስቶስ_ሰምራ_በዓለ_ዕረፍት_የሚከበርባቸው_ደብራት_፤ ✣ 1. በደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ✣ 2. በደብረ ይባቤ ቅዳሴ ያሬድ ቤ.ክ ✣ 3. በሰዓሊተ ምሕረት ማርያም ቤ.ክ ✤✤ #በአዲስ_አበባ_የአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_በዓለ_ዕረፍት_የሚከበርባቸው_፤ ✣ 1. በደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ✣ 2. በመንበረ ክብር ደብረ ታቦር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ✣ 3. በዳግማዊት ደብረ ሊባኖስ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም 4. በጥንታዊው በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም 5. በደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ

ታሪከ አቡነ ተክለሃይማኖት ወቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ ✤✣✤ #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ_ የመርዓስ ኤጵስ ቆጶስ የነበረው አባት አባ ቶማስ ክርስቶስን በማመን በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊት በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የሚኖር ነበር። በዚህ ፅናቱ የክብር ባለቤት ጌታችን መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ዘንድ መንጋውንም ይጠብቅ ዘንድ መረጠው አባታችን ቶማስም ሐዋርያዊ ተልዕኮውን እየፈፀመ፣ ሕዝቡን እየመራ ሳለ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በሱ ላይ፣ በአጠቃላይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ላይም ተነሳባቸው፣ ክርስቲያኖችንም ያሰቃያቸው ጀመር በአንድ ወቅት ከመኳንንቶች አንዱ የነበረው፣ ቅዱስ ቶማስን ወደ እርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ እነርሱም እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ ወሰዱት ደሙም እንደ ውኃ ፈሰሰ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት «እኔ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ ጣኦታት አልሰግድም ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና» በዚህም ጊዜ መኮንንኑ በጣም ተቆጥቶ እጅግ የበዛ ስቃይን አሰቃየው የነዳጅ ድፍድፍን አፍልተው በላዩ በአፉና በአፍንጫው እስከመጨመርም ደረሱ ልባቸው እንደ ድንጋያ የፀና ስለ ነበር ቅዱስ ቶማስን ገድለው ቶሎ ማሣረፍ አልፈለጉም ይልቁንም የስቃዩን ዘመን አስረዘሙ እንጂ እርሱም ስለ ስህተታቸው ይዘልፋቸው ነበር፣ እንደ ማይመልስም ሲገባቸው በጨለማ ቦታ ጣሉት በየዓመቱም ወደ እርሱ እየሄዱ ከሕዋሳቱ አንድ፣ አንዱን ይቆርጡ ነበር፡፡ በዚህም ለሃያ ሁለት(፳፪) ዓመት ቆየ ሲቆይ ግን አፍንጫውን፣ ከንፈሮቹን፣ ጆሮዎቹን፣ እጆቹንና እግሮቹን ቆርጠው ነበር፤ በዚህም ምክንያት የአገሬው ሰው ሞቷል ብለው አስበው በየዓመቱ መታሰቢያ ያደርጉለት ነበር ይህ ለምን ሳይሞት ቢሉ ጊዜው ሲረዝም ቢሞት ነው እንጂ እስካሁንማ ይመጣ ነበር ብለው ስላሰቡ ነበር፤ ነገር