ETHIO CIVIL ENGINEER
Ir al canal en Telegram
For all CENG & others, we will help you on:- =)Scholarship infos =)Tutor for Exit Exams. =)Integrated civil Engineering Design. =)B.Sc. Thesis =)#YouTube ቻናላችንን subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://www.youtube.com/channel/UC8h1sfALxrsNbYbXNPuChvw/
Mostrar más3 396
Suscriptores
+224 horas
+287 días
+5730 días
Archivo de publicaciones
3 396
የቀድሞ ካርታ እያለ አዲስ የህጋዊ ካዳስተር ምዝገባ ለምን ያስፈልጋል?
--------------------------------------------------
ብዙ ባለይዞታዎች ይዞታችሁን አስመዝግቡ ሲባሉ፦ “ከመሬት አስተዳደር ልማት ቢሮ የተሰጠን ካርታ አለን፤ ሌላ ካርታ ለምን ያስፈልጋል?” ብለው ይጠይቃሉ። ይህ ጥያቄ ተገቢ ነው፤
መልሱ ግን አዲሱ ምዝገባ የቀድሞውን ሰነድ ለመሻር ወይም ተመሳሳይ መብትን ለሁለተኛ ጊዜ ለመስጠት የታሰበ ሳይሆን፣ ያለውን የይዞታ መረጃ በተደራጀ፣ በዘመናዊ እና በካዳስተር ሥርዓት ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ነው።
1. አንደኛ ነገር "መብት ሰጪ" እና "መዝጋቢ" ተቋማት ይለያያሉ!
ነባሩ ካርታ፡ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ (መብት ሰጪ ተቋም) የመሬት ተጠቃሚነት መብት ወይም ቦታ ሲፈቅድ የሚሰጥ የፈቃድ ሰነድ ነው።
የምዝገባ ሰርተፊኬት (አዋጅ ቁጥር 1381/2017)፡ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ መሬቱ ላይ ያለው ወሰን በዘመናዊ የካዳስተር ቴክኖሎጂ (GPS/ኦርቶ ፎቶ) ተለክቶ፣ የመሬቱ እና በላዩ ላይ ያረፈው ቤት/ንብረት ባለቤትነት በሕጋዊ መንገድ መረጋገጡን የሚያመላክት የዋስትና ሰነድ ነው።
2. አዲሱ የካዳስተር ካርታ ምን ይጨምራል?
አዋጅ ቁጥር 1381/2017 የሚያቋቁመው ሥርዓት በመሬት ላይ ያለውን እውነታ ብቻ ሳይሆን፣ የመሬት መብት፣ ክልከላ እና ኃላፊነትን በአንድ የሕጋዊ ካዳስተር ሥርዓት ያደራጃል።
በአዋጁ መሠረት ካዳስተራል ምዝገባ የሚያካትተው፦
የቁራሽ መሬቱን ትክክለኛ ወሰን፣
ስፋት፣ ርዝመትና ቅርጽ፣
የወሰን መገናኛ ነጥቦችን፣
የኮኦርዲኔት መረጃን፣
የአጎራባች ቁራሽ መሬቶችን፣
የመንገድና የአድራሻ መረጃን፣
የቁራሽ መሬቱን ልዩ መለያ ኮድ፣
በመሬቱ ላይ ያለውን ሕንፃ ወይም ሌላ መሬት ነክ ንብረት፣
በይዞታው ላይ ያሉ መብቶች፣ ክልከላዎችና ኃላፊነቶችን ነው።
ስለዚህ የቀድሞ ካርታ እና የካዳስተር ካርታ ተመሳሳይ ዓላማና ተመሳሳይ የሕግ መዋቅር ያላቸው ሰነዶች አይደሉም።
3. የቀድሞ ካርታ ብቻ ለምን አይበቃም?
የቀድሞ ካርታ ብቻ በመጠቀም የሚከተሉት ችግሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ፦
አንድ መሬት በተለያዩ ሰነዶች ላይ በተለያየ ስፋት ሊመዘገብ ይችላል።
የአጎራባች መሬቶች ወሰን ሊደራረብ ይችላል።
አንድ ይዞታ በተለያዩ ስሞች ወይም ቁጥሮች ሊታወቅ ይችላል።
የመሬቱ ትክክለኛ ኮኦርዲኔት ላይኖር ይችላል።
በመሬቱ ላይ ያለው ሕንፃ ወይም ቋሚ ንብረት ከመሬቱ ጋር ተያይዞ ላይመዘገብ ይችላል።
የሽያጭ፣ የውርስ፣ የውል፣ የሞርጌጅ ወይም የካሳ ጉዳዮች ላይ ክርክር ሊፈጠር ይችላል።
መረጃው በወረቀት ብቻ ስለሚቀመጥ ለዲጂታል ሥርዓት ሊዘጋጅ አይችልም።
የካዳስተር ምዝገባ እነዚህን ችግሮች ለመቀነስ የመሬቱን መረጃ ከአንድ ልዩ መለያ ኮድ ጋር ያስተሳስራል።
4. የቀድሞ ካርታ እና የካዳስተር ምዝገባ አንድ ናቸው?
አይደሉም።
የቀድሞ ካርታ የይዞታውን ቀድሞ የነበረ መረጃ የሚያሳይ ሰነድ ሲሆን፣ የካዳስተር ምዝገባ ደግሞ የይዞታውን መረጃ በዘመናዊ የካዳስተር ሥርዓት ያደራጃል።
5. የቀድሞ ካርታዬ ምን ይሆናል?
