en
Feedback
Bina revivalist 🔥

Bina revivalist 🔥

Open in Telegram

(የሐዋርያት ሥራ ምዕ. 2) ---------- 1፤ #በዓለ ኀምሳ #የተባለውም ቀን #በደረሰ ጊዜ፥ #ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው #አብረው ሳሉ፥ 2፤ #ድንገት #እንደሚነጥቅ ዓውሎ #ነፋስ ከሰማይ #ድምፅ መጣ፥ #ተቀምጠው #የነበሩበትንም ቤት #ሁሉ #ሞላው። 🔥🔥🔥🔥 @Binajesus

Show more
5 805
Subscribers
-324 hours
-197 days
-10230 days
Posts Archive
፤ በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤ -----ፊልጵስዩስ 1፥6
፤ በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤ -----ፊልጵስዩስ 1፥6

ወደ ሮሜ ሰዎች 5፥6-7 --- 6፤ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና። 7፤ ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት
+5
ወደ ሮሜ ሰዎች 5፥6-7 --- 6፤ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና። 7፤ ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል። 8፤ ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።

በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው፤ የኀጥኣንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል። ----- ምሳሌ 10:8

              ከመገኘትህ     ሊዲያ አንተነህ - Kingdom              

ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6 --- 10፤ በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ። 11፤ የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። 12፤ መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ። 13፤ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። 14-15፤ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤ 16፤ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ 17፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው። 18፤ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤

በሕይወቴ ዘመናት ሁሉ አግዚአብሔር ብቻ ትልቅ ነው❤️

የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን እንድንጠራ😍❤️

እግዚአብሔር ለእኔ ያለውን የማይለወጥና የማይሻል ፍቅሩን የተረዳሁት በበደሌና በኃጢአቴ ገና ሙታን ሳለው ልጁን ስለእኔ በመስቀል ላይ ሲሰቅለው ነው። እግዚአብሔር ለእኔ ያለውን ፍቅር የተረዳሁት በአንድያ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ነው። እግዚአብሔር ላይጠላኝ እንደወደደኝ እግዚአብሔር ከፍታውና ጥልቀቱ ስፋቱና ርዝመቱ በማይታወቅ ፍቅር እንደወደደኝ የገባኝና የተረዳሁት ኢየሱስ ክርስቶስን ሳውቀው ነው። እግዚአብሔር በማይቀንስና በማይጠፋ ፍቅር ይወደኛል ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ የማይሻርና የማይቀየር ማረጋገጫዬ ነው። እግዚአብሔር አባቴ ይወደኛል። ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። -----ሮሜ 5፥8 ሮሜ 8፥ 37፤ በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። 38፤ ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥ 39፤ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።

በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና። -----ኤፌሶን 2፥18
+2
በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና። -----ኤፌሶን 2፥18

የፀጋው ወንጌል #የዛሬ 6 ዓመት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ🥺😍 ከእግዚአብሔር አብ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል የተገለጠልን ፀጋ ከኃጢአትና ከዘለዓለም ሞት መዳኛ ብቻ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ አዲሱን
የፀጋው ወንጌል #የዛሬ 6 ዓመት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ🥺😍 ከእግዚአብሔር አብ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል የተገለጠልን ፀጋ ከኃጢአትና ከዘለዓለም ሞት መዳኛ ብቻ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ አዲሱን የትንሳኤ ሕይወት መኖሪያም ነው። አድኖን የሄደ ፀጋ ሳይሆን እለት እለት የትንሳኤን ሕይወት (የእግዚአብሔርን ዞዌ ሕይወት) የሚያኖረንን ፀጋ ተቀብለናል። ፀጋ መዳኛ ብቻ ሳይሆን የተካፈልነውን አዲሱንና የትንሳኤውን ሕይወት የምንኖርበት ከመለኮት የተሰጠን አቅምና ብቃት ነው።

