307
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-230 days
Posts Archive
307
Repost from Jura Legal Update
+5
በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የክፍፍል ጥያቄ ጋብቻው ከፈረሰበት ቀን ጀምሮ በ10 ዓመት ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል የሚል ትርጉም መስጠት የተፋቾችን ሕገ መንግሥታዊ የንብረት መብት የሚጥስ ስለሆነ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40(1፣ 7)፣ 50(5)፣ 55፣ 79(1)፣ እና 9(1) መሠረት ተፈጻሚነት የለውም።
ፌዴሬሽን ም/ቤት መ/ቁ.77/12 (ሰኔ 03 ቀን 2012 ዓ.ም)
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/
307
Repost from 🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️
+5
```````*የሰ/መዝ/ቁ 266998*```````
የካቲት 26/2018ዓ.ም
#ላልተሰራ-ስራ-የሚከፈል-ደመወዝ-ስላለመኖሩ
~~~
በትግራይ ጦርነት ምክንያት ስራ በመቆሙ አሰሪው ሰራተኛውን ስራ ለማሰራት የማይችልበት በቂ ምክንያት በመሆኑ አሰሪው የስራ ዉሉን ባያቋርጥም ላልተሰራ ስራ ደመወዝ የሚከፈልበት አግባብ ስለሌለ በዚህ ወቅት የሚጠየቅ የደመወዝ ክፍያ የህግ መሰረት የሌለው ስለመሆኑ307
በሙስና ወንጀል በጋራ የተከሰሱ ሰዎች በማስረጃ መስማት ሂደት የተወሰኑት ክስ በማንሳት ምስክር አድርጎ በቀሪዎቹ ላይ እንዲመሰክሩ ማድረግ የተነሳላቸው ክስ ቀርቶ ሊከሰሱ እንደሚችሉ እያሰቡ በጫና ውስጥ ሆነው የሚሰጡት የምስክርነት ቃል በመሆኑ ተቀባይነት የሌለው ስለመሆኑ ሰ.መ.ቁ 197540 ቅፅ 28 !!!
የሙስና ወንጀልን የሚያጋልጡ ሰዎች በቂ ማበረታቻ አግኝተው የሙስና ወንጀል ፈፃሚዎች የፈፀሙት ወንጀል እና በሙስና ያካበቱት ንብረት ተደብቆ እንዳይቀር ወደ ህግ ቀርበው ተገቢ ቅጣት እንዲወሰንባቸው ለማስቻል ፣ የሙስና ወንጀል መርማሪዎችም በቂ ማስረጃ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታን ለመፈጠር ታስቦ ወንጀሉን የሚያጋልጡ ሰዎች በማበረታታት ወደ ማስረጃነት ሊቀየር ይችላል። በተያዘው ጉዳይ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነትና ግብረአበርነት የተከሰሱ ሲሆን ማስረጃ በመስማት ሂደት አቃቢ ህግ ሁለት ግብረ አበሮች ወደ ምስክርነት በመቀየር ማስወሰኑን ተከትሎ የተሰጠው ፍርድ መነሻ በማድረግ ክርክር ሲደረግበት የቆየ ነው።
የሙስና ወንጀልን በግበረ-አበርነት የፈፀሙ ሰዎች የወንጀለ ምርምራ ተጠናቆ ወደ ፍርድ ቤት ከመቅረቡ በፊት ጠቃሚ ማስረጃ የሰጡ ሰዎች ክስ ተቋርጦላቸዉ ከተከሻስነት ወደ ምስክርነት ቃል ክደትት ማንኛውም ምስክር ከሚሰጠው ምስክርነት እኩል ዋጋ እንዲሰጠውና በህጉ ጥበቃ የተደረገለት ሲሆን ነገር ግን ክስ ከቀረበና ማስረጃ መሰማት ከጀመረ በኋላ የተወሰኑትን ተከሳሾች ክስ ተነስቶ ክስ ባልተነሳላቸው ተከሳሾች ላይ ምስክር እንዲሆኑ ማድረግ ምስክሮች ለማስረዳት የሚጠቀሙት የምስክርነት ቃል ወይም ሀሳብ ቀደም ሲል በግበረ-አበርነት በተከሰሱቡት ወቅት የተከሳሽ ማስረጃዎችን አዳምጠው ያገኙትን ግንዛቤ እንዲሁም የከሳሽ ወገንን የማስረጃ ክፍተት እና ፍላጎት ከተረዱ በኋላ የተገባላቸውን የተስፋ ቃል እያሰቡ የሚሰጡት የምስክርነት ቃል የተገባላቸው የክስ መነሳት ቀርቶ በተከሳሽነት እንደሚሚቀጥሉ እያሰቡ በጫና ውስጥ ሆነው የሚሰጡት የምስክርነት ቃል በመሆኑ የሰጡት የምስክርነት ቃል ተቀባይነት ሊያገኝ የማይችል ስለመሆኑ ሰበር በመዝገብ ቁጥር 197540 ቅፅ 28 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
307
የውርስ ሀብት ስለመመለስ
የውርስ ሀብት መመለስ ማለት ሟቹ በስጦታ ውሉ አሊያም በኑዛዜው ወይም በሌላ ሁኔታ
በቁም ስጦታ ሆነ በኑዛዜ ስጦታ የተሰጣውን ንብረት በድርሻ ክፍፍል ጊዜ የመመለስ ግዴታ
ያለበት መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ሟች በቁም ሆነ በኑዛዜ ስጦታ ላይ ለወራሽ የተሰጠውን ንብረት እንዳይመልስ በግልፅ ያስቀመጠ እንደሆነ ወራሽ የመመለስ ግዴታ የለበትም፡፡ ይኸውም በቁም ስጦታ እንዳይመልስ በተደረገ ጊዜ በቁም ስጦታው ላይ በግልፅ ካልተቀመጠ ተቀባይነት የለውም፡፡ ነገር ግን በኑዛዜ ጊዜ እንዳይመልስ የሚለው የሟች ሀሳብ በኑዛዜው ላይ ባይቀመጥም አልመልስም የሚለው ወገን ሟች እንዳይመልስ የተናዘዘለት ለመሆኑ ከኑዛዜ ውጭ ያለ ማናቸውንም ማስረጃ በማቅረብ ማስረዳት ይችላል፡፡
