es
Feedback
Addis Admass

Addis Admass

Ir al canal en Telegram

የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ ===== አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv የእርስዎና የቤተሰብዎ

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Addis Admass

El canal Addis Admass (@adissadmas) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 17 821 suscriptores, ocupando la posición 12 556 en la categoría Noticias y medios y el puesto 1 888 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 17 821 suscriptores.

Según los últimos datos del 22 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 68, y en las últimas 24 horas de 5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 9.56%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.69% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 1 703 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 371 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 6.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ ===== አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv የእርስዎና የቤተሰብዎ

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 23 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

17 821
Suscriptores
+524 horas
-47 días
+6830 días
Archivo de publicaciones
"የዱባይ ታርጋ እብደት" ወደኛ ሃገር ሊመጣ.... ? በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ እየተተገበረ ያለው አዲሱ የብሔራዊ ታርጋ ቅያሬ እና ውድ ክፍያው የማኅበራዊ ሚዲያው መነጋገሪያ ሆኗል። ስለታርጋ ከ
"የዱባይ ታርጋ እብደት" ወደኛ ሃገር ሊመጣ.... ? በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ እየተተገበረ ያለው አዲሱ የብሔራዊ ታርጋ ቅያሬ እና ውድ ክፍያው የማኅበራዊ ሚዲያው መነጋገሪያ ሆኗል። ስለታርጋ ከተነሳ ዱባይ ላይ የገጠመኝን አንድ አስገራሚ ትዝታ ላውራችሁ። ባለፈው ታኅሣሥ ወር ለአንድ የሥራ ጉዳይ ወደዚያው ሄጄ ሳለ፣ አቡዳቢን ጉብኝተን ስንመለስ ታርጋዋ ሶስት ቁጥሮች ብቻ የተጻፉባት አንድ ስፖርት መኪና በብርሃን ፍጥነት አለፈችን።እኛ ብዙም አልደነቀችን። ለአስጎብኛችን ግን የወሬ ርዕስ ሰጠችው። "ይቺ መኪና በዚህ ሰዓት እንዴት ተገኘች?" አለ። አልገባንም። በዚያው መነሻ ስለ ዱባይ ታርጋ ማውራት ጀመረ። ለካ ዱባይ ውስጥ ታርጋ የሀብትና የክብር ማዕረግ መለኪያ ነው። ሃብት የሚለካው በመኪናው ሞዴልና ውድነት ሳይሆን በመኪናው ታርጋ ላይ ባሉት ቁጥሮች ማነስ እና ከቁጥሩ ፊት በሚቀመጡት ፊደላት (Codes) ቅደም ተከተል ነው። አስጎብኚው እንዳብራራልን ከሆነ በዱባይ መንገድ ላይ ለሚንቀሳቀሰው አብዛኛው ተራ ሕዝብ ለሚነዳው መኪና፣ ለታክሲዎችና ለመደበኛ ሠራተኞች የሚሰጠው ታርጋ ባለ 5 ዲጂት ነው። ከተራው ሕዝብ ለየት ማለት የሚፈልጉ ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ባለሙያዎችና መካከለኛ ነጋዴዎች ደግሞ ባለ 4 ዲጂት ታርጋን ከፍ ባለ ዋጋ ይገዛሉ።

እውነተኛው የቅንጦትና የባለሀብትነት ዓለም የሚጀምረው ግን በባለ 3 ዲጂት ታርጋዎች ላይ ነው። እነዚህ ታርጋዎች የትላልቅ ኩባንያዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች መለያ በመሆናቸው የመሸጫ ዋጋቸው እስከ መቶ ሺህዎች ዶላር ሊያሽቅብ ይችላል። በጠቅላላው 90 አማራጮች ብቻ ያሏቸው ብርቅዬዎቹ ባለ 2 ዲጂት ታርጋዎች ደግሞ ሌላ አለም ናቸው። ለታዋቂ ቢሊየነሮች እና ለንጉሣዊ ቤተሰብ አባላት የቅርብ ወዳጆች ብቻ የሚፈቀዱ ፣ እንደወርቅ እና እንደውድ ንብረት ተገዝተው ተቀምጠው አንድ ቀን ገበያ ሲወጡ ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ንብረቶች ናቸው። የመግዣ ዋጋቸውም ለሚሊየነሮች እንኳን የሚቀመስ አይደለም። የዱባይ ሀብት የመጨረሻ ጥግ እና የንግሥና ማዕረግ የሚገለጸው ግን በባለ አንድ ዲጂት ታርጋዎች ነው። ታርጋ ቁጥር አንድ በተለምዶ ለዱባይ ገዥ ብቻ የሚቀመጥ ሲሆን፣ ከ2 ጀምሮ ያሉት ሌሎቹ ቁጥሮች ደግሞ በበጎ አድራጎት ጨረታዎች ላይ እየወጡ ታርጋው ከሚለጠፍበት በዓለም ላይ ካሉት ውድ መኪናዎች አንዱ ከሆነው መኪና ዋጋ በብዙ እጥፍ ድርብ ዶላር ይሸጣሉ። የዱባይ ታርጋ ዋጋ እብደት በአሃዞች እያነሱ መሄድ ብቻ የሚያበቃ እንዳይመስላችሁ። ከቁጥሮቹ ፊት የሚቀመጡት እንደ "A, B, AA, P" ያሉት የአልፋቤት ፊደላት (Codes) የራሳቸው የሆነ ትልቅ የዋጋ ተፅዕኖ አላቸው። ለምሳሌ በዱባይ የታርጋ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነው "Code A" ከሌሎቹ ፊደላት ይልቅ እጅግ ውድ እና ተፈላጊ ሲሆን፣ ሁለት ተመሳሳይ ፊደላት (ለምሳሌ AA) ያላቸው ታርጋዎች ደግሞ ይበልጥ ብርቅዬና ውድ ናቸው። አንድ ወቅት "P 7" የተሰኘው ታርጋ በዱባይ ጨረታ ላይ ወደ 15 ሚሊዮን ዶላር (55 ሚሊዮን ድርሃም) በመሸጥ የዓለምን የክብረ ወሰን ሰብሯል ብሎናል አስጎብኛችን። ያ ቆቅ የሆነ ፓኪስታናዊ አስጎብኚ እንደነገረን እነዚህ ባለሁለትና ባለአንድ ዲጂት መኪኖች በሆነ አጋጣሚ መንገድ ላይ ከተገኙ ሰማይ ላይ ብቅ ብሎ እንደሚጠፋው እንደተወርዋሪ ኮከብ ላያቸው ሁሉ ሰው ብርቅ ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚወጡት ማታ ማታ ተራው ህዝብ ቤቱ ሲከተት ለመዝናናት ብቻ ነው። ለምሳሌ ቡርጅ ኸሊፋ ሆቴል አካባቢ ፓርክ ለማድረግ ብቻ እነዚህ መኪኖች በሰዓት እስከ 10 ሺህ ዶላር ድረስ ይከፍላሉ። እነዚህ ታርጋዎች ልክ እንደ ቤት ወይም መሬት የሀብት ማከማቻ እና የኢንቨስትመንት ንብረት ተደርገው ስለሚወሰዱ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ዋጋቸው በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ይሄዳል። ታርጋን የሀብትና የስኬት መለኪያ አድርጎ ቢሊየነርነትን ማሳየት የሚቻለው እንደ ዱባይ ባለ ፍጹም ሰላምና የደህንነት ዋስትና ባለው ሀገር ላይ ብቻ ነው ወዳጄ ! እንደ እኛ ባሉ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ባየለባቸው ሀገራት ግን እንዲህ ዓይነቱን ቅንጦትና ሀብት ለሕዝብ ማሳየት ይዞት የሚመጣው ጦስ ቀላል አይሆንም። በመጨረሻም አስጎብኚያችን እየሳቀ የነገረንን አልዘነጋውም። "የዛሬ 54 ዓመት ገደማ (እኛ አብዮት አበጠ፣ ፈነዳ እያልን ስንጫወት ማለት ነው ) በአሸዋ መንገድ ላይ ግመል ይነዱ የነበሩት የዱባይ ነዋሪዎች (ኢሚራቲዎች) ዛሬ በዚያው ምድር ላይ የፋርስ ምንጣፍ መስሎ በተዘረጋ የኮንክሪት አስፓልት ላይ ቡጋቲ፣ ቤንትሊ እና ላምቦርጊኒ ይነዳሉ" አለን። ዱባይ የዓለማችን የቢሊየነሮች መናኸሪያ በመሆኗ ለታርጋ ይህንን ያህል ዕብድ ብር ማውጣት ላይደንቃት ይችላል። በብዙ ነገራችን ዱባይን እየኮረጅን ለምንመስለው ለኛ ደግሞ የዚህ የታርጋ ቅያሬ ሃሳብ ቀስ በቀስ ወደዚህ ሊያደርሰን ይችል ይሆን? ለማንኛውም ወደቀልባችን እንመለስና አሁን ባለን ነባራዊ አቋም አዲሱ ታርጋ እጅግ በጣም ውድ ነው። ክፍያውስ ከሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታና ከሕዝቡ የኢኮኖሚ አቅም ጋር የሚጣጣም አይደለም። አቶ ግርማ ሰይፉ በአንድ አስተያየቱ ባሰፈረው አማራጭ ሃሳብ እንዳለው፣ የታርጋ ዋጋው መተመን ያለበት ባለመኪናው እንደሚነዳው መኪና ዋጋ (በሌላ አነጋገር የባለቤቱ የገቢ አቅም) እየታየ ነው። የ60 ሚሊዮን ብር ሊንኮን ናቪጌተር እና የ 3 ሚሊዮን ብር ቢዋይዲ እኩል 56 ሺህ ብር ለታርጋ መክፈላቸው ቀልድ ነው። 20 ቀን ቆማ 1 ቀን ለምትሰራ ቮልስ ዋገንና ላዳ ታርጋ 40 ሺህ ብር መተመንም እሮሮና እንጉርጉሮ ካልሆነ በቀር ሌላ ትርፍ አያመጣም። Melaku Berhanu-

የክረምት ሥልጠና ለልጆችዎ!
የክረምት ሥልጠና ለልጆችዎ!

ታዋቂው ኮሜዲያን የመጽሐፉን ገቢ ሙሉ በሙሉ ለበጎ አድራጎት አበረከተ የሕፃናት መጻሕፍት ደራሲና የልጆች ፕሮግራም አዘጋጁ ታዋቂው ኮሜዲያን አስረስ በቀለ (ቼሪ)፣ ሰሞኑን በወመዘክር ካስመረቃቸው ሁለ
+1
ታዋቂው ኮሜዲያን የመጽሐፉን ገቢ ሙሉ በሙሉ ለበጎ አድራጎት አበረከተ የሕፃናት መጻሕፍት ደራሲና የልጆች ፕሮግራም አዘጋጁ ታዋቂው ኮሜዲያን አስረስ በቀለ (ቼሪ)፣ ሰሞኑን በወመዘክር ካስመረቃቸው ሁለት አዳዲስ የሕፃናት መጻሕፍት መካከል የመጀመሪያውን መጽሐፍ የሽያጭ ገቢ ሙሉ ለሙሉ ለሙዳይ በጎ አድራጎት ድርጅት በስጦታ አበርክቷል። ከ15 በላይ የልጆች ተረት መጻሕፍትን ለንባብ ያበቃውና በፈረንጆቹ 2022 እውቅና የተቸረው አንጋፋው ባለሙያ፣ ይህንን ታላቅ የበጎ አድራጎት ስጦታ ያበረከተው በችግር ውስጥ ያሉ ሕፃናትን፣ እናቶችንና አረጋውያንን በመደገፍ ለሚታወቀውና በአቃቂ ቃሊቲ ለሚገኘው የሙዳይ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው። የድርጅቱ መሥራች ወይዘሮ ሙዳይ ምትኩ ለአስረስ በቀለ (ቼሪ) ያላቸውን ከልብ የመነጨ ምስጋና ገልጸው፣ ለመላው የሀገራችን ሕዝብም ጥሪ አቅርበዋል። ደጋግ ኢትዮጵያውያን ይህንን ጠቃሚ የሕፃናት መጽሐፍ በመግዛት፣ በአንድ በኩል የልጆቻቸውን የዕውቀት አድማስ እንዲያሰፉ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የሽያጩን ገቢ በቀጥታ ለሙዳይ በማዋል አቅመ-ደካሞችንና ሕፃናትን እንዲደግፉ በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። #Ethiopia #Cheri #AsresBekele #MudayCharity #Kindness #EthiopianArt #SupportEachOther #Humanity First

ሆስፒታሉ የሕክምና ክህሎትን የሚፈትን ተግዳሮት ገጥሞታል! የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል እጅግ አስገራሚ እና የህክምና ክህሎትን የሚፈትን ክስተት አስተናግዷል። ሆስፒታሉ በሰውነት አካላቸው ተ
ሆስፒታሉ የሕክምና ክህሎትን የሚፈትን ተግዳሮት ገጥሞታል! የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል እጅግ አስገራሚ እና የህክምና ክህሎትን የሚፈትን ክስተት አስተናግዷል። ሆስፒታሉ በሰውነት አካላቸው ተጣብቀው የተወለዱ መንታ ሴት ህፃናትን መቀበሉን አስታውቋል። 📍የሆስፒታሉ የህክምና ቡድን ህፃናቱን በጤናማ ሁኔታ ለመጠበቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ ህፃናቱ የተጣበቁባቸውን አካላት ለመለየት የሚደረገው የቀዶ ህክምና እና ተያያዥ የህክምና ሂደቶች ውስብስብ በመሆኑ ተጨማሪ ድጋፍ ያስፈልጋል። በመሆኑም ጤና ተቋማትና ባለሙያዎች፣ ተመሳሳይ የህክምና ልምድ ያላቸው ከፍተኛ የህክምና ማዕከላት ፣ በዘርፉ ስፔሻሊስት የህክምና ባለሙያዎች በጉዳዩ ላይ ምክክር ቢያደርጉ፣ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ እንዲሰጡ እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ህፃናቱን ወደ ተሻለ የህክምና ተቋም ለማዘዋወር በሚደረገው ሂደት ትብብር እንዲያደርጉ ይህን መልእከት እንድታጋሩ እጠይቃለሁ። (ፍጹም ማሩ) Please share 🙏🙏🙏 Ministry of Health,Ethiopia Ethiopian Public Health Association (EPHA) EthiopianChildren'sMinistry Ecm St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC

ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊና ባህላዊ ሀብት በአሁኑ ወቅት ጠብቆ ለትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ትልቅ አደጋና ፈተና ገጥሞታል። ከጠቅላላው ቅርሶች መካከል 16ቱ ላይ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው በመሆኑ አስቸኳይ የጥገና እና የእንክብካቤ ድጋፍ የሚሹ ሲሆን፣ በቅርቡ በመንተኬ ሸረፋ ቀበሌ የተገኙ ተመሳሳይ አዳዲስ የሰው ቅርጽ ያላቸው ድንጋዮችና መካነ-መቃብሮች አካባቢው ገና ያልተገለጠ ታሪክ እንዳለው ያሳያሉ። በመሆኑም ስፍራው የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎችንና የአርኪኦሎጂ ተመራማሪዎችን አስቸኳይ ትኩረትና ጥናት እንደሚሻ የአሚኮ ዘገባ ያመለክታል። #የጋዲሎሜዳ #የሙሽራድንጋይ #የኢትዮጵያታሪክ #ቱሪዝምኢትዮጵያ #አርኪኦሎጂ #የኤፍራታእናግድም #EthiopianHistory #ExploreEthiopia

የጋዲሎ ሜዳ ምስጢራዊ ሐውልቶች፦ በእርግማን የቆሙ የድንጋይ ሙሽሮች? ከአጣዬ ከተማ ተነስተው ወደ መሀል ሜዳ በሚወስደው መንገድ ላይ 21 ኪሎ ሜትር ሲጓዙ፣ በታሪካዊው የጋዲሎ ሜዳ ላይ አስገራሚና ም
+2
የጋዲሎ ሜዳ ምስጢራዊ ሐውልቶች፦ በእርግማን የቆሙ የድንጋይ ሙሽሮች? ከአጣዬ ከተማ ተነስተው ወደ መሀል ሜዳ በሚወስደው መንገድ ላይ 21 ኪሎ ሜትር ሲጓዙ፣ በታሪካዊው የጋዲሎ ሜዳ ላይ አስገራሚና ምስጢራዊ የሆኑ ጥንታዊ ሐውልቶች ያጋጥማሉ። በአሁኑ ወቅት 35 የሚሆኑት በግልጽ ቆመው የሚታዩ ቢሆንም፣ በአጠቃላይ የሰው ምስል (ዓይን፣ አፍንጫ፣ ጆሮ እና የጾታ መለያ) ያላቸው 62 ያህል ድንጋዮች በአካባቢው ይገኛሉ። እነዚህ ቅርሶች እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ሳይንሳዊ የአርኪኦሎጂ ምርምርና ጥናት ያልተደረገላቸው ቢሆንም፣ የጥንቱ ማኅበረሰብ የነበረውን የላቀ የፈጠራና የኪነ-ሕንጻ ጥበብ በግልጽ የሚያሳዩ ድንቅ የታሪክ አሻራዎች ናቸው። ከአካባቢው ማኅበረሰብ ለዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው አፈ-ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ በጥንት ዘመን ሙሽሮችና ሚዜዎቻቸው እየጨፈሩ ሲጓዙ የአንድን ገበሬ ሰብል በትዕቢት ረገጡ። ገበሬው እንዳያጠፉበት ቢማጸናቸውም እምቢ ስላሉ፣ በቁጣ ተሞልቶ "በቆማችሁበት ድንጋይ ያድርጋችሁ!" ብሎ ረገማቸው። በዚያው ቅጽበትም ጭፈራው ቆሞ ሙሽሮቹ በሙሉ ድንጋይ ሆነው እንደቀሩና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቦታው "የሙሽራ ድንጋይ" ተብሎ እንደሚጠራ ይነገራል። ይህ አፈ-ታሪክ ዛሬም ድረስ ለስፍራው ተጨማሪ ምስጢራዊ ውበትንና የቱሪስት መስህብነትን አላብሶታል።

አሜሪካና ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ለመግታት እጅና ጓንት ሆነው እየሰሩ ነው ተባለ የአሜሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (US CDC) በኢትዮጵያ የሚደግፋቸው ፕሮግራሞች የሁለቱን ሀገራት ዜጎች እ
አሜሪካና ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ለመግታት እጅና ጓንት ሆነው እየሰሩ ነው ተባለ የአሜሪካ የበሽታ ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (US CDC) በኢትዮጵያ የሚደግፋቸው ፕሮግራሞች የሁለቱን ሀገራት ዜጎች እንደ ኢቦላ ካሉ አስከፊ ወረርሽኞችና አዳዲስ የጤና ስጋቶች ለመጠበቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል። በአሜሪካ ኤምባሲ ምክትል የተልዕኮ ኃላፊ ካትሪን ሮድሪጌዝ የተመራው ልዑክ በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በመገኘት የድንገተኛ አደጋ ስጋቶች መከላከል ስራዎችን የጎበኘ ሲሆን፥ በትብብሩም በዓለም አቀፍ የጤና ደህንነት፣ በኤችአይቪ/ኤድስ፣ በክትባት፣ በላብራቶሪ ስርዓትና በድንገተኛ ጤና ምላሽ ዘርፎች ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረጉት እነዚህ ስትራቴጂካዊ ትብብሮች በተለይም የላብራቶሪ ምርመራዎችን ለማዘመን፣ የድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ ስርዓትን ለማጠናከርና የምርምር ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እጅግ ከፍተኛና ጉልህ ሚና እንዳላቸው አስገንዝበዋል። ይህ አጋርነት የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ የመቋቋም አቅም ከመገንባት ባለፈ የወደፊት የጤና ስጋቶችን ቀድሞ ለመከላከል ትልቅ መሰረት እየጣለ ይገኛል። #የህብረተሰብጤና #ኢትዮጵያ #አሜሪካ #ወረርሽኝመከላከል #USCDC #Ethiopia #PublicHealth

ማንቸስተር ዩናይትድ 100ሺ ተመልካች የሚይዝ ግዙፍ ስታዲየም ሊገነባ ነው ማንቸስተር ዩናይትድ በታሪኩ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍትለትንና 100 ሺህ ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለውን ዘመናዊ ስታዲየም ለ
ማንቸስተር ዩናይትድ 100ሺ ተመልካች የሚይዝ ግዙፍ ስታዲየም ሊገነባ ነው ማንቸስተር ዩናይትድ በታሪኩ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍትለትንና 100 ሺህ ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለውን ዘመናዊ ስታዲየም ለመገንባት የሚያስፈልገውን 25 ሄክታር መሬት በይፋ ተረክቧል። በአሮጌው ኦልድትራፎርድ አቅራቢያ የሚገነባው ይህ ሜጋ ፕሮጀክት 2 ቢሊዮን ፓውንድ ገደማ ወጪ እንደሚጠይቅ የተገመተ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅም በእንግሊዝ ሀገር ግዙፉ የስፖርት ማዕከል በመሆን የክለቡን ታላቅነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል። ይህ ግዙፍ የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር በስታዲየሙ ዙሪያ 15 ሺህ አዳዲስ ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን የሚያካትት ሲሆን፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ከ90 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል። በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በየዓመቱ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከ7 ቢሊዮን ፓውንድ በላይ ገቢ በማስገባት ለታላቋ ብሪታንያ የኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገልጿል። #ManchesterUnited #MUFC #OldTrafford #NewStadium #FootballNews #ManUnited #የስፖርትዜና

📢 Call for Papers: PanAfriCon AI 2026 The 5th Pan-African Conference on Artificial Intelligence (PanAfriCon AI 2026) invites
📢 Call for Papers: PanAfriCon AI 2026 The 5th Pan-African Conference on Artificial Intelligence (PanAfriCon AI 2026) invites researchers, academics, innovators, and industry professionals to submit original research papers. 📍 Addis Ababa, Ethiopia 📅 October 15–16, 2026 The conference will feature discussions on Generative AI, Medical AI, NLP, Robotics, AI in FinTech, Cybersecurity, Efficient Dataset Generation, and other emerging AI topics. 🗓 Abstract Submission Deadline: July 1, 2026 Accepted papers will be published in the Springer CCIS series. For details and submission: https://panafriconai.org

በበዓሉ ላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጥራት ሬጉላተሪ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ያደረገውን ተቋማዊ ግንባታ በማንሳት ተቋማት
በበዓሉ ላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጥራት ሬጉላተሪ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ያደረገውን ተቋማዊ ግንባታ በማንሳት ተቋማት በቴክኖሎጂ ታግዘው በጥራትና በተወዳዳሪነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። በአሁኑ ወቅት ከ250 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠረውና በቅድመ-መከላከል፣ እንክብካቤ እንዲሁም ህክምና ላይ ያተኮረው ፍቅረሰላም ሆስፒታል፤ በውስጥ ደዌ፣ ማህፀንና ፅንስ፣ ጠቅላላ ቀዶ ህክምና፣ የአእምሮ እና የደም ካንሰር ህክምናዎችን ጨምሮ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የህክምና አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ማድረሱን አጠናክሮ ቀጥሏል። #FikreselamHospital #ISO15189 #AccreditedLab #EthiopianHealthcare #QualityMedicalService #WorldAccreditationDay #TewodajMedia

ፍቅረሰላም አጠቃላይ ሆስፒታል ዓለም አቀፉን የISO 15189 የብቃት ማረጋገጫ ተቀዳጀ ለ25 ዓመታት "ወርቃማ ልቦች፣ አገልጋይ እጆች!" በሚል መርህ የህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ፍቅረሰላም አ
+1
ፍቅረሰላም አጠቃላይ ሆስፒታል ዓለም አቀፉን የISO 15189 የብቃት ማረጋገጫ ተቀዳጀ ለ25 ዓመታት "ወርቃማ ልቦች፣ አገልጋይ እጆች!" በሚል መርህ የህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ፍቅረሰላም አጠቃላይ ሆስፒታል፣ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ (ሲኤምሲ ሚካኤል ፊት ለፊት) የሚገኝ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የISO 15189:2022 የህክምና ላቦራቶሪ ጥራት አስተዳደር ሥርዓት የብቃት ማረጋገጫን በይፋ አግኝቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ16ኛ ጊዜ "አክሪዲቴሽን ለፈጠራ፣ እምነት እና ዘላቂነት" በሚል መሪ ቃል በተከበረው የዓለም አክሪዲቴሽን ቀን ላይ የተሰጠው ይህ ዕውቅና፤ ሆስፒታሉ ከ250 በላይ የሚሆኑ ዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ የጥራት መስፈርቶችን ማሟላቱን የሚያረጋግጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። የሆስፒታሉ መስራችና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ፍቅረማሪያም ጉድታ እና የጥራት አስተዳደር ስራ መሪ ሲስተር ቅድስት ኃይለማሪያም እንደገለጹት፣ ይህ ስኬት ሆስፒታሉ ለታካሚዎች ደህንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል። ተቋሙ ያሟላቸው ቁልፍ መስፈርቶች የሰነድ አስተዳደር፣ የባለሙያዎችና መሣሪያዎች ብቃት፣ የናሙና አያያዝና የውጤት ትክክለኛነትን ያካተቱ ሲሆን፣ በቀጣይም የውጪ ግምገማዎችን በየወሩ በማጠናከር የጥራት አፈፃፀሙን በዘላቂነት ለማስቀጠል ታቅዷል። ይህንን ታላቅ የሚዲያ ሁነት በማስተባበር ረገድ ደግሞ ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል።

"የወለደች ሴት አግባ!" ትዳር ብዙ ግላዊና የወል ምርጫዎች ያሉት ጉዳይ ነው። ግን በፍቺም ይሁን በሌላ ምክንያት ልጅ ብቻቸውን የሚያሳድጉ ሴቶችን እንደማግባት ጀነት የለም። የሕይወትን ትርጉም በሚገባ የተረዱ፣ ሕፃን ሕፃን የማያጫውታቸው፣ በክፉም በደጉም የትዳርን ጫና መቋቋም የሚችሉ፣ ከሚስትነት በላይ የእናትነት ክብርና የሰውን ልክ ጠንቅቀው የሚያውቁ፣ ለሚደረግላቸውም ለሚያደርጉትም ነገር በምስጋና የተሞሉ፣ በሁሉም ነገር በመቶ የኮሌጅ ድግሪ የሚመነዘር በተግባር የተፈተነ ክህሎት ያላቸው፣ ስህተትና ቸልተኝነት የሚያስከፍለውን ዋጋ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ለሚያደርጉት ነገር ጥንቁቅ የሆኑ ምርጥ ፍጥረቶች ናቸው። ልጅ በሚባለው በር በኩል ከራስ ወዳድነት ወጥተዋል። ለአካባቢያቸው ለቤተሰብ ህያው ናቸው። ​ይሁንና ያልወለዳችሁ ሴቶች ከጋብቻ ውጭ እንዳትሞክሩት። እነዚህ ሴቶች ለዚህ ማንነት የሚበቁት እናንተ በቀላሉ የምታልፉትን የሕይወት መንገድ በብዙ እጥፍ የስጋና የስነ-ልቦና ስቃይ አልፈው ነው። ብዙዎቹ ብዙ የደከሙለትን ነገር መንገድ ላይ ትተውታል፤ መድረስ ከሚገባቸው ቦታ ሳይደርሱ ወርደዋል። ይሁንና ሌላ የተከበረ ማንነት ላይ ደርሰዋል። (አሌክስ አብርሃም)

