es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 382 suscriptores, ocupando la posición 5 588 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 193 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 382 suscriptores.

Según los últimos datos del 10 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 43, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 23.36%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 592 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 449 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 11 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 382
Suscriptores
-324 horas
-27 días
+4330 días
Archivo de publicaciones
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_#ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ዘነሐሴ_፲፭_#ክርስጢና_ስማዕት_ወ፫፼፰ወ፪#ማኀበራኒሃ_ወዕንባምሬና_ቅድስት_ወተጋብኦተ_ሐዋርያተ_ለግንዘተ_እሙ_ለእግዚእነ_ወለውረንዮስ_ሰማዕት_፡፡ #የቅ
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_#ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ዘነሐሴ_፲፭_#ክርስጢና_ስማዕት_ወ፫፼፰ወ፪#ማኀበራኒሃ_ወዕንባምሬና_ቅድስት_ወተጋብኦተ_ሐዋርያተ_ለግንዘተ_እሙ_ለእግዚእነ_ወለውረንዮስ_ሰማዕት_፡፡ #የቅዳሴ_ምንባባት † ፩ኛቆሮ.፲፪፥፲፰-ፍጻ፤ ወይእዜኒ አስተናበሮ እግዚአብሔር፡፡ † ይሁዳ ፩፥፲፯-ፍጻ፤ ወአንትሙሰ አኃዊነ ተዘከሩ ቃለ ዘነገሩክሙ:: † የሐዋ.፩÷፲፪-፲፭፤ ወእምዝ ተሠውጡ ኢየሩሳሌም፡፡ #ምስባክ_መዝ. ፲፰፥፬ አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ፤ አው (ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ)፤ ወእስከ አጽናፍ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ፡፡ ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ፡፡ (ትርጕም፤ቃላቸው ያልተሰማበት ነገራቸው ያልደረሰበት የለም፤ ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ ወጣ፤ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ደረሰ፤ ጥላውንም በፀሐይ አኖረ፡፡) #ወንጌል_ ማቴ. ፲፥፩-፲፭፤ ወጸውዖሙ ለ፲ወ፪ አርዳኢሁ፡፡ #ቅዳሴ_ዘሐዋርያት፤ ነአኵተከ እግዚኦ በፍቊር ወልድከ እግዚእነ ኢየሱስ፡

#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፲፬ #የቅዳሴ_ምንባባት † ፩ኛ ቆሮ.፩፥፲-፲፱፤ አስተበቊዐክሙ አኀዊነ በስሙ ለእግዚእነ፡፡ † ያዕ. ፲፪፥-፳፪፤ ወብፁዕ ብእሲ ዘይትዔገሣ ለእኪት፡፡ † የሐዋ.ሥ.፲
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፲፬ #የቅዳሴ_ምንባባት † ፩ኛ ቆሮ.፩፥፲-፲፱፤ አስተበቊዐክሙ አኀዊነ በስሙ ለእግዚእነ፡፡ † ያዕ. ፲፪፥-፳፪፤ ወብፁዕ ብእሲ ዘይትዔገሣ ለእኪት፡፡ † የሐዋ.ሥ.፲÷፴-፵፬፤ ወይቤሎ ቈርኔሌዎስ ረቡዐ ዮም፡፡ #ምስባክ_፵፫፥፬ ዘአዘዝከ መድኃኒቶ ለያዕቆብ፡፡ ብከ ንወግኦሙ ለኵሎሙ ፀርነ፡፡ ወበስምከ ናኀሥሮሙ ለእለ ቆሙ ላዕሌነ፡፡ (ትርጕም፤ ለያዕቆብ ድኅነትን ያዘዝኽለት፤ በአንተ ጠላቶቻችንን እንዋጋቸዋለን፤ በጠላትነት የነሡብንንም በስምህ እናዋርዳቸዋለን፡፡) #ወንጌል_ ማቴ.፲፯፥፲፬-፳፬፤ ወበጺሖሙ ኀበ አሕዛብ ቀርበ ኀቤሁ፡፡ #ቅዳሴ_ ዘእግዝእትነ (ጐሣዕ ልብየ ቃለ ሠናየ፡፡ አው (ወይም) ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ (ላዕለ ይኵን ኅሊናክሙ በሰማይ የሀሉ ልብክሙ)፡፡