“የኑዛዜ ስጦታ በሆነ ጊዜ ሟቹ ለወራሹ የሰጠውን ነገር እንዳይመልስ ነፃ በማድረግ ነው ብሎ ለማረጋገጥ በማናቸውም ዐይነት ማስረጃ ለማስረዳት ይቻላል”፡፡ ስለሆነም አሁን በተያዘው ጉዳይ ላይ ወራሽ ቤቱ የተሰጣት እንዳትመልስ በማሰብ መሆኑን በቀረበው ኑዛዜ ለችሎቱ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ኑዛዜው በችሎቱ ተቀባይነት ባይኖረው እንኳን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1067(3) ድንጋጌ መሰረት ቤት መስሪያ ቦታው የተሰጣት ወደፊት እንዳትመልስ በማሰብ መሆኑን በማናቸውም አይነት ማስረጃ ማስረዳት ስለምትችል ምስክሮች ለችሎት ቀርበው በሚመሰክሩበት ወቅት “ቤት መስሪያ ቦታው የተሰጣት ሟች ወደፊት ትመልሰዋለች ብለው አለመሆኑን ወይም እንዳትመልስ” በማሰብ መሆኑን መመስከር ይጠበቅባቸዋል፡፡ እንደ ምስክር ሆነው የሚቀርቡት፡- በተለይ እራሷ ወራሽ ፤ ቤቱን የገነቡት ግንበኞች ፤ ጎረቤቶች ፤ ሌላ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቅ እና ለችሎቱ ቤት መስሪያ ቦታው ለወራሽ እንዳትመልስ የተሰጣት መሆኑን በግልፅ ቋንቋ መመስከር ይጠበቅባቸዋል፡፡
አንድ የመመለስ ግዴታ ያለበት ወራሽ ከመመለስ ነፃ የሚወጣው ውርሱን አልፈልግም በማለት ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ወራሽ ከሟች ሊያገኘው የሚችለውን ቀሪ ውርስ ከተወ የመመለስ ግዴታው እንደሚቀር የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1073 በግልጽ ያስገነዝበናል፡፡
የጋራ ወራሾች ስለሚመልሱት ንብረቶች
የተመላሽነቱ መሠረት ውርሱን የሚቀበለው የሟቹ ወደ ታች የሚቈጠር ተወላጅ የሆነ ሰው መመለስ የለብህም ተብሎ ከሟቹ ያገኘው ችሮታ ካለሆነ በቀር ተቀብሎት የነበረውን ዋጋውን ከውርሱ ውስጥ መልሶ ማግባት አለበት፡፡ የሚመለሱትን ስጦታዎች መለየት በውርሱ ውስጥ ተመልሶ መግባት የሚገባው ነገር ከጋራ ወራሾቹ የአንዱን ለትዳሩ ማቋቋሚያ ወይም የዚህኑ የጋራ ወራሽ የሆነውን ሰው ዕዳ መክፈያ እንዲሆነው የተሰጠው ነገር ነው፡፡
ከጋራ ወራሾቹ ለአንዱ ለመማሪያው ሟቹ ያደረገው ወጪ መመለስ የለበትም፡፡ ከመመለሱ ነጻ ስለ መሆን ሟቹ ለወራሽ ያደረገለት ችሮታዎች በእልቅናና ከሚደርሰው ውጭ በማድረግ ወይም የተቀበለውን እንዳይመልስ ነጻ በማድረግ እንደሆነ የተባለው ወራሽ አስቀድሞ የወሰደውን ንብረት መመለስ የለበትም፡፡ የቁም ስጦታ በሆነ ጊዜ ይህን፣ አሳብ ለማረጋገጥ አንድ ግልጽ የሆነ የውል ቃል አስፈላጊ ነው፡፡ የኑዛዜ ስጦታ በሆነ ጊዜ ሟቹ ለወራሹ የሰጠውን ነገር እንዳይመልስ ነጻ በማድረግ ነው ብሎ ለማረጋገጥ በማናቸውም ዐይነት ማስረጃ ለማስረዳት ይቻላል፡፡ ከአንድ ነገር የሚገኝ ጥቅም ወይም የአሱራንስ ገንዘብ ሟቹ ለወራሹ ካንድ ነገር ከሚያገኘው ገቢ ላይ ችሮታ ያደርገለት እንደሆነ፣ መመለስ የለበትም፡፡ እንዲሁም ሟቹ ለወራሹ ጥቅም የከፈለውን የአሱራንስ ዋጋ መመለስ የለበትም፡፡
ቀጥታ ያልሆነ ጥቅም ወራሹ ከሟቹ ጋራ ባደረጋቸው ስምምነቶች ወይም የማኅበረተኛነት ውል ያገኛቸውን ትርፎች ወደ ውርሱ መልሶ ማግባት የለበትም፡፡ ገንዘቡን መልሶ በውርሱ ውስጥ ማግባት ያለበት ሰው አስቀድሞ የተወሰደውን ንብረት ሊመልስ የሚገባው ወደ ታች የሚቈጠር የሟች ተወላጅ ብቻ ነው፡፡ እንዲሁም ሌሎቹ ወራሾች የወሰዱትን እንዲመልሱ ሟቹ ግዴታ ሊያደርግባቸው ይችላል፡፡
ወራሽ የሆነው ሰው ችሮታው በተደረገለት ቀን የሟቹ ወራሽ ነው ተብሎ የማይገመት የሆነ ቢሆንም እንኳ ወራሹ አስቀድሞ የወሰደውን መመለስ አለበት፡፡ ምትክነት ማንም ሰው ለሌላ ሰው ምትክ በመሆን ለወራሽነት የመጣ እንደሆነ፣ እርሱ ራሱ የተቀበላቸውን ስጦታዎች በውርሱ ውስጥ መመለስ አለበት፡፡ እንዲሁም ምትክ የሆነ ሰው የተተካለት ሰው አስቀድሞ ከሟቹ የተቀበላቸውን ችሮታዎች በውርሱ ውስጥ መመለስ አለበት፡፡ ወራሽነትን አልቀበልም ባይ ውርሱን አልቀበልም ያለ ወራሽ ከሟቹ አስቀድሞ የወሰደውን ነገር በውርሱ ውስጥ መልሶ ማግባት የለበትም፡፡
መመለሱ ያለው ውጤት የጋራ ወራሾች የሚከፋፈሉትን ጠቅላላውን የሟቹን ንብረት ለመመደብ ፣ ሟቹ በተዋቸው ንብረቶች ላይ፣ በውርሱ ውስጥ መመለስ ያለባቸውን ሟቹ በቁም ወይም በኑዛዜ የሰጣቸው ንብረቶች ዋጋ የሚጨመር ይሆናል፡፡ አንድ የጋራ ወራሽ አስቀድሞ የወሰደውን ንብረት መመለስ የለበት እንደሆነ፣ ሊመልሰው እስከሚገባው ድረስ ያለውን ግምት አስቀድሞ ከድርሻው ላይ እንደተቀበለ ይቈጠራል፡፡
በጋራ ወራሾች መካከል የገንዘብ መመለስ ስላለው ወሰን አስቀድሞ የተወሰደውን ንብረት መመለስ፣ የወራሽነቱን ሀብት ክፍያና፣ ስለዚህም ጒዳይ በጋራ ወራሾቹ መካከል ያሉትን ግንኙነቶች በሚመለከት ነገር ካልሆነ በቀር አንዳችም ውጤት የለውም፡፡ ከውርሱ ላይ ገንዘብ ጠያቂዎች ወይም የኑዛዜ ስጦታ የተነገረላቸው ሰዎች ወራሹ አስቀድሞ የተቀበለውን መመለስ አለበት ብለው ሊከራከሩ አይችሉም፡፡ የገንዘብ መመለሱ አነስተኛ ገንዘብ በመውሰድ ስለሚፈጸም አስቀድሞ የተወሰደው ነገር በውርሱ ውስጥ የሚመለሰው ከድርሻው ላይ በመቀነስ ነው፡፡ ወራሽ የሆነው ሰው፣ በውርሱ ውስጥ ከሚደርሰው ድርሻ ግምት በላይ በማናቸውም ጊዜ አስቀድሞ የወሰደውን ንብረት ለመመለስ አይገደድም፡፡ አስቀድሞ የተወሰዱት ንብረቶች በዐይነታቸው እንዲመለሱ ተብሎ ሟቹ ከመሞቱ በፊት የውል ቃል ለማግባት አይፈቀድም፡፡ የሚመለሰው ንብረት ግምት ሊመለስ የሚገባው አስቀድሞ የተወሰደው ንብረት ግምት፣ ሰነድ ላይ የተሰጠው ግምት ነው፡፡ የዚህ ዐይነት ግምት አልተደረገ እንደሆነ ስጦታው በተደረገ ጊዜ በነበረው ግምት መሠረት መመለስ ያስፈልጋል፡፡ አስቀድሞ የተሰጠው ንብረት መጥፋት ወራሹ አስቀድሞ የወሰዳቸው ንብረቶች ቢጠፉና በተደረገለትም ስጦታ መበልጸጉ ያቋረጠ ቢሆንም እንኳ ንብረቶቹን በውርሱ ውስጥ መልሶ ማግባት አለበት፡፡
