Ustaz Muhammad Ferej
Ir al canal en Telegram
قال الله تعالى ( وَمَنْ أَحْسَنُ قَوْلًا مِمَّنْ دَعَا إِلَى اللَّهِ وَعَمِلَ صَالِحًا وَقَالَ إِنَّنِي مِنَ الْمُسْلِمِينَ )
Mostrar más4 433
Suscriptores
-424 horas
-127 días
-4730 días
Archivo de publicaciones
4 433
አንዱ ባጠፉው ሌላው አይወቀስም
እርግማን ወደ ተራጋሚዋ ልትመለስ ትችላለች
*عَنْ أَبِي الدَّرْدَاءِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ﷺ:* «إنَّ العبدَ إذا لَعَنَ شيئاً صَعِدَتِ اللعنةُ إلى السماءِ، فَتُغْلَقُ أبوابُ السماءِ دُونَها، ثم تَهْبِطُ إلى الأرضِ فَتُغْلَقُ أبوابُها دُونَها، ثم تأخذُ يَمِيناً وشِمالاً، فإذا لم تَجِدْ مَسَاغاً رَجَعَتْ إلى الذي لُعِنَ، فإن كان كذلكَ وإلا رَجَعَتْ إلى قَائِلِها» [رواه أبو داود].
*ከአቡ ደርዳእ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተወራው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦* (( "አንድ ባሪያ (ሰው) ማንኛውንም ነገር በረገመ ጊዜ፣ እርግማኑ ወደ ሰማይ ይወጣል፤ የሰማይም ደጃፎች በእርሱ ፊት ይዘጋሉ። ከዚያም ወደ ምድር ይወርዳል፤ የምድርም ደጃፎች በእርሱ ፊት ይዘጋሉ። ከዚያም ወደ ቀኝና ወደ ግራ ይልከሰከሳል (መግቢያ ይፈልጋል)፤ ምንም መውጫና ማረፊያ ባጣ ጊዜ ግን ወደተረገመው አካል ይመለሳል። ያ የተረገመው አካል እርግማኑ የሚገባው (የሚገባው በደለኛ) ከሆነ በእርሱ ላይ ያርፋል፤ ካልሆነ ግን (ያለ ጥፋቱ የተረገመ ከሆነ) እርግማኑ ወደ ተናጋሪው (ወደ ረጋሚው) ይመለሳል።" [አቡ ዳውድ ዘግበውታል]።
____
(ማብራሪያ በአጭሩ)
ይህ ሐዲሥ ያለ አግባብ ሰዎችን በተለይም ንጹሐንን መርገም ትልቅ ወንጀል መሆኑንና እርግማኑም ተመልሶ ረጋሚው ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ በግልጽ ያስረዳል።
ያ አላህ ተራጋሚ አታድርገን
ያ አላህ ተሳዳቢ አታድርገን
ያ አላህ ምላሳችንን ከኩፋ ነገር ጠብቅልን
4 433
ያ አላህ! የጅብሪል፣ የሚካኤልና የኢስራፊል ጌታ የሆንክ፣ ሰማያትንና ምድርን የፈጠርክ፣ የሩቁንም የቅርቡንም የምታውቅ ሆይ! አንተ በባሪያዎችህ መካከል ይከራከሩበት በነበረው ነገር ትፈርዳለህ። ሰዎች በተከራከሩበት ነገር ሐቂ ላይ በፈቃድህ ምራኝ፤ አንተ የምትሻውን ሰው ወደ ቀጥተኛው መንገድ ትመራለህና። አሚን
«اللَّهُمَّ رَبَّ جِبْرَائِيلَ وَمِيكَائِيلَ وَإِسْرَافِيلَ، فَاطِرَ السَّمَاوَاتِ وَالأَرْضِ، عَالِمَ الغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ، أَنْتَ تَحْكُمُ بَيْنَ عِبَادِكَ فِيمَا كَانُوا فِيهِ يَخْتَلِفُونَ، اهْدِنِي لِمَا اخْتُلِفَ فِيهِ مِنَ الحَقِّ بِإِذْنِكَ، إِنَّكَ تَهْدِي مَنْ تَشَاءُ إِلَى صِرَاطٍ مُسْتَقِيمٍ». (رواه مسلم)
4 433
#የነቢዩ_ﷺ_ሱና_በቁርዓን_ተቀባይነትና_አስገዳጅነት_ያለው_ስለመሆኑ :-
የአላህን መልክተኛ ﷺ መከተል ግዴታ መሆኑን የሚያስረዱ ግልጽ የቁዱስ ቁርዓን አንቀጾች :-
ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ለአላህ ይሁን። የአላህ ሰላትና ሰላም በፍጥረታት ሁሉ በላጭ በሆኑት በነቢያችን ሙሐመድ ﷺ፣ በባለቤቶቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ሁሉ ይውረድ።
አላህ ታላቁን ቁዱስ ቁርዓን ለሰዎች መመሪያ አድርጎ አውርዷል፣ ፍጥረታት መልክተኛውንም ﷺ እንዲከተሉ አዟቸዋል። ለአላህ መታዘዝን ከመልክተኛው መታዘዝ ጋር አቆራኝቷል፤ የነቢዩንም ﷺ ሱና ሁለተኛው የሸሪዓ (የሕግ) ምንጭና የቁርዓን ማብራሪያ አድርጎታል።
በዚህ አጭር ማጠቃለያ ውስጥ፣ ሱናን ለሚክዱ ወይም «ቁርዓን ብቻ ይበቃናል» ለሚሉ ወገኖች ቁርጥ ያለ ማረጃ የሚሆኑትንና የሱናን አስገዳጅነት የሚያረጋግጡትን የቁርዓን አንቀጾች እንቃኛለን።
#አንደኛ፡ ለመልክተኛው ﷺ መታዘዝን የሚያዙ የቁርኣን አንቀጾች :-
*{يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَطِيعُوا اللَّهَ وَأَطِيعُوا الرَّسُولَ} [النساء:59]*
«እነዚያ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ታዘዙ፤ መልክተኛውንም ታዘዙ።» [አን-ኒሳእ: 59]
*(«ታዘዙ» የሚለው ቃል ከመልክተኛው ጋር ተለይቶ መደጋገሙ፣ ለመልክተኛው መታዘዝ ራሱን የቻለና ከአላህ ትዕዛዝ ውጭ ብቻውን የሚቆም ራሱን የቻለ መመሪያ መሆኑን ያሳያል)*።
*{مَنْ يُطِعِ الرَّسُولَ فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ} [النساء:80]*
«መልክተኛውን የሚታዘዝ ሰው በእርግጥ አላህን ታዘዘ።» [አን-ኒሳእ: 80]
*(አላህ ለመልክተኛው መታዘዝን ልክ ለእርሱ እንደመታዘዝ አድርጎታል።)*