የቀድሞ ሰነድዎ በምዝገባ ሂደት ውስጥ እንደ ማስረጃ ሊመረመርና ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
ስለዚህ አዲሱ ምዝገባ ማለት የቀድሞ ሰነድዎን በቀላሉ መሰረዝ አይደለም።
6. ካዳስተር ምዝገባው ምን ይጨምራል?
· የይዞታውን ቦታ
· ስፋትና ቅርጽ
· ወሰንና የወሰን ነጥቦች
· ልዩ መለያ ኮድ
· አድራሻና የአጎራባች ይዞታ መረጃ
የመሳሰሉ ዝርዝር የቦታ መረጃዎችን በተደራጀ ሥርዓት ያስቀምጣል።
7. ሁለተኛ መብት እየተፈጠረ ነው?
አይደለም።
ዓላማው በአንድ ይዞታ ላይ ሁለት መብቶችን መፍጠር ሳይሆን፣ ያለውን የይዞታ መረጃ በሕጋዊ ሂደት ማረጋገጥ፣ ማደራጀትና መመዝገብ ነው። ይህን ጉዳይ በግልጽ መረዳት ያስፈልጋል። አዲሱ ምዝገባ፡-
አዲስ መሬት ለመስጠት አይደለም፤
ቀድሞ ያለውን ሕጋዊ መብት ለመሰረዝ አይደለም፤
የመሬት ስፋትን በዘፈቀደ ለመቀነስ ወይም ለመጨመር አይደለም፤
ባለይዞታውን ለማስጨነቅ የተዘጋጀ ተጨማሪ ሂደት አይደለም።
ዓላማው የቀድሞ መረጃን በመፈተሽ፣ በትክክለኛ ቅየሳ በማረጋገጥና በዘመናዊ የካዳስተር ሥርዓት በማደራጀት የይዞታውን ሕጋዊነትና ትክክለኛ መገኛ ማረጋገጥ ነው።
8. ታዲያ ለምን ማስመዝገብ አለብኝ?
Ø የይዞታ መረጃዎን በተደራጀ ሥርዓት ለማስቀመጥ፣
Ø የይዞታዎን ቦታና ወሰን በግልጽ ለማሳወቅ፣
Ø ዘመናዊ የካዳስተር መረጃ ለመፍጠር፣
Ø የይዞታ መብት ዋስትናን ለማጠናከር ነው።
9. ባለይዞታዎች ማወቅ ያለባቸው ዋና መልእክት፡-
ነባሩ ካርታ የመሬት መጠቀሚያ ፈቃድዎ ሲሆን፤ በአዋጅ ቁጥር 1381/2017 መሠረት የሚሰጠው የካዳስተር ምዝገባ ሰርተፊኬት ደግሞ የሀብትዎ እና የቤትዎ የመጨረሻ ሕጋዊ የባለቤትነት ማረጋገጫና ዋስትና ነው! ስለዚህ ይዞታዎን በወቅቱ በማስመዝገብ ሀብትዎን ከስጋት ይጠብቁ!"
3 396
የቀድሞ ካርታ እያለ አዲስ የህጋዊ ካዳስተር ምዝገባ ለምን ያስፈልጋል?
--------------------------------------------------
ብዙ ባለይዞታዎች ይዞታችሁን አስመዝግቡ ሲባሉ፦ “ከመሬት አስተዳደር ልማት ቢሮ የተሰጠን ካርታ አለን፤ ሌላ ካርታ ለምን ያስፈልጋል?” ብለው ይጠይቃሉ። ይህ ጥያቄ ተገቢ ነው፤
መልሱ ግን አዲሱ ምዝገባ የቀድሞውን ሰነድ ለመሻር ወይም ተመሳሳይ መብትን ለሁለተኛ ጊዜ ለመስጠት የታሰበ ሳይሆን፣ ያለውን የይዞታ መረጃ በተደራጀ፣ በዘመናዊ እና በካዳስተር ሥርዓት ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ነው።
1. አንደኛ ነገር "መብት ሰጪ" እና "መዝጋቢ" ተቋማት ይለያያሉ!
•ነባሩ ካርታ፡ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ (መብት ሰጪ ተቋም) የመሬት ተጠቃሚነት መብት ወይም ቦታ ሲፈቅድ የሚሰጥ የፈቃድ ሰነድ ነው።
•የምዝገባ ሰርተፊኬት (አዋጅ ቁጥር 1381/2017)፡ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ መሬቱ ላይ ያለው ወሰን በዘመናዊ የካዳስተር ቴክኖሎጂ (GPS/ኦርቶ ፎቶ) ተለክቶ፣ የመሬቱ እና በላዩ ላይ ያረፈው ቤት/ንብረት ባለቤትነት በሕጋዊ መንገድ መረጋገጡን የሚያመላክት የዋስትና ሰነድ ነው።
2. አዲሱ የካዳስተር ካርታ ምን ይጨምራል?
አዋጅ ቁጥር 1381/2017 የሚያቋቁመው ሥርዓት በመሬት ላይ ያለውን እውነታ ብቻ ሳይሆን፣ የመሬት መብት፣ ክልከላ እና ኃላፊነትን በአንድ የሕጋዊ ካዳስተር ሥርዓት ያደራጃል።
በአዋጁ መሠረት ካዳስተራል ምዝገባ የሚያካትተው፦
• የቁራሽ መሬቱን ትክክለኛ ወሰን፣
• ስፋት፣ ርዝመትና ቅርጽ፣
• የወሰን መገናኛ ነጥቦችን፣
• የኮኦርዲኔት መረጃን፣
• የአጎራባች ቁራሽ መሬቶችን፣
• የመንገድና የአድራሻ መረጃን፣
• የቁራሽ መሬቱን ልዩ መለያ ኮድ፣
• በመሬቱ ላይ ያለውን ሕንፃ ወይም ሌላ መሬት ነክ ንብረት፣
• በይዞታው ላይ ያሉ መብቶች፣ ክልከላዎችና ኃላፊነቶችን ነው።
ስለዚህ የቀድሞ ካርታ እና የካዳስተር ካርታ ተመሳሳይ ዓላማና ተመሳሳይ የሕግ መዋቅር ያላቸው ሰነዶች አይደሉም።
3. የቀድሞ ካርታ ብቻ ለምን አይበቃም?
