ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Ir al canal en Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Mostrar más1 719
Suscriptores
-124 horas
-47 días
-1430 días
Archivo de publicaciones
አወይ አንቺ አወይ እኔ
አንቺ ማለት’ኮ የሌሊት ጨረቃ
ሰስቼ የማይሽ እንደ ድንቡሽ ጮርቃ
… አንቺ ማለትማ የቀትር ፀሃይ
ደፍሬ ‘ማላይሽ ያላንቺም አላይ
..እያልኩኝ ሳወድስ እኔ ማለት ለካ
ምድጃ ሟቂ ነኝ
የነደደ ክሰል ባመድ በተተካ
@seifetemam #seifetemam
Seife Temam:
እንዋዋል
ስንቱን ውሎ
ስንቱን አዳር
ስንቱን ፍቅር
ስንቱን አሳር
ስንቱን ገድለን
ስንቱን አስረን
ስንቱን ቀብረን
ስንቱን አምነን
በአንዲት ቅጠል እንጠለል
ከማን አብረን እንገንጠል
ከማን እንሂድ ከማን እንዋል
ማን ይፈርም እንዋዋል?
@seifetemam #seifetemam
✍...ብዕር ለ ግጥም
እጆች ሁሉ ይፅፋሉ
ዓይኖች ሁሉ ያነባሉ
ጆሮዎች ሁሉ ይሰማሉ
Join ያርጉ
☞ https://t.me/joinchat/C_70PQ0-ZY4kCH214gXV2Q
አንዷ መንገድ
አንዲት መስመርብቻ
በዓይኔ ፊት አለች
ደሞም ከሷ ውጪ
ችክችክ እና ድልዝ
ለንባብ አይመች
ይቺ ደማቅ መስመር
ይቺ ደማቅ መንገድ
እራሷን ዘርግታ
ወደራሷ ምትወስድ
እራሷን አንድዳ
ነድዳ ‘ምትማገድ
ይኧው ከሷ ውጪ
ቅዠት ነው ድንብርብር
ሰልፍ የሳተ ጉንዳን
የማይቀድስ ደብር
ጭስ የሌለው እጣን
የሚያሳስቅ ቀብር
የሚታለም እውን
የሚላፋ ነብር
እውነትን ፈለኳት
እንኋት ደማምቃ
አየኋት ሳልለፋ
በመስመሯ መጥቃ
በጉልህ ተጽፋ
ማተርኩ ወደ ፍቅር
ትታያለች ዘልጋ
ክረምቱንም በጋ
ሌሊቱን ቀን አርጋ
መስመሯን አፍቅራ
ፍቅር መስመር ፈጥራ
ባ’ለም ካለው ሁሉ
በጎውን ተመኘው
በአንድነት አንድ ሁኖ
አንዲት መስመር ላይ ነው
ከዛች መስመር ውጭ
ሁሉ ችክችክ ሁሉ ድልዝ
ለንባብ አይመች
እውን አልባ ውጥንቅጥ
የ’ልም አለም አደንዛዥ
ያለ መስሎ ሚያጥጥ
ሰው በቁም ‘ሚያስቃዥ
ያባይ ስጋ ቅጥቅጥ
የበረሃ ሚራዥ
2008
@seifetemam #seifetemam
የኔ ክረምት
የከረረን ጽልመት
በምናቤ ሳክም
በከረረ ክረምት
በነጠላ ሳዘግም
ጽልመቱም አልነጋ ክረምቱም አልባተ
ልቤን ከገላዬ መለየት አቃተ
@seifetemam
#seifetemam
አበቦቹ
ተናንሽ አበቦች የፍካት ጨረሮች
የብራ አለም ሰዎች
የንጹህ አገር ዜጎች
ለሃሴት አፎቱ
ለፍቅርም ቤቱ
ውበት ምልክቱ
. . . ትናንሽ አበቦች. . .
እንደጽገሬዳ የልብ ነጋሪ
እንደ አደይ አበባ ብሩህ ቀን አብሳሪ
ውስጠትን ሰርሳሪ
በውበት አሳሪ. . .
እነዚን አበቦች ለጌጥነት ያጨ
እነዚን አበቦች ለጌትነት ያጨ
ምንጩን አደረቀ ነገውንም ቀጨ
(ለልጆቻችን. . .)
#seifetemam
@seifetemam
አቻ
ቃላት ሳታረቁ
ነገር ሳታደቁ
ያላቻ ጋብቻ
ይቅር ብሎ ብቻ
አቻ ደሃ አጥተን
ይኸው ቆመን ቀረን
ሰይፈ ተማም
2007
#seifetemam
ለአከራዬ ልጅ
መብራት የጠፋ ለት ሻማ ስታበሪ
ጥላሽን አየሁት ልብስ ስትቀይሪ
ልብስ የምታጥቢም ለት ጨምረሽ ከሳፋ
(መብራትስ ሁሌ ይሂድ ውሃ ግን አትጥፋ)
ጦረኞቹን አየሁ ሲሉ ቀና ደፋ
ቀና ደፋ እያልኩኝ ስሰራ የምታይ
እንዳያልፍብኝ ነው የናትሽ ቤት ኪራይ
ቤት ኪራይ ፍለጋ ጊቢያችሁ ስመጣ
አንቺን ብዬ ከፈልኩ ቤቱስ አያዋጣ
አያዋጣም ከቶ 'ማይከለል መስኮት የማይዘጋ በር
እናትሽ ሲወጡ ካልመጣሽ በስተቀር
#seifetemam #አሁን
@seifetemam @seifetemam
ድምጽ፣ ሽታ፣ ጣዕም
ምስኪኑ ሰአሊ በወጠረው ሸራ
የሳላት ጉራንጉር የሳላት መንደሯ
ድምጽ የላትም ጭራሽ
ምኗም አይሰማም
ድምጽ ቀለም ሆኖ ከሸራው ላይ የለም
እነማማ እንትና ሰውን ሲቦጭቁ
እነ ጋሽ እከሌ አዳልጧቸው ሲወድቁ
ወይዘሮ እከሊት ጠበል ሲጠድቁ
የተሰማው ሁሉ የለም ከቀለሙ
የተጠጣው አቦል ከየት አለ ጣ'ሙ
ከየት አለ ሽታው የቡናው የጣኑ
ድምጽ ሽታ ጣዕም
በቀለም አይወጡም
በብሩሽ አይሰፍሩም
ወይስ
አይን የለም እነዚን ለማስፈር ከሸራ
አይን የለም እኒህን ለማየት ከሸራ
ምስኪኑ ሰዓሊ የሳላት መንደሯ
ስንቱን እንዳወጣች ስንቱን ነገር ቀብራ
ወይም
ድምጽ ሽታ ጣዕም ከዚህ ሰፈር የሉም
አይሰሙ አይሸቱ ጨርሶም አይጥሙም
እንደድሮ አይደሉም
ወይም...
ወይም ይጮሃሉ
ወይም የገማሉ
ወይም ይመርራሉ
ድምጽ ሽታ ጣዕም ኑሮነን እያሉ
ባለመሳል መስመር ሁሌ እየተሳሉ
#seifetemam #ድምጽሽታጣዕም
ፍቅርና ደሞዝ
ስራ ተቀጥሬ ከዋክብት ቆጠራ
እጅግ አደከመኝ እንዴት ብዬ ልስራ
ቆጥሬ ቆጥሬ እየተምታታብኝ
አልሰራህም ብለው ደሞዝ ከለከሉኝ
ስራዬ ፍቅር ነው ከዋክብት ውበቷ
ደሞዜም እሷው ነች በጄየገባች ለታ
(ለ...)
ሰይፈ ተማም 1996
ሃሞተ ቢስ ጀግና
ዛሬ አዲስ አባ ውስጥ
ብዙ ሰው መሮታል
አፉ ሬት ሆኖታል
የሚጠጣው ድራፍት
መሪር እንደጅኑ
እንደጠላው ሁሉ
የሚበላውም ጫት
መሪር እንደኑሮ
የሚጣፍጥ መርሮ
ይህን ጀግና ትውልድ
እንደው በለበጣ
ሃሞተ ቢስ አሉት
ሃሞት እየበላ
ሃሞት እየጠጣ
#seifetemam
ባንቺ መንቃት
ፈዝዘሃል አትበሉኝ ነቅቻለሁ በጣም
ከዓይኔ 'ሚገባ የሚታይ ሰው ባጣም
ስለሷ አስባለሁ እጅጉን ታትሬ
መኖሯን ለከርሞ ማደሯን ለዛሬ
#seifetemam
ምርጫ
====
ቤት ሥራ ፤ ተፈንከት
ምርጫው የራስህ ነው ድንጋይ ሲወረወር
አናትህን ስትባል ግንባር እየሰጠህ ሕይወትህን ማማረር?
ወይ እየጠራረብህ በልክ እየሰተርህ ግንብህን ማበጀት አጥርህን መደርደር
#የጌታነህ_ልጅ
ነሐሴ 2009
አቋራጭ
የኔን መጥፎ 'ሚሻ መሆኑን እያየሁ
እንዴት እንደራሴ ጠላቴን ልውደደው
… ይልቅስ…
ከቃሉ እንዳልወጣ እንዳይቀየመኝ
እራሴን ጠልቼ ጠላቴን ባልወደው
አቋራጭ መሰለኝ
ሰይፈ ተማም 2004
#seifetemam #አቋራጭ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
