es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 463 suscriptores, ocupando la posición 6 026 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 324 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 463 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 526, y en las últimas 24 horas de 12, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 38.31%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.22% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 538 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 477 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 463
Suscriptores
+1224 horas
+1357 días
+52630 días
Archivo de publicaciones
እንኳን ለጼዴንያ ማርያም በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። መልካም ቀን! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eo
እንኳን ለጼዴንያ ማርያም በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። መልካም ቀን! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ የተከበራችሁ አንባብያን የዚህን ጽሑፍ የመጀመሪያ የሆነውን እና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ተሐድሶ መናፍቃን እና ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች የሚያነሷቸውን የ
ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ የተከበራችሁ አንባብያን የዚህን ጽሑፍ የመጀመሪያ የሆነውን እና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ተሐድሶ መናፍቃን እና ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች የሚያነሷቸውን የፈጠራ ድርሰቶች መነሻ ምክንያት የሚያስነብበውን ጽሑፍ ለንባብ ማብቃታችን የሚታወቅ ነው። ቀጣዩን ክፍል ደግሞ እንደሚከተለው አቅርበነዋል። መልካም ንባብ፡- .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ከደቂቀ-እስጢፋኖስ-እስከ-መንበረ-ሰላማ-2/ ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

በሰሜን ዞን በመስቀል መዝሙር ጥናት ላይ ለሰንበት ተማሪዎች ሥልጠና ተሠጠ መስከረም 9 ቀን 2016 ዓ.ም ፤ የጌታችን የመድኃኒትአችን የኢየሱስ ክርስቶስን የመስቀል በዓልን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በ
+7
በሰሜን ዞን በመስቀል መዝሙር ጥናት ላይ ለሰንበት ተማሪዎች ሥልጠና ተሠጠ መስከረም 9 ቀን 2016 ዓ.ም ፤ የጌታችን የመድኃኒትአችን የኢየሱስ ክርስቶስን የመስቀል በዓልን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስር በ5 ዞኖች የመስቀል መዝሙር ጥናት እየተካሔደ ሲሆን በሰሜን ዞን ጥናታቸውን በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ አዳራሽ እያካሄዱ ላሉ ከ22 ደብራት የተወጣጡ 890 ሰንበት ተማሪዎች የቤተክርስቲያን ተግዳሮች ከሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎት አንፃር በሚል ርዕስ በመምህር ዶ/ር ዝናወርቅ ከ አ.አ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና ተሰጥቷቸዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ አባ እስጢፋኖስን እና ተከታዮቹንበተመለከተ ብዙ ይጻፋል፣ ይነገራል። የእርሱ እና የተከታዮቹ ጉዳይ ማንም እንደፈለገ ለመዘወር የተመቸ ነው። ከትግራይ ክልል የተ
ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ አባ እስጢፋኖስን እና ተከታዮቹንበተመለከተ ብዙ ይጻፋል፣ ይነገራል። የእርሱ እና የተከታዮቹ ጉዳይ ማንም እንደፈለገ ለመዘወር የተመቸ ነው። ከትግራይ ክልል የተነሡ ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች ባላንጣችን የሚሉትን ሸዋን ለመተቸት ይጠቅሱታል። በክልሉ ኑፋቄያቸውን ለመዝራት ፈልገው ያልተሳካላቸው ተሐድሶ መናፍቃን በዕውቀቱ አቻ የሌለው፣ በአስተምህሮው እንከን የማይገኝበት አስመስለው ያቀርቡታል። ... .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ከደቂቀ-እስጢፋኖስ-እስከ-መንበረ-ሰላማ/ ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

የቴሌግራም ገጻችንን ይጎብኙ!!! ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU
የቴሌግራም ገጻችንን ይጎብኙ!!! ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU

የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች በሲዳማና በጅማ ሀገረ ስብከቶች እየተሰጠ ነው። መስከረም 7 2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሐዋሳ ደ
+4
የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች በሲዳማና በጅማ ሀገረ ስብከቶች እየተሰጠ ነው። መስከረም 7 2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሐዋሳ ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፈለገ ሃይማኖት  ሰንበት ትምህርት ቤት በሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙርያ ገለጻና  ውይይት ተደረገ። ገለጻውን ያደረጉት በ2015 ዓ.ም በሀገር አቀፍ የሰንበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ለአኅጉረ ስብከቶች ተዘጋጅቶ በነበረው የመምህራን የአሰልጣኞች ሥልጠና ላይ ሀገረ ስብከቱን ወክለው የተሳተፉት  መምህር ሀቢብ ብርሃኑ  ናቸው። በመርሐ ግብሩ ላይ የሰንበት ትምህርት ቤቱ የየክፍላት ኃላፊዎችና የመርሐ ግብር አስተባባሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ከገለጻው በኋላ ውይይትና የትግበራ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል። እንዲሁ በጅማ ሀገረ ስብከት በጅማ ፈለገ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሎዛ ሰንበት ት/ቤት በሰንበት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙርያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጥቷል። ሥልጠናው ለሰንበት ት/ቤቱ የወጣት ክፍል እና የማእከላውያን ክፍል አባላት የተሰጠ ሲሆን ሥልጠናውን የሰጠው የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ባመቻቸው ሥልጠና ትምህርቱን ወስዶ በሄደው  መምህር ምንተስኖት ገብሬ መሆኑ ተነግሯል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

በጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ ምሥረታ ተከናወነ። መስከረም 7 2016 ዓ.ም (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጣልያንና አካባቢው ሀገረ
+2
በጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ ምሥረታ ተከናወነ። መስከረም 7 2016 ዓ.ም (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ ገ/እግዚአብሔር ወርቁ የስብከተ ወንጌልና የሰ/ት/ቤት መምሪያ ኃላፊ ፣ የሀገረ ስብከቱ አገልጋዬች ፣ ከየሰንበት ት/ቤቱ የተወከሉ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው አገልጋዬች በተገኙበት መስከረም 6/2015 ዓ.ም የሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ ተመሠረተ። የምሥረታ ገባኤው የተለያዩ መርሐ ግብራት የቀረቡ ሲሆን በተለይም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መመሥረት ዓላማና የአገልግሎት መንፈሳዊ መንገድ በተመለከተ ሰፊ ትምህርት የተሰጠ ሰጥተዋል። ከመንበረ ፓትርያርክ ዓለም አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ም/ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው በቅዱስ ሲኖዶስ ለአንድነቱ ስለተሰጠው ተልዕኮና መልእክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም በተለያዩ ሰ/ት/ቤቶች ተዘጋጅተው የቀረቡ ልዩ ልዩ የኪነ ጥበብ መርሐ ግብራት እጅግ አስተማሪ ነበሩ። በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አገልግሎት ለተደራሽነት እንዲያመች በሦስት ዞን (የጣልያን ፣ የፈረንሳይ እና የበልጂዬም ፣ ማልታና ቱርክ) በመከፋፈል ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች በማሳተፍ ለመሥራት በሚያስችል መልኩ መደራጀቱን የሀገረ ስብከቱ ኃላፊ  በመግለጽ የምሥረታ ጉባኤው በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ 20 አጥቢያዎች መካከል በዕለቱ 100 ተወካዬች በተገኙበት ምሥረታው ተከናውኗል። በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አመራር በማስተዋወቅ ጉባኤው ተጠናቋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) https://t.me/EOTCNSSU

ከስር ባለው ማስፈንጠሪያ ( ሊንክ) የመጽሐፍ ኅትመት ፍላጎት ማሳወቂያ ቅጹን ይሙሉ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-መማሪያ-መ
ከስር ባለው ማስፈንጠሪያ ( ሊንክ) የመጽሐፍ ኅትመት ፍላጎት ማሳወቂያ ቅጹን ይሙሉ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-መማሪያ-መጻሕፍት-የኅት/ የመጻሕፍት ኅትመት ፍላጎት ማሳወቂያ 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ገጻችንን ይቀላቀሉን! ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU

የመስቀል ጥናት ዝግጅት በተባበሩት አረብ ኢምሬት መስከረም 6 /1/2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የዘንድሮውን የመስቀል በዓል ዝግጅት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
+6
የመስቀል ጥናት ዝግጅት በተባበሩት አረብ ኢምሬት መስከረም 6 /1/2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የዘንድሮውን የመስቀል በዓል ዝግጅት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አኅጉረ ስብከቶች የሚከበር ሲሆን ከነዚህ አንዱ በሆነው በተባበሩት አረብ ኢምሬት የመዝሙር ጥናት ተጀምሯል። ለዚህም ዝግጅት ከተለያዩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ወጣት ተማሪዎች በአቡዳቢ በሚገኘው ምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም በመሰባሰብ በዓሉን የተመለከቱ ወረብ እና መዝሙራትን በማጥና ላይ እንደሚገኙ ተገለጸ። በዓሉ የፊታችን መስከረም 19 ዱባይ በሚገኘው አል ሽባብ እስታዲየም እንደሚከበር ተነግሯል። መረጃውን ከርዕሰ አድባራት ዱ/ሻ/አ ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ወቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ ቤዛ ብዙኃን ሰ/ት/ቤት የፌስቡክ ገጽ አግኝተነዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

MK OTC structure Impl.ppt1.75 MB

ያልተቋጨው የምዕመናንና የሰንበት ተማሪዎች ሰቆቃ መስከረም 5 /1/2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዳኖ ወረዳ እራሳቸውን “የኦሮሚያ ቤተክህነት” አባላት ብለው በሚጠሩ በመንግሥት ድጋፍ በሚንቀሳቀሱ  ኃይሎች አማካኝነት በቤተ ክርስቲያን ልጆች ላይ ከፍተኛ እንግልትና እና እስር እየደረሠባቸው መሆኑን በሥፍራው የሚገኙ ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡ ቀሲስ አበራ እንዳሻው በተባለ ከዚህ በፊት በሀገረ ስብከቱ ታግዶ በነበረ ግለሰብ መሪነት የሚንቀሳቀሰው ቡድን በወረዳው የሚገኙትን የኦሮሞ ብሔረሰብ ተወላጅ እውነተኛ የቤተክርስቲያን ልጆችን “የኦሮሚያ ቤተክህነት” ን ተቃውማችኋል  በማለት  የድብደባ የመፈናቀል ከዛም አልፎ ለእስር መዳረጋቸውን ከአካባቢው ያገኘናቸው ምንጮች ነግረውናል፡፡ ይህንን ዘገባ እስከ አዘጋጀንበት ሰዓት ድረስ በዳኖ ወረዳ ሰዬ ከተማ ደብረ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች የሆኑ ሰባት/7/ ሰንበት ተማሪዎች፤ የወረዳ ቤተክህነቱ ጸሐፊ ዲ/ን ተሠራ አበበ እንዲሁም የአካባቢው የሀገር ሽማግሌ አቶ ታደሠ መንገሻ በእስር ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ “የኦሮሚያ ቤተክህነት” አቀንቃኝ አካላት  " ወልዳ ዱካቡኦታ " የሚባል ለሕገ ወጥ ቡድን ጉዳይ አስፈጻሚ የሆነ ማኅበር በማደራጀት  የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትን በማሳደድ  ላይ የሚገኝ ሲሆን  ከዚህም በተጨማሪ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ በወረዳው የሚገኙ አገልጋዮች እንደገለጹልን ከሆነ “አዲስ ዓመት የኛ ዘመን መለወጫ በዓል አይደለም” በማለት የ2016 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ ዝማሬ በወረዳ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በየሠፈሩ እንዳይዘምሩ  ተከልክለዋል፡፡ አክለውም በወረዳው ቤተክህነት ሥር ከ25 በላይ አጥቢያ ቤተክርስቲያኖች የሚገኙ ቢሆንም በአሁን ሰዓት ክፍት ሁነው የሚገኙት 3ቱ አጥቢያዎች ብቻ መሆናቸው እና “የኦሮሚያ ቤተክህነት” አቀንቃኝ አካላት ሕዝቡን ከቤተክርስቲያን እያሸሹት፤ በሁለት ጎራም ተከፍሎ በመጋጨትም ላይ ስላለ ቀሪዎቹም የመዘጋት እድል አላቸውና በአስቸኳይ የሚመለከታቸው አካላት እና መንግሥት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሠጠን ሲሉ ለሚዲያችን መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ( የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የሕፃናት መዝሙር ግጥም ውድድር የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ በሰንበት ትምህርት ቤቶች የትግበራ ሙከራ እያደረገ ባለው የቅድመ መደበኛ(አንደኛ) ትምህርት ማስተ
የሕፃናት መዝሙር ግጥም ውድድር የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ በሰንበት ትምህርት ቤቶች የትግበራ ሙከራ እያደረገ ባለው የቅድመ መደበኛ(አንደኛ) ትምህርት ማስተማሪያ የሚሆኑ ትምህርታዊ ግጥሞችን የሚጽፉ የሰ/ት/ቤት አገልጋዮችን ማወዳደርና አሸናፊዎችን መሸለም ይፈልጋል። የግጥሞቹ ይዘትና ምን ላይ ማተኮር እንዳለባቸው የገለጻ መርሐ ግብር የተዘጋጀ ሲሆን ከነዚህ ቀናት በአንዱ በመገኘት ስለውድድሩ ዝርዝር ነገሮችን ማወቅ ይቻላል። የገለጻ ቀናት: መስከረም 12 ቅዳሜ ከ7 እስከ 9 ወይም መስከረም 16 ረቡዕ ከ11 እስከ 1 ሰዓት ለበለጠ መረጃ 0913969785 0920741461 (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

በሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙርያ ውይይት ተደረገ መስከረም 4/1/2016 (ሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በሐዋሳ ሀገረ ስብከት በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መራሔ ድኅነት ሰንበት ትምህ
+5
በሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙርያ ውይይት ተደረገ መስከረም 4/1/2016 (ሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በሐዋሳ ሀገረ ስብከት በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መራሔ ድኅነት ሰንበት ትምህርት ቤት በሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙርያ ገለጻና ውይይት ተደረገ። ገለጻውን በ2015 ዓ.ም በሀገር አቀፍ የሰንበት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ለአኅጉረ ስብከቶች ተዘጋጅቶ በነበረው የመምህራን የአሰልጣኞች ሥልጠና ላይ ሀገረ ስብከቱን ወክለው የተሳተፉ ዲያቆን ሳሙኤልና መምህር ረድኤት ተክሉ ናቸው። በመርሐ ግብሩ ላይ የሰንበት ትምህርት ቤቱ የየክፍላት ኃላፊዎችና የመርሐ ግብር አስተባባሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ከገለጻው በኋላ ውይይትና የትግበራ አቅጣጫውችን አስቀምጠዋል። የዝግጅት ክፍላችን ከዚህ በፊት የጅማ ሀገረ ስብከት ሰልጣኞች ተመሳሳይ ሥልጠናና ውይይት ማድረጋቸውን መዘገባችን ይታወሳል። መረጃውን ከመራሔ ሚዲያ (መራሔ ድኅነት ሰ/ት/ቤት መገናኛ ብዙኀን አግኝተነዋል።) (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገር ካበረክተችው አስተዋጽኦ አንዱ የሀገር አንድነት ምክንያት ሆና መኖሯ ነው። ለዚ
የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገር ካበረክተችው አስተዋጽኦ አንዱ የሀገር አንድነት ምክንያት ሆና መኖሯ ነው። ለዚህም ነው ኢትዮጵያን ማዳከም የሚፈልጉ ኃይሎች ሁሉ መጀመሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከምን ዋና አጀንዳቸው የሚያደርጉት። በተለይም ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሚስዮናውያን ቤተ ክርስቲያንን በማጥፋት ኢትዮጵያን መረከብ አጀንዳቸው ካደረጉ ከአራት መቶ በላይ ዘመናትን አስቈጥረዋል። በዘህ ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሚመኙትን ያህል ምናልባትም ከዚያ በላይ ቤተ ክርስቲያንን የሚጠሉ “ኢትዮጵያውያን ፈረንጆችን” ማፍራት ችለዋል። እነዚህ ከውጪ የሚላክላቸውን አጀንዳና ፍርፋሪ ተቀብለው በውስጥ ሆነው ቤተ ክርስቲያንን ያጠቃሉ። .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የትግራይ-ቤተ-ክህነት-እንቅስቃሴ-ለተሐድ/ የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion