es
Feedback
Law studies ⚖️

Law studies ⚖️

Ir al canal en Telegram

Welcome to Law studies telegram channel ⚖️ This channel is dedicated to helping law students succeed. ✔️ Simple & clear law notes ✔️ Past exam questions & answers ✔️ Key articles & case summaries ✔️ Exam tips & important topics

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
347
Suscriptores
+224 horas
+37 días
+330 días
Número de Publicaciones

Carga de datos en curso...

Reacciones
Comentarios
Estrellas de Telegram
PUBLICACIONES TOP por

Carga de datos en curso...

Análisis de publicación
Mensajes
Ver dinámicas
ዕለታዊ🛎 ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች ⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖ ✍ ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች የምንላቸው በወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 84 ስር የተዘረዘሩት ናቸው፡፡ ሀ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በከሀዲነት ወይም በወስላታነት ወይም በወራዳነት ወይም መጥፎ አመልን በሚያሳይ ምቀኝነት፣ጥላቻ፣ ስግብግብነት፣ መጥፎ ነገርን ለመስራት ወይም ሰውን ለመጉዳት ፍጹም ፍቃደኛ በመሆን ወይም በተለየ ክፋት ወይም ጨካኝነት እንደሆነ ፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት ቅጣትን ለማክበድ ከመካከላቸው የአንዱ መሟላት በቂ ነው፡፡  ለ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ስልጣኑን፣ ተግባሩን  ወይም የተጣለበትን እምነት ወይም ሀላፊነት ያለአግባብ በመገልገል እንደሆነ የመንግስትን ስራ ለመስራት ወይም ለመምራት ስልጣን የተጣለበት ሰው ስራውን በታማኝነት እና በቅንነት መፈጸም አለበት፡፡ በተጨማሪም ይህንኑ ስልጣን ተገን በማድረግ ለራሱም ሆነ ለሌላው ጥቅም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው ጥቅም ወይም መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ አንድን ወንጀል ከፈጸመ ቅጣት ሊከብድበት እንደሚገባ የወንጀል ህጉ ይደነግጋል፡፡ ሐ.ወንጀለኛው በቀድሞ ጥፋተኛነቱ ወይም ወንጀልን ማድረግ ሙያ ወይም ልማድ አድርጎ መያዙ፣ ወይም የወንጀሉ አፈጻጸም ዘዴ፣ ጊዜ፣ ቦታና የአፈጻጸም አኳሀን፣ በተለይም በሌሊት ወይም በሽብር ወይም በሁከት ለአደጋ ሽፋን ወይም በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ ወንጀሉን በማድረግ የተለየ አደገኝነቱን አሳይቶ እንደሆነ :: በዚህ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ስር ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ እነኚህም፡- 1.ወንጀልን ማድረግ ሙያው ወይም ልማዱ አድርጎ መያዝ 2.የወ/ል አፈጻጸም ዘዴ፣ጊዜ፣ቦታ እና የአፈጻጸም አኳሀን 3.ወንጀልን በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ መፈጸም ናቸው፡፡ በተጨማሪም ሌሊት የሚለው ሀረግ ከስንት ሰዓት ጀምሮ እንደሆነ አሻሚ ቢሆንም በተለምዶ ፍርድ ቤቶች ከሌሊቱ 6፡00-12፡00 ድረስ ያለውን የጊዜ ገደብ በሌሊትነት ወስደው ቅጣት ያከብዱበታል፡፡ በእጅ ወይም በዱላ የውንብድና ወንጀልን የፈጸመ ሰው እና የስለት ወይም የጦር መሳርያዎችን ተጠቅሞ ይህንኑ ወንጀል የፈጸመ ሰው የወንጀል ማድረግ አደገኛነቱ እኩል ሊሆን አይችልም፡፡    መ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ወንጀል ለመፈጸም በተደረገ ስምምነት መሰረት ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን ወይም ወንጀል ለመፈጸም ከተቋቋመ ቡድን ጋር በመስማማት ወይም አባል በመሆን ይልቁንም እንደ ወንጀል ቡድን ሹም ወይም አደራጅ ወይም መሪ በመሆን እንደሆነ :: ወንጀልን ለመፈጸም ከሌላው ጋር ወይም ለዚሁ አላማ ከተደራጀ ቡድን ጋር በአባልነት በመስማማት ወንጀልን ማድረግ ቅጣትን ሊያከብድ የሚችል በቂ ምክንያት ነው፡፡   ሠ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በዕድሜው፣ በጤንነቱ፣ በኑሮው ወይም በስራው ሁኔታ ልዩ ጥበቃ በሚያሻው ሰው ላይ በተለይም ለመከላከል አቅም በሌለው፣ መንፈሰ ደካማ፣ በሽተኛ ወይም አካል ጉዳተኛ ፣ እስረኛ ወይም በቅርብ ዘመዱ ላይ ወይም የበላዩ ወይም የበታቹ በሆነ ሰው ላይ፣ በህግ በተቋቋመ ባለስልጣን ወይም የስራ ግዴታውን በማከናወን ላይ በሚገኝ በአንድ የህዝብ አገልጋይ በሆነ ሰራተኛ ላይ እንደሆነ  ቅጣቱ  ሊከብድበት  ይችላል ::
111301Loading...
ድሬዳዋ ፦ የወላጅ አባቱን ሀብት ለመውረስ በማሰብ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ በተባባሪው ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደ። ሚያዝያ 23
ድሬዳዋ ፦ የወላጅ አባቱን ሀብት ለመውረስ በማሰብ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ በተባባሪው ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደ። ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት በድሬዳዋ ከተማ ማሪያም ኮንዶሚኒየም አካባቢ 1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን አሊዬ ከአዲስ አበባ በምስጢር መጥቶ ከግብረ አበሩ 2ተኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን ጋር በመሆን የወላጅ አባቱን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋሉ። ወንጀለኞቹ ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ዱካቸውን ለማጥፋትና በከተማዋ እንዳልነበሩ ለማስመሰል ወዲያውኑ ወደ አዲስ አበባ በያዙት የግል ተሽከርካሪ ይኮበልላሉ። ነገር ግን ወንጀለኞቹ ከህግ ማምለጥ አልቻሉም። የድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወንጀለኞቹ ጥለውት የሄዱትን አነስተኛ ፍንጮች በመከተል በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል። ፖሊስ ያደራጀውን የምርመራ መዝገብ የተረከበው የፌዴራል ፍትህ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት (አቃቤ ህግ)፣ የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በመተንተን ክሱን በፍርድ ቤት ሲከታተል ቆይቷል። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ፦ 1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን የወላጅ አባቱን ህይወት በመቅጠፉ በሞት ቅጣት እንዲቀጣ 2ኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን በቅንጅት በመሳተፉ በ 20 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖባቸዋል። ይህ የሞት ፍርድ ቅጣት የሚፈጸመው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ርዕሰ ብሔር ፍርዱን ሲያፀድቁ ብቻ ነው። የመዝግቡ ግልባጭም ለርዕሰ ብሔሩ ጽ/ቤት እንዲላክ ፍርድ ቤት አዟል። ቪድዮ፦ ድሬዳዋ ፖሊስ
126201Loading...
ስለ የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ አጭር ማብራሪያ *** 1.የቁጥጥር እና የአስተዳደር ማዕቀፍ ማሻሻያ የስልጣን ሽግግር፡ በነባሩ አዋጅ የነበሩ የ"ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ" ስልጣኖች በሙሉ ወደ "ፍትሕ ሚኒስቴር" ተላልፈዋል። ይህም የሕግ ባለሙያዎችን አስተዳደር ከፍትሕ አስተዳደር ጋር በማዋሃድ የአሠራር አንድነትን ለመፍጠር ያለመ ነው። የውጭ ሀገር ጠበቆች፡ በውጭ ሀገር ፍቃድ ያላቸው ጠበቆች ኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት የሚችሉት በፍትሕ ሚኒስቴር ተመዝግበው እና ከአገር ውስጥ ጠበቃ ወይም ድርጅት ጋር በመሆን ብቻ እንዲሆን ተወስኗል። 2. የብቃት መመዘኛዎች እና የሥራ ልምድ ማሻሻያው ለጠበቃነት ፍቃድ የሚጠየቀውን የትምህርት ዝግጅት እና የሥራ ልምድ በዲግሪ ደረጃዎች (ዲፕሎማ፣ የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ) ከፋፍሎ አስቀምጧል። የሙያ መግቢያ ፈተና እንዲኖር የተደነገገ ሲሆን፣ በዳኝነት ወይም በዐቃቤ ሕግነት ረጅም ዓመታት ላገለገሉ ባለሙያዎች ያለፈተና የጥብቅና ፍቃድ የሚሰጥበት ሁኔታ በሕግ መርህ መሰረት ተቀምጧል። 3. የጥብቅና ድርጅቶች አስተዳደር የሙያ ኃላፊነት መድን (Professional Indemnity Insurance): ጠበቆች ወይም የጥብቅና ድርጅቶች በሥራ ላይ ስህተት ቢፈጽሙ ለደንበኛ የሚከፈል ካሳን ለመሸፈን የግድ መድን ሊኖራቸው እንደሚገባ ተደንግጓል። ይህ የደንበኛ መብት ጥበቃን የሚያረጋግጥ ወሳኝ የሕግ መርህ ነው። የአደረጃጀት መፍረስ፡ የድርጅት መፍረስን የሚያስከትሉ ምክንያቶች በግልጽ የተቀመጡ ሲሆን፣ የድርጅት ሥራ አስኪያጅ ይህን መረጃ ለሚኒስቴሩ የማሳወቅ ግዴታ ተጥሎበታል። 4. የዲስፕሊን ሥርዓት እና ቅጣት ሰነዱ የዲስፕሊን ጥፋቶችን ወደ "ቀላል" እና "ከባድ" በመክፈል ለቅጣቶች ግልጽነት ፈጥሯል፡ የቅጣት አወሳሰን፡ የገንዘብ መቀጮ፣ የፍቃድ ዕግድ እና የፍቃድ መሰረዝ እርምጃዎች እንደ ጥፋቱ ክብደት ይወሰናሉ። ለምሳሌ፣ የሀሰተኛ ማስረጃ ማቅረብ ወይም ሙስና እንደ ከባድ የዲስፕሊን ጥፋት ተቆጥሮ የፍቃድ መሰረዝ ቅጣትን ያስከትላል። የመሰየም አቤቱታ (Rehabilitation): በከባድ ጥፋት የተቀጣ ጠበቃ፣ ቅጣቱ ከተፈጸመ ከሁለት ዓመት በኋላ የዲስፕሊን ሪከርዱ እንዲሰረዝለት ለዲሲፕሊን ጉባኤ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው። 5. የአሠራር ግልጽነት የጠበቆች ማህበር አመራሮች ከአባላት መካከል በምርጫ እንዲሾሙ መደረጉ እና ተጠሪነታቸው ለጠቅላላ ጉባኤ መሆኑ፣ የአመራር አባላትን ተጠያቂነት የሚያረጋግጥ የዴሞክራሲያዊ አሠራር መርህ ነው። ፍትሕ ሚኒስቴር ማህበሩን የመቆጣጠር፣ ሕገ-ወጥ መመሪያዎችን የማረም እና አስፈላጊ ድጋፍ የመስጠት ስልጣን ተሰጥቶታል። በአጠቃላይ፣ ይህ ረቂቅ አዋጅ የጥብቅና ሙያን በሙያዊ ብቃት፣ በኃላፊነት መድን እና በጠንካራ የዲስፕሊን ቁጥጥር ስርዓት ለማንቃት የተዘጋጀ ሰነድ ነው። የሸሪክ ለውጥ ማሳወቂያ ማሻሻያው የጥብቅና ድርጅቶችን አሠራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የሚከተለውን ግዴታ አስቀምጧል፡ ·      ማንኛውም የጥብቅና ድርጅት አዲስ ሸሪክ ሲያስገባ፣ የነበረ ሸሪክ ሲለቅ ወይም ሸሪክ ሲሞት ለውጡን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለፍትሕ ሚኒስቴር ማሳወቅ አለበት። ·      በዚህ ድንጋጌ መሠረት የሸሪክ ለውጥን አለማሳወቅ እንደ ቀላል የዲስፕሊን ጥፋት ይቆጠራል። ·      ይህንን ጥፋት የፈጸመ የጥብቅና ድርጅት ከ15,000 እስከ 25,000 ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል። የሙያ ኃላፊነት መድን (Professional Indemnity Insurance) ደንበኞችን ከጠበቆች ወይም ከጥብቅና ድርጅቶች ሊደርስባቸው ከሚችል የሙያ ስህተት ለመከላከል የሚከተሉት ድንጋጌዎች ተጨምረዋል፡ ·      ማንኛውም ጠበቃ ወይም የጥብቅና ድርጅት፣ ሥራውን በአግባቡ ባለመወጣቱ ምክንያት በደንበኛው ላይ ለሚደርስ ጉዳት ካሳ የሚሆን የሙያ ኃላፊነት መድን መያዝ አለበት። ·      ጠበቆች የጥብቅና ፍቃድ ሲያወጡ ወይም ሲያሳድሱ ይህንን የሙያ ኃላፊነት መድን የያዙ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ·      የዚህ መድን ዋና ዓላማ የደንበኛን መብት በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ማስጠበቅ እና ለሚፈጠሩ የሙያ ስህተቶች የካሳ ክፍያ ዋስትና መፍጠር ነው። ጥያቄ- ይህ ማህበር ሲቋቋም እና አዋጁ ሲወጣ ጠበቃው ራሱን በራሱ ለማስተዳደር ሚስችል መሸጋገሪያ ነው ተብሎ ነበር ፣ ጠበቃው ከደካማ እና ተለጣፊ አስተዳደር ተላቆ ከመንገስት ሞግዚተነት ወጥቶ ራሱን በራሱ ማሰተዳደር መች ይሆን የሚጀምረው???????
123000Loading...
#out_of_topic 'Trust' እና 'Google TV' የተባሉ መተግበሪያዎች የባንክ አካውንትን ለአደጋ እያጋለጡ ነው በኢንተርኔት ማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት ወደ ስልኮች በመግባት የ
#out_of_topic 'Trust' እና 'Google TV' የተባሉ መተግበሪያዎች የባንክ አካውንትን ለአደጋ እያጋለጡ ነው በኢንተርኔት ማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት ወደ ስልኮች በመግባት የባንክ ሂሳብን የሚያጠፉ "Trust"፣ "Google TV" እና "Known" የተባሉ አደገኛ የአንድሮይድ መተግበሪያዎች በስፋት እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። እነዚህ መተግበሪያዎች በተለይ በGoogle Chrome፣ Telegram እና WhatsApp መድረኮች ላይ የሚጋሩ ሲሆን፥ ተጠቃሚዎች ሳያውቁ የገንዘብ ዝውውር በመፈጸም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ። ​ይህ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሳይበር ጥቃት በስፋት እየተስተዋለ የመጣው ተጠቃሚዎች ከተላኩላቸው አጠራጣሪ ሊንኮች ላይ መተግበሪያዎቹን ሲያወርዱ መሆኑ ታውቋል። መተግበሪያዎቹ አንዴ ስልክ ላይ ከተጫኑ በኋላ ከሞባይል ባንኪንግ ጋር የተያያዙ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመስረቅ ገንዘብ የመውሰድ አቅም እንዳላቸው ተገልጿል። ህብረተሰቡ ከዚህ መሰሉ የሳይበር ዘረፋ ራሱን ለመጠበቅ መተግበሪያዎችን ከታመኑ ምንጮች (እንደ Play Store ወይም App Store) ብቻ ማውረድ እንዳለበት ባንኩ አሳስቧል። ​ከተጠቀሱት የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የሚላኩ አጠራጣሪ ሊንኮችን አለመክፈት እና በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎች ላይ የባዮሜትሪክ (የፊት ወይም የአሻራ) እና የፒን (PIN) የደኅንነት ማረጋገጫዎችን አጣምሮ መጠቀም ለአደጋው የመጋለጥ እድልን በእጅጉ እንደሚቀንስ ተነግሯል።
115001Loading...
የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍን በተመለከተ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች 1) በስጦታ፣ በሽያጭ ወይም በሌላ መንገድ ተገልጋዮች ንብረት ለማስተላለፍ ሲመጡ ካርታው ከጀርባው የተረጋገጠ መሆን አለበት፡፡ ካርታው ዲጂታል ከሆነ የጀርባ ማህተም አያስፈልገውም፡፡ 2)በካርታው ከጀርባ ላይ ንብረቱ በውርስ የተገኘና የወራሾች ዝርዝር የተፃፈበት ከሆነ ተጨማሪ ማስረጃ ማየት ሳያስፈልግ መስተናገድ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የንብረቱ መለያ ተጠቅሶ ወራሾች መሆናቸው በደብዳቤ ከተገለጸ አገልግሎቱን መስጠት ይቻላል፡፡ 3)በውርስ ወይም በስጦታ የተገኘ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት የጋብቻ ማስረጃ አይጠየቅም፡፡ 4)ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውጭ የተመዘገቡ የሚንቀሳቀሱም ሆነ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የማስተላለፍ ወይም የማከራየት አገልግሎት ማግኘት የሚቻለው ንብረቶቹ በሚገኙበት ክልል/ከተማ አስተዳደር ነው፡፡ ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሊስተናገዱ አይችሉም፡፡ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም የሚያስተናግደው በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚመለከተው መ/ቤት የተመዘገቡ ንብረቶችን ብቻ ይሆናል፡፡ 5)ከጋብቻ በፊት በተቋሙ ቀርበው የንብረት ማግለል ውል ያደረጉ ወይም በፍ/ቤት ያጸደቁ ተጋቢዎች ንብረታቸውን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት ሲመጡ የትዳር አጋራቸው ስምምነት አያስፈልግም፡፡ ሆኖም የንብረት ማግለሉ ስምምነት አሁን ጸንቶ ካለው ጋብቻ የትዳር አጋር ጋር የተደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ 6)አካለ መጠን ላልደረሱ ልጆች ንብረት ለመግዛት የሚቻል ሲሆን ሁለቱም ወላጆች ሊገኙ ይገባል ፡፡ ካልሆነ አባት ወይም እናት ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡ ሆኖም ከእናትና አባት ውጪ የሆነ ሞግዚት አካላመጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ንብረት ለመግዛት በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡ 7.)