የቀድሞ ካርታ ብቻ በመጠቀም የሚከተሉት ችግሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ፦
•አንድ መሬት በተለያዩ ሰነዶች ላይ በተለያየ ስፋት ሊመዘገብ ይችላል።
•የአጎራባች መሬቶች ወሰን ሊደራረብ ይችላል።
•አንድ ይዞታ በተለያዩ ስሞች ወይም ቁጥሮች ሊታወቅ ይችላል።
•የመሬቱ ትክክለኛ ኮኦርዲኔት ላይኖር ይችላል።
•በመሬቱ ላይ ያለው ሕንፃ ወይም ቋሚ ንብረት ከመሬቱ ጋር ተያይዞ ላይመዘገብ ይችላል።
•የሽያጭ፣ የውርስ፣ የውል፣ የሞርጌጅ ወይም የካሳ ጉዳዮች ላይ ክርክር ሊፈጠር ይችላል።
•መረጃው በወረቀት ብቻ ስለሚቀመጥ ለዲጂታል ሥርዓት ሊዘጋጅ አይችልም።
የካዳስተር ምዝገባ እነዚህን ችግሮች ለመቀነስ የመሬቱን መረጃ ከአንድ ልዩ መለያ ኮድ ጋር ያስተሳስራል።
4. የቀድሞ ካርታ እና የካዳስተር ምዝገባ አንድ ናቸው?
አይደሉም።
የቀድሞ ካርታ የይዞታውን ቀድሞ የነበረ መረጃ የሚያሳይ ሰነድ ሲሆን፣ የካዳስተር ምዝገባ ደግሞ የይዞታውን መረጃ በዘመናዊ የካዳስተር ሥርዓት ያደራጃል።
5. የቀድሞ ካርታዬ ምን ይሆናል?
የቀድሞ ሰነድዎ በምዝገባ ሂደት ውስጥ እንደ ማስረጃ ሊመረመርና ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
ስለዚህ አዲሱ ምዝገባ ማለት የቀድሞ ሰነድዎን በቀላሉ መሰረዝ አይደለም።
6. ካዳስተር ምዝገባው ምን ይጨምራል?
•የይዞታውን ቦታ
•ስፋትና ቅርጽ
•ወሰንና የወሰን ነጥቦች
•ልዩ መለያ ኮድ
•አድራሻና የአጎራባች ይዞታ መረጃ
የመሳሰሉ ዝርዝር የቦታ መረጃዎችን በተደራጀ ሥርዓት ያስቀምጣል።
7. ሁለተኛ መብት እየተፈጠረ ነው?
አይደለም።
ዓላማው በአንድ ይዞታ ላይ ሁለት መብቶችን መፍጠር ሳይሆን፣ ያለውን የይዞታ መረጃ በሕጋዊ ሂደት ማረጋገጥ፣ ማደራጀትና መመዝገብ ነው። ይህን ጉዳይ በግልጽ መረዳት ያስፈልጋል። አዲሱ ምዝገባ፡-
•አዲስ መሬት ለመስጠት አይደለም፤
•ቀድሞ ያለውን ሕጋዊ መብት ለመሰረዝ አይደለም፤
•የመሬት ስፋትን በዘፈቀደ ለመቀነስ ወይም ለመጨመር አይደለም፤
•ባለይዞታውን ለማስጨነቅ የተዘጋጀ ተጨማሪ ሂደት አይደለም።
ዓላማው የቀድሞ መረጃን በመፈተሽ፣ በትክክለኛ ቅየሳ በማረጋገጥና በዘመናዊ የካዳስተር ሥርዓት በማደራጀት የይዞታውን ሕጋዊነትና ትክክለኛ መገኛ ማረጋገጥ ነው።
8. ታዲያ ለምን ማስመዝገብ አለብኝ?
የይዞታ መረጃዎን በተደራጀ ሥርዓት ለማስቀመጥ፣
የይዞታዎን ቦታና ወሰን በግልጽ ለማሳወቅ፣
ዘመናዊ የካዳስተር መረጃ ለመፍጠር፣
የይዞታ መብት ዋስትናን ለማጠናከር ነው።
9. ባለይዞታዎች ማወቅ ያለባቸው ዋና መልእክት፡-
ነባሩ ካርታ የመሬት መጠቀሚያ ፈቃድዎ ሲሆን፤ በአዋጅ ቁጥር 1381/2017 መሠረት የሚሰጠው የካዳስተር ምዝገባ ሰርተፊኬት ደግሞ የሀብትዎ እና የቤትዎ የመጨረሻ ሕጋዊ የባለቤትነት ማረጋገጫና ዋስትና ነው! ስለዚህ ይዞታዎን በወቅቱ በማስመዝገብ ሀብትዎን ከስጋት ይጠብቁ!"
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለበለጠ መረጃ 👇👇👇
👉Website; https://addiscadaster.gov.et/
👉Facebook; Addis Ababa City Admin. Landholding Registration and Information
👉TikTok; A.Acadaster2016
👉Telegram; https://t.me/lhria
👉you tube; Legal cadaster
👉Customer Call Center: 6577
addiscadaster.gov.et (https://addiscadaster.gov.et/)
Addis Ababa City Administration Landholding Registration and Information Agency | Home Page
3 396
🤔የአንድ ፕሮጀክት Defect Liability period (365 ቀናት) ተጠናቆ ሲያበቃ Retention እንድንከፍል ስንጠየቅ የተፈጠረው Structural Defect ከተያዘው ገንዘብ በላይ ቢሆን ምን እናደርጋለን?
👇
.
.
.
.
.
መልስ:-
በconstruction contract administration ውስጥ በጥንቃቄ መያዝ ያለበት ጉዳይ ነው። Defect Liability Period (DLP) 365 ቀን መጠናቀቁ ብቻ ማለት የStructural Defect ኃላፊነት በራሱ ያበቃል ማለት አይደለም።
በተለይ Structural Defect ከRetention ገንዘብ በላይ ከሆነ፦
1. Retention በቀጥታ አትክፈሉ። መጀመሪያ defect-ው በቴክኒክ እንዲረጋገጥ ያድርጉ።
2. Structural assessment/investigation በብቃት ባለው Structural Engineer/consultant ያስደርጉ። የdefect-ው መንስኤ፣ ክብደት፣ የመጠገኛ ወጪና የህንፃው ደህንነት ይረጋገጥ።
3. Contractor በcontract መሠረት እንዲያስተካክል በጽሑፍ ይጠየቅ። ችግሩ በContractor's defective workmanship/material/design ምክንያት ከሆነ፣ የመጠገን ኃላፊነቱ በRetention መጠን ብቻ አይወሰንም።
4. Retention ከጠየቀው ገንዘብ በላይ የሚያስፈልግ የrepair cost ካለ፣ በcontract ውስጥ ያሉ ሌሎች security/remedy provisions መሠረት ይመርመሩ። ለምሳሌ Performance Security አሁንም ተፈጻሚ ከሆነ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።
5. ተጨማሪው ወጪ ከContractor እንዲመለስ የሚያስችለው የcontract clause ካለ መሠረቱን በግልጽ ይያዙ። Retention ብቻ እንደ “maximum liability” መቆጠር አይገባም፣ ይህ ግን በተፈረመው contract ቃላት ይወሰናል።
6. ክፍያ ለመልቀቅ ከመወሰን በፊት የFinal/Completion Certificate፣ defect notification፣ inspection report፣ structural assessment፣ repair estimate እና contract clauses አንድ ላይ ይመርመሩ።
በተለይ የሚለየው
DLP = 365 days ማለት በዚያ ጊዜ ውስጥ የታዩ defects እንዲታረሙ የContractor's contractual obligation የሚታይበት ጊዜ ነው። ነገር ግን ከ365ኛው ቀን በኋላ የተገኘ Structural Defect ላይ ኃላፊነት አለ/የለም የሚለው በContract Particular Conditions, GCC/PCC, applicable law እና defect-ው በመጀመሪያ መነሻው ላይ ይወሰናል።
ስለዚህ በጉዳዩ ላይ “365 ቀን አልቋል፣ Retention ክፈሉ” ብሎ ብቻ መወሰን ትክክል አይሆንም። Structural defect-ው በcontractor ኃላፊነት ውስጥ መሆኑ ከተረጋገጠ በመጀመሪያ የrepair/remedy ጉዳዩ መፍትሄ ማግኘት አለበት።
3 396
👉Delay Justification, Extension of time(EOT) እና የጊዜ ጉዳት መቀጮ/Liquidated damage/:
በኢትዮጵያ ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ የግንባታ ፕሮጀክቶች (Construction Projects) ላይ በስፋት ስለሚተገበሩት (Delay Justification)፣(Time Extension Request) እና (Liquidated Damages) አተገባበር በመጠኑ ሃሳብ ለመስጠት የተጋጀ አጭር ፅሁፍ ነው፡፡
1ኛ. የፕሮጀክት መዘግየት ምክንያታዊነት ማብራሪያ (Delay Justification)
Contractor የተሰጠውን ስራ በቅድሚያ በውል በተወሰነው ጊዜ ማጠናቀቅ ግዴታ እንዳለበት ግልፅ ነው። ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ፕሮጀክቱ በጊዜ ላይጠናቀቅ ይችላል። ስለዚህ ለነዚህ የባከኑ ጊዜዎች አሳማኝ ምክንያቶች በማቅረብ የፕሮጀክቱን ቀሪ ስራዎች ለማጠናቀቅ የሚያስችለውን የጊዜ ማራዘሚያ ለመጠየቅ ይችላል።
🌟ለፕሮጀክት መዘግየት ምክንያቶች
1. የፈጣሪ ቁጣ (Force Majeure):
*ከባድ ዝናብ፣ጎርፍ፣አውሎነፋስና የመሳሰሉ ከቁጥጥር ውጭ የሆኑ ምክንያቶች ናቸው።
2 በተቋራጭ ምክንያት የሚፈጠር መዘግየት:
*በውሉ ዕቅድ መሰረት የግንባታ ሀብቶችን/ማቴሪያል፣የሰው ሀይል፣ ማሽነሪና ባጀት ማቅረብ አለመቻል።
*የስራ አመራር ችግር/ከእቅድ ዝግጅት ችግር፣የማደራጀት ብቃት ማነስ፣የመምራት፣የክትትልና ቁጥጥር ብቃት ከማነስ/
3. በአማካሪ ምክንያት የሚከሰቱ
*ለማፅደቅ ማዘግየት/ዕቅድ፣ዲዛይን፣ሜትዶሎጂ፣ክፍያ... /
4. በአሰሪ ምክንያት የሚከሰቱ
*የክፍያ ማዘግየት፣ ቢሮክራሲ፣ የፍላጎት ለውጥ/Change & Variations.. /፣....