#አጋፋሪ_ይደግሳል_፡፡ ፩ኛ ትርጕም አጋፋሪ፤ አሁን በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ደረጃ የማኅሌቱን ሥርዐት ፥ የዝክር ሁኔታን የሚያስተባብር አጋፋሪ ሲባል፤ ምክትሉ መጨኔ ይባላል፡፡ ፪ኛ ትርጕሙ፤ አጋፋሪ፤ በቀድሞ ዘመን በሃገራችን በተለይም በቤተ መንግሥት ያለ ሹመት ሲሆን፤ (በጎንደር ፥ በሸዋ ፥ በትግሬ ፥ በወለጋ፥ በአሊባቡር፥ በሐረርጌ፥ በጅማ፥ በወሎ አጋፋሪ ተብሎ ሲጠራ በጎጃም መጨኔ ይባላል/ ሁለቱንም በቀድሞ ዘመንም ሆነ አሁን ባለው ሁኔታ ትርጕሙን እናያለን ፤ ፠፠፩ኛ ፠፠ አሁን ካለው የቤ/ክን አገልግሎት አንጻር፤ አጋፋሪ ማለት የማኅሌቱን ሥርዐት ፥ የዝክር ሁኔታን የሚያስተባብር ሲሆን ምክትሉ መጨኔ ይባላል፡፡ ይህ አጋፋሪ በደብረ ታቦር በዓል ላይም በቅዱስ ሚካኤል ተመስሎ፤ ‹‹ሆያ ሆዬ›› ይባላል፡፡ ይኸውም ‹‹#ሆያ_ሆዬ_ሆ_››፤ ማለት ጌታው ሆዬ ፥ እሜቴ ሆዬ ለማለት ነው፡፡ ‹‹#እዚያ_ማዶ_ጢስ_ይጤሳል_›› የተባለው፤ እስራኤላውያን በበረሃ ለ40 ዓመታት ሲጓዙ ደመና እየጋረዳቸው (እየጤሰ) ስለመራቸው ነው፡፡ ‹‹#አጋፋሪ_ይደግሳል_››፤ የተባለው አጋፋሪው /አለቃው/ ቅዱስ ሚካኤል ሲሆን፤ ይደግሳል መባሉ እስራኤላውያንን ‹‹በዕደ መልአኩ ይዕቀበነ ፥ ሰላመ ዚአሁ የኀበነ›› እንዲል፤ በአምላክ ትዕዛዝ ቅዱስ ሚካኤል መናን ከደመናን ፥ ውኃን ከጭንጫ ዓለት እያፈለቀ (እየደገሰ) መርቷቸዋልና ነው፡፡ ****እንዲሁም የአብነት (የቆሎ) ተማሪዎች በክረምት ሲለምኑ የቆዩትን አጠራቅመው፤ የደብረ ታቦር ዕለት ብርሃነ መለኮቱን የገለጠ ጌታ ለኛም እንዲገልጥልን ብለው፤ ደግሰው ለሕዝቡ ያበላሉ ፥ ያጠጣሉ፡፡ /ይህ ሥርዐት በደብራችንም የሚከናወን ድርጊት ነው፡፡/ ‹‹#ያችን_ድግስ_ውጬ_ውጬ_››፤ የተባለውና በድግስ የተመሰለው መና ሲሆን፤ በደጋሹ ቅዱስ ሚካኤል አማካይነት እስራኤል 40 ዓመታት መመገባቸውን (መና መዋጣቸውን) መናገር ነው፡፡ ‹‹#ከድንክ_አልጋ_ተገልብጬ_›› ፤ ድንክ አልጋ የምትመች እንደሆነች ሁሉ ፥ በድንክ የምትመሰለውንና የምትመቻቸውን ተስፋዪቱ ምድር ኢየሩሳሌምን መውረሳቸው መናገር ነው፡፡ ‹‹#ያቺ_ድንክ_አልጋ_አመለኛ_፥ #ያለአንድ_ሰው_አታስተኛ_››፤ መባሉ እስራኤል ከግብጽ ሲወጡ 600,000 ሆነው ሲሆን፤ ሁሉም በምድረ በዳ አልቀው ኢየሩሳሌምን የወረሳት ሴትና ሕፃናት ሳይቈጠሩ፤ አንድ ኢያሱና አንድ ካሌብ ናቸው ለማለት ነው፡፡ ፠፠፪ኛ ፠፠ አጋፈረ፤ግስ ሲሆን በቤተ መንግሥት ፥ በግብዣ ቦታ፥ …. በር ላይ ቆሞ የሚገባውንና የሚወጣውን ሰው አስተናበረ አስተናገደ፡፡ *አጋፋሪ፤ ቅጽል ሲሆን፤ ቃሉ የቀድሞ አማርኛ ሲሆን አስተናባሪ (ብዙውን ጊዜ በግብዣ ወይም በቤተ መንግሥት በር ላይ በመቆም ሥርዐት የሚያስከብር ማለት ነው፡፡ *አጋፋሪ፤ የድግስ አለቃ ፥ አስተናጋጅ ነገሥታት ግብር ሲያገቡ (ግብዣ ሲጋብዙ ፥ ድግስ ሲደግሱ) ወደ አዳራሹ (ወደ ድግሱ) እንዲገቡ የሚፈቅድ ፥ የማይገባቸውንም የሚከለክል፤ ከገቡም በኋላ እንደ የክብራቸውና እንደየማዕርጋቸው አንተ በዚህ ሁን ፥ አንተ በዚህ ተቀመጥ እያለ የሚያስቀምጥ፤ ኋላ የድግሱ ምግብና መጠጥ መታደል ሲጀምርም፤ እንጀራና ጠጅ አሳላፊዎችን የሚያዝና የሚቈጣጠር ትልቅ ሹም ነው፡፡ * አጋፋሪ፤ የሚለው መጠሪያ በ17ኛወና በ18ኛው ክፍለ ዘመን የታወቀ የቤተ መንግሥት ሹም መጠሪያ ነው፡፡ ‹‹ህዱግ ራስ›› በመባል የሚታወቅም ነው፤ በቤተመንግሥት የሚካሄዱ ሥራዎችንና የፍርድ ሂደቶች ያስተባብራል፤ አንዳንዴ ደግሞ የክፍላተ ሃገር የፍርድ ሰጪ ሰዎች ስም ሆኖም ያገለግላል፤ የስሜን (ከጎንደር በስተሰሜን የሚገኝ ግዛት ነው) አስተዳደር የሚገዛ ሰው ደግሞ የሰሜን አጋፋሪ እየተባለም ይጠራል፤ (ለምሳሌም አፄ ሱስንዮስ ልጃቸውን ፋሲለደስን የስሜን አጋፋሪ ብለው ሹመወት ነበር፤ ይህ የስሜን አጋፋሪ የሚለው ሹመትም እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ቆይቶ ነበር፡፡ #ቡሄ_፤ ቡሄ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጸበት የነሐሴ 13 ቀን መጠሪያ ስሙ ነው የሚሉ ሊቃውንት እንዳሉ ሁሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፤ ቡሄ የሚባለው፤ ከነሐሴ 13 በኋላ እስከ መስከረም 17 መስቀል ድረስ ሲሆን፤ በተለይም