ሕግ እግዚአብሔርን ያንተ ጠላት ያደርገዋል። ፀጋ ደግሞ እግዚአብሔርን ያንተ ወዳጅ ያደርገዋል።

እግዚአብሔር ያንን ሁሉ ፍቅር ያንን ሁሉ ምህረት በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ያፈሰሰው የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን ነው። እግዚአብሔር ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ኃጢአት አድርጎት በመስቀል ላይ መከራን
እግዚአብሔር ያንን ሁሉ ፍቅር ያንን ሁሉ ምህረት በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ያፈሰሰው የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን ነው። እግዚአብሔር ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ኃጢአት አድርጎት በመስቀል ላይ መከራን እንዲቀበል ያደረገው ቁጣውን በልጁ ላይ ያፈሰሰው እኛ የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ እርግማናችንን ወስዶ እርግማን የሆነው በመስቀል ላይ ኃጢአተኛ ሳይሆን የሁላችንንም በደልና ኃጢአት ተሸክሞ ኃጢአት የሆነው እኛ የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን ነው። እግዚአብሔር በአንድያ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የጨከነው አንድ ነገር ፈልጎ ነው እሱም ደግሞ እኛ የእርሱ ልጆች እንድንሆን ነው። የእግዚአብሔር ልጅነት የትጋታችንና የልፋታችን ውጤትና ሽልማታችን ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሆነው ማንነታችን ነው። የእግዚአብሔር ልጅነትን በትጋት ሰርተን ያመጣነው ማዕረግ ሳይሆን ማንነትና ዝርያ ነው። የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን። ------1ኛ የዮሐንስ 3፥1 #አሁን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የእግዚአብሔር ልጆች ነንወዳጆች ሆይ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን። -----1ኛ የዮሐንስ 3፥2 #አገልጋይ_ቢና🔥❤️

1ኛ የዮሐንስ 3፥1 --- 1፤ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን። ስለዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን ስላላወቀው እኛን አያውቀንም።
+3
1ኛ የዮሐንስ 3፥1 --- 1፤ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን። ስለዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን ስላላወቀው እኛን አያውቀንም።

መረጋጋትና በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ያለ ስጋትና ያለ ፍርሃት መኖር እግዚአብሔርን የመስማት ውጤት ነው። እግዚአብሔርን የሚሰማ የማዕበለና የወጀቡ ጩኸት አያስፈራውም። የእግዚአብሔር ድምፅ እንደ መልሕቅ የልቡን እምነት አጥብቆ ይይዘዋል ከማእበሉና ከወጀቡ በላይ በሚሰማው የእግዚአብሔር ድምፅ ላይ ተደግፎ ይኖራል። የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። -----ምሳሌ 1፥33

ነገር ግን #አምላካቸውን_የሚያውቁ ሕዝብ #ይበረታሉ#ያደርጋሉም።   — ዳንኤል 11፥32

የፀጋው ወንጌል በአስኮ ገበያ🔥❤️ ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥ ----የዮሐንስ ራእይ1፥4
+5
የፀጋው ወንጌል በአስኮ ገበያ🔥❤️ ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥ ----የዮሐንስ ራእይ1፥4

ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ። -----ገላትያ 6፥14

መንፈስ ቅዱስ❤️🔥 ወደ ሮሜ ሰዎች 8፥26-27 --- 26፤ እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤ 27፤ ልብንም የሚመረምረው የመንፈስ አሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል፥ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ ቅዱሳን ይማልዳልና።

የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰል.... 📌መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማሰላሰል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ርዕሰ ጉዳዮችን፤ በሂደት ከእኛ ጋር እስኪዋሐዱና ከእኛነታችን ጋር እስኪዛመዱ ድረስ፤ በትኩረት፤ ዘለግ ላለ ጊዜ ማሰብ፣ በቀስታ መናገርና በእምነት የማወጅን ተግባር ያካተተ መንፈሳዊ ጥበብ ነው። 📌የእግዚአብሔር ቃል በውስጡ በእውነት፣ በመንፈስ፣ በህይወትና በጸጋ የታጨቀ ነው። ✍ #የእውነት_ቃል 📌የእግዚአብሔር ቃል የእውነት ቃል ነው። መፅሐፍ ቅዱሳችን በብዙ ስፍራ የእግዚአብሔር ቃል እውነተኛነትን አስረግጦ ይናገራል። ጽድቅህ የዘላለም ጽድቅ ነው፥ ቃልህም እውነት ነው። -----መዝ 119፥142 በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። ------ዮሐንስ 17፥17 📌የእግዚአብሔር ቃል እውነትና ውሸት አልባ ነው ስንል ለመፈጸሙ ምንም ጥርጣሬ ላይ አንጥልም ማለታችን ነው። ሐሰትን ይናገር ዘንድ እግዚአብሔር ሰው አይደለም፥ ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ ይደለም። እርሱ ያለውን አያደርግምን? የተናገረውንስ አይፈጽመውምን? ------ዘኁልቁ 23፥19#የህይወት_ቃል 📌የእግዚአብሔር ቃል ከእውነት ቃልነቱ ባሻገር በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ የህይወት ቃል በሚል ተጠርቷል። ስለህይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤ -----1ኛ ዮሐንስ 1፥1 📌የእግዚአብሔር ቃል የህይወት ቃል በሚል ሲጠራ ለመስራት ዛሬም ድረስ አቅምና ብቃት ያለው ህያው መሆኑን አመልካች ነው። ከዚህም በተጨማሪ የህይወት ቃል ተብሎ መጠራቱ፤ በመረዳትና በእምነት የተቀበሉትን ሁሉ ሕያው ማድረግ የሚችል መለኮታዊ አቅም እንዳለው አስረጂ አባባል ነው። የእግዚአብሔር ቃል ህያው ነውና፥ የሚሰራም፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ -------ዕብ 4፥12 ህግህ ተድላዬ ባይሆን፥ ቀድሞ በጉስቁልናዬ በጠፋሁ ነበር። በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም። -------መዝሙር 119፥92-93 📌የእግዚአብሔርን ቃል በሚገባ ስናሰላስል ከእግዚአብሔር ቃል ህያው ማንነትና ጉልበት ጋር እንገናኛለን። #የጸጋ_ቃል 📌የጸጋ ቃል የእግዚአብሔር ቃል በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ የተጠራበት ሌላኛው መጠሪያ ስም ነው። አሁንም ለእግዚአብሔርና ያነጻችሁ ዘንድ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ይሰጣችሁ ዘንድ ለሚችል #ለጸጋው_ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ። ------የሐዋርያት ሥራ 20፥23 📌ጸጋ ማለት ፈጽሞ የማይገባን፤ አንዳች ነገር ያላበረከትንበት፤ እንዲሁም በነፃ የተሰጠን ስጦታ ማለት ነው። 📌የጸጋ ቃል ማለት የቃሉ ተስፋ ለእኛ በሚገባን ልክ የተሰፈረ፤ አልያም በሰው እምነት ልክ የተሰራ ሳይሆን በእግዚአብሔር የመስራት አቅም ልክ ስለ እኛ የሆነ ነገር ነው። 👉ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቃል በአግባቡ በምናሰላስልበት ጊዜ እነዚህ የቃሉ ባህሪይዎች በህይወታችን እየተገለጡ ይመጣሉ። 📌እግዚአብሔርን የትም አናገኘውም ቃሉ ውስጥ ነው ስንጸልይ እግዚአብሔር ይሰማናል የእግዚአብሔርን ቃል ስናሰላስል ግን እግዚአብሔር ይናገረናል። ዘውትር ነፍሳችሁን የእግዚአብሔርን ቃል በማሰላሰል አስለምዷት። ቃሉ በሙላት ይኑርባይሁ በህይወታችሁም ሞልቶ ይፍሰስ.... ማሰላሰል ከሚለው ከ ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ መጽሐፍ የተወሰደ@Binarevivalist @Binarevivalist @Binarevivalist

ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤ አሜን። -----ራእይ 1:5