es
Feedback
[[ተምሳሌቶችሺን ሰለፎችሺን አስታዉሺ]]

[[ተምሳሌቶችሺን ሰለፎችሺን አስታዉሺ]]

Ir al canal en Telegram

وَأَعْظَمُ مَا أَمَرَ اللَّهُ بِهِ التَّوْحِيدُ، وَهُوَ : إِفْرَادُ اللَّهِ بِالْعِبَادَةِ. وَأَعْظَمُ مَا نَهَى عَنْهُ الشِّركُ، وَهُوَ: دَعْوَةُ غَيْرِهِ مَعَهُ، https://t.me/LetusfearAllah ጆይን በሉ

Mostrar más
6 473
Suscriptores
-324 horas
-167 días
-7430 días
Archivo de publicaciones
አድስ ሙሐደራ ደሴ አረብ ገንዳ መስጅድ 💉ስለ ሽርክና ተያያዥ ርዕሶች ምረጥ ምክር 🎙በኡስታዝ አቡ ሒዛም (ሀፊዘሁሏህ) t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

ዛሬ ከአሱር ቡሀላ ደሴ ሸዋበር መስጅድ ኡስታዝ አቡ ሒዛም ደዕዋ ያደርጋል ደሴዎች ተዘጋጅታችሁ ጠብቁን

📚የሠለፍያ ጎዳና ከጥመት ለመዳን ዋና ዋስትና ነው 🎙️ ውዱ ኡስታዛችን፦ ኡስታዝ ኸድር አህመድ አላህ ይጠብቀውና t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

3ኛው የኪታብ ኮርስ አልቀዋኢዱል ሙስላ ተጀምሯል በታላቁ ሸይኽ ዐሊይ አራዚህይ ሀፊዘሁሏህ https://t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy?livestream=144b3a59c732531013

• በማይመለከትሽ ነገር ውስጥ አትግቢ ተግባርሽ እንጅ ንግግርሽ አይብዛ ብዙ ማዳመጥ እንጅ ! ብዙ ማውራት አዋቂ አያደርግም! ንግግርሽ ያነሰ ተግባርሽ የበዛ እንስት ሁኚ ! = t.me/https_Ass
በማይመለከትሽ ነገር ውስጥ አትግቢ ተግባርሽ እንጅ ንግግርሽ አይብዛ ብዙ ማዳመጥ እንጅ ! ብዙ ማውራት አዋቂ አያደርግም! ንግግርሽ ያነሰ ተግባርሽ የበዛ እንስት ሁኚ ! = t.me/https_Asselefya1

ለመርከዝ ቢላል የሒፍ ዝ ተማሪወች እየተሰጠች ያለች ሪሳላ https://t.me/Ibnu_siraj_Alkemissie?livestream=06845ddaff1b942e89

📚በኮበልቻው ኮርስ ላይ የሚቀሩ ኪታቦች🌿📚 ይህ ደውራ በሐበሻ ምድር ለምትገኙ የእውቀት ፈላጊዎችና የሱና ወዳጆች የቀረበ ታላቅ የምስራችና መለኮታዊ ስጦታ ነው! የጥንቁቅ ሰለፎችን ፈለግ የተከተሉ የዒልምና የዚክር መድረኮችን ለሚናፍቁ፣ በሱና ጥማት ለደረቁ ልቦች እነሆ የዒልም ብርሃን በሀገራችሁ መጥቶላችኋል። በኮንቦልቻ ከተማ የሚካሄደውን ታላቅና የተባረከ የዒልም ዑደት (ደውራ) ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው፦ 🏛️ ቦታ– ኮምቦልቻ ከተማ – መስጂደል አንሷር ነው ይሄን ኮርስ የሚሰጡት ታዋቂው የሐዲስ ሊቅ፣ አስተማሪና መካሪው ሸይኽ አል-ሙሐዲስ አቡል ሐሰን ዐሊ ቢን አሕመድ አል-ራዚሒ (አላህ ይጠብቃቸው) ናቸው። ሸይኹ በሐዲስ፣ በዐቂዳና በመንሐጅ ዙሪያ ጠቃሚ የሆኑ እውቀቶችንና መሠረታዊ ግንዛቤዎችን በሚከተሉት ኪታቦች ማብራሪያ አማካኝነት ለተማሪዎች ያካፍላሉ፦ 📚በኮርሱ ላይ የሚቀሩ የኮርሱ ኪታቦች 1️⃣ «ኑኽበቱል ፊከር» «نخبة الفكر في مصطلح أهل الأثر» (በሐዲስ የቃላት መፍቻ/መስፈርት ዙሪያ) – በታላቁ የሐዲስ ሊቅ ኢብኑ ሐጀር አል-ዐስቀላኒ። 2️⃣ «አል-ቀዋዒዱል ሙስላ» «القواعد المثلى في صفات الله وأسمائه الحسنى» (ስለ አላህ ውብ ስሞችና ባህሪያት) – በታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ሷሊሕ አል-ዑሠይሚን። 3️⃣ «መታ የኩኑ አር-ረጁሉ ሚን አህሊስ-ሱና» متى يكون الرجل من أهل السنة وبمَ يخرج منها»: (አንድ ሰው መቼ ከሱና ሰዎች ይመደባል? በምንስ ይወጣል?) – በታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ዐብዲላህ አል-ኢማም ተፅፎ፣ በሸይኽ ዐሊ አል-ራዚሒ ሸርህ የተደረገው። ⚠️ እነዚህ ኪታቦች በቤታችሁ  ያሏችሁ ይዛችሁ ኑቶሎ ለሌላችሁ ደግሞ  ኪታቦችን ስላዘጋጄን እኛ እንሰጣችኋለን ምንም ክፍያ የለውም 🎙️ በተጨማሪም በመድረኩ ላይ የተለያዩ ታላላቅ መሻይኾችና የእውቀት ተማሪዎች የሚሳተፉባቸው ወቅታዊ ምክሮችና የዒልም ውይይቶች ይካሄዳሉ። 🌱 የዒልም ፈላጊ ሆይ! ና ተቀላቀል። 🌱 የሐዲስና የአሠር ተማሪ ሆይ! ዕድሉን ተጠቀም። 🌱 የሱና ወዳጅ ሆይ! ለመገኘትና ለመቅሰም ትጉ። የሸይኽ አል-ሙሐዲስ ዐሊ ቢን አሕመድ አል-ራዚሒ በእነዚህ ቀናት በሀገራችን መገኘት እጅግ ውድ አጋጣሚ ነው። እርሳቸው ለነቢዩ (ﷺ) ሐዲሶች ባላቸው ጥንቃቄ፣ ለሱና ባላቸው ጽናትና ትክክለኛውን የሰለፊያ ደዕዋ በማሰራጨት የሚታወቁ በመሆናቸው፤ ማንኛውም ተማሪ ይህንን ታላቅ ዕድል ሊያመልጠው አይገባም። 📅 የደውራው ጊዜ፦ ከቅዳሜ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም  ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀን የሚቆይ ይሆናል። 🕌 ይሄ ጥሪ፦ ለሁሉም ሙስሊሞች ክፍት ነው። ለሴቶችም በቂ ቦታ አለን አላህ ይህንን የዒልም መድረክ የተባረከ እንዲያደርግልን፣ ሸይኻችንንም በጤናና በስኬት እንዲጠብቅልን እንለምነዋለን። ይህ ደውራ ጠቃሚ እውቀት የሚሰራጭበት፣ ሱና ሕያው የሚሆንበት፣ ቢድዓና መከፋፈል የሚከሽፍበት ሰበብ እንዲሆን ምኞታችን ነው። ለዚህ ስራ አስተዋጽኦ ላደረጉ፣ ላገዙና ለጠቆሙትም አላህ ታላቅ ምንዳን ይክፈላቸው። ይሄን ፕሮግራም በLIVE መካታተል ለምትፈልጉ በዚህ በሌሎችም ቻናሎች ይተላለፋል🌹t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy 🌹t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

የማይዘጋው በር… ሰው የሚሉት ፍጥረት እንደ ውሃ የጠማሽ፤ እህ የሚል አድማጭ ጆሮ የናፈቀሽ: አብሽር የሚለው ቃል ከልብሽ የራበሽ፤ ስትታይ ደልቶሻል ሀዘን የማያውቅሽ፤ እንደ እሷ በሆንን ብለው ሚመኙሽ አንች ግን በውስጥሽ ህመምሽን ቋጥረሽ፤ ብቸኝነትሽን ለብቻሽ ችለሽ፤ ላይ ታች ትያለሽ ሰሚን ተርበሽ። አይንሽ ተንከራቶ ከጥበቃ ብዛት፤ ጥግን ይፈልጋል እንባውን ለማንባት፤ ከሰው ደጅ ቆመሻል ምላሽን ፍለጋ፤ ግና ማንም የለም ሊሆንሽ መጠጊያ። እኔ ግን ልንገርሽ አንድ ከልብ ወዳጅ፤ በሩ የማይዘጋ ሁሌም ያለ ከደጅ፤ ወደ አዛኙ ጌታ ተጓዢ ወደ እርሱ ጋር። የውስጥሽን እሳት የሚያቃጥልሽን፤ ከሰው ፊት ለመቆም ምክንያት የሆነሽን፤ ያንን ሰቅጣጭ ህመም የሚያስለቅስሽን፤ ንገሪው ለአንድዬ ሁሉ ስሜትሽን። አንዱንም ሳትተይ አውጊው ወጎችሽን፤ "ሰለቸሽኝ" አይል አትርሽ ይህንን፤ በቃኝ ሂድልኝ" ብሎ አይገፋሽም፤ አብዝተሽ ቅረቢው ፍፁም አያሳፍርሽም!

🌟 ቲለዋ:-በሙሽራው ወንዲማችን ሙራድ" አቡ ኢምራን 🎤▫️ https://t.me/Mf11q https://t.me/Mf11q

🌟 ቲለዋ:-በሙሽራው ወንዲማችን ሙራድ" አቡ ኢምራን 🎤▫️ https://t.me/Mf11q https://t.me/Mf11q

ዛሬ በኢማን ጥሩ ሁኔታ ላይ መገኘትህ፣ነገ በዚሁ ላይ መጽናትህን አያመለክትም፣አላህ እንጂ ራስህ ለራስህ ዋስትና መሆን አትችልም። ስለዚህ የደከሙትን አትናቅ።  ባልገራላቸው አትሳቅ። የሰው ልጅ  ቀልብ ሁሉ በአላህ እጅ ናት። እሱም እንደሻው ይገለባብጣታል። በኃጢአተኛ ላይ አትጀነን። እኔ ከሱ የበለጥኩ ነኝ አትበል።በንቀት ዐይንም አትመልከተው።

አዲስ የ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ ሪሳላ ነች

⚠️ለኻሊድ ክብሮም ሹቡሃቶች የተሰጠ አጠር ያለች ረድ❗️ ⚠️ኻሊድ ክብሮም የተባለው ግለሰብ የሚዘራው መርዝ በአሁኑ ሰዓት በብዙ የዋህ ሙስሊሞች ዘንድ "አዲስና ዘመናዊ እይታ" እየመሰለ ቀልብን እየሰረቀ ይገኛል። ነገር ግን ንግግሩንና አካሄዱን ላስተዋለ ሰው፣ ይህ ግለሰብ የጥንቶቹን "ቁርኣንዮች" መንገድ በመከተል የኢስላምን መሰረት ለመናድ እየሰራ መሆኑን መረዳት ይቻላል። ⚠️ አላህ ዲኑን የሚጠብቁለትና የጠማሞችን ትርጓሜ የሚያጋልጡለት ኡለሞችንና ተማሪዎችን በየዘመኑ ያስነሳል። ዛሬ ላይ ደግሞ "ቁርኣን በራሱ ተብራርቷል፣ የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይሻም" በሚል የቀለም ቅብ ዲኑን ሊበርዙ የሚሞክሩ ግለሰቦች ተከስተዋል። ይህ ካሊድ ክብሮም የሚባል ግለሰብ በተናገራቸው ንግግሮች ላይ "ቁርኣንን ከቁርኣን ውጭ ያለ አካል የሚያብራራው የለም" በማለት የነቢዩን ﷺ ሱና ሙሉ በሙሉ ዋጋ ቢስ ለማድረግ ደፍሯል። 1ኛ. "ቁርኣን የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይሻም" የሚለው ንግግር ሁክም (ፍርድ) ምንድን ነው የሚለውን እንይ፦ ⚠️አንድ ሰው "ቁርኣን የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይፈልግም" ወይም "ቁርኣን ብቻ ይበቃናል፣ ሱና አያስፈልግም" ካለ በዑለሞች ዘንድ ያለው ፍርድ ከባድ ኩፍር (ከኢስላም መውጣት) ነው። ⚠️ ኢማም አስ-ሱዩጢይ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ "አዋጅ! እወቁ... የነቢዩን ﷺ ሐዲስ (ንግግርም ይሁን ተግባር) በንግግርም ይሁን በተግባር ውድቅ ያደረገ፣ ሐዲሱ ሐሰን ይሁን ሶሒሕ መረጋገጡን እያወቀ ውድቅ ያደረገ ሰው፤ ከኢስላም ክበብ ወጥቷል፤ ከአይሁዶችና ከነሳራዎች ጋር (በፍርዱ) ይመደባል ብለዋል።" (ሚፍታሕ አል-ጀናህ፡ 14) ⚠️ኢብኑ ሐዝም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ "አንድ ሰው 'እኛ የምንይዘው ቁርኣን ላይ ያገኘነውን ብቻ ነው' ካለ፤ እርሱ በሁሉም ሙስሊሞች ስምምነት (ኢጅማዕ) ካፊር ነው።" (አል-ኢሕካም፡ 2/80) ለምን ካፊር ይባላል? ምክንያቱም አላህ በቁርኣን ውስጥ ነቢዩን ﷺ እንድንታዘዝ፣ የሳቸውን ማብራሪያ እንድንይዝ በብዙ ቦታዎች አዝዟል። የሳቸውን ማብራሪያ "አያስፈልግም" የሚል ሰው የአላህን ትዕዛዝ "ስህተት ነው" እያለ ስለሆነ ነው። 2ኛ. የሰለፎችና የታላላቅ ኡለሞች ንግግር ስለ ሱና አስፈላጊነት እንመልከት ፦ ⚠️ኢማም አል-አውዛዒይ (ረሒመሁላህ)፦ "ቁርኣን ወደ ሱና ያለው ፍላጎት፣ ሱና ወደ ቁርኣን ካለው ፍላጎት ይበልጣል።" (ማለትም ቁርኣን ጠቅለል ያለ (ሙጅመል) በመሆኑ፣ ሱና ካላብራራው በስተቀር ልንተገብረው አንችልም)። ⚠️ ያሕያ ቢን አቢ ከሢር (ረሒመሁላህ)፦ "ሱና በቁርኣን ላይ ፈራጅ (መሪ) ነው እንጂ ቁርኣን በሱና ላይ ፈራጅ አይደለም።" (ይህ ማለት ሱናው ቁርኣኑ እንዴት መረዳት እንዳለበት ይወስናል ማለት ነው)። ⚠️ ኢማም አል-በርበሃሪ (ረሒመሁላህ)፦ "አንድ ሰው ሐዲስን ሲሰማ 'ይህንን ተወውና ቁርኣንን አምጣልኝ' ካለ፤ እወቅ እርሱ ዚንዲቅ (ከሀዲ) መሆኑን!" (ሸርሕ አስ-ሱናህ) ⚠️ኢማም አሕመድ፦"ሱና ቁርኣንን ያብራራል፣ ይመራልም።" ⚠️ሸይኽ ቢን ባዝና ሸይኽ አልባኒ፦** ሱናን የሚክዱ ወይም የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ አይሻም የሚሉ ግለሰቦች ከኢስላም መንገድ የወጡ (ሙርተድ) መሆናቸውን በሰፊው አስረድተዋል። ⚠️ኻሊድ ክብሮም "ቁርኣን በራሱ ተብራርቷል" ሲል አላህ ለነቢዩ ﷺ የሰጣቸውን ስልጣን እየካደ ነው። - ﴿وَأَنزَلْنَا إِلَيْكَ الذِّكْرَ لِتُبَيِّنَ لِلنَّاسِ مَا نُزِّل