ለአካለ መጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ ሞግዚቱ እናትና አባትም ቢሆኑም በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡ 8.)ያላገባ ማስረጃ ላይ ቀደም ሲል ጋብቻ ስለመኖሩ የሚጠቁም የጊዜ መረጃ ሲኖር ንብረቱ በጋብቻ ወቅት የተፈራ ሊሆን ስለሚችል ንብረቱ የተፈራበትን ጊዜ የሚያመለክት ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ተጨማሪ ማስረጃ ሊቀርብ ይገባል፡፡ 9.)ተነጻጻሪ ካርታ ማለት በአንድ የቦታ ስፋት ውስጥ የተለያዩ ቤቶችና ባለመብቶች ያሉበትና በተለያዩ ሰዎች ሊያዝ የሚችል ነው፡፡ ነገር ግን በዚህ ይዞታ ላይ የባለቤትነት መብት ያለው ሰው የራሱን ካርታ በመያዝ ድርሻውን ጠቅሶ መሸጥ ይችላል፡፡ 10)ካርታ ላይ የሚጠቀሰው ቀን ካርታው የተሰጠበትን ቀን እንጂ ንብረቱ የተፈራበትን ቀን በቀጥታ ላያመለክት ይችላል፡፡ ስለሆነም ንብረቱ የተፈራበትን ቀን ለማወቅ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ የንብረቱ ባለቤት ተጨማሪ ማስረጃ እንዲያቀርብ መደረግ አለበት፡፡ ለምሳሌ ከመሬት አስተዳደር ለገቢዎች እና ለካርታው ባለቤት የሚሰጡ ደብዳቤዎችን አያይዞ መስራት ይቻላል፡፡ 11) የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭም ሆነ በስጦታ ለማስተላለፍ የፍቺ ውሳኔ ይዘው የሚቀርቡ ባለጉዳዮች ንብረቱ የጋራ ወይም የግል ስለመሆኑ በፍርድ ቤት የጸደቀ የንብረት ክፍፍል ስምምነት ወይም ውሳኔ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 12)ንብረት በስጦታ ለማስተላለፍ የተሠጠ የውክልና ሥልጣን ስጦታው ለማን እንደሚሰጥ እና ንብረቱ ምን አይነት እንደሆነ በውክልናው ላይ በግልፅ መቀመጥ አለበት፡፡ ነገር ግን በውክልና ስጦታ ለመቀበል ሲሆን ስጦታ ይቀበልልኝ የሚለው አገላለጽ በቂ ነው፡፡ 13) የጋራ ንብረት በሽያጭ በሚተላለፍበት ጊዜ ገዢው ከንብረት ተጋሪው ውጪ የሆነ እንደሆነ የተጋሪው የቅድሚያ መግዛት መብት መጠበቁን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪውን ምስክር በማድረግ፣ የሚንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪው ማረጋገጫ እንዲሰጥ ማድረግ ይቻላል፡፡ 14) የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ከሆነ የታደሰ በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ወይም በኢንቨስትመንት አዋጁ መሠረት ቢያንስ አሥር ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ በሥራ ላይ ማዋሉን የሚገልጽ ማስረጃ እና የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሊቀርብ ይገባል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ሌላ የመኖሪያ ቤት በስሙ የሌለ ስለመሆኑ የሚገልጽ ከሚመለከተው የንብረት መዝጋቢ አካል ማስረጃ ማቅረቡን እንዲሁም ከተቋሙ የመረጃ ቋት ማጣራት ያስፈልጋል፡፡
119300Loading...
ፀደቀ‼️ የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️ *ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በዛሬው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው። በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦ ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል። ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል። የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል። ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
109000Loading...