307
Repost from N/a
የማዕ_ኢት_ክልል_ፍቤት_ዳኞችና_የጉባኤ_ተሿሚዎች_የፈቃድ_አሰጣጥ_እና_የህክምና_ማስረጃ_አቀራረብ_መመሪያ.pdf3.66 MB
307
የአጥንት ስብራት መኖሩ ብቻውን ወንጀሉን ከባድ የአካል ጉዳት አያደርገውም።
"አንድ ሰው በፈፀመው የወንጀል ድርጊት የተጎጂው አጥንት መሰበሩ የተረጋገጠ ቢሆንም ስብራቱ ታክሞ መዳኑ በባለሙያ ከተረጋገጠና በስብራቱ ምክንያት የተጎጂ ሰውነትም ሆነ በአዕምሮው ላይ ለዘወትር ጠንቅ የሚያተርፍ መሆኑ ፤ከአካሉ ወይም አስፈላጊ ከሆኑ ብልቶቹ መካከል አንደ ወይም ከዘያ በላይ መጉደል እና በጉዳቱ ምክንያት አስፈላጊው ብልት አገልግሎት አለመስጠቱ ወይም በሚያሳቅቅ ጉልህ ሆኖ በሚታይ ሁኔታ የተጎጂው መልክ መበላሸቱ፤ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ሌላ ከባድ የሆነ ጉዳትን ወይም በሽታን የሚያስከትል መሆኑ ካልተረጋገጠ በስተቀር ተጎጂ ላይ የደረሰው የአጥንት ስብራት ታክሞ መዳኑ ከተረጋጠ ድርጊቱ የሚሸፈነው በወንጀል ሕግ አንቀፅ 556(2) በመሆኑ ቅጣቱ ሊጣልበት የሚገባ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 556 መሰረት መሆን አለበት።" የሰበር መ/ቁ 219862 ቅፅ 28
307
ከእስር ማምለጥ እና እስረኛ እንዲያመልጥ መርዳት የሚያስከትለው
የወንጀል ተጠያቂነት
መግቢያ
ሰዎች የወንጀል ድርጊት ፈፅመው በወንጀል ሲፈረድባቸው በማረሚያ ቤት፣ በወንጀል ተጠርጥረው በወንጀል ሥነ ሥርአት ሕግ ቁጥር 63 እና 67 መሠረት ዋስትና ሲከለከሉ ወይም በፍትሐብሔር ጉዳይ የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ለመፈጸም ፍቃደኛ ባልሆኑ ጊዜ እስኪፈጽሙ በማረፊያ ቤት ሊቆዩ ይችላሉ፡፡ በቆይታቸውም በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት በሕግ ስለተያዙ ሰዎች መብት፣ ስለተከሰሱ ሰዎች እና በጥበቃ ሥር ስላሉና በፍርድ ስለታሰሩ ሰዎች መብት እና በሌሎች ሕጎች የተቀመጡ መብቶች ሊጠበቅላቸው ይገባል፡፡ በአንፃሩም በሕግ አግባብ የተያዙ ወይም የታሰሩ ሰዎች የማረሚያ ወይም የማረፊያ ቤት ቆይታቸው ሕጎችና ደንቦች እንዲሁም የወንጀል ሕጉን የማክበር ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህም ጽሁፍ በሕግ አግባብ የተያዙ ወይም የታሰሩ ሰዎች ከእስር ማምለጥ እና እስረኛ እንዲያመልጥ መርዳት የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነትን በአጭሩ የሚዳስስ ይሆናል፡፡
የእስረኛ ወይም የታራሚ ምንነት
ከፌደራል ማረሚያ ቤት አዋጅ ቁጥር 1174/2012 አንቀጽ 2 እንደምንረዳው “እስረኛ” ማለት በፍርድ ቤት የተወሰነበትን ፍርድ በማረሚያ ቤት ውስጥ በመፈፀም ላይ ያለን ታራሚ፣ በወንጀል ፍርድ ሂደት ማረፊያ ቤት የሚቆይ ተከሳሽ ወይም በፍርድ ቤት በፍትሐብሔር የአፈጻጸም ክርክር በማረፊያ ቤት እንዲቆይ ትዕዛዝ የተሰጠበት የፍትሐብሔር ታሳሪ እንደሆነ ለመረዳት ይቻላል፡፡ አዋጁ በተጨማሪም ማረሚያ ቤትን በአንቀጽ 2(5) ላይ ሲገልጽ፣ ታራሚዎች ፍርዳቸውን የሚፈጽሙበት፣ የሚታረሙበትና የሚታነፁበት እንዲሁም ማረፊያ ቤትን የሚጨምር ቦታ መሆኑን ይደነግጋል። በአዋጁ አንቀጽ 2(6) “ማረፊያ ቤት” ማለት ደግሞ መደበኛ ክስ ተከፍቶባቸው ቀጠሮ ላይ ያሉ ተከሳሾች ወይም በፍትሐብሔር ክርክር ትዕዛዝ የሚቆዩበት ቦታ እንደሆነ ተደንግጓል።
ከእስር ማምለጥ
የፌደራል ማረሚያ ቤት አዋጅ ቁጥር 1174/2012 አንቀጽ 47 መሠረት ማረሚያ ቤት የእስረኞቹን እና የማረሚያ ቤቱን ማኅበረሰብ ደህንነት ለመጠበቅ፣ የማረሚያ ቤትን ደንብና ሥርዓት ለማስጠበቅ እንዲሁም ፀጥታው የተከበረ ሰላማዊ የማረሚያ ቤት አካባቢ እንዲኖር ለማድረግ አስፈላጊ የሆነ የጥበቃ እና ቁጥጥር ሥርዓት የመዘርጋት እንዲሁም በአዋጁ አንቀጽ 48 መሠረት እስረኞችን እንደተቀበለ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ የእያንዳንዱን እስረኛ ፀባይ፣ የቀድሞ ታሪክ፣ የታሰረበትን ምክንያት፣ በማረሚያ ቤት የሚቆይበትን የጊዜ ርዝመት እንዲሁም ሌሎች ተያያዥነት ያላቸውን ሁኔታዎች በማጥናት እስረኛው በማረሚያ ቤት ቆይታው ከእስር ቤት ለማምለጥ፣ በሌሎች እስረኞች እንዲሁም የማረሚያ ቤት ሠራተኞች ላይ ጉዳት ለማድረስ፣ ፀጥታ እና ሰላምን ለማደፍረስ፣ የማረሚያ ቤትን ደንብ እና ሥርዓት ለመጣስ፣ በንብረትና በራሱ ላይ ጉዳት ለማድረስ ይኖረዋል ተብሎ የሚገመተውን የስጋት ደረጃ በመለየት በከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ የመመደብ፤ የስጋት ደረጃዎችን ከለየ በኋላም ከስጋት ደረጃው ጋር ተመጣጣኝ የሆነውን የጥበቃ እና ቁጥጥር ሥርዓት የመዘርጋት የመተግበር ኃላፊነት ተጥሎበታል፡፡ በአንፃሩ ታራሚዎች መልካም ሥነ ምግባር ሊኖራቸው የሚጠበቅ ሲሆን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ከማረሚያ ቤት ለማምለጥ ሲሞክር ወይም ሲዘጋጅ የተገኘ፣ በሌሎች እስረኞች ወይም በኮሚሽኑ ሠራተኞች ላይ ጉዳት ለማድረስ የሞከረ ወይም ያደረሰ ወይም የማረሚያ ቤቱን ደንብና ሥርዓት ለማክበር ፍቃደኛ ያልሆነ ወይም የማረሚያ ቤቱን ኃላፊዎች እና ፖሊሶች ትዕዛዝ ለመቀበል ፍቃደኛ ያልሆነ ወይም በጤና ሁኔታው በራሱ ላይ ጉዳት ለማድረስ የሞከረ እስረኛ ለተወሰነ ጊዜ ብቻ በማረሚያ ቤቱ ግቢ ውስጥ በሚገኝ የተለየ የእስር ክፍል ውስጥ እንዲቆይ ሊደረግ እንደሚችል የአዋጁ አንቀጽ 50 ይደነግጋል፡፡