إِلَيْهِمْ﴾ “ለሰዎችም ወደ እነርሱ የተወረደውን (ቁርኣን) ታብራራላቸው ዘንድ ቁርኣንን ወደ አንተ አወረድን።” (አን-ነሕል 44)። አላህ "ቁርኣን በራሱ ይብራራል" አላለም፤ "አንተ መሐመድ ሆይ ታብራራላቸው ዘንድ" ነው ያለው። ⚠️ነቢዩ ﷺ ይህ ዓይነቱ ጥመት ወደፊት እንደሚመጣ ቀድመው አስጠንቅቀው ነበር፦ «أَلَا إِنِّي أُوتِيتُ الْقُرْآنَ وَمِثْلَهُ مَعَهُ، أَلَا يُوشِكُ رَجُلٌ شَبْعَانُ عَلَى أَرِيكَتِهِ يَقُولُ: عَلَيْكُمْ بِهَذَا الْقُرْآنِ...» “አዋጅ! እኔ ቁርኣንንና መሰሉን (ሱናን) አብሮ ተሰጥቻለሁ። አዋጅ! አንድ በምቾት ወንበሩ ላይ የተደገፈ ሆዱ የጠገበ ሰው፦ 'ቁርኣን ብቻ ይበቃችኋል' የሚልበት ጊዜ ሊመጣ ተቃርቧል...ብለዋል።” (አቡ ዳውድ፡ 4604) ኻሊድ ክብሮም ልክ ነቢዩ ﷺ እንዳሉት የቁርኣን አንቀጾችን እየቆነጸለ፣ የነቢዩን ﷺ ትምህርት "አያስፈልግም" እያለ ነው። የነቢዩን ﷺ ማብራሪያ ውድቅ ማድረግ ማለት፦ * እንዴት እንደምንሰግድ (በቁርኣን ውስጥ የረከዓ ብዛት የለም!) * እንዴት ዘካት እንደምንከፍል (በቁርኣን ውስጥ ኒሷብ የለም!) * እንዴት ሐጅ እንደምናደርግ... ይህንን ሁሉ የኢስላም መሰረት ማፍረስ ማለት ነውና። ከዚህ ጠሞ አጥማሚ ሰውዬ ተጠንቀቁ ⚠️ ይሄ ጠሞ አጥማሚ ካሊድ ክብሮም ከዚህ በፊትም ስለ ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም) እና ስለ ተውራት የዘባረቃቸው ውሸቶችም አሉ ፦ ⚠️ የዕቁብ ኢስራኢል አይደለም ማለቱ ይሄ የግለሰቡን የቋንቋና የታሪክ ድንቁርና ብቻ ሳይሆን ግልጽ የሆነ ቅጥፈት ያሳያል። * ስለ ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም)፦ አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ይላል፦ ﴿كُلُّ الطَّعَامِ كَانَ حِلًّا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ إِلَّا مَا حَرَّمَ إِسْرَائِيلُ عَلَىٰ نَفْسِهِ﴾ *“ምግብ ሁሉ ለእስራኤል ልጆች የተፈቀደ ነበር፤ እስራኤል (ያዕቆብ) በራሱ ላይ እርም ካደረገው በስተቀር።”* (አል-ዒምራን 3:93) ሙፈሲሮች በሙሉ "እስራኤል" ማለት ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም) መሆኑን በአንድ ድምጽ (ኢጅማዕ) ተስማምተዋል። * ካሊድ ክብሮም ስለ ተውራትም የቀጠፈው ቅጥፈት አለ፦ ተውራት ለሙሳ (ዐለይሂ ሰላም) የወረደ መሆኑን ቁርኣን በብዙ ቦታዎች ይገልጻል። ﴿ثُمَّ آتَيْنَا مُوسَى الْكِتَابَ تَمَامًا عَلَى الَّذِي أَحْسَنَ وَتَفْصِيلًا لِّكُلِّ شَيْءٍ﴾ (አል-አንዓም 154) (አል-አንዓም 154፣ አል-አዕራፍ 145)። ይህንን የሚክድ ሰው የአላህን ቃል እያስተባበለ ነው። ሌሎችም ብዙ ማስረጃዎች አሉ ። ⚠️ኻሊድ ክብሮም የተባለው ግለሰብ የሚከተለው መንገድ "ቁርኣን ብቻ በቂ ነው " በሚል ሽፋን ኢስላምን የማፍረስ መንገድ ነው። ቁርኣንን ከነቢዩ ﷺ ትርጓሜና ከሰለፎች ግንዛቤ ነጥሎ "በራሴ ጭንቅላት እተረጉማለሁ" ማለት፣ ቁርኣንን ለስሜት መጫወቻ ማድረግ ነው። ሱናን የካደ ሰው ደግሞ ሶላቱንም፣ ዘካውንም፣ ሐጁንም መተግበር አይችልም፤ ምክንያቱም የእነዚህ ሁሉ ዝርዝር ሕግጋት የሚገኙት በሱና ውስጥ ብቻ ነውና። ወንድምና እህቶቼ ይህንን "ጠሞ አጥማሚ" ግለሰብ ከመስማት ተጠንቀቁ! ዲናችሁን ከታማኝና የሰለፎችን መንገድ ከሚከተሉ ኡለሞችና ኡስታዞች ተማሩ። አላህ በቁርኣን አጥርቶ የነገረንን እውነት "አይደለም" የሚል ሰው፣ ነገ የአላህን ሕግጋት በሙሉ "አያስፈልጉም" ማለቱ አይቀሬ ነውና ተጠንቀቁ አስጠንቅቁ። ሸር በማድርገ ለሌሎችም አድርሱ t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy