es
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Students' Union

Ir al canal en Telegram

This is official , Ethiopian Higher Education Institutions Students' Union channel. Right info will be posted here. "we serve students!"

Mostrar más
4 873
Suscriptores
-324 horas
-117 días
-4730 días
Archivo de publicaciones
ማስታወቂያ የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰ
ማስታወቂያ የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና  (NGAT) ምዝገባ የሚካሄደው ከሐምሌ 24 - ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ትምህርት ሚኒስቴር

ማስታወቂያ ጉዳዩ፡- የመውጫ ፈተና ድጋሜ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን ይመለከታል በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የሚሰጠው የመውጫ ፈተናን በድጋሜ ለምትወስዱ ተፈታኞች፡- 1. በሰኔ 2015 ዓ.ም እና በየካቲት
ማስታወቂያ ጉዳዩ፡- የመውጫ ፈተና ድጋሜ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን ይመለከታል በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የሚሰጠው የመውጫ ፈተናን በድጋሜ ለምትወስዱ ተፈታኞች፡- 1. በሰኔ 2015 ዓ.ም እና በየካቲት 2016 ዓ.ም ተፈትናችሁ የነበረ እና አሁን በድጋሜ ለመፈተን ማመልከት ለምትፈልጉ እና፣ 2. ከሰኔ 2015 ዓ.ም በፊት የሕግ መውጫ ፈተና ወስዳችሁ የማለፍያ ነጥብ ያለገኛችሁ አሁን በድጋሚ ለመውሰድ ለምትፈልጉና ስም ዝርዝራችሁ ከቀድሞው ዩኒቨርስቲያችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር የተላከላችሁ አመልካቾች ምዝገባው እስከ ግንቦት 25 ቀን 2016 ዓ.ም የተራዘመ በመሆኑ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ምዝገባውን እንድታጠናቅቁ እናሳውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- • ከላይ ከተገለጸው ጊዜ ውጭ የሚቀርቡ የምዝገባ ጥያቄዎች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡፡ • በሰኔ 2015 ዓ.ም እና በየካቲት 2016 ዓ.ም ተፈተናችሁ የማለፊያ ውጤት ያልመጣላችሁ አሁን በድጋሜ መፈተን ለምትፈልጉ አመልካቾች የሚጠበቅባችሁን የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር ብቻ የምትፈጽሙ ይሆናል፡፡ • ከሰኔ 2015 ዓ.ም በፊት ለሕግ መውጫ ፈተና ተቀምጣችሁ በድጋሜ ለመፈተን የምትፈልጉ አመልካቾች ስም ዝርዝራችሁ ከቀድሞ ዩኒቨርሲቲያችሁ መላኩን በማረጋጥ የሚጠበቅባችሁን የአገልግሎት ክፍያ ለዚሁ ጉዳይ በተከፈተው የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000553176097 ገቢ በማድረግ ደረሰኙን በግልፅ በሚታይ ስካን ኮፒ በማድረግ በseneexit2016@gmail.com ኢሜል አድራሻ እንድትልኩ እናሳውቃለን። ትምህርት ሚኒስቴር

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ድጋሚ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን አሳወቀ። በ2016 ዓ/ም ሰኔ ወር ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ተፈታኞች ምዝገባ የሚከናወነ
ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ድጋሚ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን አሳወቀ። በ2016 ዓ/ም ሰኔ ወር ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ተፈታኞች ምዝገባ የሚከናወነው ከግንቦት 14 እስከ 21/2016 መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በመክፈል በ https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል። የአገልግሎት ክፍያ  500.00 ብር በ ' ቴሌ ብር ' ብቻ የሚፈጸም መሆኑ አስገንዝቧል። #ለመጀመሪያ_ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚፈተኑ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚካሄደው እና የአገልግሎት ክፍያ በተቋማቸው በኩል መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ አስፈላጊ የመፈተኛ መረጃዎችን በተቋማቸው በኩል እንደሚደርሳቸው አሳውቋል። @tikvahethiopia