አየር መንገዱ በካናዳው ዘመናዊ አውሮፕላን የቱሪዝም ዘርፉን ሊያነቃቃ ነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከካናዳው ታዋቂ አውሮፕላን አምራች ዴ ሃቪላንድ ከገዛቸው ሁለት DHC-6 Twin Otter Class
+1
አየር መንገዱ በካናዳው ዘመናዊ አውሮፕላን የቱሪዝም ዘርፉን ሊያነቃቃ ነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከካናዳው ታዋቂ አውሮፕላን አምራች ዴ ሃቪላንድ ከገዛቸው ሁለት DHC-6 Twin Otter Classic 300-G ዘመናዊ አውሮፕላኖች መካከል የመጀመሪያዋን በይፋ ተረክቧል። ይህ አዲስና ሁለገብ አውሮፕላን በሀገሪቱ የተለያዩ ክልሎች መካከል ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በተለይም ለአስቸጋሪ የአየር ንብረትና አጫጭር የአውሮፕላን ማረፊያ መንገዶች ፍጹም ተመራጭ መሆኑ አየር መንገዱን ይበልጥ ተወዳዳሪ ያደርገዋል። ይህ ዘመናዊ አውሮፕላን መደበኛ የመንገደኞች በረራን ከማሳለጥ ባለፈ፣ በሀገሪቱ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ላይ ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ለአየር ላይ ቅየሳና ጥናቶች እንዲሁም በአስቸኳይ ጊዜ ህይወት አድን አገልግሎት ለሚሰጡ የአየር ላይ አምቡላንሶች የሚውል በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተለያዩ የገበያ ፍላጎቶችን በላቀ ብቃት፣ በታማኝነትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለማገልገል ያለውን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል። #EthiopianAirlines #DeHavillandCanada #AviationNews #Ethiopia #TwinOtter #FlyEthiopian

photo content

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas

አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ በ800 ሺህ ብር ተቀጡ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 (ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ) የሚገኙት አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ ከፍተኛ የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ
+3
አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ በ800 ሺህ ብር ተቀጡ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 (ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ) የሚገኙት አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ ከፍተኛ የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ አዲስ በተገነባው የኮሪደር ልማት መስመር ላይ ያለአግባብ በመልቀቅ አካባቢውን በመበከላቸው አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እንዳስታወቀው፥ እርምጃው የተወሰደው በከተማ አስተዳደሩ የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 መሠረት ሲሆን፣ ህግ በመተላለፋቸው እያንዳንዳቸው 400 ሺህ ብር፣ በድምሩ 800 ሺህ ብር እንዲቀጡ ተደርጓል። ይህ የተወሰደው እርምጃ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅና የብክለት ህጎችን ለማስከበር የተጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር አካል መሆኑን የገለጸው ባለስልጣኑ፣ ማንኛውም ተቋምም ሆነ ግለሰብ ከእንዲህ መሰል የብክለት ተግባራት እንዲቆጠብ አሳስቧል። መሰል የደንብ መተላለፍ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ አካላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጸው ባለስልጣኑ፣ ህብረተሰቡ መሰል ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል። #AddisAbaba #CorridorDevelopment #CityBeauty #Enforcement #PollutionControl #Bole #Ethiopia

ኦፌኮ በኦሮሚያ እየተስፋፋ ነው ስላለው አዲስ የግጭት አውድ አስጠነቀቀ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) በአንዳንድ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች ተወስኖ የቆየው የግጭት አውድ አሁን ላይ “እጅግ አደ
ኦፌኮ በኦሮሚያ እየተስፋፋ ነው ስላለው አዲስ የግጭት አውድ አስጠነቀቀ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) በአንዳንድ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች ተወስኖ የቆየው የግጭት አውድ አሁን ላይ “እጅግ አደገኛ” በሆነ መልኩ ወደ መካከለኛውና ምሥራቃዊው የክልሉ ክፍሎች እየተስፋፋ ይገኛል ሲል ስጋቱን ገለጸ። ፓርቲው በአርሲ፣ ምሥራቅ ሸዋ እና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች የሚፈጸሙ ጥቃቶች ከዚህ ቀደም ታይቶ ወደማይታወቅ ምዕራፍ መሸጋገራቸውን በመጥቀስ፤ በተለይም በምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ከሳምንታት በፊት በተፈጸመ “የተቀናጀ” ጥቃት፣ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ በአማራና ኦሮሞ ተወላጆች እንዲሁም በክርስቲያኖችና ሙስሊሞች ላይ “የጅምላ ግድያ” መፈጸሙን አጋልጧል። በተጨማሪም በሴሩ ወረዳ በተካሄደ መንደሮችን ሙሉ በሙሉ የማቃጠል ዘመቻ ወደ 17 ሺሕ የሚጠጉ አባወራዎች መፈናቀላቸውንና በዓስር ሺሕዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን ጠቅሷል። በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚደርሰው ይህ ጥቃት “በአስቸኳይ” እንዲቆም የጠየቀው ኦፌኮ፣ ለተጎጂዎች ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ጥሪ አቅርቧል። ፓርቲው አክሎም የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎች የታጠቁ አካላት የጦርነትና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሕግጋትን እንዲያከብሩ በጥብቅ አሳስቧል። #Oromia #Ethiopia #OFC #HumanRights #Arsi #PeaceForEthiopia #BreakingNews