በተያያዘም በ1996 የወጣው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 461(1) መሰረት ማንም ሰው በሕግ አግባብ ተይዞ ወይም ታስሮ ካለበት ቦታ በሰዎች ወይም በንብረት ላይ ምንም የኃይል ተግባር ሳይፈጽም ያመለጠ እንደሆነ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እሥራት እንደሚቀጣ ተደንግጓል፡፡ ነገር ግን ወንጀሉ የተፈፀመው በሰዎች ላይ ዛቻ ወይም የኃይል ተግባር በመፈፀም ወይም በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ዓመት የማይበልጥ ቀላል እሥራት እንደሚሆን አንቀጽ 461(2) ይደነግጋል፡፡ ጥፋተኛው በመጀመሪያው ወንጀል የተፈረደበት ወይም የሚፈረድበት ሲሆን ስለወንጀሎች መደራረብ ወይም ስለተደጋጋሚነት የተመለከቱት ድንጋጌዎች እንደ አግባብነቱ ተፈፃሚ ሊሆኑ እንደሚችሉም ተደንግጓል፡፡
እሥረኛ እንዲያመልጥ ማመቻቸትና መርዳት
በ1996 የወጣው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 462 መሰረት ማንም ሰው የመንግሥት ሠራተኛ ሳይሆን በሕግ አግባብ የተያዘ ተወይም የታሰረ ሰው እንዲያመልጥ በኃይል ድርጊት፣ በማስገደድ፣ በዛቻ፣ በተንኰል፣ በግል ተሰሚነቱ ያለአግባብ በመገልገል ወይም በማንኛውም ሌላ ዘዴ ወይም መንገድ ያመቻቸ ወይም የረዳ እንደሆነ በቀላል እሥራት እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ ማምለጡ የተፈፀመው፣ የተሞከረው ወይም የተመቻቸው በቡድን የኅብረት ሥራ፣ በጦር መሣሪያ ወይም በማናቸውም ሌላ መሣሪያ እንደሆነ ወይም እንዲያመልጥ እርዳታ የተደረገለት ሰው ቢያንስ የሃያ ዓመት ፅኑ እሥራት የተፈረደበት ወንጀለኛ እንደሆነ ቅጣቱ ከሦስት ወር የማያንስ ቀላል እሥራት ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ ከሰባት ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እሥራት እንደሆነ ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ተደንግጓል፡፡ ወንጀለኛው ዕቅዱን ለማሳካት ሁከት አንስቶ፣ በሰው ወይም በንብረት ላይ የኃይል ድርጊት ፈፅሞ ወይም ሠራተኛን ወይም ጠባቂን ደልሎ፣ ወይም ማንኛውም ሌላ ተደራቢ ወንጀል ፈፅሞ እንደሆነ የተደራረቡ ወንጀሎች በተፈፀሙ ጊዜ ቅጣትን ስለማክበድ የተደነገጉት ድንጋጌዎች ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ንዑስ አንቀጽ 3 ይደነግጋል፡፡
ነገር ግን እስረኛው እንዲያመልጥ የረዳው የመንግሥት ሠራተኛ ከሆነ የመንግሥተ ሠራተኛ ከተሰጠው ኃላፊነት ጋር ተያይዞ ለሚያደርገው ተግባር ወይም ግድፈት በሙስና ወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆን የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 881/2007 ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የመንግሥት ሠራተኛ ወይም ጠባቂው ፖሊስ ጉቦ ወይም መደለያ በመቀበልም ሆነ በሌላ በማንኛውም ምክንያት እስረኛው እንዲያመልጥ የረዳ እንደሆነ በአዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9ን በመጣስ በሥልጣን አላግባብ መገልገል ወይም አንቀጽ 10 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ጉቦ መቀበል ወንጀል ተጠያቂ ሊሆን እንደሚችል መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡
ማጠቃለያ
ከእስር ማምለጥም ሆነ እስረኛ እንዲያመልጥ መርዳት በአገራችን የወንጀል ተጠያቂነት የሚያስከትሉ በመሆናቸው ከመሰል ድርጊት መታቀብ ይገባል፡፡
ምንጭ:- ከፍትህ ሚኒስቴር የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ
307
Repost from ⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️
+5
ሰበር በቅፅ 28 በሰ/መ/ቁ 150290 በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም
በባንክ የገንዘብ ሐዋላ መላኪያ ወረቀት ሰነድ ገንዘብ መላኩን ከማስረዳት ውጪ በምን ምክንያት ገንዘቡ መላኩን ወይም ገንዘቡ በብድር፣በአደራ የተሰጠ መሆኑን ሊያስረዳ የማይቻል ስለመሆኑ። የፍ/ሕ/ቁጥር 2472፣ 2782/1/2/2802/2 ጠቅሶ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
ተከሳሽ የነበረውም ድምፃዊ ንዋይ ደበበ ነው!
