en
Feedback
🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥

🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥

Open in Telegram

እነሆ፥እኔ እላችኋለሁ፥ዓይናችሁን አንሱና እርሻው አሁን እንደ ነጣ እዩ።" — ዮሐንስ 4፥35 🔥 missional መነቃቃትን ማምጣት (Revival) 📢 የወንጌል ስምሪትን መፍጠር (Mobilization) 📖 አገልጋዮችን ለታላቁ ተልዕኮ ማብቃት (Mission) 👉 እርስዎም ባለራዕይ ከሆኑ ተቀላቅለው አብረውን ያገልግሉ!⚠️I'm missionary and mission mobilizer.

Show more
1 716
Subscribers
+5024 hours
+2697 days
+68730 days
Posts Archive
በቅርቡ soon..... ከመፅሃፉ ከተሰጡት አስተያየት መካከል 👇 አብሰክስከን የክርስቶስን ማዕከላዊነት፣ የመስቀሉን ጥልቅ ምስጢር እና የወቅቱን የትውልድ ጥያቄዎች በውብ የስነ ፅሁፍ ዘዬ ያቀረበ ድ
+1
በቅርቡ soon..... ከመፅሃፉ ከተሰጡት አስተያየት መካከል 👇 አብሰክስከን የክርስቶስን ማዕከላዊነት፣ የመስቀሉን ጥልቅ ምስጢር እና የወቅቱን የትውልድ ጥያቄዎች በውብ የስነ ፅሁፍ ዘዬ ያቀረበ ድንቅ መጽሐፍ ነው። ወጣቱ ደራሲ ፊልሞን ነጋ መንፈሳዊ እውቀትን ከጥልቅ የንባብ ባህል ጋር አጣጥሞ ያቀረበበት፣መንገድ ያስደንቃል :: እያንዳንዱ አማኝ ሊያነበው የሚገባ የሕይወት መነጸር ነው።      ፍራኦል ተመስገን (መጋቢ ) ኮምቦልቻ ቃለህይወት ቤተክርስቲያን

ማስታወቂያ በዳምቦያ ከተማና አካባቢው ለምትገኙ አገልጋዮች በጌታ የተወዳዳችሁ ቅዱሳን ሰላምና ፀጋ ይብዛላችሁ፤ይህ ማስታወቂያ በዳምቦያ ከተማና አካባቢው ለምትገኙ አገልጋዮች ነው። የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከሆነ የፊታችን ቅዳሜ፣ማለትም ነሐሴ 29፣በዳምቦያ ከተማ በወንጌል ስርጭት ሪቫይቫል ቲም ሞቢላይዘርነት የተዘጋጀ የ 'ኤን ቪዥን' (N Vision) ወይም የእግዚአብሔር ተልዕኮ ስልጠና ስላለ፤በየትኛውም አጥቢያ የምታገለግሉ አገልጋዮች መጥታችሁ እንድትካፈሉ በጌታ ፍቅር እየለመንናችሁ እንማጸናችኋለን። ስልጠናው ቅዳሜ ከጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ ይሆናል።ሙሉ ቀን ስለ እግዚአብሔር ተልዕኮ እያሰብን፣ራሳችንን እያረምን፣ደግሞ እየጸለይንና እየተነቃቃን እናሳልፋለን።ምሳም አንድ ላይ እንበላለን። እናንተ ብቻ ኑልን፤ከቻላችሁ ለምሳ የተወሰነ ብር ይዛችሁ ኑ፣ከሌለም እናንተን ነው የምንፈልገው። በፍጹም አይቀርም ቅዳሜ ቀን። 👉ቦታው የት እንደሚሆን አሳውቃችኋለሁ። አሰልጣኝ ተሳጠኝ ፡ ከወላይታ ሶዶ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡ 0938768487 & @godwithusbibletruthchannel

ቤተክርስቲያን የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ዳግም መምጣት ካልዘነጋች በስተቀር የወንጌል ስርጭትን ችላ ልትል ወይም ልትረሳ አትችልም!

ሮሜ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹-² ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ። ³-⁴ ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ⁵ በእርሱም ስለ ስሙ በአሕዛብ ሁሉ መካከል ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን፤ ⁶ በእነርሱም መካከል የኢየሱስ ክርስቶስ ልትሆኑ የተጠራችሁ እናንተ ደግሞ ናችሁ። ⁷ በእግዚአብሔር ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። ⁸ እምነታችሁ በዓለም ሁሉ ስለ ተሰማች አስቀድሜ ስለ ሁላችሁ አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።

"በእርሱም ስለ ስሙ በአሕዛብ ሁሉ መካከል ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን፤" — ሮሜ 1:5