ግን ከሕዋሳቶቹ አብዛኛው ክፍል ቆርጠው ቢጥሉትም አካሉ ግን ተቆራርጦ ሲጣል አንዲት ሴት አየችው፣ ይህችም ሴት በሌሊት ወደርሱ ተሠውራ በመሔድ ትመግበው ነበር፡፡ ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከገለጥ ድረስ እንዲህ ሲሰቃይ ኖረ፡፡ ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ስለክርስቶስ በመታመን የታሠሩ እስረኞች ሁሉ እንዲፈቱ በማዘዙ ሁሉም ተፈቱ፡፡ ቅዱስ ቶማስ ግን የተጣለበት ቦታ፤ በሕይወት ያለም ስላልመሠላቸው አላወጡትም ነበር፤ ነገር ግን ይህን አዋጅ ትመግበው የነበረችው ሴት ሰምታ ነበርና ወደ ካህናቱ ዘንድ ሄዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ሃያ ሁለት ዓመት በዚያ ስለመኖሩ ነገረቻቸው ቦታውንም አመለከተቻቸው እነርሱም ባገኙት ጊዜ አንስተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑም ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደስ ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱንም ይሳለሙ ነበር፡፡ ከቦታ ቦታ ይዘዋወር የነበረውም በቅርጫት ኹኖ በዘህያ ላይ ተጭኖ ነው፡፡ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ የከበሩ ፫፻፲፰ ኤጲስ ቆጶሳትን (ሠለስቱ ምዕት) የአንድነት ጕባኤን በኒቂያ አገር በሰበሰበ ጊዜ ይህ አባት (ቅዱስ ቶማስ) ከሠለስቱ ምዕት አንዱ ነበር፤ ወደ ኒቅያ ጕባኤ በቅርጫት ሁኖ በአህያ ተጭኖ እየሄደ መሆኑን አርዮሳውያን ሲሰሙ፤ ቶማስማ በጕባኤው ከተገኘ ተከራክሮ ይረታናል አንችለውም በማለት መንገድ ላይ ባደረበት ይዘውት ይጓዙት የነበሩትን አህዮች በጨለማ በሰይፍ መተዋቸዋል፤ ነገር ግን ሌሊት ሊነጋጋ ሲል ለመንገድ ሲነሱ ቶማስ በተዓምራት አግልጋይ ረድኡን የተቆረጡትን የአህያዎቹን አንገታቸውን ከሰውነታቸው አጋጥመው ይነሳሉ ብሎ ሲያዘው የአንዱን አህያ ከሌላኛው አህያ ቢያጋጥመውም ቅሉ አህዮቹ ሕይወት አግኝተው ጕባኤ ኒቅያ አድርሰውታል፤ በዚያም አርዮስን መልስ እስኪያጣ ድረስ በጽናት ሲከራከረውና መልስ ሲያሳጠው የጕባኤው ሊቀ መንበር ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እስኪደነቅ ድረስ በማየቱ ሃይመኖትስ የእነ ቶማስ ዘመርዓስ ነች ብሎ አጽንቶ ወስኗል፡፡ በጕባኤውም አርዮስን ተከራክረው ከረቱ በኋላ አውግዘው ለይተውታል፤ ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ፤ ሕግና ሥርዐትን ሥጋዊና፤ መንፈሳዊ ፍርድንም ሰሩ። ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ከተመለሰ በኋላ ካህናቱና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲያስተውሉት እንዲጠበቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው፡፡ ይህ አባት ለ፵ ዓመት ያህል በሢመቱ አገልግሎ በነሐሴ ፳፬ ቀን አርፋል፡፡

ታሪከ አቡነ ተክለሃይማኖት ወቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ ✤✣✤ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በ1186 ዓም በሰሜን ሸዋ ቡልጋ ጽላልሽ (እቲሣ) ተወለዱ፡፡ አባታቸው ጸጋ ዘዓብ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲያስተምሯቸው አካባበቢያቸው ደግሞ በዘመኑ የነበሩ ልጆች ይማሩ የነበረውን ፈረስ መጋለብን፣ ቀስት መወርወርን፣ እርሻንና አደንን አስተምረዋቸዋል፡፡ በሰባት ዓመታቸው ከግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ከተቀበሉ በኋላ እግዚአብሔር በክህነት ሕዝቡን እንዲያገለግሉ መረጣቸው፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ለክህነት መጠራት በዚህ ዓለም ትዳር መሥርቶ፣ የዓለሙንም ሥራ ሠርቶ መኖር አያስፈልግም ከሚል ፍልስፍና የመነጨ አይደለም፡፡ ከ8ኛው መክዘ ጀምሮ በሀገሪቱ የመንፈስ መቀዛቀዝ ይስተዋል ነበር፡፡ ዮዲት ጉዲት መንግሥቱን ይዛ በክርስትናው ላይ ከዘመተች በኋላ ሰሜኑ እና ደቡቡ ተቆራርጧል፡፡ የሐሳብን ልዕልና የሚያመጣው የመንፈስ ልዕልና ተዳክሟል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያን የሚዋጅ ኢትዮጵያዊ ያስፈልግ ነበር፡፡ ይህ ነው የተክለ ሃይማኖት የጥሪ ምክንያት፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከአባታቸው ዕረፍት በኋላ ቅስናን ከአቡነ ቄርሎስ ተቀብለው በጽላልሽ አካባቢ በክህነት ከአባታቸው ጋር አገልግለዋል፡፡ አባታቸው ሲያርፉ በወንጌሉ ማንም ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር ያለውን ሁሉ ትቶ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ ያለውን በመከተል ሀብታቸውን ለድኾች መጽውተው ለወንጌል ስብከት ወጡ፡፡ የዋልድባው ገድለ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ከመሄዳቸው በፊት ቅስናን ተቀብለው በሸዋ እና በዳሞት ማገልገላቸውን ይገልጣል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዳሞት እና በሸዋ ካገለገሉ በኋላ መጀመርያ ደቡብ ወሎ ቦረና ላይ ገዳማቸውን ደብረ ጎል ገድመው ወደሚገኙት ታላቁና ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወደኾኑት ጻድቅ አባት አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው ዐሥር ዓመት (12 የሚልም አለ) በትምህርት እና በሥራ (በአርድእትነት) አሳልፈዋል፡፡ በዚያም ዋሻ ፈልፍለው አስደናቂ ሕንፃ ሠርተው ነበር፡፡ ገድለ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ እንደሚለው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ ሐይቅ የገቡት በሠላሳ ዓመታቸው ነው፡፡ ይህም የሚያሳየን በሸዋ እና በወላይታ ያገለገሉት ገና በወጣትነታቸው ጊዜ መሆኑን ነው፡፡ በ1216 ዓም አካባቢ ወደ ሐይቅ የገቡት አቡነ ተክለ ሃይማኖት በሐይቅ ከመመንኰሳቸው በፊት ሰባት ዓመት ከመነኰሱም በኋላ ሦስት ዓመት በትምህርት፣ በሥራና በአገልግሎት ቆይተዋል፡፡ ሐይቅ እስጢፋኖስ በዚያ ዘመን እንደ አዳሪ ትምህርት ቤት ያለ ዩኒቨርሲቲ ነበረ፡፡ ወደዚያ የሚገባ ሁሉ ሦስት ነገሮችን ይማራል፡፡ ትምህርት፣ የጥበበ እድ ሥራና ሥርዓዐተ ምንኵስና፡፡ ትምህርቱ የቤተ ክርስቲያኒቱን መላ ትምሀርት ያካትታል፡፡ የሞያ ትምህርቱም መጻፍ፣ መደጎስ፣ ሕንፃ ማነጽ፣ ልብስ መሥራት፣ እርሻ፣ የከብት ርባታና የሥዕል ሥራን ይመለከታል፡፡ ከእነዚህ ጎን ለጎን ደግሞ ጽሙድ እንደ ገበሬ፥ ቅኑት እንደ በሬ እንዲሆኑ ሥርዐተ ምንኩኵስናን ይማራሉ፡፡ በእነዚህ ትምህርቶች የታነፁት መነኮሳት ከገዳሙ ሲወጡ ዛሬ የፒኤች ዲ ተማሪ ጥናታዊ ጽሑፍ እንደሚያቀርበው የተማሩትን