ይህ በዓል የሚታወቀው በሸዋና ወሎ /እስከ ጋይንት ጫፍ መጋጠሚያ) ድረስ ሲሆን፤ በዚህ ወቅትም ክርስትና አባት ለክርስትና ልጁ ተማሪ ከሆነ መጻሕፍትን (ዳዊት፣ …)፣ እንዲሁም አልባሳትን፣ በግና ሙክት ፍየልን የሚሰጥበት ነው፡፡ ሕፃናትና ወጣቱም ‹‹ቡሄ ፥ ሆ ….. ›› እያለ ይጨፍራል ፤ የሚሰጠውንም ሙክትና በግ እስከ መሰቅል ድረስ ሲያጠራቅም ከርሞ ለመስቀል ዕለት አርዶ ይበላል ፥ ደስታን ያደርጋል፡፡ ምንጭ፤ የቃል ትምህርት /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ዜና_እረፍት_ ‹‹ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል፡፡›› ሲራክ 38፥26 #የሰ/ት/ቤታችን#አባል_ንጉሤ_አወቀ_ያገለግለው_የነበረው_መድኀኔ_ዓለም_ጠርቶት_ስላረፈ_፤ #የምሽት_መርሐ_ግብር_እሑድ_ነሐ
#ዜና_እረፍት_ ‹‹ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል፡፡›› ሲራክ 38፥26 #የሰ/ት/ቤታችን#አባል_ንጉሤ_አወቀ_ያገለግለው_የነበረው_መድኀኔ_ዓለም_ጠርቶት_ስላረፈ_፤ #የምሽት_መርሐ_ግብር_እሑድ_ነሐሴ_2_ከምሽቱ_12_ሰዐት_ላይ_ይካሄዳል_፡፡ #ቤቱ_2ኛው_መንገድ_ከሚሲዮን_ት/ቤት_ገባ_ብሎ_፡፡ ፠ወንድማችን አወቀ ንጉሤ፤ ከ2001-2003 ዓ.ም. በሰ/ት/ቤታችን ይሰጥ የነበረውን የሦስት ዓመታት ተከታታይ ትምህርት የተማረ ሲሆን፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ደግሞ በሰ/ት/ቤታችን ታሪክ ወደ ራብዓይ ክፍል በ2004ዓ.ም. ከተሸጋገሩ 19ኝ የተከታታይ ትምህርት (Course) ተማሪዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ፠ወንድማችን በኪዳን ተአምራት ምንባብ ጊዜ ተዓምራትን በማሳለም፤ በቅዳሴ ጊዜ የቅዳሴ ጠበል ለምዕመናን በማድረስ የሚያገለግለን ወንድማችን ነው፡፡ ፠በጾመ ፍልሰታ ወቅት ዘወትር የሚያገለግለውን ግልጋሎት እስከ ነሐሴ 5 ሲሰጥ ቆይቶ፤ ሰኞ ነሐሴ 6 ወደ ጅሩ ቅድስት አርሴማ ገዳም ሄዶ ሥጋ ወደሙን ተቀበለ (ቈረበ)፤ በዚያው ገዳም 3ት ቀናትን ከቆየ በኋላ ኀሙስ ነሐሴ 9 ከሰዐት ላይ አረፈ፤ እዚያ ገዳም ያረፈ ሰው እዚያው ግብዐተ መሬት የሚከናወንለት ቢሆንም ገዳማውያን አባቶችን በማስፈቀድ ወደ አዲስ አበባ ሌሊቱን አስከሬኑ ተመልሷል፤ በነጋታውም ዐርብ ነሐሴ 10/2011 ዓ.ም. ከ9-10 ሰዐት፤ ከልጅነቱ ጀምሮ ዕለት ዕለት በተማረበትና በተለያዩ ግልጋሎት ባገለገለበት በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ ሥርዐተ ግብዓተ መሬቱ ተፈጽሟል፡፡ ‹‹ወእመኒ ሐየውነ ለእግዚአብሔር ነሀዩ፤ ወእመኒ ሞትነ ለእግዚአብሔር ንመውት፡፡ /በሕይወት ብንኖር ለእግዚአብሔር እንኖራለን፤ ብንሞትም ለእግዚአብሔር እንሞታለን›› ሮሜ. 14፥17 (የቀ/ደ/ሰ/መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍ/ሕ/ሰ/ት/ቤት::)

፩ ቀን ቀረው በ1966ዓ.ም. አገልግሎቱን ለጀመረው አንጋፋ ቤተ መጻሕፍታችን መጻሕፍትን የምናሰባስብበት ልዩ መርሐ ግብር ነሐሴ 11፤ ከ11፡30 - 2፡00 ፩ ቀን ቀረው ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያ
፩ ቀን ቀረው በ1966ዓ.ም. አገልግሎቱን ለጀመረው አንጋፋ ቤተ መጻሕፍታችን መጻሕፍትን የምናሰባስብበት ልዩ መርሐ ግብር ነሐሴ 11፤ ከ11፡30 - 2፡00 ፩ ቀን ቀረው ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያናችን ድንቅና ዕንቊ የሆኑ ፭ት መጻሕፍትን ደርሶ አብርክቶልናል እኛስ ለቤተ መጻሕፍቶቻችን ምን ያህል መጻሕፍት አስተዋጽዖ አድርገናል፡፡ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡

#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_#ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ዘነሐሴ_፲_ማኀበረ_በኵር_ወመጥራ_ሰማዕት_ወሐርስጥፎሮስ_ወቢካቦስ_ወዮሐንስ_፡፡ #የቅዳሴ_ምንባባት † ዕብ.፲፪፥፳፪-ፍጻ ወአንትሙሰ በጻሐክሙ ኀበ ጽዮን