“በእግዚአብሔር ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።” — ሮሜ 1፥7

ፍለጋዬ_ሆነሃል_AZAHEL_ADDISE_new_Protestant_mezimur_out_now.m4a6.34 MB

አንድን ከባድ መኪና ከውጭ ሆኖ ለመግፋት የሰው ጉልበት (Human Energy) በጣም ውስን ነው።ነገር ግን መኪናው ውስጥ ያለው ሞተር (Dynamic Power) ከበራ፣ያንን ከባድ ብረት ያለ ምንም ድካም በቀላሉ ያንቀሳቅሰዋል።በተመሳሳይ፣የክርስቶስን ዓለም አቀፋዊ ተልዕኮ በሰውኛ ሞራል፣በዕውቀት ወይም በገንዘብ ብቻ መፈጸም አይቻልም፤የተልዕኮው ክብደት መንቀሳቀስ የሚችለው ከውስጥ በሚመነጨው በመንፈስ ቅዱስ(በመለኮታዊው ሞተር) ኃይል ብቻ ነው። ደህና እደሩ        •••••••••••••••••••••••••••••

መንፈስ ቅዱስ በቤተክርስቲያን ••••••••••••••••••••••••••••••••• ቤተክርስቲያን ልክ እንደ አንድ ትልቅ ፋብሪካ ወይም ሞተር ናት።ምንም እንኳን ማሽኑ ጥሩ ቢሆንም እና ሁሉም ክፍሎቿ በትክክል ቢገጠጠሙም፣የሚያንቀሳቅስ የኤሌክትሪክ ወይም የነዳጅ ኃይል ከሌላ ምንም ሥራ መስራት እንደማይችል፤ቤተክርትያንም ልክ እንደዚሁ ነት መንፈስ ቅዱስ በኃይል የማይሰራ ከሆነ የእግዚአብሔርን ታላቅ ተልዕኮ ልትሳራ አትችልም። ምክንያቱም ወንጌላችን ኃይልን በመግለጥና በብዙ መከራ እንጅ በቃልና በንግግር፣ በእውቀት ብቻ ወደ እኛ አልመጣምና። 👉ደግሞ በጸሎት አስቡኝ🙏

የጸሎት ጥር ስለ ሀላባ ሙስልሞች ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በሉ ቅዱሳን ዛሬ ቸርች አትቅሩ፣እናም ስለ በሀላባ ሙስልሞች ጸልያችሁ ውጡ፤እግዜር በሀላባ ምድር ያሉ ሙስሊሞችን በክርስቶስ እንዲያጠቃልላቸው፣ኢየሱስ እንዲበራላቸው፤ እናም ሀላባ ያለች ቸርች ከጣሪያ ስር በኃይል መውጣት እንድትችል፣ለወንጌል በየአደባባዮች የሚሰያፉ፣ለክርስቶስ ወንጌል በነፍሳቸው የተወራረዱ ሚሽነሪዎች እንዲነሱ ሳትረሱ ጸልዩ! ተባረኩ፣ጸጋ ይብዛላችሁ!

​የቤተክርስቲያን ዋና ዓላማ ስለ ክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ለዓለም ሁሉ መመስከር ነው።ስለዚህ የእግዚአብሔር መንግሥት የሚሰፋው በመሰብሰብ ኃይል ሳይሆን፣ከኢየሩሳሌም ጀምሮ እስከ ምድር ዳርቻ በሚደርስ ተከታታይ የምስክርነት ሥራ ነው።ምክንያቱም ምስክርነት ጥብቅና መቆም አይደለም፤በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የክርስቶስን ወንጌል ለሰው ልጅ ሁሉ መናገር እንጂ። አንድ ጥያቄ ምስክር ወይስ ጠበቃ ነችሁ?

በዚህ ቻናል፦ 👇 ​🎵 መዝሙር 📖 ስብከት 🔴 የሚስዮን ስልጠና በቀጥታ ስርጭት (ማክሰኞና አርብ) 📚 መጽሐፍቶች 🎙️ ከሚስዮናውያን ጋር ምስክርነት 🕊️ የተለያዩ ነፍስን የሚያንጹ ትምህርቶች ይገኛሉ 🙏 የጋራ የጸሎት ጊዜ 🌍 ሚሽን የመስራት ራዕይ ላላቸው ምክርና ጸሎት ​🎯 የዚህ አገልግሎት ዋና ዓላማ፡- መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ሚስዮናዊ እና እየበዛች የምትሄድ ቤተክርስቲያን መፍጠር ነው። ⛪✨ https://t.me/onegodtruth

​"የወንጌል ስርጭትን ወይም የሚስዮናዊነትን ጽንስ ወደ ተግባር ማለትም ወደ ሕያውነት የሚያወርደው ጸሎት ነው!" ​— ሚሽነሪ (ሚስዮናዊ) አበራ ዶታሞ

Pestar betam taberak taberak taberak taberak dqi new

📌ከሚስዮናዊ አበራ ዶታሞ ጋር የምስክርነት ጊዜ። ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ ቅዱሳን! ​ዛሬ ቃል ገብቼ እንደነበረው ከሚስዮናዊ ጋር ስለ ወንጌል ተልዕኮ የምንወያይበት ልዩ ፕሮግራም ይዘንላችሁ ቀርበናል። በተለይም አገልጋዩ ለሃያ ዓመታት ሚስዮናዊ ሆኖ እያገለገለ የቆየ እንደመሆኑ መጠን፤ሚስዮናዊነት ምን እንደሚመስል በሰፊው እናነሳለን፤እንዲሁም መንፈሳዊ ቅንዓታችንን እንካፈላለን። ​ይህንን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት ፕሮግራማችሁን አስተካክላችሁ እንድትጠብቁን በጌታ ፍቅር እናሳስባለን። የወንጌል ተልዕኮ ራዕይና ሚስዮናዊ አስተሳሰብ ያለውን ትውልድ ለመፍጠር አብረን እንታገላለን፤እግዚአብሔር ደግሞ እውነተኛ የወንጌል ስርጭት መነቃቃትን ያስነሳል! ​ 👉እንግዳ፡ ሚስዮናዊ አበራ ዶታሞ (ከሃያ ዓመታት በላይ በሚስዮናዊነት ያገለገሉ) 👉ዛሬ ማታ ከ 3፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት ​ 👉በዚህ ቻናል 🎯​(ፕሮግራሙ እንዳያመልጣችሁ፣ለሌሎችም አሁኑኑ ያጋሩ!)

እውነተኛ ምስክር ••••••••••••••••••• ሰው በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ከልሆነ በስተቀር እውነተኛ የክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ምስክር ልሆን አይችልም ፤ ምክንያቱም እውነተኛ ምስክርነት እጅግ በጣም ዋጋ የሚያስካፊል ነውና፤ እንደውም ምስክር የሚለው ቃል እራሱ "ማርቲር" (Martyr) ከሚለው የሰማዕትነት ቃል ጋር አንድ ነው።ስለዚህ እውነተኛ ምስክር መሆን ዋጋ ያስከፍላል።
ራእይ 2:13 13 የሰይጣን ዙፋን ባለበት የምትኖርበትን አውቃለሁ፤ ስሜንም ትጠብቃለህ፥ ሰይጣንም በሚኖርበት፥ በእናንተ ዘንድ የተገደለው የታመነው ምስክሬ አንቲጳስ በነበረበት ዘመን እንኳ ሃይማኖቴን አልካድህም።
የታመነ እንደ አንቲጳስ ያለ የክርስቶስ ምስክር ይብዛልን🙏