43ኛው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሄደ፡፡ ================================= 43ኛው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሂዷል፡፡ በጉባኤው መክፈቻ የቀድሞ የሀገር አቀፍ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ሚካኤል ያቦነሽ የሀገር አቀፍም ሆነ የዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎች ህብረት አመራሮች የቆይታ ጊዜ ሁለት አመት መሆኑንና በጉባኤው በሀገር አቀፍ ደረጃ ህብረቱን የሚመሩ አዲስ አመራሮች የሚመረጡ መሆኑን ጠቅሰው ነባሩ አመራር ባበረከተው አስተዋጻኦ ባለፉት ሁለት አመታት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ዩኒቨርሲቲዎቻችን በውስጣቸው ከሚፈጠሩ ሁከቶች ጸድተው በአንጻራዊነት በሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የቆዩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የህብረቱ አመራሮች በተቋማት ውስጥ የሰሩዋቸው በርካታ ስራዎች መኖራቸውን ጠቅሰው በተጨማሪነትም ተማሪዎች ከእለት ምግባቸው ጭምር ቀንሰው በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻቸው በመርዳት አለኝታቸውን እንዲገልፁ የማስተባበር፣ ባለፈው አመት የአፍሪካ ተማሪዎች ቀን በሀገራችን በአዲስ አበባ ከተማ እንዲከበር የማድረግ፣ በሀገርና አህጉር አቀፍ መድረኮች ላይ የሀገራችንን የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችን በመወከል የሚጠበቅባቸውን ተሳትፎ ማድረጋቸው እና የመሳሰሉትን ለአብነት ተነስተዋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የመሰረተ ልማትና አስተዳደር ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ የሀገረችንን ብልጽናና ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ሂደት የበኩላቸውን ሚና መወጣት የሚችሉ ምሩቃንን ለማፍራት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የሚያደርጉት ሁለንተናዊ ጥረት ስኬታማ እንዲሆን የተማሪዎች ህብረት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ተሳትፎ ይበልጥ እንዲያድግና ውጤታማ እንዲሆን ትምህርት ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ህብረቱ የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ቆይታ በተቻለ አቅም የተመቸ እንዲሆን የተማሪዎች መብት እንዲጠበቅና በዚያው ልክ ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ከትምህርት ሚኒስቴርና የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ጋር ተቀራርቦና ተቀናጅቶ ከመስራት በተጨማሪ የተማሪዎች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲጠናከር ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራበት እንሚሚገባም አስገንዝበዋል፡፡ ዶ/ር ስለሞን አክለውም ባለፉት ሁለት አመታት በዩኒቨርሲቲዎች ደረጃም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀላፊነታቸውን ሲወጡ የነበሩ የተማሪዎች ህብረት አመራሮችንና ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲዘጋጅ ወስነው የሰሩ በየደረጃው ላሉ የክልሉ፣ዩኒቨርሲቲውና የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት አመራሮች ያላቸውን አድናቆትና ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ሀላፊ አቶ አብዶ ናስር በበኩላቸው የነባሩን የህብረቱ አመራሮች ላበረከቱት ውጤታማ አስተዋጻኦ አመስግነው አዲስ የተመረጡ አመራሮች የነበሩ ድክመቶችን በማረምና የነበሩ ጥንካሬዎችን ይበልጥ አጠናክረው ከማስቀጠል ጎን ለጎን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል ሀገርን ያስቀደመ የተጠናከረ ህብረብሄራዊ አንድነት፣አብሮነት፣መቻቻልና ፍቅር እንዲጎለብት ተግተው መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ አቶ አብዶ ጨምረም ለአዲሱ የህብረቱ አመራሮች መልካም የሥራ ጊዜ በመመኘት በቀጣይ ጊዜያት ለአካል ጉዳተኞችና ሴት ተማሪዎች ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶኣቸው የሚሠራ መሆኑን ከግንዛቤ በማሰገባት በዚሁ ልክ በእቅዳቸው በመያዝ መተግበር እንደሚጠበቅባቸው አሰገንዝበው ህብረቱ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ትምህርት ሚኒስቴርም ከሚሰጣቸው የተለያዩ ድጋፎች በተጨማሪ አግባብነት ያላቸው የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን በቀጣይነት ለመስጠት እቅድ መያዙን አሳውቀዋል፡፡ በጉባኤው በዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የተመርጡ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንቶች፣ የቀድሞ የተማሪዎች ፕሬዝዳንቶች፣ የሴቶች ጉዳይ ዘርፍ ተጠሪዎች እና የልዩ-ፍላጎት ዘርፍ ተጠሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ለቀድሞ የተማሪ ህብረት ፕሬዝዳንቶች በትምህርት ሚኒስቴር የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በጉባኤው የሀገር አቀፍ ህብረቱን ለቀጣይ አመታት የሚመሩ ስራ-አስፈፃሚዎች የተመረጡ ሲሆን የምርጫውን ሙሉ ዘገባ ይዘን እንመለሳለን። @EHEISUOfficialChannell

የተማሪዎች ሕብረት በጥቂት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የተፈፀመውን ያልተገባ ድርጊት ሁሉንም ተማሪ የማይወክል እና የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ገለፀ ------------------------------------ አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2016(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሕብረት በጥቂት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የተፈፀመውን ያልተገባ ድርጊት የሚወገዝ እና ሁሉንም ተማሪ የማይወክል ተግባር መሆኑን አስታወቋል። ሕብረቱ የተፈጸመው ድርጊት ፍፁም ተቀባይነት የሌለው የጥቂት ተማሪዎች ጥፋት መሆኑንም ገልጿል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውስጥ አሠራሩን ለማዘመን ባደረገው እንቅስቃሴ ዓርብ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊቱን በተፈጠረ ስህተት ተገቢ ያልሆነ የገንዘብ እንቅስቃሴ መደረጉ ይታወቃል። በዚሁ ሌሊት ከ490 ሺህ በላይ ጤናማ ያልሆነና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ልውውጥ እንደነበርም በባንኩ ተገልጿል። በዚህ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ልውውጥና እንቅስቃሴ የአንዳንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥቂት ተማሪዎች የተሳተፉ መሆኑም ይታወቃል። ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገረው የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዝዳንት ሚካኤል ያቦነሽ፤ በዚህ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ተማሪዎች ተግባር በፍፁም ተቀባይነት የሌለውና የሚወገዝ መሆኑን ገልጿል። በመንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አሁን ላይ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች መኖራቸውን የጠቀሰው ፕሬዝዳንቱ፤ የተፈፀመው ድርጊት ሁሉንም የማይወክል የጥቂቶች ጥፋት መሆኑን ተናግሯል። በመሆኑም የተማሪዎቹን ያልተገባ ድርጊት የተማሪዎች ሕብረት በፅኑ እንደሚያወገዘው ገልጿል። በነበረው ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ በማያውቁት መንገድ ተሳታፊ የነበሩ ተማሪዎች እንደነበሩ አንስቶ፤ የወሰዱትን ገንዘብ መመለስ እንደቻሉም ጠቅሷል። በዚሁ ተግባር ላይ ተሳትፈው የነበሩ ሌሎች ተማሪዎችም በወቅቱ የተመዘበረውን የሀገርና የሕዝብ ኃብት በመመለስ ላይ መሆናቸውን ጠቅሶ፤ ገንዘቡን በማስመለስ ረገድ ሕብረቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የሀገር ሁለንተናዊ አቅምና የልማት መሠረት መሆናቸውን የተናገረው የሕብረቱ ፕሬዝዳንት፤ በዚሁ ልክ ኃላፊነት ወስደው መንቀሳቀስ አለባቸው ሲልም አሳስቧል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ሁሉም ወጣቶች የነገ ሀገር ተረካቢዎች በመሆናቸው አደራቸውን በታማኝነት እንዲወጡም መልዕክቱን አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፤ አብዛኛው ተማሪዎች በባንኩ በተደረገላቸው ጥሪ የወሰዱትን ገንዘብ እየመለሱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተመላሽ ላደረጉ ተማሪዎች ባንኩ ምንም ዓይነት ክስ እንደማይመሰርትም ማረጋገጣቸው ይታወሳል። @EHEISUOfficialChannell

#Update ከየካቲት 6-9/2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ የመፈታኛ የይለፍ-ቃል (Password) ከስር በተገለፁት
#Update ከየካቲት 6-9/2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ የመፈታኛ የይለፍ-ቃል (Password) ከስር በተገለፁት አማራጮች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። 1. በምዝገባ ወቅት በሞላችሁት email በኩል፣ 2. https://exam.ethernet.edu.et ላይ በመግባት የከፈላችሁበትን Transaction Number በማስገባት፣ 3. ከተመደባብችሁብት የመፈተኛ ተቋም ማግኘት ትችላላችሁ። ማሳሰቢያ፦ ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች የይለፍ-ቃል የምታገኙት ከምትማሩበት ወይም ከተመደባብችሁበት የመፈተኛ ተቋም ብቻ መሆኑ ተገልጿል። ተፈታኞች የሞዴል ፈተና እስከ የካቲት 5/2016 ዓ.ም መውሰድ እንዳለባችሁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። @tikvahuniversity

#Update የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ተራዝሟል። የመውጫ ፈተናው ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም። ትምህርት ሚኒስቴ
#Update የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ተራዝሟል። የመውጫ ፈተናው ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም። ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ይፋ ባደረገው መርሐግብር ፈተናው ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ታውቋል። ለአዲስ ተፈታኞች ሞዴል ፈተና ከጥር 27 እስከ 30/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል። የተፈታኞች ዝርዝር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚላክም ተገልጿል። @tikvahuniversity

እንኳን ለብርሀነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ! ==================================== የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ክብረ በዓሉን ለሚያከብሩ የከፍተኛ ትምህ
እንኳን ለብርሀነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ! ==================================== የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ክብረ በዓሉን ለሚያከብሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ2016 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ በዓሉ የደስታ፣ ሰላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ከልብ ይመኛል።   ✝️መልካም የጥምቀት በዓል!!!✝️ @EHEISUOfficialChannell

Repost from Tikvah-University
#MoE የ2016 ዓ.ም አጋማሽ የመውጫ ፈተና ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም በሐምሌ 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ወስዳችሁ ያላለፋችሁ ፈ
#MoE የ2016 ዓ.ም አጋማሽ የመውጫ ፈተና ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም በሐምሌ 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ወስዳችሁ ያላለፋችሁ ፈተናውን በድጋሚ (Re-exam) ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተፈታኞች ምዝገባ ከጥር 08 እስከ 15/ 2016 ዓ.ም ድረስ ማከናወን ይጠበቅባችኋል። የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በቴሌ ብር ብቻ በመክፈል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። ለመመዝገብ እና የመፈተኛ ተቋም ለመምረጥ፦ https://exam.ethernet.edu.et ተጨማሪ ድጋፍ ለማግኘት በስልክ ቁጥር 0118132176 ይደውሉ ወይም በኢ-ሜይል registration@ethernet.edu.et ይፃፉ። Note: ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የምታካሒዱት እና የአገልግሎት ክፍያ የምትፈፅሙት በተቋማችሁ በኩል መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። @tikvahuniversity

እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ! ---------------------------------------- የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች
እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ! ---------------------------------------- የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዓሉ የደስታ፣ ሰላምና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ ይመኛል። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለምትገኙ በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ ተማሪዎች፣ የተማሪ ህብረት አመራሮችና አባላት መልካም የገና በዓል እንዲሆንላችሁ አብዝተን እንመኛለን።            ✝️መልካም የገና በዓል!!!✝️ @EHEISUOfficialChannell

2ኛ ዙር ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (GAT) ምዝገባ ዛሬ ይጀምራል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚሰጡት 2ኛ ዙር ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ
2ኛ ዙር ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (GAT) ምዝገባ ዛሬ ይጀምራል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚሰጡት 2ኛ ዙር ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (GAT) ምዝገባ ዛሬ የተጀመረ ሲሆን እስከ አርብ ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል። የመግቢያ ፈተናው ከህዳር 03 እስከ 07/2016 ዓ.ም ይሰጣል። ፈተና በመጀመሪያ ዙር የመግቢያ ፈተናው መውሰድ ላልቻሉ እንዲሁም ፈተናው ወስደው ማለፍ ላልቻሉ ተጨማሪ ዕድል የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፖርታል ላይ በመግባት ምዝገባ ያድርጉ፦ https://portal.aau.edu.et @tikvahuniversity

በዚህ ዓመት ካለፈው ዓመት በተሻለ በርካታ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና (Exit-exam) እንዲያልፉ መልካም ምኞታችን ነው፡፡ ከምኞት ባለፈ ደግሞ፣ ሳንዘናጋ ሁሉንም አማራጮች ተጠቅመን በግዜ በቂ ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ ለዝግጅት ከሚያግዙን አማራጮች መካከል በርካታ የሞዴል (መልመጃ) ፈተናዎችን መስራት፣ ያለፉ የመውጫ ፈተናዎችን ካገኘን መሞከር እንዲሁም ከመምህራኖቻችን ጋር በቅርበት ጥያቄዎችን መስራት የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ በተጨማሪም ለዚህ ዓላማ የሚያግዙ የቴክኖሎጂ አማራጮችን መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ፣ ZigijuTemari የሚባል አፕሊኬሽን ከ Google Playstore ላይ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ወይም በኮምፒውተራችሁ ኢንተርኔት መፈለጊያ ብራውዘር ላይ www.wonbis.com ብላችሁ በመግባት የሞዴል ፈተናዎችን፣ ያለፉ የመውጫ ፈተናዎችን እና የመምህራንን እገዛ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ በድጋሚ ለሁላችሁም መልካም የዝግጅት ግዜ እና መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

ብቃት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት ሂደት ውስጥ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀረበ። ============================= በትምህርቱ ዘርፍ በሚከናወኑ ቁልፍ የሪፎርም ተግባ
+3
ብቃት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት ሂደት ውስጥ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀረበ። ============================= በትምህርቱ ዘርፍ በሚከናወኑ ቁልፍ የሪፎርም ተግባራትና የባለድርሻ አካላት ሚናን በተመለከተ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። በምክክር መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ቁልፍ መልእክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኤባ ሚጀና ባደረጉት ገለጻ ብቃት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት ሂደት ውስጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። መሪ ስራ አስፈጻሚው አያይዘው እንደገለጹት የትምህርት ሚኒስቴር በሚያከናውናቸው የሪፎርም ስራዎችና በሚያስቀምጣቸው አቅጣጫዎች የባለድርሻ አካላት ሚና እና አበርክቶ ወሳኝ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አብራርተዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ ትምህርትና ፕሮግራሞች ዴስክ ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ነገዎ በበኩላቸው ባደረጉት ገለጻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያከናውናቸው ቁልፍ ስራዎችና የሪፎርም ተግባራት ሀገራዊና ማህበራዊ ፋይዳቸው አዎንታዊ በሆነ መልኩ ጎልቶ እንዲወጣ የባለድርሻ አካላት ሚና እና አበርክቶ ወሣኝ በመሆኑ አናቦና አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል። በምክክር መድረኩ ላይ የጤና ሚኒስቴርን ጨምሮ ሌሎች ቁልፍ የባለድርሻ አካላት በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ሚና እና አበርክቶ በተመለከተ ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን በዘርፉ የሚከናወኑና የሚወሰኑ ውሳኔዎች በጥንቃቄ የመፈጸሙ ሂደት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው አስገንዝበዋል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረትን ጨምሮ የተለያዩ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። @EHEISUOfficialChannell

#Urgent በራያ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በሚዛን ቴፒ እና በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመድባችሁ የተመረቃችሁ ተማሪዎች ስልክ ቁጥራችሁ ስለተፈለገ እ
+2
#Urgent በራያ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በሚዛን ቴፒ እና በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመድባችሁ የተመረቃችሁ ተማሪዎች ስልክ ቁጥራችሁ ስለተፈለገ እስከ ጥቅምት 16/2016 ዓ.ም ድረስ በተከታዮቹ ስልክ ቁጥሮች 0920478530 / 0914750148 ላይ በመደወል እንድታስመዘግቡ ራያ ዩኒቨርሲቲ አሳስቧል። (ዩኒቨርሲቲው ያወጣው የተማሪዎች ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።) @tikvahuniversity

