es
Feedback
KALITY GENERAL SECONDARY SCHOOL

KALITY GENERAL SECONDARY SCHOOL

Ir al canal en Telegram

ውድ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች እንዲሁም የትምህርት ማህበረሰብ በዚህ ቻናል የሚለቀቁት ጉዳዪች በዋናነት ትምህርትቤቱ ለተማሪዎቹ የሚያስተላልፈው ማስታወቂዎች፤ትኩስናወቅታዊ ትምህርታዊ መረጃዎች እንዲሁም በክፍል ደረጃችሁ ለምትማሩት ትምህርት አጋዥ በሚሆናችሁ ትምህርት መሆኑን እንገልፃለን።

Mostrar más
3 568
Suscriptores
+624 horas
+407 días
+11030 días
Archivo de publicaciones
የሠአት ማስተካከያ 1, የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪወች በቀን 23/11/2018 ዓ.ም ከ7:30 ጀምሮ 2. የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቀን 24/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እስከ 11:30 ብቻ ይሆናል።

ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ነባር ተማሪዎች ቀን 22/11/2018 ዓ.ም በ2018 ዓ. ም 12ኛ ክፍል ነባር ተማሪዎች በሙሉ እንደሚታወቀዉ የ2018 ዓ. ም የሀገር አቀፍ ፈተና እስኪጠናቀቅ መፅሀፍ እንዳትመልሱ ያደረግን መሆኑን ይታወቃል። ስለዚህ ከነገ 23 /11/2018 ዓ.ም እስከ 24/11/2018 ዓ.ም መፅለፍ እንድታስረክቡ በጥብቅ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

photo content

ቀን፡-08/11/2018 5ኛ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ 1.AASTU University የተመደባችሁ ጧት 12፡00 ብርሃን ዓነስውራን አዳሪ ትምህርት ቤት የተመደባችሁ ደግሞ ጧት 12፡45 ት/ቤት ተገኝታችሁ በጊዜ ወደተመደባችሁበት እንድትሄዱ በጥብቅ እናሳስባለን። እዳትረሱ 👎 1.Admission card 2.the school ID 3. Complete uniform 4. Normal hair style 5. Excellent Discipline The school wishes Good luck!!!

photo content

ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክረምት          የማጠናከሪያ ትምህርትን በተመለከተ - በ2018 ዓ.ም ከ10ኛ እና 11ኛ ክፍል በየክፍሉ ከ1 እስከ 30ኛ የወጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ ከሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ጀምሮ የማጠናከሪያ ትምህርቱ የሚጀምር መሆኑን ከዚህ ቀደም ያሳወቅናችሁ መሆኑ ይታወቃል።     ስለሆነም ትምህርቱ የሚሰጠው ጠዋት ከ2:30 እስከ 6:30 በመሆኑ በተጠቀሰው ቀን የመማሪያ ቁሳቁስ በመያዝ መምጣት እንዳለባችሁ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ - በማጠናከሪያው መማር እያለበት ያልተማረ ተማሪ ለ2019 ዓ.ም ምዝገባ አይስተናገድም (አይመዘገብም)። - እስከ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ድረስ በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት ትምህርቱ የሚሰጠው በቃሊቲ የመ/ደ/ት/ቤት ውስጥ መሆኑን እናሳውቃለን። - ጥብቅ የስም ቁጥጥር ስለሚደረግ ማንም ተማሪ መቅረት የለበትም!!!

ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክረምት          የማጠናከሪያ ትምህርትን በተመለከተ - በ2018 ዓ.ም ከ10ኛ እና 11ኛ ክፍል በየክፍሉ ከ1 እስከ 30ኛ የወጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ ከሐምሌ 6/2018 ዓ.ም ጀምሮ የማጠናከሪያ ትምህርት የሚጀምር መሆኑን ከዚህ ቀደም ያሳወቅናችሁ መሆኑ ይታወቃል።     ስለሆነም ትምህርቱ የሚሰጠው ጠዋት ከ2:30 እስከ 6:45 በመሆኑ በተጠቀሰው ቀን የመማሪያ ቁሳቁስ በመያዝ መምጣት እንዳለባችሁ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ - በማጠናከሪያው መማር እያለበት ያልተማረ ተማሪ ለ2019 ዓ.ም ምዝገባ አይስተናገድም (አይመዘገብም)። - እስከ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ድረስ በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት ትምህርቱ የሚሰጠው በቃሊቲ የመ/ደ/ት/ቤት ውስጥ መሆኑን እናሳውቃለን። - ጥብቅ የስም ቁጥጥር ስለሚደረግ ማንም ተማሪ መቅረት የለበትም!!!

Around 4 ተፈታኝ ተማሪዎች ነገ በ6/11/18 ጧት 12:30 ት/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን

ጥብቅ ማስታወቂያ ቶፕ 30 11ኛና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሁላችሁም እንደምታውቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባወጣው የውጤት የማላቅያ ስትራቴጂ የክረምት ትምህርት ሰኞ/06/11/2018 ዓ.ም በይፋ ይጀምራል። ስለሆነም ይህ ፕሮግራም ውስጥ የተካተታችሁ ተማሪዎች በከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር ስለሚመራ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሚጠበቅባችሁን ክፍያ እስከ ነገ /እሁድ/በማጠናቀቅ ሰኞ ጧት 2፡00 ላይ ቃሊቲ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት ቤት እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ፡- በምንም ዓይነት ምክንያት ይህንን ፕሮግራም የማይከታተል ተማሪ ለ2019 ትምህርት ዘመን ለምፈጠረው መስተጓጎል ትምህርት ቤቱ ሃላፍነት እንደማይወስድ በአፅኖት እናሳውቃለን። ት/ቤቱ

ቀን 3/11/18 ማስታወቅያ ለቀንና የማታ ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች # በ4ኛና 5ኛ ዙር ሆናችሁ Boarding School/ብርሃን አይነ ስዉራን ት/ ቤት የተመደባችሁ የቀንና የማታ ተማሪዎች ነገ በ4/11/18 ለኦሬንተሽን ስለተጠራችሁ ጧት 1:00 ትምህርት ቤታችን እንድትገኙ # 5ኛ ዙር AASU የተመደባች ነገ 4/11/18 5:00 ትምህርት ቤታችን ተገኝታችሁ ለኦሬንተሺን የምትሄዱ መሆኑን እናሳውቃለን

Stream ያልመረጣችሁ የ10ኛ ክፍል Top 30 ተማሪዎች ለመጨረሻ ነገ የማታስገቡ ከሆነ የምመጣዉ ተጠያቂነት በራሳችሁ የምትወስዱ መሆኑ በጥብቅ እናሳውቃለን

ጥብቅ ማሳሰቢያ ለ11ኛና 12ኛ ክፍል Top 30 ተማሪዎች በሙሉ የሚጠበቅባችሁ ጉዳዮች፡- 1.stream ምርጫ በተባለው ቀንና ሰዓት በትክክል ማጠናቀቅ 2.የሚጠበቅባችሁን የክረምት ትምህርት ክፍያ ትምህርት ከመጀመሩ በፊት (5/11/2018) አጠናቅቃችሁ 3.ለዚህ የክረምት ትምህርት ተመርጦ (Top 30) ሆኖ የማይማር ተማሪ ለ2019 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት ለመቀጠል ለሚፈጠረው ችግር ት/ቤቱ ሃላፍነት አይወስድም። ቃሊቲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት

Stream.pdf6.49 KB

ቀን: 28/10/2018 ዓ/ም ማስታወቂያ ለተማሪዎች እና ለወላጆች/አሳዳጊዎች ​ከ 10ኛ ክፍል ወደ 11ኛ ክፍል ለተሻገራችሁ የትምህርት ቤታችንTop 30 ተማሪዎች በሙሉ፤ ​ተማሪዎች በ11ኛ ክፍል የሚከታተሉትን የትምህርት ዘርፍ (Stream) ለመምረጥ ከዚህ ማስታወቂያ ጋር የተያያዘውን "የስትሪም (Stream) ምርጫ ቅጽ" ፕሪንት (Print) በማድረግ እና በትክክል በመሙላት እንድታስገቡ ይሳሰባል። ​የማስረከቢያ ዝርዝር መረጃ፦ቀን፦ እሮብ ጠዋት(01/11/2018 ዓ/ም) ​ሰዓት፦ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 4:00 ሰዓት ​ቦታ፦ በትምህርት ቤቱ በር ላይ ለሚገኙ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር አካላት ​ማሳሰቢያ፦የፎርሙ ይዘት፦ ቅጹ የተማሪ መረጃ፣ የስትሪም ምርጫ (Natural Science ወይም Social Science)፣ የምርጫ ምክንያት፣ እንዲሁም የተማሪ እና የወላጅ/አሳዳጊ ማረጋገጫ ፊርማዎችን ያካተተ መሆን አለበት። ​ፊርማ፦ ቅጹ ያለ ተማሪው እና ያለ ወላጅ/አሳዳጊ ፊርማ ተቀባይነት አይኖረውም። ​ሰዓት ማክበር፦ ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ (2:30 - 4:00) ውጭ የሚመጡ ቅጾችን ማስተናገድ ስለማይቻል ተማሪዎች በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን። ት/ት ቤቱ 

Photo from gutamaderessa4
Photo from gutamaderessa4

Photo from gutamaderessa4
Photo from gutamaderessa4

photo content

To all the (17) Natural Science students of 2nd ROUND!!tomorrow (26_30/10/2018) Please, try to reach on time at school exactly at 12:30 The school wishes GOOD LUCK!!

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለተፈታኞች የማይፈቀዱ ቁሳቁስ… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከነገ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር ይሰጣል፡፡ ለፈተናው 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም 257 ሺህ 45 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 563ሺህ 501 ተፈታኞች መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡ አገልግሎቱ ለፈተናው የሚያስፈልጉ ሁሉንም ዝግጅቶች ማጠናቀቁንና የፈተና አስፈጻሚዎችን ወደ ፈተና ማዕከላት ማሰማራቱን ገልጿል። ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲቀርቡ የመፈተኛ መግቢያ ካርዳቸውን (አድሚሽን ካርድ)፣ የተማሪ ወይም ህጋዊ መታወቂያ፣ በፈተና አስተዳደሩ የተፈቀደ እስክሪብቶ እና ባዶ ወረቀት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል። ሞባይል ስልክ፣ ስማርት ሰዓት፣ ብሉቱዝ፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ፍላሽ ዲስክ፣ ሜሞሪ ካርድ፣ የግል ላፕቶፕ ወይም ታብሌት እና ሌሎች ያልተፈቀዱ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት አይፈቀድም። ፈተናው በበይነ መረብ በ6 ዙር የሚሰጥ ሲሆን፣ በወረቀት የሚፈተኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 1 እስከ 3፣ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 6 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚፈተኑ ተገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም ተፈታኞች መልካም እድል እየተመኘ ፈተናውን በመረጋጋት፣ በሥነ ምግባርና በራስ መተማመን እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል።

ቀን 22/10/2018 ዓ. ም የመጀመሪያ ዙር 117 ተፈታኞቾ ነገ በቀን 23/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰአት ት/ቤት ቅጥር ግቢ እንድትገኙ በጥብቅ በጥብቅ እናሳስባለን።