es
Feedback
Bina revivalist 🔥

Bina revivalist 🔥

Ir al canal en Telegram

(የሐዋርያት ሥራ ምዕ. 2) ---------- 1፤ #በዓለ ኀምሳ #የተባለውም ቀን #በደረሰ ጊዜ፥ #ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው #አብረው ሳሉ፥ 2፤ #ድንገት #እንደሚነጥቅ ዓውሎ #ነፋስ ከሰማይ #ድምፅ መጣ፥ #ተቀምጠው #የነበሩበትንም ቤት #ሁሉ #ሞላው። 🔥🔥🔥🔥 @Binajesus

Mostrar más
5 956
Suscriptores
-124 horas
-247 días
-12130 días
Archivo de publicaciones
የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰል.... 📌መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማሰላሰል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ርዕሰ ጉዳዮችን፤ በሂደት ከእኛ ጋር እስኪዋሐዱና ከእኛነታችን ጋር እስኪዛመዱ ድረስ፤ በትኩረት፤ ዘለግ ላለ ጊዜ ማሰብ፣ በቀስታ መናገርና በእምነት የማወጅን ተግባር ያካተተ መንፈሳዊ ጥበብ ነው። 📌የእግዚአብሔር ቃል በውስጡ በእውነት፣ በመንፈስ፣ በህይወትና በጸጋ የታጨቀ ነው። ✍ #የእውነት_ቃል 📌የእግዚአብሔር ቃል የእውነት ቃል ነው። መፅሐፍ ቅዱሳችን በብዙ ስፍራ የእግዚአብሔር ቃል እውነተኛነትን አስረግጦ ይናገራል። ጽድቅህ የዘላለም ጽድቅ ነው፥ ቃልህም እውነት ነው። -----መዝ 119፥142 በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። ------ዮሐንስ 17፥17 📌የእግዚአብሔር ቃል እውነትና ውሸት አልባ ነው ስንል ለመፈጸሙ ምንም ጥርጣሬ ላይ አንጥልም ማለታችን ነው። ሐሰትን ይናገር ዘንድ እግዚአብሔር ሰው አይደለም፥ ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ ይደለም። እርሱ ያለውን አያደርግምን? የተናገረውንስ አይፈጽመውምን? ------ዘኁልቁ 23፥19#የህይወት_ቃል 📌የእግዚአብሔር ቃል ከእውነት ቃልነቱ ባሻገር በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ የህይወት ቃል በሚል ተጠርቷል። ስለህይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤ -----1ኛ ዮሐንስ 1፥1 📌የእግዚአብሔር ቃል የህይወት ቃል በሚል ሲጠራ ለመስራት ዛሬም ድረስ አቅምና ብቃት ያለው ህያው መሆኑን አመልካች ነው። ከዚህም በተጨማሪ የህይወት ቃል ተብሎ መጠራቱ፤ በመረዳትና በእምነት የተቀበሉትን ሁሉ ሕያው ማድረግ የሚችል መለኮታዊ አቅም እንዳለው አስረጂ አባባል ነው። የእግዚአብሔር ቃል ህያው ነውና፥ የሚሰራም፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ -------ዕብ 4፥12 ህግህ ተድላዬ ባይሆን፥ ቀድሞ በጉስቁልናዬ በጠፋሁ ነበር። በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም። -------መዝሙር 119፥92-93 📌የእግዚአብሔርን ቃል በሚገባ ስናሰላስል ከእግዚአብሔር ቃል ህያው ማንነትና ጉልበት ጋር እንገናኛለን። #የጸጋ_ቃል 📌የጸጋ ቃል የእግዚአብሔር ቃል በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ የተጠራበት ሌላኛው መጠሪያ ስም ነው። አሁንም ለእግዚአብሔርና ያነጻችሁ ዘንድ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ይሰጣችሁ ዘንድ ለሚችል #ለጸጋው_ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ። ------የሐዋርያት ሥራ 20፥23 📌ጸጋ ማለት ፈጽሞ የማይገባን፤ አንዳች ነገር ያላበረከትንበት፤ እንዲሁም በነፃ የተሰጠን ስጦታ ማለት ነው። 📌የጸጋ ቃል ማለት የቃሉ ተስፋ ለእኛ በሚገባን ልክ የተሰፈረ፤ አልያም በሰው እምነት ልክ የተሰራ ሳይሆን በእግዚአብሔር የመስራት አቅም ልክ ስለ እኛ የሆነ ነገር ነው። 👉ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቃል በአግባቡ በምናሰላስልበት ጊዜ እነዚህ የቃሉ ባህሪይዎች በህይወታችን እየተገለጡ ይመጣሉ። 📌እግዚአብሔርን የትም አናገኘውም ቃሉ ውስጥ ነው ስንጸልይ እግዚአብሔር ይሰማናል የእግዚአብሔርን ቃል ስናሰላስል ግን እግዚአብሔር ይናገረናል። ዘውትር ነፍሳችሁን የእግዚአብሔርን ቃል በማሰላሰል አስለምዷት። ቃሉ በሙላት ይኑርባይሁ በህይወታችሁም ሞልቶ ይፍሰስ.... ማሰላሰል ከሚለው ከ ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ መጽሐፍ የተወሰደ@Binarevivalist @Binarevivalist @Binarevivalist

ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤ አሜን። -----ራእይ 1:5

ጌታን ጠብቁት አታፍሩም😭❤️ ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣ አዎን፤ ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣ ነፍሴ ጌታን ትጠባበቃለች። — መዝሙር 130፥6 (አዲሱ መ.ት)

ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።   — ዮሐንስ 10፥28

ዕብራውያን 4፥14-16 14፤ እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ። 15፤ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም። 16፤ እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።

እባካችሁ ጨርሳችሁ ስሙት የሆነ ረሃብ ያገኛችኋል 😭😭😭😭😭 ለምትወዱትም ሰው ላኩላቸው😭🔥 @Binarevivalist @Binarevivalist @Binarevivalist

ደስታችሁ እና ሰላማችሁ ፍፁም እንዲሆን ይህንን አድርጉ🔥❤ @Binarevivalist @Binarevivalist @Binarevivalist

የሕይወቴ ጉዳይ ኢየሱስ ምደነግጥልህ ኢየሱስ ልቤ የሚርድልህ ኢየሱስ የተሸነፍኩልህ ኢየሱስ🥹😭 ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን። -----ኤፌሶን 6፥24
+2
የሕይወቴ ጉዳይ ኢየሱስ ምደነግጥልህ ኢየሱስ     ልቤ የሚርድልህ ኢየሱስ     የተሸነፍኩልህ ኢየሱስ🥹😭 ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን። -----ኤፌሶን 6፥24

            ምደነግጥልህ ❤       ሻሎም አዱኛ - Doriel   @Binarevivalist   @Binarevivalist   @Binarevivalist

ከእግዚአብሔር ጋር የታረቅንበት መንገድ🔥 የወንጌል ድምፅ🔥

እግዚአብሔር ለእስራኤል ቤት ከተናገረው መልካም ነገር ሁሉ ተፈጸመ እንጂ ምንም አልቀረም። -----ኢያሱ 21፥45 ሐሰትን ይናገር ዘንድ እግዚአብሔር ሰው አይደለም፥ ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ አይደለም።     እርሱ ያለውን አያደርገውምን?     የተናገረውንስ አይፈጽመውምን? ------ዘኍልቍ 23፥19

አይኖቻችን በኃይል ሲከፈቱ መስቀሉ ላይ የተከናወነውን የእግዚአብሔርን ምስጢርና ጥበብ መረዳት እንጀምራለን።
አይኖቻችን በኃይል ሲከፈቱ መስቀሉ ላይ የተከናወነውን የእግዚአብሔርን ምስጢርና ጥበብ መረዳት እንጀምራለን።

መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ? -----ሮሜ 10፥15
መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ? -----ሮሜ 10፥15

ዛሬ በሜክሲኮ ተርሚናል ውስጥ ለብዙ ሺዎች የፀጋው ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተሰበከ🔥🔥🔥🔥 ✍ኢየሱስ የእግዚአብሔር የምህረት በር ነው። ✍ኢየሱስ የእግዚአብሔር የፍቅሩ የይቅርታው መገለጥ ነ
+4
ዛሬ በሜክሲኮ ተርሚናል ውስጥ ለብዙ ሺዎች የፀጋው ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተሰበከ🔥🔥🔥🔥ኢየሱስ የእግዚአብሔር የምህረት በር ነው። ✍ኢየሱስ የእግዚአብሔር የፍቅሩ የይቅርታው መገለጥ ነው። ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና። ----ዮሐንስ 3፡17

✍የእምነታችን ራስና ፈፃሚ ወደ ዕብራውያን 12፡1 --- 1፤ እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ #የ
የእምነታችን ራስና ፈፃሚ ወደ ዕብራውያን 12፡1 --- 1፤ እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ #የእምነታችንንም_ራስና #ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። #ክርስትና የሚሮጠው በመፍጠን ሳይሆን በእምነት ነው። #የክርስትናን መንገድ መጨረስ የሚቻለው በፍጥነት በመሮጥ ሳይሆን በእምነት ፀንቶ በመሮጥ ነው። #የእምነታችን ምንጭ ደግሞ የእምነታችን ራስና ፈፃሚ የሆነው ክርስቶስ። #የእምነታችን_ራስ፦ ሕይወት ከ ራስ በሚገኝ እውቀትና ሐሳብ ይመራል። ራስ ውስጥ ያለ እውቀትና ሐሳብ በአካል ይገለጣል። #ኢየሱስ የእምነታችን ራስ ነው ስንል የእምነታችን ምንጭ የእምነታችን መሰረት ነው እያልን ነው። እምነታችን እያደገና አየበረታ የሚሄደው ረስ ከሆነን ከክርስቶስ በምናገኘው እውቀትና ሐሳብ ነው ማለት ነው። #የእውቀት ምንጭ ራስ ነው፣ እምነት የሚመጣው መለኮታዊ እውቀትንና መገለጥን በመቀበል ነው። ስለዚህ የእምነታችን ምንጭና የእምነታችን ጥንካሬ እንዲሁም የእምነታችን ብርታት ያለው ራስ ከሆነን ከክርስቶስ መገለጥንና እውቀትን ስንቀበል ነው። የእምነታችን ሕያውነትና አቅም ምንጩ ራስ ከሆነን ከክርስቶስ ነው። #የእምነታችን_ፈፃሚ፦ እምነታችን ፍፁምና ሙሉ ሊሆን የሚችለው ክርስቶስን በተረዳንና ስለክርስቶስ ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘነው መገለጥ ልክ ነው። #እምነታችን የፀና እና ፍፁም ወይም ሙሉ ሊሆን የሚችለው ራስ ከሆነው ከክርስቶስን በምናገኘው መረዳትና እውቀት ነው። #አገልጋይ_ቢና🔥❤