#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጄና አማካኝነት ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ደብዳቤ በ2016
+1
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጄና አማካኝነት ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ደብዳቤ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ለማድረግ እንዲቻል ለፈተናው የሚቀመጡ ተማሪዎች መረጃ በአስቸኳይ እንዲላክለት ጠይቋል። ሚኒስቴሩ ፤ ተቋማት መረጃው እጅግ ቢዘገይ እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲልኩ ያሳሰበ ሲሆን የማያሳውቅ ዩኒቨርሲቲ " ተፈታኝ ተማሪ የለውም " በሚል ተይዞ የሚታቀድ መሆኑን በጥብቅ አስገንዝቧል። በ2015 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰጠው የመውጫ ፈተና በመንግስት ተቋማት ለፈተናው ከተቀመጡት 77,981 ተማሪዎች ውስጥ 50 እና ከዚያ በላይ በማምጣት ያለፉት 48,632 ተማሪዎች ወይም 62.37 በመቶ መሆናቸው አይዘነጋም። በግል ተቋማት ደግሞ ለፈተና ከተቀመጡት 72,203 ተማሪዎች ውስጥ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተው ያለፉት 12,422 ተማሪዎች ወይም 17.2 በመቶ ብቻ ነበሩ። በድምሩ ከአጠቃላይ 150,184 የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ፈተናውን ያለፉት 61,054 ብቻ ወይም 40.65 በመቶ ናቸው። የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና አስተዳደር መመሪያ እንደሚያሳየው ከሆነ ፈተናው በዓመት ሁለት ጊዜ ይሰጣል። የመጀመሪያው በአመቱ መጨረሻ ሲሆን ሁለተኛ በአመቱ አጋማሽ ነው። የመጀመሪያውን የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች በዚህ አመት አጋማሽ ላይ በሚዘጋጀው ሌላ ፈተና መፈተን የሚችሉ ሲሆን ከዚህ ቀደም ትምህርት ሚኒስቴር  ተፈታኞች ዳግም ፈተና ለመውሰድ መጀመሪያ ሲማሩበት ወደነበረበት ተቋም መሄድ ሳይጠበቅባቸው ባሉበት አካባቢ ባሉ ተቋማት ፈተናውን እንደሚወስዱ የሚደረግበት ስርዓት እንደሚዘረጋ መግለፁ አይዘነጋም (በዚህ ጉዳይ ወደፊት የሚወጣ መረጃ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን)። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ፣ ተመራማሪና ተጋባዥ መምህር የሆኑት ፕ/ር ገቢሳ ኤጀታ የአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል። ፕ/ር ገቢሳ ሽልማታቸውን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እጅ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ፣ ተመራማሪና ተጋባዥ መምህር የሆኑት ፕ/ር ገቢሳ ኤጀታ የአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል። ፕ/ር ገቢሳ ሽልማታቸውን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እጅ ተቀብለዋል። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ዘርፍ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ የአሜሪካ ዜጎች በሚሰጠው በዚህ ሽልማት 19 ሰዎች የተካተቱ ሲሆን የፐርድ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባው ፕ/ር ጋቢሳ አንዱ ሆነዋል። ፕ/ር ጋቢሳን ለሽልማቱ ያበቃቸው በከፍተኛ የምርምር ሥራቸው የእፅዋት ዘረመል ምህንድስና በመጠቀም በረሃማ የአየር ንብረትና ነፍሳትን የሚቋቋሙ የአዝርዕት ዘሮችን በማግኘታቸው እና በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ ዋስትና ለማረጋግጥ ያደረጉት አበርክቶ መሆኑ ተገልጿል። ፕ/ር ገቢሳ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ባከናወኗቸው የምርምር ሥራዎች የዝናብ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች በአነስተኛ እርጥበት በአጭር ጊዜ ብዙ ምርት የሚሰጡ የማሽላ ዝርያዎችን በማውጣት ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ በማድረግ አስተዋፅዖ አበርክተዋል። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለአየር ንብረት ተስማሚ የግብርና ቴክኖሎጂና የብዝሀ ህይወት ጥበቃ የአፍሪካ የልህቀት ማዕከል እንዲቋቋም ከፍቸኛ አስተዋፅዖ ማድረጋቸው ከዩኒቨርሲቲው የተገኘ መረጃ ያሳያል። የዓለም ሎሬት ፕ/ር ገቢሳ ኤጄታ በምግብ ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ከዚህ በፊት ከዓለም የምግብ ፕሮግራም ሽልማት የተበረከተላቸው መሆኑ ይታወቃል። የአርሶ አደሮችን ህይወት ለመቀየር በኢትዮጵያ ውስጥ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት እንዳበረከተላቸው ይታወሳል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#GAT የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። " 62 እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ / 80 ፐርሰንታይል ያገኙ በሚፈልጉበት ተቋም ገብተው መማር ይችላሉ " የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች
+1
#GAT የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። " 62 እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ / 80 ፐርሰንታይል ያገኙ በሚፈልጉበት ተቋም ገብተው መማር ይችላሉ " የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ የአገራዊ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (National GAT) የመቁረጫ ነጥብ አሳውቋል። በዚህም መሠረት ፤ አጠቃላይ ከተፈተኑት ጥያቄዎች ውስጥ 62 (50%) እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ ወይም 80 ፐርሰንታይል (80 Percentile) ያገኙ ተፈታኞች #ብቻ ለመማር በሚፈልጉበት ተቋም አመልክተው መማር የሚችሉ እንደሆነ ተገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመልካቾች ለማመልከት ሲመጡ ውጤታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus በመግባት እና የተማሪውን የመግቢያ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) በመጠቀም ማረጋገጥ ይቻላሉ ተብሏል። * ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከላይ ተያያዘውን ደብዳቤ ከትምህርት ሚኒስቴር አመራር ማረጋገጡ በዚሁ አጋጣሚ ያሳውቃል። @tikvahuniversity