es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 557 suscriptores, ocupando la posición 5 983 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 319 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 557 suscriptores.

Según los últimos datos del 04 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 524, y en las últimas 24 horas de 17, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 32.00%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.39% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 652 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 510 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 20.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 557
Suscriptores
+1724 horas
+1237 días
+52430 días
Archivo de publicaciones
ቅዳሜ ከ10፡00 ጀምሮ በEOTC Tv ፈለገ ጥበብ ሚዲያ ላይ ይጠብቁን! [ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን – ክፍል ሦስት የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን   ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጽሑፎች የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን በፈተና የተከበበ መሆኑን አንሥተናል። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ቅድስት ቤተክርስቲያን ከራሷ መነኰሳት ጳጳሳትን እንድትሾም ያደረጉት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ቢሆንም በራሳቸው ወርድ ለመስፋት ያደርጉት የነበረው ጣልቃ ገብነት ደግሞ አሁን ለደረስንበት ችግር እንደ አንድ ምክንያት ሊጠቀስ የሚችል ነው።  ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንዲሾሙ ያደረጉት ተጋድሎ በሌላ በኩል አባቶች መንግሥት ካከልን ብለው እንዲዘናጉ ሳያደርግ አልቀረም። በ፲፱፻፳፩ዓ.ም ከራሳችን መነኰሳት ኤጲስ ቆጶሳት እንደተሾሙ ሊቀጳጳሱና ኤጲስ ቆጶሳቱ ጉባኤ አድርገው በመምከር ሊያደርጉት የሚገባውን የሀገረ ስብከት ምደባ ንጉሠ ነገሥቱ መፈጸማቸው ለጉዳዩ ትኩረት ለመስጠት ጠቅሟል የሚል አካል ቢኖርም በየዘመናቱ ለተነሡ ባለሥልጣናት መንገድ ቀይሰዋል።… ማንበብ ይቀጥሉ… https://eotc-gssu.org/a/የኤጲስ-ቆጶሳት-ምርጫ-ታሪካችን-ክፍል-ሦስ/ https://t.me/EOTCNSSU

የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት ታሪክ ውስብስብ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ውስብስብ እንዲሆን ያደረገው በአንድ በኩል ግብፆች ሢመቱን ለጊዜያዊ ጥቅም ማግኛ በማድረግ ፓትርያርኮች ከራሳችን መነኰሳት እንድንሾም ቢፈቅዱ እንኳ የእስልምና እምነት ተከታይ መሪዎቻቸው መከልከላቸው ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የአገራችን ነገሥታት በአዎንታዊ መንገድም ቢሆን ጣልቃ መግባታቸው “መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው” በማለት በዐደባባይ ምለው የሚገዘቱ የዘመናችን መሪዎችም በተግባር ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም በእጅጉ “የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ፈጻሚ” ሆነው እንዲታዩ በር የከፈተ በመሆኑ ነው። ... ማንበብ ይቀጥሉ https://eotc-gssu.org/a/የኢጲስ-ቆጶሳት-ታሪካችን-ክፍል-ሁለት/ የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት https://t.me/EOTCNSSU

ረቢ መካነ ጎሎጎታ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና
+4
ረቢ መካነ ጎሎጎታ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና

ቀጨኔ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና
+7
ቀጨኔ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና

ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና
+5
ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና

የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የ12ኛ የሞዴል ፈተና ገጽታ
+2
የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የ12ኛ የሞዴል ፈተና ገጽታ

ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።
+1
ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።

ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።
+1
ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።

በአ.አ ሰ/ት ቤቶች አንድነት የኢኮኖሚ እና ምጣኔ ሃብት ክፍል የተዘጋጀውና ለሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የተሰጠው የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብትና የአመለካከት ለውጥ ዙር ሁለት ሥልጠና ተጠናቀቀ። አርብ ነሐሴ ፭ ፳፻፲፭ ዓ.ም ፤ አቃቂ ቃሊቲ ፤ ልደታ፤ ቂርቆስ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ከተሞች ለተወጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት እንዲሁም የአመለካከት ለውጥ ሥልጠና ሁለተኛ ዙር ተጠናቅቋል። በዚህ ሥልጠና ከአራት ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ 70 ሰልጣኞች ተሳትፈውበታል። እንደመጀያው ዙር ሰልጣኞች ወደ ፕሮፖዛል ዝግጅት እና ብድር ሥርዓት የተሸጋገሩ ሲሆን ሥልጣናው በቀጣዩ ዓርብ በተመረጠው ክፍል ከተማ እንደሚቀጥል የሥልጠናው አስተባባሪዎች ገልጸዋል። [ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ታሪክ የመጀመርያው የ ፲፪ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና ሊሰጥ ነው። ነሐሴ ፬ ፳፻፲፭ ዓ.ም ፤በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት የተማሩ የ፲፪ ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና ነሐሴ ፯ ፳፻፲፭  ዓ.ም እንደሚሰጥ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስታወቀ። የ፲፪ኛ ክፍል ፈተናው የሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጀውና በሁሉም አህጉረ ስብከቶች በመተግበር ላይ የሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ከተደረገ ጀምሮ ለመጀመርያ ጊዜ መሆኑን የሥርዓተ ትምህርት አስተባባሪ የሆኑት ዲ/ን ሚኪያስ ግዛቸው ገልፀዋል።  አያይዘውም የፊታችን እሑድ ነሐሴ ፯ ፳፻፲፭ ዓ.ም የ ፲፪ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመጀመርያ በሆነው በዚህ የሞዴል ፈተና ፻፹፬ ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያያዘም ከሁለት ሳምንት በኋላ ነሐሴ ፳፩   በ ፪ የፈተና ማዕከላት ለ ፭ አጥቢያዎች ዋናው ፈተና እንደሚደረግ አያይዘው ገልጸዋል። [ ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ] https://t.me/EOTCNSSU

በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል የተዘጋጀ ለተተኪ መምህራን ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ነሐሴ 2 2015 ዓ.ም ፤ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ
+6
በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል የተዘጋጀ ለተተኪ መምህራን ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ነሐሴ 2 2015 ዓ.ም ፤ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል የተዘጋጀ ለሰንበት ት/ቤቶች ተተኪ መምህራን ስልጠና በወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ እየተሰጠ ይገኛል። ከነሐሴ 1-15/2015 ዓ/ም የሚሰጠው ስልጠና በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ወረዳዎች የተውጣጡ 114 የሰ/ት/ቤት አባላት እና ከሌላ ሀገረ ስብከት 2 በድምሩ 116 ሰልጣኞችን ያሳተፈ ነው። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ኃላፊ ሰልጣኞች በሚኖራቸው የስልጠና ቆይታ የመጡበትን ዓላማ በማሰብ በትኩረት ተከታትለው የሚሰጣቸውን የቤተክርስቲያን ኃላፊነትና ተልዕኮ እንዲፈጽሙ እንዲሁም ተግባራዊ ክርስትና በመኖር በጾም፣ በጸሎት፣ በማስቀደስና በመቁረብም እንዲተጉ አሳስበዋል። [ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ] [የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

ኤፍሬም እንዳለ የተባለ ደራሲ “እንጨዋወት” በሚል ርእስ ያዘጋጀው ትኩረቱን ማኅበራዊ ሂስ ላይ ባደረገው መጽሐፍ አንድ ታሪክ እናገኛለን። ታሪኩ እንዲህ ነው። አንድ ድርጅት ከከተማ ወጣ ባለ ቦታ ያከ
ኤፍሬም እንዳለ የተባለ ደራሲ “እንጨዋወት” በሚል ርእስ ያዘጋጀው ትኩረቱን ማኅበራዊ ሂስ ላይ ባደረገው መጽሐፍ አንድ ታሪክ እናገኛለን። ታሪኩ እንዲህ ነው። አንድ ድርጅት ከከተማ ወጣ ባለ ቦታ ያከማቻቸው አሮጌ መኪናዎች፣ የወላለቁ ብረታ ብረቶች እና ከጥቅም ውጭ የሆኑ የተለያዩ ቁሰቁሶች ነበረው፡፡ ክምችቱ ያለ ጥበቃ ለረጅም ጊዜ ቆይቷል፡፡ በኋላ ግን የድርጅቱ ባለ ሥልጣናት መጠበቅ አለበት ብለው ስላመኑ ሁለት የጥበቃ ሠራተኞች እንዲቀጠሩ ወሰኑ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጥበቃዎቹ በሰዓት መግባት መውጣታቸውን ከዋናው መሥሪያ ቤት ሆኖ በርቀት መከታተል እንዳልተቻለ ዘገባ ቀረበ፡፡ እነርሱን በፈረቃ የሚከታተሉ ሁለት ሰዎች ተቀጠሩ፡፡ ከቆይታ በኋላ ለአራቱ ሠራተኞች ደመወዝ ከፋይ እንደሚያስፈልግ ታመነበትና ተቀጠረ፡፡ ከዚያም የሰው ኃይል አስተዳደር መኖር አለበት ተብሎ እርሱም ተቀጠረ፡፡ የሰው ኃይል አስተዳደሩ ጸሐፊ ስላስፈለገው ጸሐፊ ተጨመረ፡፡ ይህን ሁሉ ያለ ሥራ አስኪያጅ ማስተዳደር እየከበደ ስለመጣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተሾመለት፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ቀስ በቀስ ብዙ ሠራተኞች ያለው ድርጅት ሆነ፡፡ ማንበብ ይቀጥሉ ... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/መዋቅሩ-ለወንጌል-ወይስ-ወንጌሉ-ለመዋቅሩ/ መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ? ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ሊቃውንት ኤጲስ ቆጶሳት ለመሾም ያሰቡትና የጠየቁት ጥንት ነው። ከዛግዌ ነገሥታት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሐርቤ ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ጳጳሳት እ
የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ሊቃውንት ኤጲስ ቆጶሳት ለመሾም ያሰቡትና የጠየቁት ጥንት ነው። ከዛግዌ ነገሥታት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሐርቤ ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ጳጳሳት እንዲሾሙ አሳብ አቅርቦ ነገሥታት ከትምህርተ ሃይማኖትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አንጻር እንዲመረምሩት አድርጎ ነበር። አሳቡ ተግባራዊ እንዲሆን የፈለገውም ጳጳስ ከግብፅ ማስመጣቱን እንደ ቅኝ ግዛት ቈጥሮት ሳይሆን ከአገራቱ ርቀት አንጻር ጳጳስ እንዲሾም የሚጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ለብዙ ዓመታት የሚቆይ በመሆኑ፣ በዚያውም ላይ ባሕሉን የሚያውቀው፣ ቋንቋውን ከሚናገረው ቢሾም ክህነት ከመስጠት በተጨማሪ አስተምሮ ብዙዎችን መመለስ ይችላል ብሎ በማመን ነበር። ማንበብ ይቀጥሉ ... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የኤጲስ-ቆጶሳት-አሿሿም-ታሪካችን/ የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion