ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 463 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 026,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 324

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 463 名订阅者。

根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 526,过去 24 小时变化为 12,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.31%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.22% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 538 次浏览,首日通常累积 1 477 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 463
订阅者
+1224 小时
+1357
+52630
帖子存档
ቅዳሜ ከ10፡00 ጀምሮ በEOTC Tv ፈለገ ጥበብ ሚዲያ ላይ ይጠብቁን! [ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን – ክፍል ሦስት የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን   ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጽሑፎች የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን በፈተና የተከበበ መሆኑን አንሥተናል። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ቅድስት ቤተክርስቲያን ከራሷ መነኰሳት ጳጳሳትን እንድትሾም ያደረጉት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ቢሆንም በራሳቸው ወርድ ለመስፋት ያደርጉት የነበረው ጣልቃ ገብነት ደግሞ አሁን ለደረስንበት ችግር እንደ አንድ ምክንያት ሊጠቀስ የሚችል ነው።  ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንዲሾሙ ያደረጉት ተጋድሎ በሌላ በኩል አባቶች መንግሥት ካከልን ብለው እንዲዘናጉ ሳያደርግ አልቀረም። በ፲፱፻፳፩ዓ.ም ከራሳችን መነኰሳት ኤጲስ ቆጶሳት እንደተሾሙ ሊቀጳጳሱና ኤጲስ ቆጶሳቱ ጉባኤ አድርገው በመምከር ሊያደርጉት የሚገባውን የሀገረ ስብከት ምደባ ንጉሠ ነገሥቱ መፈጸማቸው ለጉዳዩ ትኩረት ለመስጠት ጠቅሟል የሚል አካል ቢኖርም በየዘመናቱ ለተነሡ ባለሥልጣናት መንገድ ቀይሰዋል።… ማንበብ ይቀጥሉ… https://eotc-gssu.org/a/የኤጲስ-ቆጶሳት-ምርጫ-ታሪካችን-ክፍል-ሦስ/ https://t.me/EOTCNSSU

የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት ታሪክ ውስብስብ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ውስብስብ እንዲሆን ያደረገው በአንድ በኩል ግብፆች ሢመቱን ለጊዜያዊ ጥቅም ማግኛ በማድረግ ፓትርያርኮች ከራሳችን መነኰሳት እንድንሾም ቢፈቅዱ እንኳ የእስልምና እምነት ተከታይ መሪዎቻቸው መከልከላቸው ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የአገራችን ነገሥታት በአዎንታዊ መንገድም ቢሆን ጣልቃ መግባታቸው “መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው” በማለት በዐደባባይ ምለው የሚገዘቱ የዘመናችን መሪዎችም በተግባር ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም በእጅጉ “የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ፈጻሚ” ሆነው እንዲታዩ በር የከፈተ በመሆኑ ነው። ... ማንበብ ይቀጥሉ https://eotc-gssu.org/a/የኢጲስ-ቆጶሳት-ታሪካችን-ክፍል-ሁለት/ የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት https://t.me/EOTCNSSU

ረቢ መካነ ጎሎጎታ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና
+4
ረቢ መካነ ጎሎጎታ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና

ቀጨኔ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና
+7
ቀጨኔ መድኃኒዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሞዴል ፈተና

ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና
+5
ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና

የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የ12ኛ የሞዴል ፈተና ገጽታ
+2
የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት የ12ኛ የሞዴል ፈተና ገጽታ

ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።
+1
ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።

ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።
+1
ካራ ኦሎ መድኅኒዓለም ወአባ ገሪማ ቤተክርስቲያን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሞዴል ፈተና ላይ።

በአ.አ ሰ/ት ቤቶች አንድነት የኢኮኖሚ እና ምጣኔ ሃብት ክፍል የተዘጋጀውና ለሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የተሰጠው የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብትና የአመለካከት ለውጥ ዙር ሁለት ሥልጠና ተጠናቀቀ። አርብ ነሐሴ ፭ ፳፻፲፭ ዓ.ም ፤ አቃቂ ቃሊቲ ፤ ልደታ፤ ቂርቆስ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ከተሞች ለተወጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት እንዲሁም የአመለካከት ለውጥ ሥልጠና ሁለተኛ ዙር ተጠናቅቋል። በዚህ ሥልጠና ከአራት ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ 70 ሰልጣኞች ተሳትፈውበታል። እንደመጀያው ዙር ሰልጣኞች ወደ ፕሮፖዛል ዝግጅት እና ብድር ሥርዓት የተሸጋገሩ ሲሆን ሥልጣናው በቀጣዩ ዓርብ በተመረጠው ክፍል ከተማ እንደሚቀጥል የሥልጠናው አስተባባሪዎች ገልጸዋል። [ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ታሪክ የመጀመርያው የ ፲፪ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና ሊሰጥ ነው። ነሐሴ ፬ ፳፻፲፭ ዓ.ም ፤በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት የተማሩ የ፲፪ ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና ነሐሴ ፯ ፳፻፲፭  ዓ.ም እንደሚሰጥ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስታወቀ። የ፲፪ኛ ክፍል ፈተናው የሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጀውና በሁሉም አህጉረ ስብከቶች በመተግበር ላይ የሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ከተደረገ ጀምሮ ለመጀመርያ ጊዜ መሆኑን የሥርዓተ ትምህርት አስተባባሪ የሆኑት ዲ/ን ሚኪያስ ግዛቸው ገልፀዋል።  አያይዘውም የፊታችን እሑድ ነሐሴ ፯ ፳፻፲፭ ዓ.ም የ ፲፪ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። የመጀመርያ በሆነው በዚህ የሞዴል ፈተና ፻፹፬ ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያያዘም ከሁለት ሳምንት በኋላ ነሐሴ ፳፩   በ ፪ የፈተና ማዕከላት ለ ፭ አጥቢያዎች ዋናው ፈተና እንደሚደረግ አያይዘው ገልጸዋል። [ ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ] https://t.me/EOTCNSSU

በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል የተዘጋጀ ለተተኪ መምህራን ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ነሐሴ 2 2015 ዓ.ም ፤ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ
+6
በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል የተዘጋጀ ለተተኪ መምህራን ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ነሐሴ 2 2015 ዓ.ም ፤ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል የተዘጋጀ ለሰንበት ት/ቤቶች ተተኪ መምህራን ስልጠና በወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ እየተሰጠ ይገኛል። ከነሐሴ 1-15/2015 ዓ/ም የሚሰጠው ስልጠና በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ወረዳዎች የተውጣጡ 114 የሰ/ት/ቤት አባላት እና ከሌላ ሀገረ ስብከት 2 በድምሩ 116 ሰልጣኞችን ያሳተፈ ነው። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ኃላፊ ሰልጣኞች በሚኖራቸው የስልጠና ቆይታ የመጡበትን ዓላማ በማሰብ በትኩረት ተከታትለው የሚሰጣቸውን የቤተክርስቲያን ኃላፊነትና ተልዕኮ እንዲፈጽሙ እንዲሁም ተግባራዊ ክርስትና በመኖር በጾም፣ በጸሎት፣ በማስቀደስና በመቁረብም እንዲተጉ አሳስበዋል። [ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ] [የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

ኤፍሬም እንዳለ የተባለ ደራሲ “እንጨዋወት” በሚል ርእስ ያዘጋጀው ትኩረቱን ማኅበራዊ ሂስ ላይ ባደረገው መጽሐፍ አንድ ታሪክ እናገኛለን። ታሪኩ እንዲህ ነው። አንድ ድርጅት ከከተማ ወጣ ባለ ቦታ ያከ
ኤፍሬም እንዳለ የተባለ ደራሲ “እንጨዋወት” በሚል ርእስ ያዘጋጀው ትኩረቱን ማኅበራዊ ሂስ ላይ ባደረገው መጽሐፍ አንድ ታሪክ እናገኛለን። ታሪኩ እንዲህ ነው። አንድ ድርጅት ከከተማ ወጣ ባለ ቦታ ያከማቻቸው አሮጌ መኪናዎች፣ የወላለቁ ብረታ ብረቶች እና ከጥቅም ውጭ የሆኑ የተለያዩ ቁሰቁሶች ነበረው፡፡ ክምችቱ ያለ ጥበቃ ለረጅም ጊዜ ቆይቷል፡፡ በኋላ ግን የድርጅቱ ባለ ሥልጣናት መጠበቅ አለበት ብለው ስላመኑ ሁለት የጥበቃ ሠራተኞች እንዲቀጠሩ ወሰኑ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጥበቃዎቹ በሰዓት መግባት መውጣታቸውን ከዋናው መሥሪያ ቤት ሆኖ በርቀት መከታተል እንዳልተቻለ ዘገባ ቀረበ፡፡ እነርሱን በፈረቃ የሚከታተሉ ሁለት ሰዎች ተቀጠሩ፡፡ ከቆይታ በኋላ ለአራቱ ሠራተኞች ደመወዝ ከፋይ እንደሚያስፈልግ ታመነበትና ተቀጠረ፡፡ ከዚያም የሰው ኃይል አስተዳደር መኖር አለበት ተብሎ እርሱም ተቀጠረ፡፡ የሰው ኃይል አስተዳደሩ ጸሐፊ ስላስፈለገው ጸሐፊ ተጨመረ፡፡ ይህን ሁሉ ያለ ሥራ አስኪያጅ ማስተዳደር እየከበደ ስለመጣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተሾመለት፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ቀስ በቀስ ብዙ ሠራተኞች ያለው ድርጅት ሆነ፡፡ ማንበብ ይቀጥሉ ... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/መዋቅሩ-ለወንጌል-ወይስ-ወንጌሉ-ለመዋቅሩ/ መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ? ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ሊቃውንት ኤጲስ ቆጶሳት ለመሾም ያሰቡትና የጠየቁት ጥንት ነው። ከዛግዌ ነገሥታት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሐርቤ ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ጳጳሳት እ
የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ሊቃውንት ኤጲስ ቆጶሳት ለመሾም ያሰቡትና የጠየቁት ጥንት ነው። ከዛግዌ ነገሥታት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሐርቤ ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ጳጳሳት እንዲሾሙ አሳብ አቅርቦ ነገሥታት ከትምህርተ ሃይማኖትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አንጻር እንዲመረምሩት አድርጎ ነበር። አሳቡ ተግባራዊ እንዲሆን የፈለገውም ጳጳስ ከግብፅ ማስመጣቱን እንደ ቅኝ ግዛት ቈጥሮት ሳይሆን ከአገራቱ ርቀት አንጻር ጳጳስ እንዲሾም የሚጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ለብዙ ዓመታት የሚቆይ በመሆኑ፣ በዚያውም ላይ ባሕሉን የሚያውቀው፣ ቋንቋውን ከሚናገረው ቢሾም ክህነት ከመስጠት በተጨማሪ አስተምሮ ብዙዎችን መመለስ ይችላል ብሎ በማመን ነበር። ማንበብ ይቀጥሉ ... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የኤጲስ-ቆጶሳት-አሿሿም-ታሪካችን/ የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ሲሰጥ የነበረው የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና ተጠናቀቀ። ሐምሌ 27 2015 ዓ.ም፤ በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሲሰጥ የነበረው የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የአሠልጣኝ መምህራን ሥልጠና በዛሬው ዕለት ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የተለያዩ መምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት ተጠናቋል። በመርሐግብሩ ተመራቂ ተማሪዎች የቆይታ ሪፖርትን ጨምሮ የተለያዩ መርሐግብሮች የቀረቡ ሲሆን ሠልጣኝ መምህራኑ ከዚህ በኋላ ለሚኖራቸው ሐዋርያዊ አገልገሎት ቤተክርስቲያንን በሚፈለገው መጠንና ዘመኑን በዋጀ መልኩ አገልግሎታቸውን እንዲያከናውኑ የማሳሳቢያ መልዕክት ከመምሪያው ኃላፊዎች ተቀበልዋል። የማደራጃ መምሪያው ምክትል ሰብሳቢ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ እንደተናገሩት "ዛሬ የተሰጣችሁ ከተዘጋጀው ትምህርት በጣም ጥቂት ቢሆንም እናንተ  ሥርዓተ ትምህርቱን ጠንክራችሁ ለፍሬ እንዲበቃ ማድረግ አለባችሁ" በማለት አሳስበዋል። በማስከተልም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ስንታየሁ የሥልጠናውን ጠቅላላ ሪፖርት አቅርበዋል። በመጨረሻም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለተመራቂ መምህራኑ የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕታቸውም "እናንተ ቤተክርስቲያን የመጠበቅ ኃላፊነት አለባችሁ አሁን በተማራችሁት ትምህርት ነገ ሌሎች እንዲፈሩ ማድረግ አስፈላጊ ነው፤ እንደነ ቅዱስ ጳውሎስ ለተመረጣችሁበትና ለተሾማችሁበት ወንጌል በመታመን ማገልገል አለባችሁ" በማለት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ በዚህ ሥልጠና ለተሳተፉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበው ቃለ በረከት በመስጠት ምርቃቱን አብስረዋል። ተመራቂ መምህራኑ ከመምሪያው ኃላፊዎችና ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳቱ የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለዋል። [የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion