es
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Ir al canal en Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Mostrar más
2 619
Suscriptores
+324 horas
+207 días
+3730 días
Archivo de publicaciones
በዛሬው እለት ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በዕለተ  ቀዳም ሥዑር የገብረ ሰላመ በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይም በፈጸመው የማዳን ሥራ ለዓለም ድኅነትን መስጠቱ የሚታወጅበት ታላቅ ሃይማኖታዊ በዓል ነው። በኖኅ ዘመን መጥቶ የነበረው ጥፋት ማብቃቱ ርግቧ ይዛ በመጣችው የወይራ ቅጠል እንደታወቀ ሁሉ በአዳም በደል ምክንያት በሰው ልጆች የውድቀት ዘመን ማብቃቱ የሚታወጅበት በዓል ሲሆን ርግቧ በአፏ ይዛ ለመጣችው ለምለም ቅጠል ምሳሌም ለምለም ቄጤማን በቅዱስ ፓትርያርኩ አማካኝነት ለካህናቱና ለምዕመናን የታደለ ሲሆን ለበዓሉ ያሬዳዊ ዜማውን የደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ሊቃውንት እና ሰንበት ት/ት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን  አባላት ያሬዳዊ ወረብ ቀርቧል። በበዓሉ ላይ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ፣ብፁዕ አቡነ ሣሙኤል፣ እና ሌሎች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን  የማነ ዘመንፈስ ቅዱሰ እና ሌሎች የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ካህናት ፣ጀግኖች አርበኞች የሰ/ት/ቤት ተማሪዎችና ምእመናን ተገኝቸው በዓሉ ተከብሯል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ወዮ አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቅንዋት ተቸነከሩ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቅንዋት ተቸነከሩ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸው የእሾህ ዘውድ አቀዳጁት ለኪሩቤል የግርማ ልብስ የሚያለብሰው ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት የመላእክት ሠራዊት በመደንገጥ ለሚሰግዱለት እየዘበቱ በፊቱ ተንበረከኩ በምራቁ ዕውራንን ያበራቸው እርሱ የእርኩስ ምራቅ ተቀበለ ሁሉን የያዘውን ያዙት ሁሉን የሚገዛውን አሰሩት በቁጣ ጎተቱት እርሱ ግን በፍቅር ተከተላቸው "
      ቅዳሴ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ     ✞ዘአልበስዎ✞ ዘአልበስዎ አይሁድ ከለሜዳ(፪) ከለሜዳ ዘለይ ከለሜዳ(፫) የእኛ ጌታ መድኃኔዓለም አማኑኤል(፪) በአይሁዶች እጅ ተሰቀለ በእንጨት መስቀል(፪)        አዝ= = = = = መላእክትም እራቁቱን ሆኖ ሲያዩት(፪) ከእግሮቹ ሥር ተንበርክከው ሰገዱለት(፪)        አዝ= = = = = ደናግላት አለቀሱ ብለው ወዮ(፪) ጌታን ሲያዩት በመስቀል ላይ ቀራንዮ(፪)        አዝ= = = = = ድንግል ማርያም መቃብሩን ተመልክታ(፪) ተንገላታች ከለቅሶ ጋር ጎልጎታ(፪)       መዝሙር አበበ ቱምሳ              

#ስቅለተ_ዓርብ ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ ማቴ 27፥ 35 ፍኖ
#ስቅለተ_ዓርብ ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ ማቴ 27፥ 35 ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት

ስቅለት በጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
+7
ስቅለት በጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ

በቅድሚያ የጌታችንን መከራ መስቀልን ለምናዘክርበት የሰሞነ ሕማማት ሳምንትና ለጸሎተ ሐሙስ እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እያልን፤ ባሳለፍነው እሑድ የሆሣዕናን በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀነውን ልዩ
በቅድሚያ የጌታችንን መከራ መስቀልን ለምናዘክርበት የሰሞነ ሕማማት ሳምንትና ለጸሎተ ሐሙስ እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እያልን፤ ባሳለፍነው እሑድ የሆሣዕናን በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀነውን ልዩ የኢየሩሳሌም በሮች ታሪክ፣ የዓብይ ጾም ሰንበታት ለሕጻናት በቀላሉ የሚያስተምር ታሪክ፣ የደብራችን እና የሰንበት ት/ቤትን የሚያወሳ ታሪክ ማቅረባችን ይታወቃል። በቦታና በጊዜ መጣበብ ምክንያት ከተለያዩ ሰንበት ት/ቤት ከተገኙት ሕጻናት ውጪ ለአባላት እና ለምዕመናን ልጆች ባለማስጎብኘታችን ይቅርታ እየጠየቅን፤ በቀረበልን ጥያቄ መሠረት ሐሙስ 10:30-1:00 እና አርብ ከጠዋት ጀምሮ በስግደት መሀል በሚኖረን ጊዜ ለሕጻናት ልጆቻችን ታሪኩን የምናስጎበኛቸው ስለሆነ፣ በዕለቱ ተገኝታችሁ የክርስቶስን መከራ መስቀል በስግደት እያሰብን ለሕጻናት ልጆች መጽሐፍ ቅዱስን በትዕይንተ እንዲማሩ እንድታደርጉ በአክብሮት ጠርተናል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በቅድሚያ የጌታችንን መከራ መስቀልን ለምናዘክርበት የሰሞነ ሕማማት ሳምንትና ለጸሎተ ሐሙስ እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እያልን፤ ባሳለፍነው እሑድ የሆሣዕናን በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀነውን ልዩ
በቅድሚያ የጌታችንን መከራ መስቀልን ለምናዘክርበት የሰሞነ ሕማማት ሳምንትና ለጸሎተ ሐሙስ እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እያልን፤ ባሳለፍነው እሑድ የሆሣዕናን በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀነውን ልዩ የኢየሩሳሌም በሮች ታሪክ፣ የዓብይ ጾም ሰንበታት ለሕጻናት በቀላሉ የሚያስተምር ታሪክ፣ የደብራችን እና የሰንበት ት/ቤትን የሚያወሳ ታሪክ ማቅረባችን ይታወቃል። በቦታና በጊዜ መጣበብ ምክንያት ከተለያዩ ሰንበት ት/ቤት ከተገኙት ሕጻናት ውጪ ለአባላት እና ለምዕመናን ልጆች ባለማስጎብኘታችን ይቅርታ እየጠየቅን፤ በቀረበልን ጥያቄ መሠረት ሐሙስ 10:30-1:00 እና አርብ ከጠዋት ጀምሮ በስግደት መሀል በሚኖረን ጊዜ ለሕጻናት ልጆቻችን ታሪኩን የምናስጎበኛቸው ስለሆነ፣ በዕለቱ ተገኝታችሁ የክርስቶስን መከራ መስቀል በስግደት እያሰብን ለሕጻናት ልጆች መጽሐፍ ቅዱስን በትዕይንተ እንዲማሩ እንድታደርጉ በአክብሮት ጠርተናል።

ጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ
+9
ጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ

የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር ሥነ ስርዓት በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው በተገኙበት ተከናወነ ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/
+9
የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር ሥነ ስርዓት በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው በተገኙበት ተከናወነ ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com