*{...وَأَطِيعُوا اللَّهَ وَالرَّسُولَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ} [آل عمران:132]*
«ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህንና መልክተኛውን ታዘዙ።» [አል-ዒምራን: 132]
#ሁለተኛ፡ መልክተኛውን ﷺ ከመቃረን የሚያስጠነቅቁ የቁዱስ ቁርኣን አንቀጾች :-
*{فَلْيَحْذَرِ الَّذِينَ يُخَالِفُونَ عَنْ أَمْرِهِ أَنْ تُصِيبَهُمْ فِتْنَةٌ أَوْ عَذَابٌ أَلِيمٌ} [النور:63]*
«እነዚያም ትዕዛዙን የሚጥሱ መከራ እንዳትደርስባቸው ወይም አሳማሚ ቅጣት እንዳያገኛቸው ይጠንቀቁ።» [አን-ኑር: 63]
*{وَمَنْ يَعْصِ اللَّهَ وَرَسُولَهُ فَقَدْ ضَلَّ ضَلَالًا مُبِينًا} [الأحزاب:36]*
«አላህንና መልክተኛውንም ያመጸ ሰው ግልጽ የሆነን መሳሳት በእርግጥ ተሳሳተ።» [አል-አሕዛብ: 36]
#ሶስተኛ፡ በነቢዩ ﷺ ፍርድ መዳኘት ግዴታ መሆኑን የሚያሳዩ የቁዱስ ቁርኣን አንቀጾች :-
*{فَلَا وَرَبِّكَ لَا يُؤْمِنُونَ حَتَّىٰ يُحَكِّمُوكَ فِيمَا شَجَرَ بَيْنَهُمْ ثُمَّ لَا يَجِدُوا فِي أَنْفُسِهِمْ حَرَجًا مِمَّا قَضَيْتَ وَيُسَلِّمُوا تَسْلِيمًا} [النساء:65]*
«በጌታህም እምላለሁ በመካከላቸው በተከራከሩበት ነገር ሁሉ እስከሚያስፈርዱህ፣ ከዚያም ከፈረድከው ነገር በነፍሶቻቸው ውስጥ ጭንቀትን እስከማያገኙና ሙሉ መታዘዝንም እስከሚታዘዙ ድረስ አያምኑም።» [አን-ኒሳእ: 65]
*(አላህ በዚህ አንቀጽ በቅዱስነቱ በመማል፤ አማኞች እምነታቸው ሙሉ የሚሆነው በነቢዩ ﷺ ሙሉ ፍርድና ውሳኔ ሲረኩና ሲቀበሉ ብቻ መሆኑን ገልጿል)*።
#አራተኛ፡ የነብዩ ﷺ ሱና ከአላህ የተወረደ ወህይ (ራዕይ) መሆኑን የሚያስረዱ የቁዱስ ቁርኣን አንቀጾች :-
*{وَمَا يَنْطِقُ عَنِ الْهَوَىٰ (3) إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ} [النجم:3-4]*
«(ነብዩ ሙሐመድ)ከስሜቱም አይናገርም። እርሱ (ንግግሩ) የሚወረድ ራዕይ እንጂ ሌላ አይደለም።» [አን-ናጅም: 3-4]
*{...وَأَنْزَلْنَا إِلَيْكَ الذِّكْرَ لِتُبَيِّنَ لِلنَّاسِ مَا نُزِّلَ إِلَيْهِمْ...} [النحل:44]*
«ለሰዎችም ወደ እነሱ የተወረደውን ልታብራራላቸው ዘንድ ማስታወሻውን (ቁርዓንን) ወደ አንተ አወረድን።» [አን-ናሕል: 44]
*(እዚህ ላይ «ማስታወሻ» የተባለው ቁርዓን ሲሆን፣ የነቢዩ ማብራሪያ ደግሞ «ሱና» ነው)*።
#አምስተኛ፡ ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ ያመጡትን ሁሉ የመያዝ የመቀበል ግዴታን የሚያሳዩ የቁዱስ ቁርኣን አንቀጾች :-
*{...وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانْتَهُوا..}[الحشر:7]*
«መልክተኛውም የሰጣችሁን (ማንኛውንም ነገር) ያዙት፣ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ።» [አል-ሐሽር: 7]
*(ይህ አንቀጽ ከነቢዩ ﷺ የፈለቀን እያንዳንዱን ነገር ንግግር፣ ተግባር ወይም አይተው ወይም ሰምተው በዝምታ ያረጋገጡትን (ተቅሪር) ሁሉ በጠቅላላ የሚያካትት ሰፊ ሕግ ነው)*።
#ስድስተኛ፡ በነብያችን ﷺ ሱና የመዳኘትና የእርሳቸውን ፍርድ የአላህ ፍርድ ብሎ በመጥራት የጃሂልያ (የመሃይምነት ኋለ ቀር) ሥርዓትን መተው እንዳለብን የሚያስገድዱ የቁዱስ ቁርኣን አንቀጾች :-
*{أَفَحُكْمَ الْجَاهِلِيَّةِ يَبْغُونَ ۚ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّهِ حُكْمًا لِقَوْمٍ يُوقِنُونَ} [المائدة:50]*
«የመሃይምነትን ፍርድ ይፈልጋሉን? ለሚያምኑም ሕዝቦች ከአላህ ይበልጥ ፍርዱ ያማረ ማን ነው?» [አል-ማኢዳህ: 50]
*{...فَإِنْ تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ...} [النساء:59]*
«በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ ወደ አላህና ወደ መልክተኛው ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መልሱት።» [አን-ኒሳእ: 59]
*(ወደ አላህ መመለስ ማለት፡ ወደ መጽሐፉ (ቁርዓን) መመለስ ሲሆን፣ ወደ መልክተኛው መመለስ ማለት ደግሞ፡ ከህልፈታቸው በኋላ ወደ ሱናቸው መመለስ ማለት ነው)*።
*{قُلْ إِنْ كُنْتُمْ تُحِبُّونَ اللَّهَ فَاتَّبِعُونِي يُحْبِبْكُمُ اللَّه} [آل عمران:31]*
«በላቸው፦ አላህን የምትወዱ እንደ ሆናችሁ ተከተሉኝ፤ አላህ ይወዳችኋልና።» [አል-ዒምራን: 31]
አላህ የእርሱን ውዴታ ማግኘት በነቢዩ ﷺ መከተል ላይ አጽንቶታል፤ በቁርዓን ብቻ መከተል ላይ አላደረገውም። ስለዚህ ሱናን የካደ ሰው የአላህን ውዴታ ለማግኘት የተቀመጠውን ቅድመ-ሁኔታ ጥሷል።
#ማጠቃለያ፦
ይህን ሁሉ ግልጽና የማያሻማ ማብራሪያ ካየ በኋላ «ቁርዓን ብቻ ከሱና ያብቃቃኛል» የሚል ሰው ካለ፣ እስኪ ይመልስልን፡- እንዴት ነው የምትሰግደው? እንዴትስ ነው የምትጾመው? እንዴትስ ነው ሐጅ ምታደርገው ? የሱብሂና የመግሪብ ሰላቶች ስንት ረከዓ ናቸው? ለመሆኑ በቁርዓን ውስጥ የነዚህ ዝርዝር ማብራሪያ መጥቷልን?!
_______
4 433
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ
ዛሬ የደርስ ፕሮግራማችን ይጀመራል ኢንሻ አላህ ።
የዛሬ ደርሳችን የቁርኣን ተፍሲር ይሆናል
4 433
ضوابط التكفير وأهمية إعذار المسلم
አንድን ሙስሊም ከኢስላም ውጭ ነው ለማለት የሚቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች እና ዑዝርን የማስወገድ አስፈላጊነት
*إِنَّ مَسْأَلَةَ التَّكْفِيرِ الْحُكْمَ عَلَى الْمُسْلِمِ بِالْخُرُوجِ مِنَ الْإِسْلَامِ مِنَ الْمَسَائِلِ الْخَطِيرَةِ الَّتِي ضَلَّتْ فِيهَا أَفْهَامٌ وَزَلَّتْ فِيهَا أَقْدَامٌ وَقَدْ وَضَعَ عُلَمَاءُ أَهْلِ السُّنَّةِ وَالْجَمَاعَةِ قَوَاعِدَ صَارِمَةً لِحِمَايَةِ عِرْضِ الْمُسْلِمِ وَدِينِهِ فَلَا يَجُوزُ إِطْلَاقُ حُكْمِ الْكُفْرِ عَلَى مَنْ ثَبَتَ إِسْلَامُهُ بِالْيَقِينِ إِلَّا بَعْدَ تَمْحِيصٍ دَقِيقٍ وَتَوَفُّرِ الشُّرُوطِ وَانْتِفَاءِ الْمَوَانِعِ وَهُوَ مَا يُعْرَفُ بِـ إِزَالَةِ الْعُذْرِ*
አንድን ሙስሊም ከእስልምና ወጥቷል ብሎ መፍረድ ተክፊር እጅግ አደገኛና በርካታ ግንዛቤዎች የተሳሳቱበት እግሮችም የተንሸራተቱበት ከባድ ርዕስ ነው ።
የነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መንገድ ተከታዮች (አህሉሱና ወልጀማዓ) የሙስሊሙን ክብርና እምነት ለመጠበቅ ጽኑ የሆኑ መርሆዎችን አስቀምጠዋል ። በእርግጠኝነት ሙስሊምነቱ የታወቀን ሰው ፍጹም ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ሳይጣራ ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሟሉና እንቅፋቶች ሳይወገዱ ወይም ዑዝሩን ሳያስወግዱ ከእስልምና ማውጣት ጨርሶ አይፈቀድም ።
ለዚህ መርህ ከቁርኣንና ሀዲስ ማስረጃዎች :-
_ قال الله تعالى :- (وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا)
አላሁ ተዓላ እንዲህ ይላል :- (መልዕክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አልነበርንም) [ሱረቱ አል ኢስራእ 15]
_ قال الله تعالى :- ((وَمَن يُشَاقِقِ الرَّسُولَ مِن بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ الْهُدَىٰ وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ الْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصْلِهِ جَهَنَّمَ وَسَاءَتْ مَصِيرًا))
((ቅኑም መንገድ ለእርሱ ከተገለጸለት በኋላ መልክተኛውን የሚከраከርና ከምእመናንም መንገድ ሌላ የሚከተል ሰው ጀሀነም ውስጥ እናገባዋለን መመለሻዋም ምንኛ ከፋች ሱረቱ)) [አን ኒሳእ 115]
የነቢዩ ሐዲሶች :-
ማክፈርን በጥብቅ ስለ መከልከል
(( عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ ﷺ قَالَ إِذَا قَالَ الرَّجُلُ لِأَخِيهِ يَا كَافِرُ فَقَدْ بَاءَ بِهَا أَحَدُهُمَا فَإِنْ كَانَ كَمَا قَالَ وَإِلَّا رَجَعَتْ عَلَيْهِ )) رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ وَمُسْلِمٌ
( ከአብደላህ ኢብኑ ዑመር ረዐ እንደተወራው የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል አንድ ሰው ወንድሙን አንተ ካፊር ካለው ንግግሯ ከሁለቱ ወደ አንዱ መመለሷ አይቀሬ ነው የተባለው ሰው እንደተባለው ካልሆነ ንግግሯ ወደ ተናጋሪው ትመለሳለች) ቡኻሪና ሙስሊም
قاعدة دفع الحدود بالشبهات ቅጣቶችን በጥርጣሬ ማስቀረት
(( رُوِيَ عَنِ النَّبِيِّ ﷺ أَنَّهُ قَالَ ادْرَؤُوا الْحُدُودَ عَنِ الْمُسْلِمِينَ مَا اسْتَطَعْتُمْ فَإِنْ كَانَ لَهُ مَخْرَجٌ فَخَلُّوا سَبِيلَهُ )) رَوَاهُ التِّرْمِذِيُّ
(( ከነቢዩ ﷺ እንደተረገጠው እንዲህ ብለዋል በቻላችሁት መጠን ከሙስሊሞች ላይ ቅጣቶችን ገፍትሩ አስወግዱ ለእርሱ ለተከሳሹ መውጫ መንገድ ካለው መንገዱን ልቀቁለት ይቅር በሉት)) ቲርሚዚ.