307
✅የሰ/መ/ቁ 39940፡- የይዞታ ክስ የሚቀርበው ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ንብረት በወቅቱ ለመያዝ ምንም አይነት መብት በሌለው ሰው ሲያዝ ነው፡፡ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ አቅራቢ ንብረቱ በህግ አግባብ በይዞታው የነበረና የሁከት ድርጊት ፈጻሚው የኃይል ተግባር በመጠቀም ወይም በሚስጥር ንብረቱን የወሰደበት መሆኑን፤ ሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ አቅራቢው ሁከት ፈጥሯል ከተባለው ሰው በንብረቱ ላይ የተሻለ መብት ያለው መሆኑን ማረጋገጥ አለበት፡፡ ሁከት ፈጥሯል የተባለው ሰው ከከሳሽ የተሻለ መብት ያለው እና በአግባቡ መብት አግኝቶ ንብረቱን ይዞ ከተገኘ ሁከት ፈጥሯል ሊባል አይገባም፡፡ ቅጽ/9
✅የሰ/መ/ቁ 42861፡- ይዞታና ባለቤትነትን የሚመለከቱ ጉዳዮች የተለያዩ እንደ መሆናቸው መጠን የሚሸፈኑት በተለያዩ የህግ ድንጋጌዎች ነው፡፡ አንድ ሰው ባደረገው የኪራይ ውል ሰበብ ቤቱን በሃይል ይዞ ለመልቀቅ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ኪራዩን ከፍሎ ቤቱን እንዲለቅልኝ በሚል የሚያቀርበው አቤቱታ ባለሀብት የሆኑበትን ቤት ለማስለቀቅ የቀረበ የመፋለም ክስ እንጂ የይዞታ ክርክር አይደለም፡፡ በሃይል ይዟል ስለተባለ ብቻ ክሱን የሁከት ይወገድልኝ ክስ የሚያሰኘው አይደለም፡፡ እንደዚህ አይነት ክስ ላይም የፍ/ብ/ህ/ቁ 1149 ተፈጻሚ አይሆንም፡፡ ቅጽ/10
✅ የይዞታ ይርጋ
የሰ/መ/ቁ 60392፡- ይዞታን አስመልክቶ የሚነሳ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ ጋር በተያያዘ ተፈጻሚ የሚሆነው የይርጋ ጊዜ መቆጠር ያለበት አቤቱታ አቅራቢው የይዞታ መብቱን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ከሚመለከተው አካል ካገኘበት ቀን ጀምሮ እንጂ አቤቱታ የቀረበበት ድርጊት መፈጸም ከጀመረበት ዕለት አንስቶ አይደለም፡፡ ቅጽ/11
✅የሰ/መ/ቁ 49985፡- የፍ/ብ/ህ/ቁ/ 1149(1) ሁከት የተፈጠረበት ሰው እንዲወገድለት እና ይዞታው የተወሰደበት ሰው የተወሰደበት ነገር እንዲመለስለት የሚሉትን ሁለቱንም ዓይነቶች ሁኔታዎች ለይቶ የደነገገ ነው፡፡ ተለይቶ የታወቀ ንብረት ተወስዶብኛል ይመለስልኝ በሚል የሚቀርብ አቤቱታ በፍ/ብ/ህ/ቁ 16 እና 226(3) መሰረት ትክክለኛ ዋጋው ተገምቶ ነገሩን አይቶ ለመወሰን ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ተገቢው የዳኝነት ገንዘብ ተከፍሎበት ይቀርባል እንጂ የተፈጠረ ሁከት እንዲወገድ (cessation of interference) እንደሆነ ተቆጥሮ በገንዘብ በማይመዘኑ አቤቱታዎች በሚቀርቡበት ሁኔታ ሊስተናገድ አይገባም፡፡ አቤቱታው ተለይቶ የታወቀን ንብረት ለማስመለስ የቀረበ መሆኑን ይዘቱ የሚያመለክት ከሆነ የክስ አርዕስት ሁከት ይወገድልኝ ስለተባለ ብቻ ጉዳዩ ሁከት ይወገድልኝ ነው በማለት በፍ/ብ/ህ/ቁ 1149(2) የተቀመጠው ይርጋ ተፈጻሚ ሊሆን አይችልም፡፡ ቅጽ/11
✅የሰ/መ/ቁ 42824፡- በፍ/ብ/ህ/ቁጥር 1225 ስር በባለቤትነት መብት ያለመጠን መገልገልን የሚደነግገው ድንጋጌ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1149 ስር ከተመለከተው በይዞታ ላይ ሁከት ስለመፍጠር እጅጉን የተለየ ነው፡፡ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1225 ስር የተመለከተው ጉዳይ በሰፊው በባለቤትነት መብት ላይ በህጉ ከተመለከቱት ገደቦች መካከል አንዱ ነው፡፡ ባለቤት ድርጊቱን የሚፈጽመው ወይም ሥራውን የሚፈጽመው በራሱ ንብረት ወይም ቤት ውስጥ ቢሆንም የድርጊቱ ወይም የሥራው ውጤት መገለጫዎች ሌላውን ጎረቤት ወይም ባለቤት፤ በሌላ ህጋዊ አግባብ ተጠቃሚ የሆነውን ሰው እንዳይረብሽ፤ እንዳያውክ ወይም በማንኛውም መልኩ ከተገቢው በላይ የሆነ ችግርን እንዳያስከትል በማድረግ መብቱን በልክ ባለቤቱ ይጠቀም ዘንድ ህጉ ያስቀመጠው፤ የባለቤትነት መብትን አጠቃቀም አድማሱን የሚወስን ሥርዓት ስለመሆኑ ከአንቀጽ 1226 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ጋር አዛምደን በምናነብበት ጊዜ የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም በፍ/ብ/ህ/ቁ. 1149 ስር የተመለከተው የይርጋ ጊዜ ለጉዳዩ አግባብነት የለውም፡፡ የጉዳዩ ይዘት በፍ/ብ/ህ/ቁ. 1225 እና 1226 ድንጋጌ ስር የተመለከተውን የሚመለከት ሆኖ እያለ በይዞታ ላይ ሁከት ሲፈጠር የይርጋ ጊዜን የሚመለከተውን ድንጋጌ መሰረት በማድረግ ውሳኔ መስጠት መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ነው፡፡ ቅጽ/11
በጠበቃ አደም ሰይድ
307