😭 ዳኒዬ ያ ባለሞገሱ ድምጽህ ከጆፘችን አይጠፋም። አክብሮትህን ቀመር የሌለው ወዳጅነትህን አንረሳም። ከምንም በላይ ጊዜ የማይፈትነው ሰውነትህ ከልባችን ይኖራል። ሳትሰስት ስለሰጠኸን ነገር ሁሉ እናመሰግነሃለን። ዛሬ ሬዲዮ አፍ ቢኖራት ትመሰክር ዐይን ቢኖራት ታነባ ነበር። እንወድሃለን😭 መስከረም-

ኢትዮጵያ ሬዲዮ ለ24 ዓመታት የታመነላትን አጥብቆ ወዳጇን ሸኘች! ሬዲዮን የሚወድ ይወደዋል- ጋዜጠኝነትን የሚያከብር ያከብረዋል። ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሰ። ዳኒ ሰው የሆነ ሰው ነበረ። ታላቅነቱን በሙያ
ኢትዮጵያ ሬዲዮ ለ24 ዓመታት የታመነላትን አጥብቆ ወዳጇን ሸኘች! ሬዲዮን የሚወድ ይወደዋል- ጋዜጠኝነትን የሚያከብር ያከብረዋል። ጋዜጠኛ ዳንኤል ታደሰ። ዳኒ ሰው የሆነ ሰው ነበረ። ታላቅነቱን በሙያው ክብርና ለታናሾቹ ዝቅ በማለት የሚያሳይ፣ እንደጓደኛ አቅርቦ በቀልድ እያዋዛ የሚመክር ወንድም ነበረ። ዳኒ ለአድማጩ የሚጨነቅ ጥንቅቅ ያለ ጋዜጠኛ ነበረ። ዳኒ የአድናቆት ስስት አልነበረበትም- ጥሩ ፕሮግራም ስትሰሩ የታላቅነት “ኢጎ” ሳይዘው ሲያገኛችሁ ለመናገር ወይ ለመደወል አያመነታም። ዳኒ😭😭😭 ለእኔ ደግሞ የተለየ ትዝታ አለኝ። ተማሪ ሁኜ ለኢትዮጵያ ሬዲዮ ልብወለድ እየላክሁ ይነበብ ነበር። ከዚያ ዩኒቨርሲቲ ገባሁ ሥራ ያዝሁ-ረሳሁት። ኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሲዋሐድ እጅግ የማከብራቸው የሬዲዮ ጋዜጠኞች ወደ ቴሌቪዥን ሕንፃ ገቡ። ደጀኔ ጥላሁን፣ ዳንኤል ታደሰ፣የእናት ፋንታ ውቤ፣ የወይንሸት አስፋው የመሳሰሉ ጋዜጠኞች ደግሞ መዝናኛ ፕሮግራም አዘጋጅ በመሆናቸው እኔ ወዳለሁበት ክፍል ተቀላቀሉ። ከሆነ ጊዜ በኋላ ዳኒ ወደ እኔ መጣና “ዳሞት ነው የተማርሽው?”አለኝ። አዎ አልኩት። የሆኑ የተጣጠፉ ወረቀቶችን አወጣና የአንች ናቸው አይደል? አለኝ። ጮኹኝ። ወረቀቶቹ ተማሪ ሁኜ የምልካቸው ነበሩ። ከየት እንዳገኘው ጠየቅሁት። “ከሚላኩልን የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ለአድማጭ ካነበብሁ በኋላ የወደድኌቸውን በክብር አስቀምጣቸዋለሁ” በማለት ነገረኝና ደስ መሰኘቴን አይቶ በዚህ ሙያ ለመቆየት ማድረግ ያለብኝን መከረኝ። በጣም ደስስስስ ብሎኝ ነበር። ያ የማከብረው ሰው ለዓመታት ሳጥን አጠገብ ቁጭ ብዬ በሬዲዮ የሰማሁት ዳኒ እኮ ነው እንደዚያ ያለኝ! ከጣቢያው ከወጣሁ በኋላ ዳኒ የእከሌ ስልክ ይኖርሃል? …ዳኒ እከሌን ልጠይቅ ነበር መረጃ ስጠኝ…እሽ እሽ…ዳኒ ቤተ መጻሕፍት ነበር። 😭