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_#ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ዘነሐሴ_፲_ማኀበረ_በኵር_ወመጥራ_ሰማዕት_ወሐርስጥፎሮስ_ወቢካቦስ_ወዮሐንስ_፡፡ #የቅዳሴ_ምንባባት † ዕብ.፲፪፥፳፪-ፍጻ ወአንትሙሰ በጻሐክሙ ኀበ ጽዮን፡፡ † ፩ኛ ጴጥ.፩፥፮-፲፫ ወባሕቱ ኀዳጠ ይእዜ ሀለውክሙ:: † የሐዋ.፬÷፴፩-ፍ ወእንዘ ይጼልዩ አድለቅለቀ ውእቱ መካን፡፡ #ምስባክ_መዝ. ፸፫፥፪ ተዘከር ማኀበረከ ዘአቅድምከ ፈጢረ፡፡ ወአድኀንከ በትረ ርስትከ፡፡ ደብረ ጽዮን ዘኀደርከ ውስቴታ፡፡ (ትርጕም፤ አስቀድመህ የፈጠርከውን ምኅበርህን አስብ፡፡ የርስትህንም በትር አዳንክ፡፡ በውስጧ ያደርክ የጽዮን ተራራን፡፡) #ወንጌል_ ሉቃ. ፲፯፥፲፮-፱፤ ወአነሂ እብለክሙ ግበሩ ለክሙ አዕርክተ፡፡ #ቅዳሴ_ዘእግዝእትነ ፤ ጐሣዕ ልብየ ቃለ ሠናየ፡፡

#3ት_ቀናት_ብቻ_ቀሩት!!! ፠#በ1966ዓ.ም.#አገልግሎቱን_ለጀመረው_አንጋፋ_ቤተ_መጻሕፍታችን #መጻሕፍትን_የምናሰባስብበት_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠#ቅዱስ_ያሬድ_ለቤተ_ክርስቲያናችን_ድንቅና_ዕንቊ_የሆኑ_5ት_መጻሕፍትን_ደርሶ_አብርክቶልናል_እኛስ_ለቤተ_መጻሕፍቶቻችን_ምን_ያህል_መጻሕፍት_አስተዋጽዖ_አድርገናል_??፡፡ ፠ የመጨረሻ መርሐ ግብሩ #ቅዳሜ_ነሐሴ_11_ቀን_2011_ዓ.ም. ከ11፡30 - 2፡00 ላልሰሙት ያሰሙ፤ <<Like, Share>> በማድረግ ይተባበሩ

#ክርስቲያን_እንኾን_ዘንድ_እመቤታችንን_እናንብባት_እንማርባትም_ክፍል_፪:: ፠#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_እጅግ_ትሑት_ነች_፡፡ ትንቢተ ኢሳይያስን ስታነብና “ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች” በሚለው አንቀጽ ስትደርስ “ምነው እኔ በኾንኩኝ?” አላለችም፤ “ምነው በዘመኗ ደርሼ ይኽቺን ድንግል ባገለገልኳት?” አለች እንጂ፡፡ መልዐኩ “ተፈስሒ” ሲላት “ይገባኛል” አላለችም፤ “ነየ አመተ እግዚአብሔር - የእግዚአብሔር ገረዱ እነሆኝ” አለች እንጂ /ሉቃ.፩፡፴፰/፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ “የጌታዬ እናቱ እመቤቴ ወደኔ ትመጭ ዘንድ እኔ ምንድነኝ?” ስትላት “ልክ ነሽ፤ ይደልወኒ - ይገባኛል፤ አምላክን ፀንሻለኹና” አላለችም፤ “የባርያይቱን ውርደት ተመልክቷልና” አለች እንጂ፡፡ ብትል እኮ ያምርባታል፡፡ ነገር ግን አላለችም፡፡ ምንም ሳንሠራ “ይገባኛል” የምንል የማን ልጆች እንኾን? እመቤታችን ኤልሳቤጥ እንዳረገዘች ሰምታ ትጠይቃት ዘንድ መሔዷ የትሕትናዋን ጥልቀት ያሳያል፡፡ ለልማዱ ባርያ ወደ ጌታው ይሔዳል፡፡ አኹን የኾነው ግን እንዲኽ አይደለም፡፡ የመጣችው ኤልሳቤጥ አይደለችምና፤ ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ሔደች እንጂ፤ ያውም በዚያ ተራራማው ስፍራ፡፡ የእመቤታችን ትሕትናዋ ግሩም ነው፡፡ ትሕትና ሰዎችን አማልክት ዘበጸጋ ታደርጋለች፤ ትዕቢት ደግሞ ቅዱሳን መላዕክትን ታዋርዳለች፡፡ ትዕቢት እጅግ ክፉ ነው፡፡ ትዕቢት ሰዎች ከተለመደው ባሕርያቸው አስወጥቶ ያደነዝዛቸዋል፤ የስንፍናን ካባ ያጐናጽፋቸዋል፡፡ ትዕቢት እንደ ዕብድ ያናግራል፡፡ አንድ ሰው ቁመቱ ሦስት ክንድ ከስንዝር ቢኾን እንኳን ትዕቢቱ ተራራን ያሳክሏል፤ ተራራን ባያክልም እንደዚያ እንደኾነ እንዲያስብ ያደርጓል፡፡ ትዕቢት ከዕብደት የከፋ በሽታ ነው፡፡ ምክንያቱም ትዕቢት በእኛ ፈቃድ የሚይዘን በሽታ ሲኾን ዕብደት ግን ሳናውቀው ሊይዘን የሚችል የጤና እክል ነውና፡፡ ወዮ! መቼ ይኾን ከዚኽ በሽታ የምንላቀቀው? ፠#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_እጅግ_የምታምንና_ታዛዥ_ነበረች_፡፡ ሕይወቷ ኹሉ “ይኵነኒ በከመ ትቤለኒ - እንደ ቃልኽ ይደረግልኝ” በሚል የተመላ ነው፡፡ ወላጆቿ ለቤተ እግዚአብሔር ቢያስረክቧት “ይኵነኒ”፤ ካህናት “ቤተ መቅደሳችንን ታረክስብናለች” ብለው ቢያስወጧት “ይኵነኒ”፤ “በድንግልና ፀንሰሽ በድንግልና ትወልጃለሽ” ስትባል “ይኵነኒ”፤ “ከሦስቱ ቅዱስ አንዱን ቅዱስ በበረት ትወልጂዋለሽ” ስትባል “ይኵነኒ”፤ “የስዱዳን ተስፋቸውን አዝለሽ ትሰደጃለሽ” ስትባል “ይኵነኒ”፤ ሽፍቶች ቢያስደነግጧት “ይኵነኒ”፤ ማየ ሕይወትን አዝላ ውኃ ቢጠማት አንድም ልጇ ቢጠማው “ይኵነኒ”፤ አባቶቿ ፵ ዓመት የፈጀባቸውን መንገድ በልጅነት ዕድሜዋ “ልጅ አዝለሽ ትሔጃለሽ” ስትባል “ይኵነኒ”፤ “ሄሮድስ ሞቷልና ተመለሺ” ስትባል “ይኵነኒ”፤ አንዱን ልጇ ሲያሰቃዩባት ሲገርፉባትና ሲገድሉባት “ይኵነኒ”፡፡ ታዛዥነቷ ከአዕምሮ የሚያልፍ ነው፡፡ ሄሬኖዎስ የተባለው ቅዱስ አባት የእመቤታችንን ታዛዥነት ለምን እንደኾነ ሲያስተምር እንዲኽ አለ፡- “እነሆ ጌታ የራሱ ወደኾኑት በግልጥ (በለቢሰ ሥጋ) መጣ፡፡ ትዕዛዙን ተላልፎ በዕጽ የሞተውን አዳም በዕጽ ላይ ታዝዞና ካሣውን ከፍሎ፣ ወደ ጥንተ ተፈጥሮው ይመልሰው ዘንድ በራሱ ጥበብ ከፍጥረቱ ተወለደ፡፡ ለአንድ ወንድ የታጨችው ድንግል በምክረ ከይሲ ያመጣችውን ያለመታዘዝ ኃይል የእውነት መልዐክ ለአንድ ወንድ ለታጨችው ድንግል ባበሠራት ጊዜ ፈራረሰ፡፡ ቀዳማይቱ ሔዋን ከእግዚአብሔር እንድትርቅና ቃሉን እንድትቃወም ክፉ መልዐክ አታለላት፡፡ ዳግማይቱ ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን ደጉ መልዐክ ይዞት የመጣው መልካሙን ዜና እንድትቀበለውና እግዚአብሔርን በከዊነ ቃሉ እንድትወልደው አመነች፡፡ ቀዳማይቱ ሔዋን እግዚአብሔርን እንዳትታዘዘው ክፉ መልዐክ አታለላት፤ ወደቀችም፡፡ ዳግማይቱ ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን እግዚአብሔርን እንድትታዘዝ ቅዱስ መልዐክ አሳመናት፤ ርሷም ሔዋንን ረዳቻት፡፡ ነገደ አዳም በአንዲት ድንግል አለመታዘዝ ምክንያት ሞት ተፈረደበት፣ ኾኖም በሌላይቱ ድንግል መታዘዝ ምክንያት ዳነ፡፡” በሕይወታችን “ይኵነኒ” ማለትን መልመድ ጸጋ እግዚአብሔርን በሕይወታችን ማትረፍረፍ ነው፡፡ እንላለን ወይ ነው ቁምነገሩ? እግዚአብሔርን የሚጋርዱብን ነገሮች (ለምሳሌ ሥራ፣ ውበት፣ ሥልጣን፣ ሀብት፣…) ከሕይወታችን ይወገዱ ብንባል “ይኵነኒ” ለማለት ምን ያኽል ዝግጁዎች ነን? ፠#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_ርኅሪኅተ_ኅሊና_ናት_፡፡ እጅግ አዛኝ እናት!!! ሊቃውንት እንደሚያስተምሩት ምኅረት (ምጽዋት) ሦስት ዓይነት ነው፡፡ ምኅረት ሥጋዊ፣ ምኅረት መንፈሳዊና ምኅረት ነፍሳዊ፡፡ ምኅረት ሥጋዊ የታረዘን ማልበስ፣ የተራበን ምጉረስ ነው፡፡ ምኅረት መንፈሳዊ የተጨነቀን ወይም ያዘነን ሰው መርዳት፣ ወይም ማጽናናት ነው፡፡ ምኅረት ነፍሳዊ ደግሞ ሰዎች የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኙ መርዳት ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰውስ ይቅርና ለተጠማ ውሻም ሳይቀር በወርቅ ጫማዋ ውኃን ያጠጣች ርኅርኅተ ኅሊና ናት፤ ምኅረት ሥጋዊ፡፡ እናቶቻችንን በምጥ ጊዜ እንዴት እንደምትረዳቸው መናገርም ለቀባሪ ማርዳት ነው፤ ምኅረት መንፈሳዊ፡፡ ክርስቲያን፥ በተለይ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ክርስቲያን ኾኖ ከእመቤታችንን ርኅራኄ (ምልጃና ቃል ኪዳን) ያልቀመሰ የለም፤ ምኅረት ነፍሳዊ፡፡ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም በቅዳሜ ውዳሴው ላይ “የዚኽ ዓለም ሰዎች አማልዱኝ ቢሏቸው ነገር አጽንተው ይመለሳሉ፡፡ ርሷ ግን ማእምንት ሰአሊተ ምኅረት - የታመነች የምሕረት አማላጅ ናት” ያለውም ስለዚኹ ነው፡፡ እኛስ ምን ያኽል ርኅሩኀን እንኾን? ኧረ በወርቅ ጫማ ቀርቶብን በንጹሕ ሳህን ለመመጽወት ልቡናችን በራራ? ኧረ ለውሻው ቀርቶብን ለሰዉም ባዘንን? የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሕይወት ገና ስንዠምር እንደተናገርነው በሕይወት ዘመን አንብበው የማይጨርሱት እጅግ ትልቅ መጽሐፍ ነውና አንድ ኹለት ብለን መቁጠር አይቻለንም፡፡ ማንበብ ከቻልን ሕይወቷ ለእያንዳንዱ እንቅስቃሴአችን አስተማሪ ነው፡፡ “ማርያም ፊደል ናት ….” ብለን መዘመራችንም ስለዚኹ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ! እንኪያስ የምንዘምር ብቻ አንኹን፤ እናንብባትም ጭምር እንጂ፡፡ የምናነብ ብቻ አንኹን፤ እንለወጥም ጭምር እንጂ፡፡ ማንበቡንማ ዲያብሎስም ያነባል፡፡ እንኪያስ አንብበን እንለወጥና በእውነት የድንግል ልጆች እንኹን፡፡ ይኽን እንድናደርግ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላዕክት ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን ወአሜን፡፡ /ምንጭ፤ ምክረ አበው ቁጥር 5/ /ከጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ የተወሰደ/