✅ የፍርድ ቤቶች ዋናኛ ሚና ክርክሮች በተገቢው የህግ ስርዓት እንዲመሩ ማድረግ ነው፡፡ የክሱ ርዕስ ሁከት ይወገድልኝ እና በሁከት ምክንያት ያወጣሁት ወጪ እንዲከፈለኝ የሚል ሆኖ ይዘቱ ግን ሲታይ የኪራይ ውል ይፈፀምልኝ የሚል ይዘት ካለው ፍርድ ቤቱ በክርክሩ ላይ ባለው የመሪነት ሚና ክሱ እንዲሻሻል ማድረግ ይገባዋል እንጂ ሁከት አለ የለም የሚል ጭብጥ መያዝ የቀረበውን ክስ አከራክሮ መወሰን የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 187(2)ን ያላገናዘበ ነው መ/ቁ 12249
ቅጽ/20 የሰ/መ/ቁ 80241፡- የአንድ ንብረት ባለይዞታ የሆነ ሰው ይዞታውን ለመንጠቅ ወይም በይዞታው ላይ ሁከት ለመፍጠር የሚፈፀምን ማንኛውንም ድርጊት እንዲቆም ወይም ንብረቱ እንዲመለስለት ህግ ከጠበቃቸው መንገዶች አንዱ አማራጭ የይዞታ ክስ ማቅረብ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1149(1) ድንጋጌ ያሳያል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የሁከት ይወገድልኝ ክስ መቅረብ የሚችለው አቤቱታ አቅራቢው ለክርክሩ መነሻ በሆነው ነገር በቀጥታ ወይም በጠባቂ ይዞታ ሲኖረው ነው፡፡ እንዲሁም የይዞታ ክስ የሚቀርበው ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ንብረት በወቅቱ ለመያዝ ምንም አይነት መብት በሌለው ሰው ላይ ስለመሆኑም የድንጋጌው መንፈስ ያስረዳል፡፡ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ አቅራቢ በማስረጃ ማረጋገጥ ያለበት ንብረቱ በይዞታው ስር የነበረና የሁከት ድርጊት ፈጻሚው የኃይል ተግባር በመጠቀም ወይም በሚስጥር ንብረቱን የወሰደበት መሆኑን ነው፡፡ ሁከት መፍጠር የሚኖረው ባለይዞታ የሆነው ሰው በይዞታው ስር የሚገኘውን ንብረት እንዳይገለገልበት ሌላ ሰው ጣልቃ ገብቶበት መሰናክል ሲፈጠርበት ወይም ረብሻ ሲፈጠርበት ነው፡፡ ቅጽ/15 የሰ/
✅ የሰ/መ/ቁ 67691፡- አንድ የቤት አከራይ ባለቤት የሆነ ሰው ቤቱን በኪራይ የያዘው ሰው እንዲለቅለት ማስጠንቀቂያ መጥራና የኪራይ ውሉን ለማቋረጥ ሃሳብ ያለው መሆኑን በፍ/ብ/ህ/ቁ. 2966(1) መሰረት ማሳወቁ ከአከራይ ተከራይ ውልና ግንኙነት አንፃር የሚታይ እንጂ እንደ ሁከት ተግባር የሚቆጠር አይደለም፡፡ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1149(1) እንዲህ አይነት ጉዳይን አይሸፍንም፡፡ በእንዲህ አይነት ጊዜም መጠየቅ ያለበት ዳኝነት የቤቱ አከራይ ከህግ ውጭ የኪራይ ውሉን ለማቋረጥ ካሰበ በኪራይ ውሉ እንዲገደድ ውሳኔ ይሰጠኝ በማለት እንጂ ማስጠንቀቂያ በመስጠቱ ሁከት ስለፈጠረብኝ ይወገድልኝ የሚል መሆን የለበትም፡፡ ሁከት ተፈጠረብኝ ተብሎ ክስ የተመሰረተ ቢሆን እንኳን ፍ/ቤቶች የሚይዙት ጭብጥ ሁከት አለ ወይስ የለም የሚል ጭብጥ ሳይሆን አከራዩ ውሉን ለማቋረጥ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተገቢ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን መያዝ የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 182(2)ን የሚከተል ነው፡፡ ቅጽ/13
✅ የሰ/መ/ቁ 70801፡- አንድ ንብረት በአንድ ህጋዊ ተግባር ሰበብ ወደ እጅ ገብቷል፡፡ በይዞታዬ ላይ እያለ ሁከት ተፈጠረብኝ የሚል ክስ ትክክለኛውን የሁከት ገብነት ሃሳብ ተከተሎ መቅረቡ ከተረጋገጠ ተከሳሹ ከተሰማ በኋላ በፍርድ የህግ ፅንሰ ሃሳብ ተከተሎ መቅረቡ ከተረጋገጠ ቤቱ ሊሰጥ የሚገባው ዳኝነት ሁከት ተፈጥሯል ይወገድ ወይም የተፈጠረ ሁከት የለም በማለት የሚወሰን እንጂ በከሳሽ እጅ ንብረቱ ሊገባ የቻለበትን ህጋዊ ተግባር ለመመርመር የሚያበቃ ወይም የሚያስችል ምክንያት አይኖርም፡፡
በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 224 መሰረት የሚሰጠው ውሳኔ ተከሳሽ የጠየቀው መሆን አለበት፡፡ ሁከት ተፈጠረብኝ ይወገድልኝ በሚል ለሚጠየቅ ዳኝነትም ሁከት መፈጠሩ መረጋገጥ አለበት፡፡ ካልተረጋገጠ ደግሞ የተፈጠረ ሁከት የለም የሚል ውሳኔ እንጅ አመልካች ንብረቱን የያዘበት ውል ወይም መንገድ ዋጋ ያለው ነው ወይስ የለውም በሚል አጥሮ መወሰን ከተጠየቀው የዳኝነት ክልል የወጣ ነው፡፡ በሽያጭ ውል መሰረት በእጅ የገባ የንግድ ድርጅት ተወሰደበት ከሆነ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 226 ንዑስ አንቀጽ 3 እንደተመለከተው የተወሰደውና ተለይቶ የታወቀን ንብረት ለማስመለስ የፈለገ እንደሆነ የዚህ ንብረት ዋጋ ተገምቶ የስረ-ነገር ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ተገቢውን የዳኝነት ክፍያ በመክፈል ክሱን አቅርቦ በዚህ የክስ መስመር ተገቢው ክርክርና ንጥጥር ተደርጎ ተገቢውን ዳኝነት ማግኘት ይገባል እንጅ እንዲህ አይነቱ ሁኔታ በሁከት ይወገድልኝ አቅርቦ አይችልም፡፡ ምክንያቱም በፍ/ብ/ህ/ቁ 1149 እንደተመለከተው በሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ ሊስተናገድ የሚገባው ጉዳይ በንብረት ላይ የተፈጠረውን ሁከት ለማስቆም ወይም ሁከት መፍጠር ተግባር እንዲታገድ (injection) ለመጠየቅ እንጂ የተወሰደ ንብረት እንደገና ወደ እጅ ለማስገባት የሚያስችል አይደለም፡፡ ቅጽ/13
