Law studies ⚖️
前往频道在 Telegram
Welcome to Law studies telegram channel ⚖️ This channel is dedicated to helping law students succeed. ✔️ Simple & clear law notes ✔️ Past exam questions & answers ✔️ Key articles & case summaries ✔️ Exam tips & important topics
显示更多未指定国家未指定类别
365
订阅者
无数据24 小时
+97 天
+2030 天
帖子数量
数据加载中...
反应
评论
Telegram 星星
按以下排序的热门帖子
数据加载中...
发布分析
帖子 | 浏览量动态 | |||||
# አስደሳች የሕግ ውሳኔ! የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያስተላለፈው ታሪካዊ ውሳኔ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰጠው ውሳኔ፣ የወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ ወይም ክስ ሳይመሰረት ተጠርጣሪዎች በእስር እንዲቆዩ ትዕዛዝ መስጠት ሕገ-ወጥ መሆኑን አብራርቷል።
# ዋና ዋና ነጥቦች፦
የጉዳዩ አመጣጥ፡ አመልካች (አቶ አበበ ዳሙሳ) በተጠረጠሩበት የኃይማኖት ማጥፋት እና የቴሌኮም የገንዘብ ማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ፣ ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ15 ቀን ጊዜ በመስጠት ክስ እንዲመሰረት አዟል።
የቀረበው ክርክር፡ "የምርመራ ጊዜ ተሰጥቶ ክስ ሳይመሰረት እና ከእስር ሳይፈቱ እንደገና ለሁተኛ ጊዜ የምርመራ ጊዜ መጠየቅ ሕገ-ወጥ ነው፤ የሰዎች የነፃነት መብት ሊከበር ይገባል" የሚል የሰበር ቅሬታ ቀርቧል።
የሰበር ችሎት ትንተና፡
በሕገ መንግሥቱ አንደ 17/2 እና 19/6 መሠረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገው ሥርዓት ውጪ ነፃነቱ ሊነፈግ እንደማይችል ተደንግጓል።
የወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ እና ክስ ሳይመሰረት ተጠርጣሪውን ከእስር ሳይፈቱ በተደጋጋሚ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ማራዘም መሠረታዊ የሕግ ስህተት መሆኑ ተረጋግጧል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ፡
የታችኛው ፍርድ ቤቶች የሰጡዋቸው የምርመራ ጊዜ ማራዘሚያ ትዕዛዞች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸው በመሆኑ ተሻሽለዋል።
አመልካች 50,000 (አምሳ ሺህ) ብር ዋስትና በማስያዝ ወይም በቂ ዋስትና ቀርቦ ከእስር እንዲፈቱ ተወስኗል። | 139 | 4 | 0 | 1 | Loading... |