5. ከመሬት በታች ያልተጠበቁ ክስተቶች/Unforseen works/:
*ከመሬት በታች በሚሰራ ቁፋሮ ስራ ወቅት በመጠን ወይም በዓይነት የተለየ ስራ ሲያጋጥም/በውል ያልተጠቀሰ የአፈር ዓይነት/Unpredicted soil strata/፣ ቫኩም ወይም ቮይድ/void/፣ የማያቋርጥ የሚፈልቅ/ምንጭ ውሃ/Underground Water/፣ የደካማ አፈር ጥልቀትና መጠን/over volume of loss soil/፣...
6. በመንግስት የፖሊሲ ለውጥ ምክንያትና
7 የፖለቲካ ጫና፣ጦርነትና ርሃብ
2ኛ. የጊዜ ማራዘሚያ ጥያቄ ስለማቅረብ/EOT/
ሥራ ተቋራጩ ለስራው መዘግየት ምክንያት ናቸው የሚላቸውን ነጥቦች አንድ በአንድ በመጥቀስ፣በማስረጃ በማብራራት ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ የሚያስፈልገውን ተጨማሪ ጊዜ እንዲፈቀድለት ማቅረብ የሚችል ይሆናል።
3ኛ. ለባከነ የግንባታ ጊዜ ''የጊዜ ጉዳት መቀጫ''/Liquidated damage/
ተቋራጩ የውሉን የግንባታ ስራ በውሉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ በወቅቱ ሰርቶ ያላጠናቀቀ እንደሆነ ከውሉ ማጠናቀቂያ ጊዜ/completion date/ በኋላ ግንባታው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ ለእያንዳንዱ ቀን ተቋራጩ የግንባታ መዘግየት ምክንያት ለአሰሪው የጊዜ ጉዳት መቀጫ/Liquidated damage/ የመክፈል ሀላፊነት ይኖርበታል፡፡
በኮንስትራክሽን ውል ስለ ጊዜ አቆጣጠር:
-የግንባታ ውል የተደረገበት ቀን/contract signing date/ ፣
-ሞቢላይዜሽን ፔሬድ/mobilization period/፣
-የሳይት መረከቢያ ቀን/site handover/፣
-የስራ መጀመሪያ ቀን/commencement date/ እና
-የስራ ማጠናቀቂያ ቀን/completion date/ የሚሉትን መረዳት የግንባታ የጊዜ የጉዳት መቀጫ/Liquidated damage/ የሚለውን በአግባቡ ለማወቅ ይጠቅማል፡፡
እዚህ ላይ ሊታወቅ የሚገባው ነገር በኮንስትራክሽን ውሉ ላይ የተወሰነውን የስራ ክፍል ከውሉ የማጠናቀቂያ ጊዜ አስቀድሞ ማጠናቀቅ ውል ሊደረግ የሚችልበት እድልም አለ፡፡/Partial completion/ ማለት ነው፡፡የቀን አቆጣጠሩ ከላይ እንደተብራራው የሚሰላ ይሆናል፡፡
**ሌላው ተቋራጩ ወደ መዘግየት ቅጣት እንዲገባ ከመደረጉ አስቀድሞ በአግባቡ መረጋገጥ ያለበት ነገር መሀንዲሱ ለተቋራጩ የጊዜ ማራዘሚያ/Extension of Time / ፈቅዷል ወይስ አልፈቀደም የሚለው ነጥብ ነው፡፡
ምክንያቱም ለተቋራጩ የጊዜ ማራዘሚያ ተፈቅዶለት ከሆነ የግንባታ ማጠናቀቂያ ጊዜውም አብሮ ስለሚራዘምና ቀኑ ስለሚቀየር ነው፡፡
የሀገራችን የህግ ማዕቀፍ በዚህ ረገድ ምን ይላል?
በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1887 እስከ 1895 ድረስ የተደነገጉትን መዳሰስ ይጠይቃል፡፡
በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1889 ላይ ተዋዋዮች በውላቸው ምናልባት አንደኛው ወገን እንደውሉ ግዴታውን ያልፈጸመ እንደሆነ ወይም አጓድሎ የፈጸመ እንደሆነ ወይም አዘግይቶ የፈጸመ እንደሆነ የሚከፍለውን የመቀጮ መጠን አስቀድመው በውላቸው ለመወሰን እንደሚችሉ በሚፈቅድ መልኩ ተደንግጓል፡፡እዚህ ላይ የውል ግዴታን አዘግይቶ መፈጸም ስለሚያስከትለው ቅጣት የሚዋዋሉት በተለይ የግንባታ ጊዜ የጉዳት መቀጫ/liquidated damage/ የሚመለከት ይሆናል፡፡
የመዘግየት ቅጣት ስምምነት ባለ ጊዜ አሰሪው የውሉ ስራ እንዲፈጸምና የቅጣት ገንዘቡንም ለመቀበል መብት እንደሚኖረው የፍ/ህ/ቁ 1890(2) ይደነግጋል፡፡እንደዚሁም አሰሪው ኪሳራ ባይደርስበት እንኳ የመዘግየት ቅጣት ገንዘቡ ሊከፈለው እንደሚገባ የፍ/ህ/ቁ 1892(1) ይደነግጋል፡፡እንግዲህ ተቋራጩ ግንባታውን በወቅቱ ያላጠናቀቀው አሰሪውን ሆነ ብሎ ለመጉዳት አስቦ ጉልህ በሆነ ቸልተኝነት ወይም በከባድ ጥፋት መሆኑ የተረጋገጠ እንደሆነ አሰሪው በውሉ ከተቀመጠው የቅጣት ገንዘብ በላይ በደረሰበት ትክክለኛ ጉዳት መጠን ልክ ከተቋራጩ ላይ ኪሳራ ለመጠየቅ እንደሚችል የፍ/ህ/ቁ 1892(2) ይደነግጋል፡፡
ሌላው የመዘግየት ቅጣት መጠን በዳኞች ሊቀነስ የሚችልበት እድል ስለመኖሩ የፍ/ህ/ቁ 1893 ይደነግጋል፡፡ይሄውም ተቋራጩ ግዴታውን በከፊል የፈጸመ ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ይህ ማለት ተቋራጩ ባከናወነው ስራ ሁሉ ቅጣት የሚጣልበት አይሆንም ማለት ነው፡፡
በዚህ ረገድ በሲቪል ግንባታ ስራዎች ቋሚ የውል መተዳደሪያ አንቀጽ 47(1) ላይ ተቋራጩ ስራውን በውሉ የማጠናቀቂያ ጊዜ ካላጠናቀቀ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ቀን የውሉን ዋጋ 1/1000 እንደሚከፍል እና ይሄውም አጠቃላይ መጠኑ ከውሉ ዋጋ ከ10% መብለጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ሆኖም ግን በከፊል ለተከናወነው ስራ መሀንዲሱ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በሰጠ ጊዜ የቅጣቱ መጠን የሚሰላው ባልተከናወነው ስራ መጠን ዋጋ ላይ በመመስረት ይሆናል ማለት ነው፡፡
በመጨረሻም የመዘግየት ቅጣት በኛ ሀገር ከላይ እንዳየነው እንደቅጣት የሚቆጠርና በህጉ ቅጣቱ እውቅና የሚሰጠው ሲሆን በኮመን ሎው የህግ ስርአት ግን ቅጣት አይደለም፡፡በኮመን ሎው የጊዜ የጉዳት መቀጫ በአሰሪው ላይ ከደረሰው ጉዳት ጋር እኩል ሆኖ መመዛዘን የሚኖርበት ሲሆን የቅጣት አይነት ተመሳሳይ ባህሪ ካለው ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡
3 396
📍 VACANCY ANNOUNCEMENT: RESIDENT CIVIL ENGINEER
We are seeking qualified and experienced engineering professionals to join our team.
Position: Resident Civil Engineer
Total Openings: 8 Positions
Experience Required: Minimum 8 Years
Salary: 60,000+ ETB (Negotiable based on experience)
If you meet the requirements, send your CV on Telegram to @Belay_Ceng
3 396
👉በሳይት ላይ የፓድ ፋውንዴሽን (Pad Footing) የጥራት እና የመለኪያ ፍተሻ🏗️
☄በምስሉ ላይ እንደምናየው የፓድ ፋውንዴሽን ቁፋሮ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የሊን ኮንክሪት (Blinding Concrete) ከመፍሰሱ በፊት የፓዱ ስፋት፣ ጥልቀት እና የኮለሙ መካከለኛ ነጥብ (Centerline) ከፕሮፋይል ገመድ (Grid Line) ጋር እየተፈተሸ ይገኛል።
🚥በ Pad Footing ቁፋሮ ወቅት ትኩረት የሚሹ 3 ዋና ዋና ነጥቦች፦
1. Soil Bearing Capacity (የአፈር የመሸከም አቅም)፦ ቁፋሮው በዲዛይኑ የተጠቆመው ጠንካራ የአፈር ንብርብር (Bearing Strata) ላይ መድረሱን ማረጋገጥ።
2. Excavation Dimensions (የቁፋሮ ስፋትና ጥልቀት)፦ የፓዱ ርዝመት፣ ወርድ እና ጥልቀት ከስትራክቸራል ስዕሉ ጋር ሙሉ በሙሉ መጣጣሙን መፈተሽ።
3. Centerline Alignment፦ የኮለሙ መካከለኛ ነጥብ ከፓዱ መካከለኛ ነጥብ ጋር መግጠሙን ማረጋገጥ፤ ይህም Eccentric Loading (ያልተጠበቀ ጭነት) እንዳይኖር ይከላከላል።
⬆️በእርስዎ ሳይት ላይ የPad Footing ቁፋሮ ሲያካሂዱ አፈሩ ልቅ (Loose Soil) ቢሆን ምን አይነት መፍትሔ ይወስዳሉ?
💡ተመሳሳይ ሙያዊ የሳይት ኢንጂነሪንግ መረጃዎችን ለማግኘት የ YouTube ገጻችንን Subscribe ያድርጉ👇
https://youtube.com/@ethiopianconstruction7?si=ils307xXQQpIdCwG
@etconp
3 396
በሳይት ላይ የSelect Material ጥራት ቁጥጥር!