✅ የሰ/መ/ቁ 27506፡- አቤቱታው ሁከት ይወገድልኝ የሚል ከሆነ ክርክሩ የይዞታ መብትን/Possessory action/ የሚመለከት በመሆኑ በጭብጥ ተይዞ እልባት ሊሰጠው የሚገባው ነጥብ ሁከት ተፈጥሯል ወይስ አልተፈጠረም የሚለው ነው፡፡ የባለቤትነት የመፋለም ክስ (petitory action) ራሱን የቻለ ክርክር ነው፡፡ በመሆኑም በሁከት ይወገድልኝ ክርክር የባለቤትነት ክርክር ማንሳት አግባብነት አይኖረውም፡፡ ቅጽ/6
✅ የሰ/መ/ቁ 36645፡- አንድ ሰው በአንድ ንብረት ላይ ባለይዞታ ለመባል ነገሩን በእጅ አድርጎ መገኘትና በእውነት የሚያዝዝበት ሆኖ መገኘት አለበት፡፡ በእውነት ብቻ ሳይሆን በዚህ ንብረት ላይ በእውነት ማዘዝ እንዲችል የንብረቱ አያያዝ ያልተጭበረበረ እና በማንኛውም መንገድ ህገ ወጥ በሆነ ሁኔታ ያልተገኘ መሆን እንደማይገባው ነው፡፡ አንድ ሰው አንድን ንብረት በሽያጭ የያዘው ከሆነ ውሉ ተገቢውን የአፃፃፍ ስርዓት /form/ ተከተሎ አልተደረገም ቢባል እንኳን ገዥው ስለመያዙ እና ገዥው በንብረቱ በእውነት የማያዝዝ መሆኑን አያረጋግጥም፡፡ የውል የአጻጻፍ ጉድለት አለበት ከተባለ በንብረቱ መብት አለን የሚሉ ሰዎች ውሉ ፈራሽ ነው እንዲባል የክስ ምክንያት ከሚሆን በስተቀር ሁከት ይወገድልኝ ተብሎ በሚቀርብ ክስ ላይ ሊስተናገድ የሚችል አይደለም፡፡ በመሆኑም ገዥው ንብረቱን ከሻጭ ጋር ባደረኩት ውል መሰረት ይዘው እያለ ሻጭ ሁከትእየፈጠረብኝ ነው በማለት የሚያቀርበው የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ ተቀባይነት ካለው የፎርም ጉድለት ተለይቶ ሊስተናገድ ይገባዋል (አብላጫ ድምጽ)፡፡
በልዩነት ሃሳብ አንድ ዳኛ በውሉ መሰረት ንብረቱ በገዢው ስም እስካልተዛወረ ድረስ ሻጭ ባለንብረት ተደርጎ ስለሚወሰድ የንብረቱ ባለይዞታ የሆነው ገዢ ሊፈጽም የሚችለው የባለቤትነት መብት ያለውን ሰው ሁከት ፈጥሮብኛል ብሎ ሊከሰስ አይችልም፡፡ የይዞታ መብትን ለማስከበር የሚቀርብ ክስ የንብረቱ ባለቤትነት ሳይሆን በይዞታ ጣልቃ የሚገቡ ሌሎች ሰዎችን ለማስቆም እና ለመከላከል የሚቀርብ የክስ አይነት ነው በማለት በልዩነት ወስኗል፡፡ ቅጽ/9
307
ሁከትን በተመለከተ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጣቸው አስገዳጅ የሕግ ትርጉሞች
✅ የሁከት ይወገድልኝ ክስ የሚያቀርብ ሰው ማረጋገጥ የሚጠበቅበት ዋና ዋና ፍሬ ነገሮች ሁከት ተፈጠረበት የተባለውን ንብረት/ሀብት/ ባልተቆራረጠ መንገድ በእጁ አድርጎ በእውነት የሚያዝበት መሆኑን እና በዚህ ይዞታው ላይ በተከሳሽው ሰው/አካል ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ሁከት የተፈጠረበት መሆኑን፣ በአንጻሩ የባለቤትነት መብት የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት የሆነ ሰው ከንብረቱ ላይ መብት ሳይኖረው ከሕግ አግባብ ውጭ ንብረቱን በእጁ ባደረገው ሰው ወይም ንብረቱን በያዘው አካል ላይ ክስ በማቅረብ የሚያስመልስበት ህጋዊ መብት (Right to bring Petitory Action) ስለመሆኑ፤ የፍ/ብ/ህ/ቁ/1140፣ 1146 እና 1149 ድንጋጌዎች ማብራሪያ ንባብ እና የፍ/ብ/ህ/ቁ/1206
የሰ/መ/ቁ: 220031 ቅጽ 27
✅ የሁከት ይወገድልኝ ክስ ለማቅረብ የሚቻለው አቤቱታ አቅራቢው ለክርክሩ መነሻ በሆነው ንብረት ላይ በቀጥታ ወይም በወኪል ይዞታ ሊኖረው እና ይህንኑ በኃይል ሊነጠቅ ወይም በይዞታው ስር ባለ ንብረት ላይ የመጠቀም መብቱን የሚያውክ ተግባር ሲፈጸም፣ እንዲሁም ንብረቱ በሕግ አግባብ በይዞታው ስር የነበረና የሁከት ድርጊት ፈጻሚው የኃይል ተግባር በመጠቀም ወይም በሚስጥር ንብረቱን እንደወሰደበት ማረጋገጥ ያለበት ስለመሆኑ መዝገብ ቁጥር፦ 197183 (ቅጽ 26)
✅ ከሁከት ይወገድልኝ ክስ ጋር በተያያዘ የፍርድ ቤት ክርክር የክስ ማቅረቢያ ጊዜ አስመልክቶ ለአስተዳደር አካል የመብት ጥያቄ ማቅረቢያ ጊዜ እና ለፍርድ ቤት ክስ ማቅረቢያ ጊዜን ለይቶ ማየትና የቀረበ የመብት ጥያቄ በእርግጥም በይርጋ የሚታገድ መሆኑን ለማረጋገጥ ለመብቱ መጠየቅ መሰረት የሆነው ጉዳይ የተፈጠረበትን እና ለአስተዳደር አካል እና ለፍርድ ቤት የመብት ጥያቄው የቀረበበትን ጊዜ በአግባቡ ማየት የሚገባ ስለመሆኑ።
መዝገብ ቁጥር፦ 202845 (ቅጽ 26)