በእግዚአብሔር ታመን፤ መልካምንም አድርግ፤ በምድሪቱ ተቀመጥ፤ ዘና ብለህ ተሰማራ። በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፤ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል። መንገድህን ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤ በርሱ ታመን፤ እርሱም ያከናውንልሃል፤ ------መዝሙር 37፥3-5

YAHWEH🔥 The Self Existent One🔥 I AM WHO I AM ---Exodus 3:14
YAHWEH🔥 The Self Existent One🔥 I AM WHO I AM ---Exodus 3:14

የእግዚአብሔር የክብርና የኪዳን ስሞች🔥🔥🔥🔥 #ስምህን_የሚያውቁ ሁሉ በአንተ ይታመናሉ፥ አቤቱ፥ የሚሹህን አትተዋቸውምና። — መዝሙር 9፥10 በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ #ስሜንም_አውቆአልና
የእግዚአብሔር የክብርና የኪዳን ስሞች🔥🔥🔥🔥 #ስምህን_የሚያውቁ ሁሉ በአንተ ይታመናሉ፥ አቤቱ፥ የሚሹህን አትተዋቸውምና።   — መዝሙር 9፥10 በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ #ስሜንም_አውቆአልና እጋርደዋለሁ። -----መዝሙር 91፥14 መዝሙረ 118፥ 10-12 --- 10፤ አሕዛብ ሁሉ ከበቡኝ፥ #በእግዚአብሔርም_ስም አሸነፍኋቸው፤ 11፤ መክበቡንስ ከበቡኝ፥ #በእግዚአብሔርም_ስም አሸነፍኋቸው፤ 12፤ ንብ ማርን እንዲከብብ ከበቡኝ፥ እሳትም በእሾህ ውስጥ እንዲነድድ ነደዱ፥ #በእግዚአብሔርም_ስም አሸነፍኋቸው። የዮሐንስ 17 --- 6፤ ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች #ስምህን_ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤ ቃልህንም ጠብቀዋል። ዮሐንስ 17 26 እኔንም የወደድህባት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ #ስምህን_አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2 --- 9፤ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ #ከስምም_ሁሉ #በላይ #ያለውን #ስም_ሰጠው፤ 10፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ #በኢየሱስ_ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ 11፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።

ወንጌል የሚያድን የመንፈስ ቅዱስ እውቀት ነው። የመንፈስ ቅዱስ ኮርስ ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ወንጌል ብቻ ነው። መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድር በአማኞች ሕይወት ውስጥ ለመኖር የወረደው የወንጌልን እውነ
ወንጌል የሚያድን የመንፈስ ቅዱስ እውቀት ነው። የመንፈስ ቅዱስ ኮርስ ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ወንጌል ብቻ ነው። መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድር በአማኞች ሕይወት ውስጥ ለመኖር የወረደው የወንጌልን እውነትና ኃይል በአማኞች ሕይወት ውስጥ ሊገልጥና ሊተገብር ነው። ለሰው ልጆች ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ትምህርትና መገለጥ በወንጌል ውስጥ ያለው የክርስቶስ ሕይወት ነው። ከመንፈስ ቅዱስ ውጪ ለሰው ልጆች የወንጌልን እወነት ሊገልጥና ሊያስተምር የሚችል የለም። ወንጌል የመጨረሻው የእግዚአብሔር ክብር የእግዚአብሔር ጉልበት የእግዚአብሔር ኃይል የእግዚአብሔር ጥበብ የእግዚአብሔር ፍቅረ የእግዚአብሔር ጥበብና እውቀት መገለጥ የእግዚአብሔር አጀንዳ የእግዚአብሔር አሰራር ነው። ወንጌል የእግዚአብሔር የልቡ ሃሳብ ሁሉ ተጠቅልሎ የተገለጠበት የእግዚአብሔር መልእክት ነው።

My Jesus🔥❤️
My Jesus🔥❤️