en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 955
Subscribers
+1424 hours
+247 days
+38330 days
Posts Archive
ለ201ኛ ኮር 54ኛ እና 74ኛ ክ/ጦር ስር ለሚገኙት ለሕግ አካላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ። ============================= ግንቦት28/2018ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሕግና ሥነ-ሥርዓት ጉባኤ፤ ለ201ኛ ኮር እና በሥሩ ለሚገኙ የክፍለ-ጦር እንዲሁም የወረዳ ጊዜያዊ መንግሥት የሕግ አካላት ለተከታታይ 8ቀናት ከግቦት 21_28/2018 ዓ.ም የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል። ይህ ስልጠና በዋናነት በሕግ ግንዛቤና በድርጅታዊ መመሪያዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን የፍሬ ነገር ህግ እና የስነ ሰርዓት ህጎች ነው። የስልጠናው ዋና ዋና ነጥቦችና የተላለፉ መልዕክቶች፦ 1. የኃላፊዎች መልዕክትና ማሳሰቢያ: ጠበቃ ምንያምር አዲስ (የጉባኤው ም/ሰብሳቢ)፦ ስልጠናው ድርጅታዊ መመሪያን መሠረት ያደረገ ከመሆኑም በላይ የተቀላጠፈ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ሰልጣኞችም የተሰጣቸውን ጥራት ያለው እንዲሁም ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን የሚቆጥብ የፍትሕ አገልግሎት የመስጠት ኃላፊነት በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል። አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ (የ201ኛ ኮር ሰብሳቢ) እና አረበኛ ሻለቃ ዘላለም ጥላሁን የኮሩ ወታደራዊ አስተዳደር ፦ ሰልጣኞች በስልጠናው ባገኙት የሕግ ግንዛቤ መሠረት የሕዝባቸውን ማኅበራዊ ፍትሕ ማረጋገጥ እንዳለባቸው አሳስበው፤ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በቅንነትና በታማኝነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 2. የሰልጣኞች ቁርጠኝነት: የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተሻለ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ከፍተኛ የሕግ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም ቀልጣፋና ፈጣን የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የአፋብን ቴዲ ዕዝ 201ኛ ኮር፣ ለሕግ አካላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ። የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሕግና ሥነ-ሥርዓት ጉባኤ፤ ለ201ኛ ኮር እና በሥሩ ለሚገኙ የክፍለ-ጦር እንዲሁም የወረዳ ጊዜያ
+1
የአፋብን ቴዲ ዕዝ 201ኛ ኮር፣ ለሕግ አካላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ። የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሕግና ሥነ-ሥርዓት ጉባኤ፤ ለ201ኛ ኮር እና በሥሩ ለሚገኙ የክፍለ-ጦር እንዲሁም የወረዳ ጊዜያዊ መንግሥት የሕግ አካላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል። ይህ ስልጠና በዋናነት በሕግ ግንዛቤና በድርጅታዊ መመሪያዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። የስልጠናው ዋና ዋና ነጥቦችና የተላለፉ መልዕክቶች፦ 1. የኃላፊዎች መልዕክትና ማሳሰቢያ: ጠበቃ ምንያምር አዲስ (የጉባኤው ም/ሰብሳቢ)፦ ስልጠናው ድርጅታዊ መመሪያን መሠረት ያደረገ ከመሆኑም በላይ የተቀላጠፈ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ሰልጣኞችም የተሰጣቸውን ጥራት ያለው እንዲሁም ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን የሚቆጥብ የፍትሕ አገልግሎት የመስጠት ኃላፊነት በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል። አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ (የ201ኛ ኮር ሰብሳቢ)፦ ሰልጣኞች በስልጠናው ባገኙት የሕግ ግንዛቤ መሠረት የሕዝባቸውን ማኅበራዊ ፍትሕ ማረጋገጥ እንዳለባቸው አሳስበው፤ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በቅንነትና በታማኝነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 2. የሰልጣኞች ቁርጠኝነት: የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተሻለ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ከፍተኛ የሕግ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም ቀልጣፋና ፈጣን የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ምንጭ፦ አፋብን | ቴዎድሮስ ዕዝ ቀን፦ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም

የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ንፁኋን ላይ ያነጣጠረ የመድፍ ድብደባ በመፈፀም የሰው ሕይወት ቀጠፈ! የአገዛዙ ኃይል በሐይቅ ከተማ ሸይኽ ሙሳ ተራራ ላይ ባጠመደው ከባድ መሣሪያ ንፁኋን ላይ ያነጣጠረ ድብደባ በመፈፀም አንዲት የሁለት ልጆች እናትን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገድል መኖሪያ ቤቶችን ማውደሙን መረብ ሚዲያ አረጋግጧል። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ግንቦት 27/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን፡ በሐይቅ ከተማ ዙሪያ ልዩ ስሙ ግም ውሃ ክሬቸር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ ሲሆን፡ ጥቃቱ አገዛዙ ለአማራ ሕዝብ ያለውን ጥላቻና ሃገር አውዳሚነቱን ዳግም ያረገጠ ነው ተብሏል። የአገዛዙ ወታደሮች ንፁኋንን እና መኖሪያ ቤቶችን ኢላማ አድርገው በፈፀሙት በዚህ የመድፍ ድብደባ፡ የሁለት ታዳጊ ልጆች እናት የነበረችው ወይዘሮ ተምሬ ይማም በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሏንም መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል። ወይዘሮ ተምሬ ይማም የተገደለችው ቤት ውስጥ እንዳለች በላዩዋ ላይ ባረፈ የመድፍ ቅምቡላ ነው።በዚህ ጥቃት ሌሎች ንፁኋኖች ክፉኛ መቁሰላቸው ታውቋል። ጥቃቱ ከተፈፀመ በኋላ የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አዛዦችና ካድሬዎች በቦታው ተገኝተው የደረሰውን የንፁኋን እልቂትና ውድመት ከተመለከቱ በኋላ "ፅንፈኛው ፋኖ ነው የመታችሁ" በሚል እየተሳሳቁ አከባቢውን ለቀው ሄደዋል። በተለይ ኮማንደር ሞሃመድ የተባለ የብልፅግና የጦር አዛዥ፡ "ነገሩን አታካብዱ፡ ሞትን እናንተም ቅመሷት" በሚል በተጎጅዎች ላይ ተሳልቆ መሄዱም ተነግሯል። የተፈፀመብን የመድፍ ድብደባ መሆኑንና ፋኖም መድፍ እንደሌለው እያወቅን እንዲሁም ጥቃቱ ከየት በተጠመደ መድፍ እንደተፈፀመብን እያየን እንዴት በዚህ ልክ በሞታችን ላይ ትሳለቁብናላችሁ በሚል በአከባቢው ማሕበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ ተቀስቅሷል። ህዝቡ የጠላትን የውሸት ዳራማ ለይቶ ያወቀ ሲሆን፡ ይህ የጭካኔ ተግባር የብልፅግናውን አገዛዝ መጨረሻ የሚያፋጥን ነው ተብሏል።

በእለታት አንድ ቀን...ብሎ ታሪኩ ይጀምራል አስታወሳችሁ ያችን ቀን ? ጥቁር ያስለበሱን ቀን😥 "ቅዳሴ በኦሮምኛ ካልሆነ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ይመሥረት" ብለው የኦሮሚያን ልዩ ኃይል አስከትለው ቤተ
+2
በእለታት አንድ ቀን...ብሎ ታሪኩ ይጀምራል አስታወሳችሁ ያችን ቀን ? ጥቁር ያስለበሱን ቀን😥 "ቅዳሴ በኦሮምኛ ካልሆነ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ይመሥረት" ብለው የኦሮሚያን ልዩ ኃይል አስከትለው ቤተክርስቲያን በመሳሪያና በወታደር ሊረሽኗት የተነሱ ቀን🤭 አዎ እነዚያ ጳጳሳት ወንበዴውን አስታወሳችሁት አይደል አባ ዲያቢሎስ አሁን ወርሀዊ ደመወዙም ከ500,000 በላይ ሁኖለታል በትረ ስልጣኑንም የቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆን ተረክቧል። አሁን ኦርቶዶክሳውያን ታረዱ አልታረዱ ምን አገባው🤭 ዝም ጭጭ ምሥራቅ አርሲ =የአዳነች አቤቤ የትውልድ ቦታ እሷም ብትሆን የመጣችበትን ረስታ የአዲስ አበባ ከንቲባ ሁናለች🤭 ርዕሰ መስተዳድር = ሽመልስ አብዲሳ የሸኔው መሪ በሉ ፍጠኑ ቶሎ በሉ የሚል ይመስለኛል😥 ለተሰውት ነፍስ ይማር በቁም ለሞቱት ግን ... ሁላችንም ያልታረድነው ምሥራቅ አርሲ ስላልሆንን ብቻ ነው😥

የተከበራችሁና የምትወደዱ የመላው አማራ ህዝብ፣ የፋኖ ታጋዮች እና የትግሉ መሪዎች፤ ​ይህ መልዕክት በአራቱም ማዕዘን ለምትገኝ፣ በየቀኑ ስለ ፖለቲካ ውስብስብነት ሳታውቅ በንፅህና ሰርተህ ለምትኖረው የአማራ ህዝብ፣ እንዲሁም ከታችኛው ሰራዊት እስከ ከፍተኛ አመራሮች ድረስ ላላችሁ የትግሉ ግንባር ቀደም መሪዎች የሚደርስ ታላቅ ህዝባዊ ጥሪ ነው። እያንዳንዱ አማራ የሆነ ወገን ሁሉ ወታደራዊና ወገንተኝነት ግዴታውን ይወጣ ዘንድ፣ በ«ፍኖተተ አማራ» ሚዲያዎች እና በጀግኖች ሰማዕቶቻችን ስም ይህ የአስቸኳይ ጊዜ መልዕክት እንዲደርሳችሁ ሸር አድርጉልኝ። ​የአብይ አህመድ አረመኒያዊ ስርዓህ አማራን ከምድር ገፅ ለማጥፋት፣ ከአማራ ርስት አልፎ የደም መሬት በሆነችው በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በአብይ አህመድ የሚመራው አረመኔያዊ መዋቅር (ከመከላከያ እስከ ሸኔ) ምን ያህል እየሰራ እንደሚገኝ ግልፅ ነው። አብይ አህመድ በኦሮሚያ ምድር ላይ ስልጣን ከያዘበት ሰዓት ጀምሮ በእየቀኑ ንፁሃን አማራዎች እንደ በግ የሚታረዱበት እውነታ ፀሐይ የሞቀው የሁልጊዜም ሃቅ ነው። ​የአማራ ፋኖ ይህንን አረመኔያዊ ስርዓት ለማስወገድ ሌት ከቀን በዱር በገደሉ እየተዋደቀ ቢሆንም፣ አሁን ግን ጠላት አዲስና ረቂቅ የደህንነት ወጥመድ ወደ አማራ ግዛት አስገብቷል። ይህ አረመኒያዊ ስርዓት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር አማካኝነት፣ የኢትዮ ቴሌኮም እና የሳፋሪኮም ሲም ካርዶችን በጥቁር ገበያ (Black Market) በብዛት ወደ መላው የአማራ ግዛት ማለትም ወደ ጎጃም፣ ወሎ፣ ጎንደር እና ሸዋ አስገብቶ እየሸጠ ይገኛል። ​ይህ ማለት ​እነዚህ ወደ አማራ በአራቱም ማዕዘን የሚገቡት ሲም ካርዶች፣ በአብይ አህመድ የደህንነት መዋቅር በሚፈለገው ሰው ስም አስቀድመው የተመዘገቡና የወጡ ሲሆኑ አላማውም ታጋዮችን ለመከታተል፣ መረጃዎችን ለመጥለፍና የመስመር ግንባር ምስጢራትን እንደፈለጉት ለመውሰድ የተዘረጋ የስለላ መረብ ነው። ​ይህንን የተደቀነ አደጋ ለማስወገድ፣ "በግድም በውድም ጥንቃቄ ማድረግ የመጀመሪያው ወታደራዊ ጥበብ ነው!" ይህንን እውነታ እናንተም እኔም እዚሁ ግንባር ላይ የምናውቀው ሃቅ ነው። ​ስለሆነም፣ ማንኛውም የአማራ ልጅና የፋኖ አባል ወደ አማራ ግዛት የሚገቡ አዳዲስ ሲም ካርዶችን በጥልቀት ከሚያውቁት የቅርብ ሰው ወይም ከቤተሰብ ካልሆነ በስተቀር፣ በጥቁር ገበያ ከሚዞሩ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች በፍጹም እንዳይገዛ በውድ ጓዶቼና በሰማዕታት ስም ጥሪዬን አስተላልፋለሁ! ​ለመላው ህዝባችን እና ለምወዳቸው ታጋይ ጓዶቼ ይደርስ ዘንድ፣ ይህንን መረጃ የያዛችሁ የሚዲያ አካላት በሙሉ መልዕክቱን በአስቸኳይ እንድታሰራጩልኝ አደራ እላለሁ። ድል ለታጋዩ እና የአማራ ህዝብ! #Dawit #Amhara ከንጉሶች መንደር

በተደረገ የደፈጣ ውጊያ ራሱን ጥምር ጦር ነኝ ብሎ የሚጠራው የአብይ ወንበር ጠባቂ ኃይል እንደቅጠል ሲረግፍ፣ የራሳቸውን ከፍተኛ አመራር የገደሉ የመከላከያ የኮማንዶ አባላት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝን በይፋ ተቀላቀሉ::     ግንቦት 27/2018 ዓ.ም   የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር የአስቻለው ደሴ ክፍለጦር ሶስተኛ ሻለቃ ቃኝዎች  ከመንዝ ሞላሌ ወደ መሃል ሜዳ ሲንቀሳቀስ በነበረው የ104ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር ላይ ልዩ ስሙ መለያ በተባለ ቦታ  ፋኖዎች ደፈጣ በመጣል የጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል:: የሸዋ መሬት ረመጥ እሳት የሆነበት እራሱን ጥምር ጦር ነኝ ብሎ የሚጠራው የጠላት ኃይል  መለያ ላይ በደረአሰበት ከፍተኛ የደፈጣ ጥቃት ሙት እና ቁስለኛውን ሳያነሳ ወደ መሃል ሜዳ ከተማ እንዳያልፍ በመደረጉ ወደ መጣበት ሞላሌ ከተማ ተመልሷል:: በሌላ ዜና የኮማንዶ የመከላከያዎቹ የሻለቃ አመራሮች የመከላከያውን ከፍተኛ አመራር የሆነውን ባለ ቀይ ቦኔቱን የመቶ አለቃ ማዕረግ ያለውን  እስከወዲያኛው አሰናብተው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አጼ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ብሩኬ ደምሴ ክፍለጦርን በይፋ ተቀላቀሉ። በወረኢሉ ወረዳ መሽጎ የነበረዉ የአገዛዙ የ84ኛ ክፍለ ጦር 4ኛ ሻለቃ አመራሮች እና በፋኖ በኩል የብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር የሻለቃ  አመራሮች  ሚስጥራዊ ግንኙነት ሲያደርጉ ቆይተው በስተመጨረሻ የአገዛዙ ኃይሎች በራሳቸው አመራር ላይ ኦፕሬሺን ሰርተዉ እንዲመጡ  ተነጋግረው መግባባት ላይ ከደረሱ በኋላ በትላንትናዉ ዕለት ከምሺቱ 12:00 ሰአት አካባቢ በወኢሉ ወረዳ 01 ቀበሌ ማርያም ደብረ-ንግስት አካባቢ መቶ አለቃ ታደሰ እምቢአለ  የተባለዉን የራሳቸውን ከፍተኛ  የጦር መሪ ገድለዉ በእጁ ላይ ያለዉን መገናኛ እና ሙሉ ትጥቁን ይዘው እንዲሁም የራሳቸውን በእጃቸው ያለውን ሙሉ ትጥቅ ከነ መሳሪያቸው ይዘው ወደ ብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር በክብር ተቀላቅለዋል::  በክብር የተቀላቀሉትም:- 1. የሻለቃ ዘመቻ መሪ 2. የሻለቃ ሎጄስቲ  ኃላፊ       3. የሻለቃ ኦርዲናንስ ኃላፊ 4. የሻለቃ አልባሳት ኃላፊ በአካባቢው የምትንቀሳቀሰው የብሩኬ ደምሴ ክፍከጦር የፋኖ የሻለቃ አመራራሮች አገዛዙን ከድተው የመጡትን የመከላከያ የኮማንዶ አባላትን በክብር ተቀብለዋቸልዋል።                                                           ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!!       ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! ​የአ.ፋ ብ.ን  ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ!!

ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር በጠላት ላይ የማያዳግም እርምጃ በመዉሰድ ድል ተቀዳጀ! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 23ኛ እና 24ኛ ክፍለጦር በዘመቻ አንሻ ሰይድ የሰሩትን ጀብዱ  በዘመቻው ማግስትም ደግመውታል። 24ኛ ክ/ጦር ከደላንታና ጎሽ ሜዳ በመድፍ፣ ዙ23 እና በበርካታ ሞርተርና ድሽቃ ታጅቦ ወደ አምባሰል ተሬ የመጣውን ጠላት ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11:00 ሰዓት በዘለቀ ውጊያ በደፈጣ፣ በቆረጣና በስቦ መምታት የተካኑት የጀኔራል አሳምነው ፅጌ የመንፈስ ልጆች የመጣውን ወራሪና ጨፍጫፊ የግለሰብ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል። ነበልባሎቹ የ23ኛ ክፍለጦር አናብስት በሌላኛው ግንባር 23ኛ ክ/ጦር  ከተለያዬን ጫፍ ከኩታበር በሁለት መድፍ፣ በዙ-23ና በ120 ሞርተር ታጅቦ የመጣው ወራሪ የ23ኛ ክፍለጦር አባላት  ስቦ ወደገዥ ቦታ በማስገባትና በቆረጣ ክፉኛ የመቱት ሲሆን ሁለት መኪና ሙትና ቁስለኛውን ጭኖ ወደ መጣበት ተመልሷል። በቀሉን ህዝብ ላይ መወጣት ጮቤ የሚስረግጠው አገዛዝ የዘወትር ልማዱን በዘፈቀደ ከባድ መሳሪያ ወደ ንፁሀን  በመተኮስ ሀብትና ንብረት በማውደም አሳይቷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ግንቦት 27/2018ዓ.ም