✅ ሁከት እንዲወገድ በሚል በቀረበ ክስ ሁከት ተፈጠረበት የተባለው ቤት ባለቤትነት አከራካሪ፤ ከሳሽም ቤቱ በውርስ የተገኘ ባለቤት እንደሆነ የገለጸ ከሆነ፤ ተከሳሽ የሚያነሳው ባለቤትነትን የተመለከተ ክርክር አግባብነት ያለውና ቤቱ የከሳሽ የግል ሀብት አለመሆኑ ተጣርቶ የሚሰጥ ውሳኔ ከሳሽ ለጠየቁት ዳኝነት ምላሽ የሰጠ እና በአግባቡ የተሰጠ ፍርድ ነው ከሚባል በስተቀር ፍርድ ቤት ከቀረበለት የሁከት ይወገድልኝ ክስ ጭብጥ ወጥቶ የቤት ባለቤትነት ጉዳይ ላይ ፍርድ ሰጥቷል የሚያሰኝ ስላለመሆኑ መዝገብ ቁጥር፦ 203882 (ቅጽ 26)
✅ የሁከት ይወገድልኝ የክስ አቤቱታ ቀርቧል ለማለት የሚቻለው ለክርክሩ መነሻ የሆነው ንብረት በእጁ አድርጎ የሚገኝ እና ንብረቱ ላይ በእውነት ለማዘዝ እንዲችል የንብረቱ አያያዝ ያልተጭበረበረና በማናቸውም መንገድ ሕገ ወጥ በሆነ ሁኔታ ያልተያዘ መሆኑ ሲረጋገጥ እና ተከሳሽ ድርጊቱን እንዲፈጽም የተፈቀደለት መብት ወይም ስልጣን የሌለው ስለመሆኑ በማያሻማ ሁኔታ ማስረዳት የሚጠበቅ ስለመሆኑ።
መዝገብ ቁጥር 218309 (ቅጽ 26)
✅ በባለቤትነት መብት አለመጠን አገልግሎት በተፈጠረ ጊዜ ይህንን አስመልክቶ በፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 1149 እና 1225 መሰረት የሁከት ይወገድልኝ ክስ ማቅረብ አይቻልም
የሁከት ይወገድልኝ ክስ ሊቀርብ የሚችለው በተጨባጭ በይዞታ መብት ላይ የተፈጠረን የሁከት ተግባር ለማስወገድ እንጂ፣ ሊሰራ የታሰበ ስራ ሊያስከትል የሚችለውን ስጋት በመገመት ባልተፈጸመና ወደፊት ሊፈጠር በሚችል ድርጊት ላይ የሁከት ክስ ሊቀርብ የማይቻል ስለመሆኑ። የሰ/መ/ቁ 181821 (ቅጽ 25)
✅ የአስተዳደር አካል በክርክር ሂደት በፍርድ አደባባይ ከተረታ በኋላ ተከራካሪው ወገን መብት ያገኘበትን ካርታ በማምከን አስቀድሞ የተሰጠው ውሳኔ እንዲለወጥለት የሚያቀርበው አቤቱታ ውድቅ ሊደረግ የሚገባው ስለመሆኑ። የሰ/መ/ቁ 184069(ቅጽ 25)
✅ በፍ/ብ/ህግ ቁጥር 1195 (1) መሰረት የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ምስክር ወረቀት በማወቅ በአስተዳደር ክፍል የተሰጠው ሰው ባለቤት እንደሆነ የተወሰደውን የህግ ግምት ማስተባበል የሚቻለው ማስረጃው የተገኘው ከህግ አግባብ ውጭ በሆነ ሁኔታ መሆኑን በማስረዳት እንደሆነ፤ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1196 በተደነገገበት ሁኔታ የሰው ምስክር በመስማትና ቦታው ድረስ በመሄድ የችሎት ምልከታ በማድረግ የሚሰጥ ውሳኔ የምስክር ወረቀት በተሰጠበት ንብረት ላይ ባለቤትነትን የማይለውጥ ስለመሆኑ የሰ/መ/ቁ 183001(ቅጽ 25)
✅ የሁከት ይወገድልኝ ክስ የቀረበለት ፍርድ ቤት ሁከት የተፈጠረ መሆን አለመሆኑን አጣርቶ በመወሰን ረገድ ሁከት ተፈጠረ በተባለበት ወቅት ንብረቱ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ በከሳሽ ይዞታ ስር የነበረ መሆን አለመሆኑን እና ተከሳሽ በክሱ የተጠቀሰውን ተግባር ለመፈጸም የሚያስችል መብት ያለው መሆኑን አለመሆኑን እንጂ፣ ከዚህ በላይ በመሄድ በውርስ እና በይዞታ ባለቤትነት መሰረት ተደርጎ የሚሰጥ ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስሕት ነው የሰ/መ/ቁ 186348(ቅጽ 25)
✅ ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚፈጠሩ መብቶች እና ግዴታዎች የሚመሩት በንብረት ህግ አጠቃላይ መርሆዎች በመሆኑ የከተማም ሆነ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀምን አስመልክቶ የሚወጡ ህጎች/አዋጆች በንብረት ህግ ማዕቀፍ ውስጥ የሚመደቡ በመሆኑ ከንብረት ጋር የተገናኙ ያሉ ጽንሰ ሃሳቦች፣ ህጎች እና መርሆዎች ከመሬት ጋር በተያያዘ ለሚቀርብ ክርክር እንደ አግባብነታቸው ተፈጻሚነት ያላቸው ናቸው አንድን ንብረት አስመልክቶ የሚቀርበውን ክስ ተከትሎ ንብረቱን የሚመለከት የህግ ክፍል ተፈጻሚ የሚሆነው ከሳሽ ክሱን ያቀረበው ንብረቱን በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ በእጁ ካደረገ በኋላ በንብረቱ ላይ ያለው መብት እንዲከበርለት የተረጋገጠ ሲሆን በመሆኑ የታዘዘው ዳኝነት ንብረቱን የሚመለከት መሆኑ ብቻውን ጉዳዩን የንብረት ክርክር የማያደርገው ስለመሆኑ የሰ/መ/ቁ 186461(ቅጽ 25)
✅ በፍ/ብ/ህግ ቁጥር 1179 ስር የተመለከተው በሌላ ሰው ይዞታ ላይ የሚደረግ ግንባታን የመቃወም ጉዳይ አግባብ ባለው የአስተዳደር አካል በተሰጠ ይዞታ ላይ በሚደረግ ግንባታ ላይ ተፈጻሚነት የለውም የሰ/መ/ቁ 186946(ቅጽ 25)
✅ የሊዝ ውል እንዲቋረጥ የተሰጠ አስተዳደራዊ ውሳኔ ባልተሻረበት ሁኔታ በሊዝ ውል የተያዘ መሬት ለማስለቀቅ የመሬት አስተዳደር አካል መሬቱን ለመረከብ እንዲያስችለው የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ የሁከት ተግባር ነው ሊባል የማይችል ስለመሆኑ መዝገብ ቁጥር =158527 ቅጽ 24።
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