#4ት_ቀናት_ብቻ_ቀሩት!!! ፠#በ1966ዓ.ም.#አገልግሎቱን_ለጀመረው_አንጋፋ_ቤተ_መጻሕፍታችን #መጻሕፍትን_የምናሰባስብበት_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠#ቅዱስ_ያሬድ
#4ት_ቀናት_ብቻ_ቀሩት!!! ፠#በ1966ዓ.ም.#አገልግሎቱን_ለጀመረው_አንጋፋ_ቤተ_መጻሕፍታችን #መጻሕፍትን_የምናሰባስብበት_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠#ቅዱስ_ያሬድ_ለቤተ_ክርስቲያናችን_ድንቅና_ዕንቊ_የሆኑ_5ት_መጻሕፍትን_ደርሶ_አብርክቶልናል_እኛስ_ለቤተ_መጻሕፍቶቻችን_ምን_ያህል_መጻሕፍት_አስተዋጽዖ_አድርገናል_??፡፡ ፠ ከነሐሴ 5 እስከ ነሐሴ 11 የመጻሕፍት ሽያጭና የመጻሕፍት ማሰባሰብ ይካሄዳል፡፡ ፠ የመጨረሻ መርሐ ግብሩ #ቅዳሜ_ነሐሴ_11_ቀን_2011_ዓ.ም. ከ11፡30 - 2፡00 ሰዐት በቅዱስ ገብርኤል አዳራሽ ከዝክረ ቅዱስ ያሬድ ጋር ግብሩ አብሮ የመጻሕፍት መምህራንና ተጋባዥ እንግዶች በሚገኙበት ይካሄዳል፡፡ ‹‹ስትመጣ …. ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ፡፡›› **ቤተ መጻሕፍታችንን ልዩ ከሚያደርጉት መካከል ማኅበረ ምዕናንንና ማኅበረ ካህናትን ታሳቢ አድርጎ የተደራጀ መሆኑ ነው፡፡ ላልሰሙት ያሰሙ፤ <<Like, Share>> በማድረግ ይተባበሩ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት::

#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ዘነሐሴ_፰_ ፠#አልዓዛር_ወሰሎሜ_ብእሲቱ_ወውሉዱ#፯ቱ_ወአሞን_፡፡ #የቅዳሴ_ምንባባት † ሮሜ ፱፥፳፬-ፍጻ ፤ ወንሕነ እሙንቱ እለ ጸውዐነ ውስተ ክብሩ፡፡
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ዘነሐሴ_፰_ ፠#አልዓዛር_ወሰሎሜ_ብእሲቱ_ወውሉዱ#፯ቱ_ወአሞን_፡፡ #የቅዳሴ_ምንባባት † ሮሜ ፱፥፳፬-ፍጻ ፤ ወንሕነ እሙንቱ እለ ጸውዐነ ውስተ ክብሩ፡፡ † ፩ኛ ጴጥ.፬፥፲፪-ፍ ፤ አኃዊነ ኢታንክርዋ ልእንተ ትመጽአክሙ:: † የሐዋ.፲፮÷፴፭-ፍ ፤ ወጸቢሖ ለዐኩ መኳንንት፡፡ #ምስባክ_መዝ. ፶፯፥፰ ወድቀት እሳት ወኢርኢክዋ ለፀሐይ፡፡ ዘእንበለ ይትዐወቅ ሦክክሙ ሕለተ ኮነ፡፡ ከመ ሕያዋን በመዓቱ ይውኀጠክሙ፡፡ (ትርጕም፤እሳት ወደቀች ፀሐይንም አላየኋትም፤ እሾኻችሁ ሳይታወቅ በትር ሆነ፤ሕያዋን ሳላችሁ በመዓቱ ይውጣችኋል፡፡) ማቴ.፯፥፲፪-፳፮ ፤ ኵሎኬ ዘትፈቅዱ ይገበሩ ለክሙ ሰብእ፡፡ #ቅዳሴ_ዘእግዝእትነ ፤ ጐሣዕ ልብየ ቃለ ሠናየ፡፡

#5ት_ቀናት_ብቻ_ቀሩት ፠በ1966ዓ.ም. አገልግሎቱን ለጀመረው አንጋፋ ቤተ መጻሕፍታችን #መጻሕፍትን_የምናሰባስብበት_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠#ቅዱስ_ያሬድ_ለቤተ
+1
#5ት_ቀናት_ብቻ_ቀሩት ፠በ1966ዓ.ም. አገልግሎቱን ለጀመረው አንጋፋ ቤተ መጻሕፍታችን #መጻሕፍትን_የምናሰባስብበት_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠#ቅዱስ_ያሬድ_ለቤተ_ክርስቲያናችን_ድንቅና_ዕንቊ_የሆኑ_5ት_መጻሕፍትን_ደርሶ_አብርክቶልናል_እኛስ_ለቤተ_መጻሕፍቶቻችን_ምን_ያህል_መጻሕፍት_አስተዋጽዖ_አድርገናል_??፡፡ ፠ ከነሐሴ 5 እስከ ነሐሴ 11 የመጻሕፍት ሽያጭና የመጻሕፍት ማሰባሰብ ይካሄዳል፡፡ ፠ የመጨረሻ መርሐ ግብሩ #ቅዳሜ_ነሐሴ_11_ቀን_2011_ዓ.ም. ከ11፡30 - 2፡00 ሰዐት በቅዱስ ገብርኤል አዳራሽ ከዝክረ ቅዱስ ያሬድ ጋር ግብሩ አብሮ ታላላቅ የመጻሕፍት መምህራንና ተጋባዥ እንግዶች በሚገኙበት ይካሄዳል፡፡ ‹‹ስትመጣ …. ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ፡፡›› **ቤተ መጻሕፍታችንን ልዩ ከሚያደርጉት መካከል ማኅበረ ምዕናንንና ማኅበረ ካህናትን ታሳቢ አድርጎ የተደራጀ መሆኑ ነው፡፡

/ከጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ የተወሰደ/