القواعد الفقهية المشهورة
ታዋቂ የፊቅህ መርሆዎች
إِقَامَةُ الْحُجَّةِ وَإِزَالَةُ الشُّبْهَةِ
ማስረጃን ማቆም ማድረስ እና ማደናገሪያን ጥርጣሬን ማስወገድ
الْيَقِينُ لَا يَزُولُ بِالشَّكِّ
እርግጠኝነት በጥርጣሬ አይሻርም
الْخَطَأُ فِي الْعَفْوِ خَيْرٌ مِنَ الْخَطَأِ فِي الْعُقُوبَةِ
በይቅርታ ላይ መሳሳት በቅጣት ላይ ከመሳሳት የተሻለ ነው ።
ምክር በፍርድ ላይ አለመቸኮል
يَا أَخِي الْكَرِيمَ إِنَّ الْحُكْمَ عَلَى مَصَائِرِ الْعِبَادِ لَيْسَ بِالْأَمْرِ الْهَيِّنِ وَالْوَلُوغَ فِي أَعْرَاضِ الْمُسْلِمِينَ بِالتَّكْفِيرِ هُوَ مَزْلَقٌ خَطِيرٌ فَالْوَاجِبُ عَلَى الْمُسْلِمِ أَنْ يَشْتَغِلَ بِإِصْلَاحِ نَفْسِهِ وَأَنْ يَكُونَ دَاعِيًا إِلَى اللَّهِ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ لَا قَاضِيًا يَطْرُدُ النَّاسَ مِنْ رَحْمَةِ اللَّهِ فَالْقُلُوبُ بَيْنَ يَدَيِ الرَّحْمَنِ وَالْأَصْلُ فِي الْمُسْلِمِ السَّلَامَةُ فَلَا تَتَسَرَّعْ بِالْحُكْمِ عَلَى النَّاسِ بِمُجَرَّدِ زَلَّةِ لِسَانٍ أَوْ جَهْلٍ حَتَّى تَعْذِرَهُمْ وَتُبَيِّنَ لَهُمُ الْحَقَّ بِرِفْقٍ وَلِينٍ
ውድ ወንድሜ ሆይ በሰዎች ፍጻሜና እጣ ፈንታ ላይ መፍረድ ቀላል ነገር አይደለም የሙስሊሞችን ስም በማክፈር ማጉደፍ ደግሞ እጅግ አደገኛ ማጥ ነው የአንድ ሙስሊም ግዴታ ራሱን በማስተካከል ላይ መጠመድ ሰዎችንም ወደ አላህ መንገድ በጥበብና በጥሩ ምክር መጣራት እንጂ ሰዎችን ከአላህ እዝነት የሚያወጣ ፈራጅ መሆን አይደለም ልቦች በአላህ እጅ ናቸው የሙስሊም መነሻው ደግሞ ሰላምነቱ ነው ስለዚህ ሰዎች በመሳሳት ወይም ባለማወቅ ስለተናገሩት ነገር ብቻ ለመፍረድ አትቸኩል ይልቁንም ዑዝራቸውን እስክታስወግድና እውነቱን በርህራሄና በለስላሳ አንደበት እስክታብራራላቸው ድረስ ታገስ ።
_________
اللَّهُمَّ أَرِنَا الْحَقَّ حَقًّا وَارْزُقْنَا اتِّبَاعَهُ وَأَرِنَا الْبَاطِلَ بَاطِلًا وَارْزُقْنَا اجْتِنَابَهُ
አላህ ሆይ እውነትን እውነት አድርገህ አሳየን መከተሉንም ለግሰን ሀሰትንም ሀሰት አድርገህ አሳየን መራቁንም ስጠን ።
اللَّهُمَّ اجْعَلْ أَلْسِنَتَنَا رَطْبَةً بِذِكْرِكَ وَاحْفَظْ جَوَارِحَنَا عَنْ أَعْرَاضِ عِبَادِكَ الْمُؤْمِنِينَ آمِينَ
አላህ ሆይ አንደበታችንን በአንተ ውዳሴ የረጠበ አድርገው ህዋሳቶቻችንንም ከምእመናን ባሮችህ ክብር ከማንኳሰስ ጠብቅልን አሚን ።
4 433
⏳ በትምህርት ወይም በሥራ ምክንያት ለሸሪዓ እውቀት የሚሆን ጊዜ አላገኙም?
✅ አፍሪካ አካዳሚ ችግሩን ፈቶልዎታል!
🔖 ሁሉንም የሸሪዓ የትምህርት አይነቶች
✅ በነፃ እና በርቀት ካሉበት መማር ይችላሉ
✔️ ማሳሰቢያ:- መማር የሚፈልጉበትን ቋንቋ ብቻ መርጠው ይቀላቀሉ፣ሁለቱም ግሩፕ ላይ መግባት የለባችሁም
🔗 በአማርኛ ቋንቋ ለመማር በዚህ ሊንክ ይግቡ:
✉️ [https://t.me/africaacademy_4th]
🔗 በኦሮሚኛ ቋንቋ ለመማር በዚህ ሊንክ ይቀላቀሉ:
✉️ [https://t.me/AkaadaamiiAfrikaa]
4 433
*የዒድ ማግስት ልዩ በረካ*
ይህን ቀን አስመልክቶ ውዱ ነብያችን ﷺ የሚከተለውን መልእክት አስተላልፈዋል :- (( «አላህ ዘንድ ታላቅ ቀናት ማለት የእርድ ቀን (የዒድ ቀን) ከዚያም የመረጋጊያ ቀን (የውመ አል-ቀሪ) ነው ።»))
ማብራሪያ :- የመረጋጊያቅ ቀን ማለት (የውመ አል-ቀሪ)፦ የእርድ ቀንን ተከትሎ የሚመጣው ቀን ሲሆን፤ ሐጃጆች ሚና ውስጥ የሚቀመጡበት (የሚረጋጉበት) ቀን ስለሆነ ነው።
«ሰሒህ አል-ጃሚዕ» (1064) | መጃሊሱ ዝክር (የውይይት መድረኮች)
قال رسول الله ﷺ: «أعظم الأيام عند الله يوم النحر ثم يوم القَرِّ» «صحيح الجامع»
የዛሬዋን ቀን ልዩ ትሩፋት በረካ እንዳያመልጠን በተለያዩ ዒባዳዎች እንበርታ !!!
*ያ አላህ በረካ ያደረክባቸው የመልካም ግዜያትን በረካ ወፍቀን*
4 433
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ
በኡስታዝ አብዱረህማን ሁሴን በሳምት ለ3 ቀን የሚሰጠው ደርስ አብዛኛው ሰው በዙልሂጃ አስርቱ ቀናት ፆም ኢባዳ ላይ ስለሆነ ደርሱ በእነዚህ ቀናት እንደ ማይኖር እና በአላህ ፈቃድ ከአረፋ በኋላ የሚቀጥል መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
4 433
ማጠቃለያ:-
ከእነዚህ የአላህ ቁርኣን፣ የመልእክተኛው (ﷺ) ሱና፣ እና የኡማው ሰለፎችና ኢማሞች ቁርጥ ያሉ ማስረጃዎች በኋላ፣ ምንም ዓይነት ጥርጣሬ በማያስተናግድ መልኩ የሚከተሉት ነጥቦች ግልጽ ሆነዋል፦
*አንደኛ፦*
ለእስልምና ብቸኛው ምንጭ፣ እና በሕግ አውጪነት፣ በሐላልና ሐራም፣ በዐቂዳ (እምነት)፣ በኢባዳ (አምልኮ) እና በሙዓመላት (መህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት) የመጀመሪያውና የመጨረሻው ማስረጃ የአላህ ቁርኣንና የመልእክተኛው (ﷺ) ሱና ብቻ ነው።
*ሁለተኛ፦*
የዑለማኦች፣ የመሻይኾች፣ የሙፍቲዎችና የወልዮች ንግግር በራሱ የቆመ ማስረጃ አይደለም፣ በሌሎችም ላይም ሁጃ ማስረጃ አይሆንም፣ የእስልምናም ምንጭ አይደለም። ተቀባይነት የሚኖረው ከቁርኣንና ሱና ማስረጃ ሲገጥም ብቻ ነው፤ ማስረጃን ከተቃረነ ግን ውድቅ ይደረጋል።
*ሶስተኛ፦*
ከአላህ መልእክተኛ (ﷺ) በስተቀር የማንኛውም ሰው ንግግር ይወሰዳልም ይጣላልም፤ ምክንያቱም እርሳቸው ከአላህ በሆነ ወሕይ ከስህተት የተጠበቁ (መዕሱም) ናቸውና፤ ከእርሳቸው ውጭ ያሉ የሰው ልጆች ንግግር ግን ይሳሳታሉ ።
*አራተኛ፦*
ማንኛውም ፍጡር ሰው —ዕውቀቱና ደረጃው ምንም ያህል ቢደርስ—አላህ ያልፈቀደውን ሃይማኖት ሊደነግግ፣ አላህ የፈቀደውን ሊከለክል፣ አላህ የከለከለውን ሊፈቅድ፣ ወይም የራሱን አስተያየት ከወሕይ ቁርኣን በላይ ሊያስቀድም መብት የለውም።
*አምስተኛ፦*
ዓሊምም ሆነ ጃሂል፣ ሙፍቲም ሆነ ፈትዋ ጠያቂው ላይ ግዴታው በሁሉም ጉዳዮች ላይ ወደ ቁርዓንና ሱና መመለስ ነው ።
የሰዎችን ንግግር ከመከተል መራቅ፣ እና ፍርዱ ለአላህ ብቻ መሆኑን ማረጋገጥ ነው።
አላህ በቁርዓንና በሱና ላይ እንዲያጸናን፣ የስሜትና የአስተያየት ተከታዮች ሳይሆን የሸሪዓ ተከታዮች እንዲያደርገን፣ እንለምነዋለን ።
የአላህ ሰላትና ሰላም በነብዩ ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ የበዛ ሰላምታ ይውረድ። ምስጋና ሁሉ ለአለማቱ ጌታ ለአላህ ይገባው።
ተፈፀመ
4 433
8. ﴿وَمَا اخْتَلَفْتُمْ فِيهِ مِنْ شَيْءٍ فَحُكْمُهُ إِلَى اللَّهِ﴾ [الشورى: 10]
«በማንኛውም ነገር ብትለያዩ ፍርዱ ወደ አላህ ነው።» [አሽ-ሹራ: 10]
አላህ በዚህ አንቀጽ ልዩነቶችን ሁሉ ወደ አላህ ቁርኣንና ወደ መልእክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሱና መለሰው።
9. ﴿ثُمَّ جَعَلْنَاكَ عَلَىٰ شَرِيعَةٍ مِنَ الْأَمْرِ فَاتَّبِعْهَا وَلَا تَتَّبِعْ أَهْوَاءَ الَّذِينَ لَا يَعْلَمُونَ﴾ [الجاثية: 18]
«ከዚያም ከነገሩ (ከሃይማኖቱ) በግልጽ ሕግ ላይ አደረግንህ፤ ተከተላትም፤ የእነዚያን የማያውቁትን ሰዎች ስሜቶች አትከተል።» [አል-ጃሢያህ: 18]
አላህ ነቢዩን ግልጽ በሆነ ሸሪዓ ላይ አደረጋቸው፣ እንዲከተሉትና የተቃዋሚዎችን ስሜት እንዲተውም አዘዛቸው።
10. ﴿أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ﴾ [الشورى: 21]
«ወይንስ ለእነርሱ አላህ ያልፈቀደውን ከሃይማኖት ለእነርሱ የደነገጉ ተጋሪዎች አሉዋቸውን?» [አሽ-ሹራ: 21]
አላህ ያልፈቀደለትን ሃይማኖት የሚደነግግለትን ከአላህ ውጭ ረዳት የያዘን ሰው አላህ አውግዟል፤ ይህም የዑለማኦችንና የመሻይኾችን ንግግር ከወሕይ ማስቀደምን ያካትታል።
ሁለተኛ፡ ከነቢያዊ ሱና የተወሰዱ ማስረጃዎች :-
የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
1. «لَتَتَّبِعُنَّ سَنَنَ مَنْ كَانَ قَبْلَكُمْ شِبْرًا بِشِبْرٍ وَذِرَاعًا بِذِرَاعٍ، حَتَّى لَوْ دَخَلُوا جُحْرَ ضَبٍّ لَاتَّبَعْتُمُوهُ» (متفق عليه)
«ከእናንተ በፊት የነበሩትን ሰዎች ፈለግ ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ፤ የእንሽላሊት (አንጃሮ) ጉድጓድ ውስጥ ቢገቡ እንኳ ትከተሏቸዋላችሁ።» (ቡኻሪና ሙስሊም)
ነብያችን (ﷺ) ሰዎች ደረጃቸው ምንም ያህል የላቀ ቢሆንም በባጢል (በጥፋት) ላይ እነሱን መከተልን ከልክሏል።
2. «كُلُّ بَنِي آدَمَ خَطَّاءٌ، وَخَيْرُ الْخَطَّائِينَ التَّوَّابُونَ» (رواه الترمذي وصححه الألباني)
«የአዳም ልጆች ሁሉ ተሳሳቾች ናቸው፤ ከተሳሳቾች ሁሉ በላጮቹ ደግሞ ተውበት አድራጊዎች (ተመላሾች) ናቸው።» (ቲርሚዚ የዘገቡትና አልባኒ ሶሒሕ ያደረጉት)
ዑለማኦችም ሆኑ ሌሎች ይሳሳታሉ፤ ከእነሱ መካከል የአንዱ ንግግር ማስረጃን (ቁርኣንና ሱናን) ከተቃረነ አስገዳጅ ሁጃ አይሆንም።
3. «إِذَا حَكَمَ الْحَاكِمُ فَاجْتَهَدَ ثُمَّ أَصَابَ فَلَهُ أَجْرَانِ، وَإِذَا حَكَمَ فَاجْتَهَدَ ثُمَّ أَخْطَأَ فَلَهُ أَجْرٌ» (متفق عليه)
«ፈራጅ (ሙጅተሂድ) ከጥረት በኋላ ቢፈርድና (ሐቅን) ቢያገኝ ለእርሱ ሁለት ምንዳዎች አሉት፤ ቢሳሳት ግን ለእርሱ አንድ ምንዳ አለው።» (ቡኻሪና ሙስሊም)
ይህ ሐዲስ ለስህተት ብይን ሰጥቷል፣ የኣሊም ሙጅተሂድ ንግግር ስህተት ተብሎ እንዲገለጽ ፈቅዷል፣ በመሆኑም የኣሊምን ንግግር አስገዳጅ ማስረጃ አላደረገውም።
4. «إني أخاف على أمتي الأئمة المضلين» (رواه أحمد والترمذي وصححه الألباني)
«እኔ በኡመቴ ላይ የምፈራው አሳሳች መሪዎችን (ዑለማኦችን) ነው።» (አሕመድና ቲርሚዚ የዘገቡትና አልባኒ ሶሒሕ ያደረጉት)
ይህ ሐዲስ ወደ ጥፋት ከሚጣሩ ወይም በሃይማኖት ውስጥ አላህ ያልፈቀደውን ከሚደነግጉ ዑለማኦችና መሪዎችን ከመከተል እንድንቆጠብ የተላለፈ ማስጠንቀቂያ።
ሶስተኛ፡ የሶሐቦች፣ የነብዩ(ﷺ) ተከታዮች (ታቢዒዮች) እና የአራቱ ኢማሞች ንግግሮች :-
አንደኛ፡ ሶሐቦች (ረዲየላሁ ዐንሁም)፦**
* የዓብዱላህ ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ሐዲስ፡ «يوشك أن تنزل عليكم حجارة من السماء، أقول: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم، وتقولون: قال أبو بكر وعمر!» (رواه أحمد والحاكم وصححه)
«ከሰማይ ድንጋይ ሊዘንብባችሁ ተቃርቧል! እኔ የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል እላችኋለሁ፤ እናንተ ግን አቡበክርና ዑመር እንዲህ ብለዋል ትሉኛላችሁ!» (አሕመድና ሐኪም የዘገቡትና ሶሒሕ የተደረገ)
እኚህ ታላቅ ሰሃብይ የማንኛውም ሰው ንግግር የነብያችንን (ﷺ)
ንግግር መቃረንን አጥብቀው አውግዘዋል— ያ ሰው አቡ በክርና ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ቢሆኑ እንኳ።
* ዑመር ቢን አል-ኸጣብ (ረዲየላሁ ዐንሁ ) እንዲህ ብለዋል፦
«لا تقلدوا الرجال، وما شهد لي به أحد فاعملوا به» (رواه ابن عبد البر)
«ሰዎችን በዕውር ድንብዝ አትከተሉ ፤ ማንም ሰው ከመረጃ ጋር ያመጣውን ነገር ስሩበት።» (ኢብኑ ዐብዲልበር የዘገቡት)
ሁለተኛ፡ ታቢዒዮች (ረሒመሁሙ አላህ)፦
* ሐሰን አል-በስሪ (ረሂመሁ አላሁ ) እንዲህ ብለዋል፦ «إنما الدين دين الله، وليس دين الرجال» (رواه الدارمي)
«ሃይማኖት የአላህ ሃይማኖት ብቻ ነው፤ የሰዎች ሃይማኖት አይደለም።» (ዳሪሚ የዘገቡት)
ሶስተኛ፡ አራቱ የመዝሐብ ኢማሞች፦
* ኢማም አቡ ሐኒፋ (ረሂመሁ አላሁ) ፦
«هذا رأيي، فمن جاء بأحسن منه فهو أولى به» (الفقيه والمتفقه للخطيب البغدادي)
«ይህ የእኔ አስተያየት ነው፤ ከእኔ የተሻለ (ማስረጃ) ይዞ የመጣ ሰው እርሱ ይበልጥ ተገቢ ነው።» (አል-ፈቂህ ወል-ሙተፈቂህ)
* ኢማም ማሊክ ቢን አነስ (ረሂመሁ አላሁ ) ፦
«كل يؤخذ من قوله ويترك إلا صاحب هذا القبر» (مصنف ابن أبي شيبة)
«ከዚህ ቀብር ባለቤት በስተቀር—ወደ ነቢዩ (ﷺ) ቀብር እየጠቆሙ—የማንኛውም ሰው ንግግር ይወሰዳልም ይጣላልም።» (ሙሶነፍ ኢብኑ አቢ ሸይባህ)
* ኢማም አሽ-ሻፊዒ (ረሂመሁ አላሁ )፦
«كل قول مني، فعن كتاب الله وسنة رسوله، فإذا خالف قولي كتاب الله وسنة رسوله فاضربوا بقولي عرض الحائط» (الفقيه والمتفقه) وقال أيضاً: «إذا صح الحديث فهو مذهبي»
«ከእኔ የተነገረ ማንኛውም ንግግር ከአላህ መጽሐፍና ከመልእክተኛው ሱና የመነጨ ነው፤ ንግግሬ የአላህን መጽሐፍና የመልእክተኛውን ሱና ከተቃረነ ንግግሬን ግድግዳው ላይ አጋጩት (ጣሉት)።» እንዲሁም «ሐዲሱ ሶሒሕ (ትክክለኛ) ከሆነ እርሱ የኔ መዝሃብ ነው።» ብለዋል።
* ኢማም አሕመድ ቢን ሐንበል (ረሂመሁ አላሁ )፦
«لا تقلدني ولا مالكاً ولا الشافعي، وخذ من حيث أخذوا» (الفقيه والمتفقه)
«እኔንም አትከተሉኝ (አትቅለዱኝ)፣ ማሊክንም ሆነ ሻፊዒንም አትከተሉ፤ እነሱ ከወሰዱበት (ከቁርዓንና ሱና) ውሰዱ።» (አል-ፈቂህ ወል-ሙተፈቂህ)
4 433
#የዑለማዎች_ንግግር_ማስረጃ_ይሆናልን ? :-
ኢስላም ምንጩ ቁርዓንና ሱና ብቻ ነው፣ የሰዎች ንግግር ራሱን የቻለ ማስረጃ አይደለም ።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
መግቢያ
ምስጋና ለአላህ ይገባው፤ መመሪያና ማብራሪያ አድርጎ መጽሐፍን (ቁርዓንን) ላወረደው፣ መልእክተኛውንም በቅን መመሪያና በእውነተኛው ሃይማኖት ለላከው፣ ሁለቱንም መከተል የቅንነት መንገድ፣ እነሱን መጣስ ደግሞ የጥፋትና የጥመት መንገድ ላደረገው አላህ ምስጋና የተገባው ይሁን። ከአንድ አላህ በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እርሱም ብቻኛና አጋር የሌለው መሆኑን እመሰክራለሁ። ነብዩ ሙሐመድም (ﷺ) ባሪያውና መልእክተኛው መሆናቸውን እመሰክራለሁ። የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸውና እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ በመልካም በተከተሏቸው ላይ ሁሉ ይሁን።
ከዚህ በመቀጠል፦
የእስልምና ሃይማኖት የተገነባው በአንድ ታላቅ መሠረትና መርህ ላይ ነው፤ የአንድ ሙስሊም ባሪያ እምነት በእርሱ እንጂ አይሞላም፣ ሃይማኖቱም እርሱን በማረጋገጥ እንጂ አይቀናም። እርሱም፦ ለየትኛውም ሕግጋትና መረጃ ብቸኛው ምንጭ የአላህ ቁርኣንና የመልእክተኛው ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) ሱና ብቻ ነው ።
የማንኛውም ሰው ንግግር — ማዕረጉ ምንም ያህል ቢገዝፍ፣ እውቀቱ ቢሰፋ፣ ደረጃው ቢረቅ፣ እናም ሸይኽ፣ ኡስታዝ፣ ዓሊም (አዋቂ)፣ ሙፍቲ፣ ወይም ወልይ ተብሎ ቢጠራም እንኳን — የሱ ንግግር በእስልምና ውስጥ (ራሱን የቻለ) ማስረጃ ሆኖ መቅረብ አይችልም ፣ የሱ ንግግር በማይቀበል ሰው ላይም አስገዳጅ ሁጃ አይደለም፣ የሃይማኖት ምንጭም ሊሆን አይችልም።
ዑለማኦች (ሊቃውንት)፣ መሻይኾችና አጠቃላይ ሙስሊሞች ሁሉ—የነሱ ግዴታ ቁርዓንና ሱናን መከተል ብቻ ነው፤ ምክንያቱም ቁርኣንና ለዲስ ከስህተት የፀዱ ናቸው ። የሰው ልጆች ግን የሚሳሳቱና የሚረሱ ናቸው ። ስለዚህ በሀይማኖት ጉዳይ የሰው ልጅ ንግግር አስገዳጅ ማስረጃ ሊሆን አይችልም። አላህ (ሱብሐነሁ ወተዓላ) የሰዎችን ስሜትና ንግግር መከተልን—ከወሕይ (ከመለኮታዊ ራዕይ) ጋር ከተጋጨ—ከልክሏል። ማስረጃ በሌለው ነገር ሰዎችን መከተል—ታላላቅ ዑለማኦች ቢሆኑም እንኳ—ወደ ጥፋት እንደሚያመራ በግልጽ አስታውቋል። በክርክርና ባለመስማማት ጊዜም መመለሻውን ወደ ቁርዓንና ሱና ብቻ አድርጎታል።
ይህች አጭር የፁሁፍ መልእክት ናት፤ ለአስታዋዮች ማስታወሻ ትሆን ዘንድ፣ እንዲሁም ፍርዱ የአላህ ብቻ መሆኑን፣ ከዑለማኦችና መሻይኾች የሚጠበቀው መከተልናመታዘዝ እንጂ የነሱ ንግግር ራሱን የቻለ ማስረጃ አለመሆኑን፣ መታዘዝም በመልካም ነገር ላይ እንጂ በአመጽ ላይ አለመሆኑን፣ እናም የነሱ ንግግር (ከቀጥተኛው መረጃ) ጋር ሲስማማ እንጂ ሲቃረን መከተል እንደማይሆን ቁርጥ ያለ ማስረጃ ከቁርዓን፣ ከሱና እና ከሰለፎች (ከቀደምት አባቶች) ንግግሮች የተውጣጡ ማስረጃዎችን ሰብስቤባታለሁ። መልካም ንባብ :-
አንደኛ፡ ከቅዱስ ቁርዓን የተወሰዱ ማስረጃዎች
አላሁ ተዓላ እንዲህ ይላል፦
1. ﴿وَأَنزَلْنَا إِلَيْكَ الْكِتَابَ بِالْحَقِّ مُصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ الْكِتَابِ وَمَهَيْمِنًا عَلَيْهِ فَاحْكُم بَيْنَهُم بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ وَلَا تَتَّبِعْ أَهْوَاءَهُمْ عَمَّا جَاءَكَ مِنَ الْحَقِّ﴾ [المائدة: 48]
«ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲሆን በዕውነት አወረድን፤ በመካከላቸውም አላህ ባወረደው ህግ ፍረድ፤ እውነቱም ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን ስሜቶቻቸውን አትከተል…» [አል-ማኢዳህ: 48]
አላህ ነቢዩን—ከኃጢአት የተጠበቁ (መዕሱም) ሆነው ሳለ—የሰዎችን ስሜት ከመከተል ከልክሏቸዋል፤ ከሳቸው ውጭ ያሉ ደግሞ ይበልጥ የተከለከሉ ናቸው።
2. ﴿وَإِن تُطِعْ أَكْثَرَ مَن فِي الْأَرْضِ يُضِلُّوكَ عَن سَبِيلِ اللَّهِ إِن يَتَّبِوعُنَ إِلَّا الظَّنَّ وَإِنْ هُمْ إِلَّا يَخْرُصُونَ﴾ [الأنعام: 116]
«በምድርም ውስጥ ያሉትን አብዛኞቹን ሰዎች ብትታዘዝ ከአላህ መንገድ ያሳስቱሃል፤ ጥርጣሬን እንጂ ሌላን አይከተሉም፤ እነሱም የሚዋሹ እንጂ አይደሉም።» [አል-አንዓም: 116]
በሀይማኖት ጉዳይ የአንድ ንግግር ተናጋሪዎቹ መብዛት ወይም የተናጋሪዎቹ ታላቅነታቸው መግዘፍ ለንግግሩ ትክክለኛነት ማስረጃ አይሆንም።
