es
Feedback
አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ)

አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ)

Ir al canal en Telegram

የሰው ልጅ ልብ ነው የገጣሚ ሀገር...! @Run_Viva_Run

Mostrar más
2 459
Suscriptores
Sin datos24 horas
+57 días
-2330 días
Archivo de publicaciones
Abrham F. Yekedas @HAKiKA1
Abrham F. Yekedas @HAKiKA1

Cochill Event Night @HAKiKA1
Cochill Event Night @HAKiKA1

የቀሬናው ስምዖን ድንገት በመንገዱ ከክፉ ቀን ግማሽ ከደግ ቀን በአንዱ ሄዶ ተረማምዶ መንገዱን ሳይጨርስ ተብሎ ተጎተተ "ና... ይሄን ሰው አግዝ" አቅማምቶ ተጠጋ ከአንድ ምስኪን ገላ ደም ከለዋወሰው
የቀሬናው ስምዖን ድንገት በመንገዱ ከክፉ ቀን ግማሽ ከደግ ቀን በአንዱ ሄዶ ተረማምዶ መንገዱን ሳይጨርስ ተብሎ ተጎተተ "ና... ይሄን ሰው አግዝ" አቅማምቶ ተጠጋ ከአንድ ምስኪን ገላ ደም ከለዋወሰው በአዳናቸው ሳይሆን በሚገርፉት ብቻ በተከበበ ሰው ግማደ መስቀሉን እንደቻለው አቅም አብሮ ተሸክሞ ከባለ ፍዳው ጋር ገፍቶ ያንን ዳገት... ወጣ ቀራንዮ ተመልከት እንዲ ነው አንዳዴ የህይወት ጎዳና የግድ ተጎትተህ ድንገት ከመከራው ገፈት ትቀምስና ካሰብከው ዘግየተክ ከአለምከው አርፍደህ መድረሻህ ይርቃል ለፅድቅ መታጨትን አንተ አትረዳውም የእግዜር ልብ ግን ያውቃል። እንግዲህ ለባለ መንገዱ ለቀሬናው ስምዖን በገጠመው ሲሳይ በስቃይ እንዲያ መሆን ምን ይሆን ምላሹ ለዚህ ኩነት ምንዳ? አምላኩን ለረዳ... Abrham F. Yekedas @HAKiKA1

📚ለንባብ ወዳጆችና እውቀትን ለሚራቡ ሁሉ! 🔵 በቻናላችን:- 👍ልብ የሚነኩና አስተማሪ ታሪኮች፣ 👍ከታላላቅ መጻሕፍት የተቀነጨቡ ምርጥ ጥቅሶች 👍የሕይወት ስንቅ የሚሆኑ ጠቃሚ ምክሮችን ያገኛሉ።
📚ለንባብ ወዳጆችና እውቀትን ለሚራቡ ሁሉ! 🔵 በቻናላችን:- 👍ልብ የሚነኩና አስተማሪ ታሪኮች፣ 👍ከታላላቅ መጻሕፍት የተቀነጨቡ ምርጥ ጥቅሶች 👍የሕይወት ስንቅ የሚሆኑ ጠቃሚ ምክሮችን ያገኛሉ። አሁኑኑ የንባብ ቤተሰብ ይሁኑ👇 ✅@tibeb145@tibeb145

እንዲ ነበር እንዴ? የእሷነቷ ፊደል ውስጥ ሀሳቧ ሁሉ ያውቅ ነበር ወይ በደል እንዲ ነበር እንዴ? ስቀምሰው የእሷ ጣ'ም (... ገረመቺኝ በጣም) ከሰቀልኳት ሰማይ አራሷን ፈጥፍጣ ከውሸቷ ጭብጥ እውነ
እንዲ ነበር እንዴ? የእሷነቷ ፊደል ውስጥ ሀሳቧ ሁሉ ያውቅ ነበር ወይ በደል እንዲ ነበር እንዴ? ስቀምሰው የእሷ ጣ'ም (... ገረመቺኝ በጣም) ከሰቀልኳት ሰማይ አራሷን ፈጥፍጣ ከውሸቷ ጭብጥ እውነት ተፈልቅቃ እንዳላሰብን በፍቅር የነገን ጎዳና እንዳላወጋነው ስንቱን ቀና ቀና እንዳልታየን ሁሉ የተስፋችን ፋና ዛሬ ሲሆን ባዶ ደርሶ ሲሆን ወና ነገሯ ሲገባኝ..... ከቅኔ ህብረቃል ሰም ወርቋ ሲረዳኝ እኔና እሷ ብዬ ስንቱን እያሰብኩኝ ልብ ልቧን ታይቶኝ እጅግ ተደንቄ ታዝቤያት አበድኩኝ። Abrham F. Yekedas @HAKiKA1

አሁን በቀደም ለት ማጣት አስከፍቶኝ ጭምት ትክዝ አርጎ ከጎዳና ጥሎኝ... አላፊ አግዳሚውን ቁጭ ብዬ እየታዘብኩ አልፎ አልፎ ሲበላኝ ጀርባዬን እያከኩ እንደተኮራመትኩ በተቀመጥኩበት ደስታ ባጣ አርኪ
አሁን በቀደም ለት ማጣት አስከፍቶኝ ጭምት ትክዝ አርጎ ከጎዳና ጥሎኝ... አላፊ አግዳሚውን ቁጭ ብዬ እየታዘብኩ አልፎ አልፎ ሲበላኝ ጀርባዬን እያከኩ እንደተኮራመትኩ በተቀመጥኩበት ደስታ ባጣ አርኪ ሀዘን እንደገባኝ ፊቴ መጣ ድንገት ልጅ እግር ሰባኪ አቋሙን በሚያስንቅ በአስገምጋሚ ድምፁ ፀሀይ በዋለበት በጠቆረ ገፁ መንፈሳዊ ሞራል ባጀገነው አቅም "ገንዘብ ደስታ አይገዛም ንዋይ አያስቅም፤  አታልቅስ በችግር አትሳቅ በጥቅም!" ብሎ አዥጎደጎደው ሰበካውን ሁሉ በቆንጆ ቆንጆ ቃል፤ ሰማሁ ሰማሁና እኔ ምርር ብሎኝ ጮሄ ተናገርኩኝ  የራሴን አባባል... "ስሙኝ ወገኖቼ ከፊሉ ስህተት ነው የዚህ ሰባኪ ቃል፤ በመኖር ኡደት ውስጥ ህይወት ተዘርቶበት        ሰው ለምድር ሲጣል፤ ገንዘብ ደስታ አይገዛም   ነገር ግን...ማጣት ደስታ የሳጣል። አይጣል... (ይሄ ነው እውነታው...) (ስማኝ) ቃሌ "እህ..." አስብሎ ሰሚ ባገኝ ጆሮ ተቸግሬም የሰው ዓይን ባይርቀኝ ኖሮ ስለሌለኝ ብስቅ ማጣት ቢያስደስተኝ እዚ ጎዳና ጥግ ምን አኮራመተኝ? በዝምታ ልኑር አሁን በቃ ተወኝ! ...ተወኝ"            Abrham F.Yekedas @HAKiKA1