በምስሉ ላይ እንደምናየው ለመሰረት (Backfilling) ወይም ለመንገድ ሰብ-ቤዝ (Sub-base) የሚያገለግል የሴሌክት ማቴሪያል (Select Material) ክምችት እናያለን። ይህ ማቴሪያል ከፋውንዴሽን በላይ ወይም በሰላብ ስር ለሚሞላው አፈር ጠንካራ መሰረት ለመፍጠር ያገለግላል።
ጥራት ያለው Select Material 3 ዋና ዋና ባህሪያት፦
1. Well-Graded Mixture (የተመጣጠነ ስብጥር)፦ በትልልቅ ድንጋዮች መካከል ያሉትን ባዶ ቦታዎች (Voids) የሚደፍን በቂ ደቃቅ አሸዋ/አፈር እና ጠጠር ስብጥር ሊኖረው ይገባል።
2. Low Plasticity Index (PI < 6-10%)፦ ከፍተኛ የሸክላ አፈር (Clay) ስብጥር ሊኖረው አይገባም፤ ምክንያቱም ውሃ ሲያገኝ የማበጥ እና የመኮማተር (Swelling & Shrinkage) ባህሪ ስለሚያሳይ።
3. Free from Organic Matter፦ ከአረም፣ ከዕፅዋት ስሮች እና ከቆሻሻ ሙሉ በሙሉ የጸዳ መሆን አለበት።
በእርስዎ ሳይት ላይ ሴሌክት ማቴሪያል ከተደፋ በኋላ በየስንት ሴንቲሜትር (cm) ንብርብር (Layer) አድርገው በኮምፓክተር ያስመታሉ? (15cm ወይስ 20cm?) ሃሳብዎን በኮሜንት ያካፍሉን!
https://t.me/ethioengineers1
3 396
#ጥቆማ
#EthiopianAirlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሆኑ ተለማማጅ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Crew) አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
➤ የሥራ መደብ፦ ET SPONSORED Trainee Cabin Crew
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ሰርተፊኬት ቢያንስ 200 ውጤት ያለው/ያላት
➤ ዕድሜ፦ ከ 21-30
➤ ቁመት፦ 1.58ሜ እና በላይ ለሴት (የክንድ ርዝማኔ 212ሴ.ሜ. ፤ 1.70ሜ እና በላይ ለወንድ
➤ ክብደት፦ ከቁመት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ
➤ ቋንቋ፦ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ደረጃ III (ሌሎች ቋንቋዎች መቻልም ጥሩ ነው)
የምዝገባ ቀናት፦
ከነሐሴ 04-08/2018 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታዎች፦
➫ አዲስ አበባ፦ በኦንላይን (የማመልከቻ ሊንክ በምዝገባ ቀናት አክቲቭ ይሆናል)
➫ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ
➫ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አምቦ
➫ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባ ምንጭ
➫ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ
➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር
➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ደሴ
➫ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ
➫ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ
➫ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር
➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ካምፓስ፣ ሐረር
➫ ሀዋሳ ኤርፖርት፣ ሀዋሳ
➫ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ
➫ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ
➫ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ
➫ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ነቀምቴ
➫ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰመራ
➫ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ
➫ ቦረና ዩኒቨርሲቲ፣ ያቤሎ
➫ ነገሌ ቦረና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ነገሌ
🔔 ምዝገባ ሲያደርጉ የአስፈላጊ ሰነዶችዎንና የትምህርት ማስረጃዎችዎን (የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ፣ የልደት ሰርተፊኬት፣ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የቀበሌ መታወቂያ) ዋናውንና ኮፒውን መያዝ ይጠበቅብዎታል፡፡
ከላይ የተገለፁ መስፈርቶችን ማሟላትዎን ያረጋግጡ፡፡ በሐሰተኛ መረጃ ለመመዝገብ ከሞከሩ ወዲያውኑ ከቅጥር ሂደቱ የሚወገዱ ይሆናል፡፡
@tikvahuniversity
3 396
+3
📢 ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
+++++++++++++++++++++++++++
አ.አ.ሳ.ቴ.ዩ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት (AASTU Community School) ብቁ እና ባለሙያ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል ፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ክፍት የስራ መደቦች ላይ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ከሃምሌ 13 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ላሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን ፡፡
3 396
ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሆኑ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና ተዘጋጅቷል።
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሚገኙ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና ማዘጋጀቱን አስታወቀ።
ተማሪዎች በቴክኖሎጂው ዘርፍ ራሳቸውን እንዲያንጹ ታስቦ በተዘጋጀው በዚህ መርሃ ግብር ላይ ፦
🤖 በፈንዳሜንታል ኦፍ ኤ.አይ፣
💻 ፕሮግራሚንግ፣
🧠 ማሽን ለርኒንግ፣
⚙️ በሮቦቲክስ እና IOT፣
📊 ዳታ ሳይንስ እና በሌሎችም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ስልጠናል ይሰጣል።
ተማሪዎች ተቋሙ ባዘጋጀውን ይፋዊ ድረ-ገጽ https://aii.et/summercamp በመጠቀም እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መመዝገብ የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
3 396
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ይፋ ተደረገ።
ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤታቸውን በ https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ።
መጀመሪያ የተቀመጠውን ሊንክ ይጫኑ በመቀጠል 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤት መመልከት ይቻላል።
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም
Via @tikvahuniversity
3 396
🌹በጨረታ (Tender/Procurement) ሂደት ውስጥ ፋይናንሻል ኢቫሉዌሽን (Financial Evaluation) እና አርትሜቲክ ኢቫሉዌሽን (Arithmetic Evaluation) በጨረታ ግምገማ ኮሚቴ (Tender Evaluation Committee) ወይም ለዚህ በተመደቡ የግዥ፣ የፋይናንስ እና የቴክኒክ ባለሙያዎች ይከናወናሉ።
1. አርትሜቲክ ኢቫሉዌሽን (Arithmetic Evaluation)
ይህ የሚያተኩረው በተጫራቾች ያቀረቡት የዋጋ ስሌት ላይ ነው።
የሚፈተሹ ነገሮች
Quantity × Unit Price = Amount በትክክል መሆኑ
Subtotal እና Total በትክክል መደመሩ
VAT ስሌት ትክክል መሆኑ
የBOQ ስህተቶች መኖራቸው
የዋጋ አሃዞች እና በፊደል የተጻፈው ዋጋ መጣጣማቸው
ምሳሌ
100 m³ × 2,000 ብር = 200,000 ብር መሆን ሲገባ
ተጫራቹ 180,000 ብር ቢጽፍ፣
➡️ ይህ አርትሜቲክ ስህተት (Arithmetic Error) ነው።
ኮሚቴው በጨረታ ሰነዱ መሠረት እርማት ያደርጋል።
2. ፋይናንሻል ኢቫሉዌሽን (Financial Evaluation)
አርትሜቲክ ማረጋገጫ ከተጠናቀቀ በኋላ ይደረጋል።
የሚፈተሹ ነገሮች
🌹የተስተካከለው ጠቅላላ ዋጋ
🌹የዋጋ ማስተካከያዎች
🌹ቅናሽ (Discount)
🌹የውጭ ምንዛሬ ቅየራ (ካለ)
🌹የግብር እና ሌሎች ክፍያዎች
👉የተጫራቾችን ዋጋ እርስ በእርስ ማወዳደር
🤔ዓላማ
ከቴክኒካል መስፈርቱ ያለፉ ተጫራቾች መካከል ዝቅተኛ ወይም ኢኮኖሚያዊ ተመጣጣኝ ዋጋ ያቀረበውን ለመለየት ነው።
🤔አንድነታቸው
🌹ሁለቱም የጨረታ ግምገማ አካል ናቸው።
🌹ሁለቱም በዋጋ መረጃ ላይ ይመሰረታሉ።
🌹ሁለቱም ለአሸናፊ ተጫራች ምርጫ መሠረት ይሆናሉ።
🌹ሁለቱም በግምገማ ኮሚቴ ይከናወናሉ።
🤔ልዩነታቸው
አርትሜቲክ ኢቫሉዌሽን -ፋይናንሻል ኢቫሉዌሽን
የሂሳብ ስህተት ማረጋገጥ -የዋጋ ውድድር ማወዳደር
በመጀመሪያ ይደረጋል - ከአርትሜቲክ በኋላ ይደረጋል
የስሌት ትክክለኛነትን ይመረምራል - የኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ይመረምራል
Quantity × Rate እና Total ይፈተሻል-Final Corrected Bid Price ይወዳደራል
🤔የተለመደ ቅደም ተከተል
🌶ጨረታ መክፈት
🌶የሰነዶች ሙሉነት ማረጋገጥ
🌶ቴክኒካል ኢቫሉዌሽን
🌶አርትሜቲክ ኢቫሉዌሽን
🌶ፋይናንሻል ኢቫሉዌሽን
🌶አሸናፊ ተጫራች መለየት
3 396
የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን የነጻ ትምህርት ዕድል ጥሪ አቅርቧል
#Ethiopia | የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ጠንካራ ሀገራዊ የኒውክሊየር መሰረተ ልማት ለመገንባት የሚያስችሉ ከፍተኛ ባለሙያዎችን ለማፍራት ለኢትዮጵያውያን ተማሪዎችና ሰልጣኞች በሩሲያ የነጻ ትምህርት ዕድል ማመቻቸቱን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን በሩሲያ በሚገኙ ስመጥር የሳይንስና የምህንድስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ መማር የሚፈልጉ ብቁ አመልካቾች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
የሚሰጡ የትምህርት ዘርፎች በኒውክሊየር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነዚህን ዘርፎችንም ያካትታል ፡-
- Nuclear Power Engineering and Heat Physics (BSc & MSc)
- Nuclear Physics and Technology (BSc)
- Nuclear Power Plants Design, Operation and Engineering (BSc)
- Heat Power Engineering (BSc)
- Management in Technological Systems (MA)
የመወዳደሪያ መስፈርቶች ?
• ለመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት ያልበለጠ እና የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ አማካኝ ውጤታቸው 500 እና ከዚያ በላይ የሆነ።
• ለሁለተኛ ዲግሪ (MSc/MA) ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት ያልበለጠ እና በሳይንስና ምህንድስና ዘርፍ በከፍተኛ ውጤት የተመረቁ።
ሴት አመልካቾች ለዘርፉ እንዲበረታቱ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል።
መስፈርቱን ምታሟሉ አመልካቾች ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 5 የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን እና ደጋፊ ሰነዶቻችሁን በPDF በማዘጋጀት በኮሚሽኑ የኢሜል አድራሻ enecinfo@enec.gov.et መላክ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 396
#Update
የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና በድጋሚ በግል ለመፈተን እየተጠባበቃችሁ የምትገኙ አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ይካሔዳል፡፡
በመሆኑም የመመዝገቢያ ሊንኩን https://exam.ethernet.edu.et በመጠቀምና የተዘረዘሩ መስፈርቶችን በማሟላት ከግንቦት 08-12/2018 ዓ.ም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር በቴሌብር በኩል መክፈል የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ የግድ የሚያስፈልግ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል፡፡
@tikvahuniversity
3 396
Repost from Tikvah-University
#Update
የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና በድጋሚ በግል ለመፈተን እየተጠባበቃችሁ የምትገኙ አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ይካሔዳል፡፡
በመሆኑም የመመዝገቢያ ሊንኩን https://exam.ethernet.edu.et በመጠቀምና የተዘረዘሩ መስፈርቶችን በማሟላት ከግንቦት 08-12/2018 ዓ.ም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር በቴሌብር በኩል መክፈል የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ የግድ የሚያስፈልግ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል፡፡
@tikvahuniversity