#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፯#ምስባኩ_ከድምፅ_ጋር_ #ነሐሴ_፯_ፅንሰታ_ለማርያም_ወተስእሎተ_ቂሣርያ_ወጢሞቴዎስ_ሊቀ_ጳጳሳት_ወልደቱ_ለዮሴፍ_ወልደ_ራሄል_ወናዖድ_ንጉሠ_ኢትዮጵያ_ #የቅዳሴ_ንባብ ፠† ዕብራ. ፱፥፩- ፲፯፤ ወለቀዳሚትኒ ደብተራ፡፡ ፠ † ፩ኛጴጥ.፪፥፮-፲፰፤ እስመ ከመዝ ጽሑፍ ናሁ እሠይም፡፡ ፠ † የሐዋ.ሥ.፲፥፩-፴፤ ወሀሎ ፩ዱ ብእሲ በሀገረ ቂሣርያ፡፡ #ምስባክ_መዝ. ፺፫፥፲፪ ብፁዕ ብእሲ ዘአንተ ገሠጽኮ እግዚኦ፡፡ ወዘመሀርኮ ሕገከ፡፡ ከመ ይትገኀሥ እመዋዕለ እኩያት፡፡ (ትርጕም፤ አቤቱ አንተ የገሠጽከው ሰው ብፁዕ ነው፤ ሕግህንም ያስተማርሀው፤ ከክፉዎች ዘመናት ይርቅ ዘንድ፡፡) #ወንጌል_ማቴ.፲፮፥፲፫-፳፬፤ ወበጺሖ ኢየሱስ ብሔረ ቂሣርያ፡፡ #ቅዳሴ_ዘእግዝእትነ_ጐሣዕ_ልብየ_ቃለ_ሠናየ #ነሐሴ_ሰባት_ጽንሰታ_ለማርያም_ድንግል፤ #ክፍል_፩_ የዓለም ኹሉ ደስታን ወዳመጣችው ዕለት አደረሳችኁ፤ አደረሰን፡፡ ነሐሴ ሰባት ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትኾን ንጽሕተ ንጹሐን፥ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከአባቱ ከኢያቄምና ከእናቷ ሐና የተፀነሰችበት ዕለት ነው፡፡ ይኽቺን ዕለት ያልናፈቀ ትውልድ የለም፡፡ ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ ለኾነባቸው ቅዱሳን አበው ወእማት ተስፋቸው የሚፈጸመው በዛሬው ዕለት በተጸነሰችው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ነውና፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችንም ከፈጣሪያችን እግዚአብሔር ቀጥሎ ከፍጥረታት እንደ እመቤታችን ከፍ ከፍ የምታደርገው ፍጥረት የሌለው ስለዚኹ ነው፡፡ መትሕተ ፈጣሪ፥ መልዕልተ ፍጡራን፤ (ከፈጣሪ በታች ፥ ከፍጡራን በላይ) ናትና፡፡ ሊቃውንቱ፤ “ሐና አንቺን የጸነሰችበት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤” ብለው የሚዘምሩላትም ይኽን ምሥጢር በልቡናቸው ቋጥረው ነው /አባ ጽጌ ድንግል፤ ማኅሌተ ጽጌ ቁ.፵፬/፡፡ ስለ እመቤታችን ከመናገር በላይ እመቤታችንን ለመምሰል እንደ ዓቅሚቲ መጣጣር የተሻለ ዋጋ አለው ማለት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ” እንዳለን ስለ ቅዱስ ጳውሎስ ከመተረክ በላይ ቅዱስ ጳውሎስን ለመምሰል ልንተጋ ያስፈልጋል ማለት ነው፡፡ “ቅዱሳን አባቶቻችን መጽሐፍ ቅዱሱን በአንድ ወገን፤ የትርጓሜ መጻሕፍትን በአንድ ወገን፤ የገድላትና የድርሳናት መጻሕፍትንም በሌላ ወገን አድርገው በብልት በብልት ከፋፍለው ያስቀመጡልን የድኅነት መንገድን ለማስረዘም አይደለም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ያለውን እንድናነበው፤ ቢጸንብን በትርጓሜያት እንድንረዳው፤ በገድላቱና በድርሳናቱ ደግሞ እንደምን ተግባራዊ እንደሚኾን እንድንገነዘበው እኛም በዚያ ሕይወት ለመመላለስ እንድንጣጣር ነው እንጂ፡፡” እውነት ነው!!! የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሕይወት በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በአንድምታ ትርጓሜያትና በተለያዩ ድርሳናትና ተአምራት ተከፋፍሎ መቅረቡም ለዚኹ ዓላማ ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አንብበው የማይጨርሷት እጅግ ትልቅ መጽሐፍ ናት፡፡ ከአዕምሮ በላይ የኾነ፥ ግን ደግሞ የተፈጸመ ሕይወቷን ስናነበው የእኛንም ሕይወት ስናየው፥ “የእመቤታችን አምላክ ሌላ ነው እንዴ?” ያስብላል፡፡ እስኪ ለማንኛውም ምንም እንደ ርሷ ባንኾንም የዓቅማችንን ያኽል ክርስቲያን እንኾን ዘንድ እመቤታችንን እናንብባት፤ እንማርባትም፡፡ ፠#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያምን_የሚያክል_ንጹሕ_ፍጥረት_በሰማይም_በምድርም_ፈጽሞ_የለም_፡፡ እግዚአብሔር አብ በሰማያት ኾኖ ምሥራቁንና ምዕራቡን፣ ሰሜኑንና ደቡቡን ቢመለከት እንደ እመቤታችን ያለ ንጹሕ ፍጥረት አላገኘም፡፡ ንጽሕናዋ ልዩ ነው፡፡ “ወኢረኵሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ ድንግል በኅሊናሃ ወድንግል በሥጋሃ - ከፈጠራት ዠምሮ በምንም በምንም ከድንጋሌ ሥጋ ከድንጋሌ ነፍስ አልተለወጠችም (አልበደለችም)” /ሃይ.