"ታውቂያለሽ? ለመጀመሪያ ግዜ ስመለከትሽ የወደድኩልሽ አይንሽን ነው" ፀጉሯን እየነካካሁ ስላት "እኔ ደግሞ ፈለግህን..." አለችኝ። "ፈለግ...ማለት ...?" "ማለትማ የኔ ካጠገቤ ተቀምጠህ እኔ ጎ
"ታውቂያለሽ? ለመጀመሪያ ግዜ ስመለከትሽ የወደድኩልሽ አይንሽን ነው" ፀጉሯን እየነካካሁ ስላት "እኔ ደግሞ ፈለግህን..." አለችኝ። "ፈለግ...ማለት ...?" "ማለትማ የኔ ካጠገቤ ተቀምጠህ እኔ ጎንበስ ብዬ መፅሀፍ እያነበብኩ አልነበር። ወደአንተ ለማየት ዓይኔ ሂደቱን ሲጀምር ከማርያም ጣትህ ነበር፤እዛች ጣትህ ላይ ፈለግ ነበረች..ከጥፍርህ ስር ሆና ከጣትህ ህይወት ተነጥላ ገንጠል ያለች ልውደቅ አልውደቅ የምትል ፈለግ ከዛ ወደድኳትና አንተን ማየት ትቼ ብዕሬን አውጥቼ 'ፈለግ' የሚል ሶስት ገፅ ግጥም ፃፍኩ።" "አይ በጣም ጎበዝ.... ያኔ ጨምድደሽ ስትጥይው ያቀበልኩሽ ወረቀት ስለፈለጌ የፃፍሽው ነው?" " አዎ አንጓው አልጥም ስላለኝ ጣልኩትና ሌላ ጀመርኩ....አቀብለኸኝ በዛው ተግባባኸኝ....ነፍስህ ጥበባዊ ስለሆነ ደስ አልከኝ። ማን አጎንብሶ የወደቀ ያቀብላል?" ምን ማለት እንዳለብኝ ግራ ገብቶኝ... ዝም አልኩ። "ቆይማ ላንብብልህ...?" "ምን..?" "ፈለግን ...." "ፈለግ?...እ ግጥሙን አይ ይቅር እማ ተይ ..... ስንጋባ" ተማፀንኩ። "ውይ ትንሽ እኮ ነው....አስፋፍቼው ስድስት ገፅ ሆኗል እንጂ..." ቦርሳዋን ከፍታ ቀይ አጀንዳዋን ብቅ አደረገችው። እንግዲህ የተቀመጥንበት ካፌ ሊበጠበጥ ነው። "ተይ እማ....ሌላ ቀን ተይ....ይሄን ቀይ አጀንዳ መልሺው ....እያጥወለወለኝ ነው" "አይ እንግዲህ አነብልሃለው... ።...የግጥሜ ርዕስ ፈለግ.... አንቺ የጣት ፈለግ ተበጠሽ ከጣቴ፤ ዝርፍፍ አትበዪ ከማርያሟ ጣቴ፤ ጥፊልኝ ከፊቴ....ከወጣትነቴ..." ''ወይኔ በላቸውውውው.... ምን ብበድል ነው ያንቺ መጫወቻ ያረገኝ።" ከገጣሚ ጋ መፋቀር ትርፉ ይሄ ይሁን በቃ?😒 Abrham F.Yekedas @HAKiKA1

"ቁርስ ምንድነው እማ?" አልኳት....ከተጋባን ጀምሮ ሚስቴን እንዴት 'እማ' ማለት እንደጀመርኩ አላውቅም...ብቻ ከየት እንደሰማሁት እንጃ ምላሴ ላይ ታትሟል። "ፍርፍር ነው አባ..." አለች ከሁለት ክፍል ቤታችን ጓዳ ውስጥ ሆና እያንጎዳጎደች። 'ስትንጎዳጎድ ዶሮ የምትሰራ አትመስልም?' ብሎ ውስጤ ሀሜት ጀመረ። 'ተው እንጂ አብርሃም! ገና በሶስት ወር አፍላ ትዳር ሚስትህን በውስጥህ ልታማት?' ብዬ እራሴን በራሴ ገሰፅኩና ዝም ብዬ ማሰላሰል ጀመርኩ። ' 3 ወር ....90 ቀናት... የመጀመሪያ 10 ቀናት የጫጉላ ሽርሽር ደብረዘይት ሄድን። ምግብ ካረፍንበት ሆቴል ስንበላ ነበር። ከተመለስን በኃላ 10 ቀናት እናቷ ታመው ልታስታምም በመሄዷ ምግብ ውጪ ስበላ ነበር። ከዛ እናቷ ተሽሏቸው ከመጣች በኃላ ለ 70 ቀናት ቁርስ ፍርፍር፣ ምሳ ውጪ፣ እራት ፍርፍር ...እንዴት እንዴት ነው ነገሩ ጎበዝ?.... ትዳሬ ላይ ጥልቅ ተሀድሶ ማድረግ እንዳለብኝ እያሳሰበኝ ውስጤ 'አካሄድ...' አለ። "እ...እማ" አልኩ ውስጤ ፈራ ተባ እያለ "ወዬ አባ..." እሷም አባ ማለት በቅርቡ ያመጣችው ነው። ምን አልባት እኔ 'እማ' ስል ለትክክለኛው አፀፋዊ ምላሽ ብላ ይሆናል። "እንደው ግን ....እንደው... ይሄ ነገር አልበዛም..." "ምኑ...?" ድምፅዋ በጣም ትንሽ የሆነ መጠነኛ ቁጣን አዝሏል። ሌላ ሰው ቢሆን አይረዳውም። ባል በመሆኔ ብቻ የሚገባኝ እኔ ብቻ ነኝ። "ፍርፍሩ.....ጨጓራዬ ተፈረፈረልሽ እኮ....ትንሽ ሌላ ነገር ቀልቀል ብታደርጊስ ካልሆነልሽም በርበሬዋን ቀነስ... አለ አይደል" አልኩ በትህትና እና በቀልድ ለማለዘብ እየሞከርኩ... "ምን?" እያለች ከጓዳ ወጣች። አስተያየቷ ያስፈራል.... ጆሮዋ ላይ ጣል ጣል ካረገቻቸው ሁለት የሽንኩርት ልጣጮች፣ ከሻሿ አምልጠው የወጡ የፀጉር ዘለላዎች መንጨባረር ጋ አስፈሪነቷ ይበልጥ ሆነብኝ። "አይ ማለቴ እኮ ለጨጓራችን እኮ ነው። ደሞ...." "ደሞ ምን?" አይኗ ፈጠጠ "ፍር...ፍር ...ፍርፍር..ሙያ አይጠይቅም ይሉ የለ...." አስተያየቷ አንገቴን አሰበረው "ምን ማለት ነው....ፍርፍሩ ስሰራ ውሀውን በሙያዬ መሠረት ባላመጣጥነው እንደ ጫጩት ፍትፍትህን ትበላ አልነበር?" ወገቧን ያዘች... "አሃሃ....የወንዱ ልጅ!...ማንን ነው ጫጩት አንቺ?....እኔ ሌላ ሙያሽን አሳይኝ ባልኩ ነው ጫጩት የምትይኝ። 70 ቀን ሙሉ ፍርፍር ስትቀልቢኝ እኮ ዝም ያልኩት ካንቺ ይምጣ ብዬ ነው። ቴስቲሶያ እንደጉድ በሞላበት ሀገር አንድ ቀን እንኳን እሱን ልስራ ብለሽ አታውቂም።... ቴስቲሶያ ይቅር ኢንዶሚ እንኳን ቀቅሎ ማቅረብ ያቅትሻል?....I'm really sorry... አዝናለሁ።....ጆሮሽ ላይ ያረግሽውን ደሞ አንሺ....ሴት ልጅ ሽንኩርት አያቃጥላትም። ምን እዛ..." የ70 ቀን ብሶት ድንገት ፈንቅሎኝ ከአፌ ተዥጎደጎደ። "አሃ ...እኔ ሜላት ሴት በመሆኔ ለአንተ አጥሚት....ጭኮ...ቡላ...ገንፎ እያልኩ መኖርና መቀለብ አለብኝ?.... አለብኝ ወይ!?" አለች እዛው በቆመችበት ወገቧን ይዛ "ጭኮማ...በምን ዕድሌ...." ብዬ ዝም አልኩ....ቅድም የለፈለፍኩት ቁርስ ካለመብላቴ ጋ አድክሞኛል። ጭኮ በፊቴ ውል አለብኝ። "ትሰማኛለህ?...እንግዲያውስ በዓይነት በዓይነት የምትቀልብህ ጋ መሄድ ነዋ....እንደውም ይሄ ትዳር ሰልችቶኛል...በቃኝ።" ቀና ብዬ ዓይኗን አየሁዋት.... "ምን...በሶስት ወር ትዳራችን በቃሽ?..... ለካ ይሄ ሁሉ ቀመር ለዚህ ነው። በፍርፍር አማረሽ እኔን ለማብረር የተነሳሽው። ህምም... እኔም ይሄ ትዳር በቃኝ ጨርሻለሁ። እክክክክ..." ተነስቼ ከቤት ወጣሁ ከዛ ወዲህ ትዳራችን ቀዝቅዞ....ቀስ በቀስ ለፍቺ ደረሰ። የፍቺ የምስክር ወረቀት ልንቀበል ወሳኝ ኩነት ወረፋ ይዘን ባሎች በግራ ሴቶች በቀኝ ተቀምጠናል። ከጎኔ ያለው አንድ ፊቱ መጠጥ ያለና ፀጉሩ እስከመሀል አናቱ ጥሎ የሸሸው ሰውዬ በእጁ የያዛትን ጉርድ ፎቶ ቀና አድርጎ እያሳየኝ "አሁን እኔ እመስላለሁ?" አለኝ። " እንዴ...እንዴ...አንተ ነህ?" አልኩት አንዴ ፎቶውን አንዴ እሱን እያየሁ በመገረም። ጎፈሬው ግጥም ያለና ፊቱ ሞላ ያለ መልከ መልካም ወጣት አሁን በዚህ ልክ መለውጡ እየገረመኝ ጠየኩት... " ታድያሳ...የሚመጥ ይምጠጣት። እንደ ቀሰም ምጥጥ አርጋ ጨረሰችኝ....በቀደም በህልሜ ነጭ መልአክ መጥቶ .... 'ሰውዬ አልቀህ መሞትህ ነው። የፍቺ ሰርተፍኬት በእጁ አድርጎ እያሳየኝ አምልጥ...አምልጥ...አምልጥ' ሲለኝ አደረ...ይኸው በፍቺ ላመልጣት ነው። አንድዬ ትቶ አይተወኝ" "ምን ነገረኛ ሆናብህ ነው?" አልኩት "እሱም አንድ ነገር ነው። ግን ዋነኛው ሌላ ነው።ምኑን እደብቅሀለው ወንድሜ፤ አብረን ቁጭ አልንም አይደል? ቁስሌ ቁስልህ ነው።....ለሊት አገላብጠኝ ነው፤ጠዋት ፍርፍር....ለሊት አገላብጠኝ ነው፤ ጠዋት ፍርፍር...ለሊት አገላብጠኝ ነው፤ ጠዋት ፍርፍር....ዘይቴም ጨጓራዬም እኩል ተቃጠሉ። ሆ ብሎ ምድሩን ቀውጢ አድርጎ በዳረን ሰፈርተኛ ፊት በሽታ እንደያዘው እያደር በመሀል ሾቅኩ....ህምምም " በጣም ግብግብ እያለና እግሩን መሬቱ ላይ እየተመተመ ነው የሚያወራኝ... ትንሽ ፋታ ወሰደና "አንተስ ምን ሆነህ ነው?" አለኝ። የእኔን ለፍልፌለት የእሱን ሳልሰማ እንዴት አለ መሰለኝ በውስጡ... "ያው...ምን ባክህ....የኔም ፍርፍር ነው" አልኩት ፈገግ እያለ"ወዳጄ ሙት አታምነኝም እንጂ ፍርፍር ብዬ ጠርጥሬ ነበር፣... አመላቸው እ ሳት ...ፍርፍራቸው እሳት... ይሄኔ እኔና አንተ እዚህ ጋ ለፍቺ በተቀመጥንበት ቅፅበት ስንቱ እየተዳረ ነው 'አልሰሜን ግባ በለው'። እዛጋ የተቀመጠውን አየኸው..." አለኝ ወደአንዱ ገርዠፍ ብሎ ወደተቀመጠ ወንድ እያመለከተኝ... "አዎ...." አልኩ ወደ ሰውየው እየተመለከትኩ "እሱም እንዲሁ....በፍርፍር ጉዳይ ነው ፍቺው...ግን ከእሷ ውጪ እንዴት ልኖር ነው ብሎ ልቡ አዝኗል... " "ይገርማል...." ብቻ ይሄን ፍርፍር ግን ከሃገር የሚያሶጣልን ከሌለ ምናምን ፐርሰንት ትዳር እየተፈረፈረ ማለቁ ነው። ነጋቲ! Abrham F. Yekedas

ማንበብ ይወዳሉ?💝

ማንበብ ይወዳሉ?💝

አልተገላገልኩት... በዕንባ ተንሰቅስቄ ወይ "እፎይ" አላልኩት... ከት ብዬ ስቄ ጨክኜ አልጨለጥኩት... ልክ እንደውሀ ጥም ሃክ እንትፍ አላልኩት... ለአፍ እንደማይጥም እንደ ክፉ ሽታ... ወይ አ
አልተገላገልኩት... በዕንባ ተንሰቅስቄ ወይ "እፎይ" አላልኩት... ከት ብዬ ስቄ ጨክኜ አልጨለጥኩት... ልክ እንደውሀ ጥም ሃክ እንትፍ አላልኩት... ለአፍ እንደማይጥም እንደ ክፉ ሽታ... ወይ አልሰነፈጠኝ ለአፍንጫ ተስማምቶ... መዓዛ አላወደኝ መሀል አቁሞ ነው ጊዜ 'ሚሸወደኝ። Abrham F. Yekedas @HAKiKA1

"መድረሱንማ ሁሉም ይደርሳል" ለየቱ መድረስ ነው ግን መታከት ከአቻ ጎሪጥ መተያየት ወሽክቶ ዋሽቶ ለመድረስ ሴራ ቀምሮ ለመንገስ ፍፃሜው እስከምን ድረስ? ለመቆም ወዳጅን ጥሎ መታበይ ከሰው ፊት ቆሞ
"መድረሱንማ ሁሉም ይደርሳል" ለየቱ መድረስ ነው ግን መታከት ከአቻ ጎሪጥ መተያየት ወሽክቶ ዋሽቶ ለመድረስ ሴራ ቀምሮ ለመንገስ ፍፃሜው እስከምን ድረስ? ለመቆም ወዳጅን ጥሎ መታበይ ከሰው ፊት ቆሞ መሸንገል ላይ ላዩን ስቆ ከፍ ከፍ ሰውን አድቅቆ ለማየት የጫፉን ዋጋ ይገፈፍ  ስንት የሰው ፀጋ? የመክሊትን ዳር ለመንካት ወይም በገንዘብ ለመርካት ከፍቅር ጎን ከንቱ ታጣን የጥላቻ ዳገት ወጣን ተታግለነው አቀበቱን ስንት በረዶ ስንት ሙቀቱን ክረምት በጋ ያለው ወቅቱን የዕድል ዱላን የዕድል ምቱን አልፎ እግር ሄዶ ሄዶ በእሾህ ቆንጥር ተረማምዶ ስንደርስ ወና ውጤት ባዶ ሆኖ ታየን... ለነፍሳችን በቃ ይሄው ነው ድካማችን? ሽቅብ ሮጠን ያለፍናቸው በፍቅር ደርሰው ደስታቸው ቀን ጠብቆ ሲያወጣለት ለቀና  ሰው የዕድል ዕጣን ስንገፋው አሳልፎን ቆሞ ብሎን ሂዱ መጣን ከጫፉ ላይ ተገናኘን በእኩሌታ ጊዜ አወጣን። ሁሉም ደርሷል ከጫፉ ላይ አቅመ ደካም አቅመ የበላይ በቀስታ ያዘገመ ልሩጥ ብሎ የፈጠነ ባለ አበሳው ያም ቅንጡ ፈዘዝ ያለ ሞኙ ብልጡ ሁሉም ደርሷል በሞት ሞቱ አሁን ይለይ፥ የሁሉም ሰው፥ መንገድና አመጣጡ። Abrham F. Yekedas @HAKiKA1