ስልታዊ ተልዕኮ (Strategic Mission) የወንጌል ስርጭት በአሁኑ ጊዜ በጥቂቱም ይሁን በብዙ እየተሰራ እንደሆነ ሁላችንም የምናውቀው ነው።ሆኖም ግን በሚፈለገው ልክ ወይም ማፍጠን ባለበት ልክ ደግሞ እየፈጠነ እንዳልሆነም ሁላችሁም የምታውቁት ነው።ስለዚህ "እንዴት አድርገን በጣም ውጤታማ የሆነ የወንጌል ስርጭት መስራት እንችላለን?" የሚለው የሁላችንም ጥያቄ ሊሆን ይገባል።ምክንያቱም ስርጭቱን ውጤታማ ለማድረግ ትክክለኛውን ስልት መጠቀም አለብንና።ካልሆነ ግን በወንጌል ያልተደረሱ የህዝብ ክፍሎችን በሚገባ ለማድረስ አዳጋች ይሆንብናል። ስለዚህ እኔ ከማየው ነገር ወይም ከትዝብት በመነሳት፣ሊሆን ይገባል ብዬ የማስበውን ሀሳብ ላካፍላችሁ። ​ከዚህ በፊትም ለማለት እንደሞከርኩት፣ቤተክርስቲያን አውትሪች (የውጭ ስርጭት) መሠራት ያለበትን አካባቢ እና ኢንሪች (የውስጥ አገልግሎት) መሠራት ያለበትን አካባቢ በጣም ለይታ (demarcate አድርጋ) ልታውቅ ይገባል።ምክንያቱም አንዳንዶቹ አውትሪች የምንሰራባቸው ቦታዎች ኢንሪች መሠራት ያለባቸው እንጂ፣ብዙም ከሩቅ ሌሎች ሰዎች ሄደው አውትሪች መስራት የማያስፈልጋቸው አካባቢዎች ናቸው። ምን ማለቴ ነው ካላችሁኝ፣ሁሌም ቢሆን ውጤታማ ሚሽን (ተልዕኮ) ደቀመዝሙር የሚያፈራ መሆን አለበት ብዬ አምናለሁ፤ልኩም ደግሞ እሱ ነው።ለምሳሌ ለአንዳንድ ሚሽን (ተልዕኮ) በሄድኩባቸው አካባቢዎች ያየሁትን እውነት ልንገራችሁ። በአካባቢው የወንጌል አማኞች በብዛት ኖረው፣ግን የተኙ አይነት ነገር ወይም ሚሽንን በራሳቸው ለመስራት እና አካባቢያቸውን በወንጌል ለማድረስ የማይነሳሱ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ።እንደውም በጣም የገረመኝ፣ አንዳንድ ቦታዎች ቢያንስ በእያንዳንዱ ቤት አንድ አማኝ አለ።ይህም በመሆኑ አንዳንዶች በተደጋጋሚ ከመስማታቸው የተነሳ፣እንደውም መልሰው ከእኛ በላይ ሊነግሩን ይችላሉ። ስለዚህ ወደ እንደዚህ አይነት አካባቢዎች አውትሪች ለመስራት ከመሄድ ይልቅ፣የደቀመዝሙርነት ስራ መስራት፣የሚሽን ስልጠናዎችን መስጠት እና ለዚያ አካባቢ እነርሱ በቂ እንደሆኑ እንዲገነዘቡ ማድረግ ያስፈልጋል።እንዲሁም በከፍተኛ ሁኔታ (Aggressively) ክርስቶስን ከንግግር በላይ በህይወት በመኖር ጭምር የሚመሰክሩ ትውልዶችን ማፍራት በጣም ውጤታማ መንገድ ነው።እኔና እናንተ በተደጋጋሚ ስለሄድን ብቻ ያንን አካባቢ ሙሉ በሙሉ ልንደርስ አንችልም። ሰብከን ያመጣናቸውን ሰዎች ሁሉ ወንጌልን የሚመሰክሩ አቅም ያላቸው ክርስቲያኖች እንዲሆኑ መስራት አለብን።እነርሱ በእጅጉ ተፅዕኖ ማምጣት ይችላሉ፤ከእኛም በተሻለ! ምክንያቱም ቋንቋ፣ባህል እና ብዙ የጋራ የሚያደርጋቸው ነገር ስላለ ለእነርሱ በጣም ቀላል ነው። ስለዚህ በቀጣይነት (Consistently) የሚሰሩ የወንጌል ስርጭት ቡድኖችን ማቋቋም፣እነርሱ ላይ ኢንቨስት ማድረግ (ሀብትና ጊዜ ማፍሰስ)፣ከቻልን በአካባቢው ደቀመዝሙር የማድረግ ስራ የሚሰራ ሰው አስቀምጠን ማለማመድ እና በቋንቋቸው እንዲሰብኩ ማበረታታት በጣም የተሻለ ነው። ​እኛ ደግሞ ወደ አልተደረሱት መሄድ አለብን፤ምክንያቱም ቅድሚያ ላልተደረሱት ነው! ​ይቀጥላል...

❓​መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችሁ እየሠራ መሆኑን በምን ታውቃላችሁ? ​መንፈስ ቅዱስ በኃይል በእናንተ ሕይወት እየሠራ መሆኑን የምታውቁት ትልቁ ነገር፤ የታላቁ ተልእኮ ጉዳይ በሕይወታችሁ፣በፕሮግራማችሁ፣በእናንተ በሆነ ነገር ሁሉ ይሄ ጉዳይ አንገብጋቢና እጅግ በጣም አስቸኳይ መሆኑ ገብቷችሁ፣በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑ የተልእኮ ጉዳይ የሚያስጨንቃችሁ ከሆነ፣መንፈስ ቅዱስ በኃይል በሕይወታችሁ እየሠራ መሆኑን መገንዘብ ትችላላችሁ፤ምክንያቱም የክርስቶስ መንፈስ የሚሲዮን መንፈስ ነውና። ​ስለዚህ የታላቁ ተልእኮ ጉዳይ ቀስ በቀስ ምናልባት በሕይወታችሁ ስፍራ እያጣ የመጣ ከሆነ፣ራሳችሁን መመርመር አለባችሁ። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተቀበልነው፣በእኛ ውስጥ የሚኖረው መንፈስ ተልእኮውን በእናንተ ለመፈጸም ያነሳሳችኋል፤ምክንያቱም የኢየሱስን የመስቀል ሥራ ሳይሳሳት መግለጥ ተግባሩ ነውና! ​«በተጨማሪ “መንፈስ ቅዱስ በኃይል የሚሠራባት ቤተ ክርስቲያን” የሚለውንም፣ ከዚህ በፊት ፖስት የተደረጉትን አንብቡ።»