ጽፈው አንድ የብራና መጽሐፍ አዘጋጅተው ይወጣሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ሐይቅ ከስምንት መቶ መነኰሳት በላይ በአንድ ጊዜ የሚማሩባት በመኾኑ በመጻሕፍት የበለጸገች መካነ አእመሮ (ዩኒቨርሲቲ) ነበረች፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እዚህ ገዳም ዐሥር ዓመታትን አሳልፈዋል፡፡ ከሐይቅ ወጥተው በዘመኑ በሥርዐተ ምንኵስና እና በትምህርት ብሎም በጥበበ እድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ወደ ነበረው ወደ ደብረ ዳሞ ሄዱ፡፡ በዚያም ከአቡነ ዮሐኒ ዘንድ መንፈሳዊ ትምህርት፣ ሥርዐተ ምንኵስና እና ጥበበ እድ ሲማሩ ሰባት ዓመት አሳለፉ፡፡ ያነጹት ፍልፍል ድንጋይ ዋሻ፣ መጻሕፍት ሲጽፉ ቀለማቸውን ያስቀምጡባቸው የነበሩትን ሽንቁሮች ዛሬም በደብረ ዳሞ ማየት ይቻላል፡፡ በደብረ ዳሞ የነበራቸውን ቆይታ ጨርሰው በገመድ ሲወርዱ ሰይጣን በቅንዐት መጥቶ ገመዱን በጠሰባቸው እግዚአብሔር አምላክ በዚህ ወቅት ነበር የሚበሩበትን እንደ መላእክት ክንፍ የሰጣቸው፡፡ ቀሪዎቹን አምስት ዓመታት ሌሎችን የትግራይ ገዳማትና ዋልድባ ገዳምን እየተዘዋወሩ ሲመለከቱ ቆይተው ከሸዋ በወጡ በሃያ ሁለት ዓመት እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ሲሆን ለበለጠው ክብር እና ርእይ በግብጽ በኩል ወደ ኢየሩሳሌም ተሻገሩ፡፡ ከኢየሩሳሌም ሲመለሱ በሐይቅ በኩል አድርገው ደብረ ጎልን ተሳልመው በሚዳ እና በመርሐ ቤቴ በኩል ወደ ሸዋ በመምጣት ከዮዲት ዘመን በኋላ በመንፈሳዊ ሕይወት የተጎዳውን ሸዋን እና ደቡብ ኢትዮጵያን በመዘዋወር ለዐሥር ዓመታት ያህል አስተምረዋል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተግተው በማስተማራቸው የተኛው ሁሉ ነቃ፣ የደከመው በረታ፣ የጠፋውም ተገኘ፡፡ በስብከታቸው እንደገና ለነቃው ለመካከለኛው እና ለደቡብ ኢትዮጵያ ሐዋርያትን ለማፍራት እንዲችሉ አንድ ገዳም ለመመሥረትና ደቀ መዛሙርትን ለማስተማር አሰቡ፡፡ እናም ወደ ደብረ አስቦ ገዳም ገቡ፡፡ ቦታውን አስተካክለው እና ከደብረ ዳሞ እና ከሐይቅ የተከተሏቸውን ጥቂት ደቀ መዛሙርት ይዘው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ልክ እንደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሁሉ ሦስቱን ነገሮች ያካተተ አገልግሎት ጀመሩ፡፡ ምንኵስና፣ ትምህርትና ሥራ፡፡ መነኰሳቱ መንፈሳዊ ትምህርት ይማራሉ፤ በሕገ ገዳም ይመራሉ፤ ለራሳቸው እና ለአካባቢው ሕዝብ ርዳታ የሚሆን እርሻ ያርሳሉ፡፡ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው፣ ገዳማቸውን አደራጅተው፣ ስብከተ ወንጌልንም አስፍተው ካደላደሉ በኋላ በሕይወታቸው የመጨረሻ ዓመታት ወደ ደብረ አስቦ ዋሻ ገብተው በአንድ እግራቸው በጾም እና በጸሎት ተወሰኑ፡፡ አቡነ ተክለሃይማኖት አገልግሎታቸውን ፈጽመው ነሐሴ ሃያ አራት ቀን 1287 ዓም በ99 ዓመታቸው ዐረፉ፡፡ ጸሎታቸውና በረከታቸው ረድኤታቸውና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

እንኳን ለዕረገተ ማርያም በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ሥርዐተ ማኅሌቱን እነሆ ብለናል፡፡
+4
እንኳን ለዕረገተ ማርያም በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ሥርዐተ ማኅሌቱን እነሆ ብለናል፡፡