አበ. ዘቴዎዶጦስ ፶፫፡፳፪/፡፡ ምንም ኀጢአት በሌለበት በሰማይ ለመላዕክት ያልተቻላቸውን ንጽሕናና ቅድስና፥ እመቤታችን እንደ ባሕር አሸዋ እንደ ሰማይ ከዋክብት በደል በበዛበት ዓለም ኾና ኑሯለች፡፡ እኛ የተቸገርነው ፈቃዳችንን እንደ እመቤታችን ለእግዚአብሔር መስጠት ነው፡፡ መለወጥ እንፈልጋለን፤ ፈቃዳችን ግን ከእኛ ጋር ነው፡፡ እመቤታችን ግን ፈቃዷን ሙሉ ለሙሉ ለእግዚአብሔር ያስረከበች ብጽዕት ናት፡፡ ፠#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_የጸሎት_የዝማሬና_የተመስጦ_ሕይወት_ነበራት_፡፡ ዘመዷ ኤልሳቤጥን በጐበኘቻት ጊዜ ያመሰገነችውን ምስጋና ስንመለከት ይኽን እውነት ፍንተው አድርጐ ያሳየናል፡፡ ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ሲበተኑ የእመቤታችን ተግባር እነርሱን በጸሎቷ መርዳት ነበር፡፡ ክንፍ የሌላት ወፍና የጸሎት ሕይወት የሌለው ክርስቲያን አንድ ናቸው፡፡ ጸሎትና እመቤታችን ግን ለቅጽበት ስንኳ ተለያይተው የማያውቁ ወዳጆች ናቸው፡፡ የእመቤታችንን የተመስጦ ሕይወት ስናነብ ደግሞ እጃችንን በአፋችን እንጭናለን፡፡ “ማርያምሰ ተዓቅብ ዘንተ ኵሎ ነገረ ቀትወድዮ ውስተ ልባ እመቤታችን ግን ይኽን ነገር ታስተውለው ነበር፤ በልቡናዋም ታኖረው ነበር” እንጂ ለሰው አታወራውም ነበር፡፡ የቆጵሮሱ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ፤ “የምትናገረው በጣም ጥቂት ሲኾን ርሱም ለማድረግ አስፈላጊ በሚኾንበት ብቻ ነበር” ይላል፡፡ ፠#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_ቃለ_እግዚአብሔርን_ዕለት_ዕለት_የምታነብ_ነበረች፡፡ “ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም” ተብሎ እንደተጻፈ ቃለ እግዚአብሔር የዕለት ተዕለት ምግቧና መጠጧ ነበር፡፡ በሉቃ.፩፡፵፯-፶፭ በምናነበው ድንቅና ጥልቅ ምስጋናዋ ላይ የምናስተውለው ነገር ቢኖር ምን ያኽል ቅዱሳት መጻሕፍትን እንደምታነብና እንደምታውቅ ነው፡፡ ማወቅ ብቻ አይደለም፤ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴዋ ትጠቀምበት ነበር፡፡ መልዐኩ መጥቶ “ትፀንሲ” ሲላት “እም አይቴ ረከብከ ዘከመዝ ብሥራት ዘእንበለ ምት እም ድንግል ፅንሰት ወዘእንበለ ዘርዕ እምድር እትወት - ምድር ያለ ዘር ታፈራ ዘንድ ሴት ያለ ወንድ ትፀንስ ዘንድ እንዲኽ ያለ የምሥራች ከማን አገኘኸው?” ያለችው ተሰምቶም ታይቶም የማይታወቅ ስለኾነ ነው፡፡ አንድ እንግዳ ነገር በሕይወታችን ሲመጣ እውነትነቱን የምንመዝነው በቃሉ ነው፡፡ ምክንያቱም ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ሲባል ከቃሉ ባለቤት ከእግዚአብሔር ጋር መጨዋወት መነጋገር ማለት ነውና፡፡ እግዚአብሔርም ለዚያ ቃሉን ለሚያነብ ሰው ፈቃዱ ምን እንደኾነ ይገልጥለታልና፡፡ ለዚኽም ነው ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲኽ በማለት የሚመክረን፡- “ዕለት ዕለት ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚያነብ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ መጻሕፍትን የማያነቡ ብዙ ሰዎች ሕገ እግዚአብሔርን ካለማወቅ የተነሣ ክሕደት የተባለ ክፉ ልጅን ወልደዋልና፡፡ ኃጢአት የተባለ ክፉ ዛፍም ዳግም በተወለደው ሰውነታቸው ላይ አብቅለዋልና፡፡ ደጋግመው ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚያነቡ ግን ቢወድቁ እንኳ ተመልሰው ይነሣሉ፡፡ ልጆቼ! እናንተም ቅዱሳት መጻሕፍትን ከማንበብ ቸል አትበሉ፡፡ በጣም ተቸግራችኁ ለተከታታይ ዐሥር ቀናት ብቻ ይኽን ብትለማመዱት ከዚያ በኋላ ልምድ ይኾንላችኋል፡፡ በርግጥ ይኽ ልምምድ ለንባብ ብቻ ሳይኾን ለሌላ መንፈሳዊ ሕይወታችኁም ብትጠቀሙበት መልካም ነው፡፡” ተንቀሳቃሽ ስልካችንን ከቤት ረስተነው ወደ ሥራ ቦታ ብንሔድ ምን ይሰማናል? ቃሉን ስንረሳውስ? /…. ክፍል ፪ን ነገ ይጠብቁ/ /ምንጭ፤ ምክረ አበው ቁጥር 5/