3. ﴿اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ وَلَا تَتَّبِعُوا مِن دُونِهِ أَوْلِيَاءَ﴾ [الأعراف: 3]
«ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ፤ ከእርሱም ሌላ ረዳቶችን ወሊዮችን (ወዳጆችን) አትከተሉ።» [አል-አዕራፍ: 3]
አላህ ቁርዓንና ሱናን ብቻ እንድንከተል አዟል፤ ከአላህ ውጭ ያሉ ወዳጆችን ወልዮችን መከተልን ደግሞ ከልክሏል።
4. ﴿وَلَا تَتَّبِعِ الْهَوَىٰ فَيُضِلَّكَ عَن سَبِيلِ اللَّهِ﴾ [ص: 26]
«ስሜትንም አትከተል፤ ከአላህ መንገድ ያሳስትሃልና።» [ሷድ: 26]
ስሜት ማለት የሰዎችን ንግግርና አስተያየት ከመለኮታዊ ፅሁፎች (ኑሱስ) ማስቀደምንም ያጠቃልላል።
5. ﴿فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ﴾ [النساء: 59]
«በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ከሆናችሁ ያን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት።» [አን-ኒሳእ: 59]
አላህ በልዩነት ጊዜ ለመዳኘት መመለሻውን ወደ አላህና መልእክተኛው (ቁርዓንና ሱና) አደረገው እንጂ ወደ ዑለማኦች ንግግር አላደረገውም።
6. ﴿اتَّخَذُوا أَحْبَارَهُمْ وَرُهْبَانَهُمْ أَرْبَابًا مِنْ دُونِ اللَّهِ﴾ [التوبة: 31]
«ሊቃውንቶቻቸውንና መነኮሳቶቻቸውን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርገው ያዙ…» [አት-ተውባህ: 31]
እናታችን ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ይህንን አንቀጽ ሲያብራሩ ፦ አያመልኳቸውም ነበር፣ ነገር ግን ሐራምን ሲፈቅዱላቸውና ሐላልን ሐራም ሲያደርጉላቸው ይታዘዟቸው ነበር፣ በዚህም ከአላህ ውጭ ሕግ አውጪ አደረጓቸው ብለዋል።
7. ﴿إِنِ الْحُكْمُ إِلَّا لِلَّهِ﴾ [الأنعام: 57]، وقوله: ﴿إِنِ الْحُكْمُ إِلَّا لِلَّهِ أَمَرَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ﴾ [يوسف: 40]
«ላፍርዱ የአላህ እንጂ የሌ አይደለም።» [አል-አንዓም: 57] እና «ፍርዱ የአላህ እንጂ የሌላ አይደለም፤ እርሱን እንጂ ሌላን እንዳታመልኩ አዟል።» [ዩሱፍ: 40]
ማለትም ሕግ ማውጣት፣ መፍቀድና መከልከል ለአላህ እንጂ ለማንም አይገባም። ከሰው ልጅ የሚወጣ ማንኛውም ነገር ደግሞ የአላህን ፍርድ ካልገጠመ በስተቀር አስገዳጅ ሸሪዓዊ ፍርድ ሊሆን አይችልም።
4 433
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ
በኡስታዝ ሙሀመድ ፈረጅ በሳምት ለ4 ቀን የሚሰጠው ደርስ አብዛኛው ሰው በዙልሂጃ አስርቱ ቀናት ፆም ኢባዳ ላይ ስለሆነ ደርሱ በእነዚህ ቀናት እንደ ማይኖር እና በአላህ ፈቃድ ከአረፋ በኋላ የሚቀጥል መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
4 433
وَقَالَتِ ٱلْيَهُودُ يَدُ ٱللَّهِ مَغْلُولَةٌ ۚ غُلَّتْ أَيْدِيهِمْ وَلُعِنُوا۟ بِمَا قَالُوا۟ ۘ بَلْ يَدَاهُ مَبْسُوطَتَانِ يُنفِقُ كَيْفَ يَشَآءُ ۚ وَلَيَزِيدَنَّ كَثِيرًۭا مِّنْهُم مَّآ أُنزِلَ إِلَيْكَ مِن رَّبِّكَ طُغْيَٰنًۭا وَكُفْرًۭا ۚ وَأَلْقَيْنَا بَيْنَهُمُ ٱلْعَدَٰوَةَ وَٱلْبَغْضَآءَ إِلَىٰ يَوْمِ ٱلْقِيَٰمَةِ ۚ كُلَّمَآ أَوْقَدُوا۟ نَارًۭا لِّلْحَرْبِ أَطْفَأَهَا ٱللَّهُ ۚ وَيَسْعَوْنَ فِى ٱلْأَرْضِ فَسَادًۭا ۚ وَٱللَّهُ لَا يُحِبُّ ٱلْمُفْسِدِينَ
አይሁዶችም «የአላህ እጅ የታሰረች ናት» አሉ፡፡ እጆቻቸው ይታሰሩ ባሉትም ነገር ይረገሙ፡፡ አይደለም (የአላህ) እጆቹ የተዘረጉ ናቸው፡፡ እንደሚሻ ይለግሳል፡፡ ከጌታህም ወደ አንተ የተወረደው (ቁርኣን) ከእነሱ ብዙዎቹን ትዕቢትንና ክህደትን በእርግጥ ይጨምራቸዋል፡፡ በመካከላቸውም ጠብንና ጥላቻን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ጣልን፡፡ ለጦር እሳትን ባያያዙ (ባጫሩ) ቁጥር አላህ ያጠፋታል፡፡ በምድርም ውስጥ ለማበላሸት ይሮጣሉ፡፡ አላህም አበላሺዎችን አይወድም፡፡
And the Jews say, "The hand of Allah is chained." Chained are their hands, and cursed are they for what they say. Rather, both His hands are extended; He spends however He wills.
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