በተደረገ የደፈጣ ውጊያ ራሱን ጥምር ጦር ነኝ ብሎ የሚጠራው የአብይ ወንበር ጠባቂ ኃይል እንደቅጠል ሲረግፍ፣ የራሳቸውን ከፍተኛ አመራር የገደሉ የመከላከያ የኮማንዶ አባላት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝን በይፋ ተቀላቀሉ:: ግንቦት 27/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር የአስቻለው ደሴ ክፍለጦር ሶስተኛ ሻለቃ ቃኝዎች ከመንዝ ሞላሌ ወደ መሃል ሜዳ ሲንቀሳቀስ በነበረው የ104ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር ላይ ልዩ ስሙ መለያ በተባለ ቦታ ፋኖዎች ደፈጣ በመጣል የጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል:: የሸዋ መሬት ረመጥ እሳት የሆነበት እራሱን ጥምር ጦር ነኝ ብሎ የሚጠራው የጠላት ኃይል መለያ ላይ በደረአሰበት ከፍተኛ የደፈጣ ጥቃት ሙት እና ቁስለኛውን ሳያነሳ ወደ መሃል ሜዳ ከተማ እንዳያልፍ በመደረጉ ወደ መጣበት ሞላሌ ከተማ ተመልሷል:: በሌላ ዜና የኮማንዶ የመከላከያዎቹ የሻለቃ አመራሮች የመከላከያውን ከፍተኛ አመራር የሆነውን ባለ ቀይ ቦኔቱን የመቶ አለቃ ማዕረግ ያለውን እስከወዲያኛው አሰናብተው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አጼ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ብሩኬ ደምሴ ክፍለጦርን በይፋ ተቀላቀሉ። በወረኢሉ ወረዳ መሽጎ የነበረዉ የአገዛዙ የ84ኛ ክፍለ ጦር 4ኛ ሻለቃ አመራሮች እና በፋኖ በኩል የብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር የሻለቃ አመራሮች ሚስጥራዊ ግንኙነት ሲያደርጉ ቆይተው በስተመጨረሻ የአገዛዙ ኃይሎች በራሳቸው አመራር ላይ ኦፕሬሺን ሰርተዉ እንዲመጡ ተነጋግረው መግባባት ላይ ከደረሱ በኋላ በትላንትናዉ ዕለት ከምሺቱ 12:00 ሰአት አካባቢ በወኢሉ ወረዳ 01 ቀበሌ ማርያም ደብረ-ንግስት አካባቢ መቶ አለቃ ታደሰ እምቢአለ የተባለዉን የራሳቸውን ከፍተኛ የጦር መሪ ገድለዉ በእጁ ላይ ያለዉን መገናኛ እና ሙሉ ትጥቁን ይዘው እንዲሁም የራሳቸውን በእጃቸው ያለውን ሙሉ ትጥቅ ከነ መሳሪያቸው ይዘው ወደ ብሩኬ ደምሴ ክፍለጦር በክብር ተቀላቅለዋል:: በክብር የተቀላቀሉትም:- 1. የሻለቃ ዘመቻ መሪ 2. የሻለቃ ሎጄስቲ ኃላፊ 3. የሻለቃ ኦርዲናንስ ኃላፊ 4. የሻለቃ አልባሳት ኃላፊ በአካባቢው የምትንቀሳቀሰው የብሩኬ ደምሴ ክፍከጦር የፋኖ የሻለቃ አመራራሮች አገዛዙን ከድተው የመጡትን የመከላከያ የኮማንዶ አባላትን በክብር ተቀብለዋቸልዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! ​የአ.ፋ ብ.ን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ!!

ህልውናችን የሚረጋገጠው በክንዳችን ነው!!💪💪💪 👉አርሲ የደም ምድር የመላው አማራ ዋስትና አገዛዙን መገርሰስ ብቻና ብቻ ነው!! ህልውናችን የሚረጋገጠው ከዓብይ አህመድ አገዛዝ ፍርስራሽ ስር ነው!! ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ

የአገዛዙ ሰራዊት በየቀኑ እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ነው‼️ ግንቦት 27/2018 ዓ/ም የአገዛዙ 9/ዘጠኝ/ የሰራዊት አባላት 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። አብይ አህመድ እና ጭፍሮቹ የስልጣን ወንበራቸውን ለማስጠበቅ በርካታ የድሃ ልጆችን ወደ ጦርነት እየማገዱ በየቀኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ የብልፅግና ሰራዊት አባላት እንደ ቅጠል በዱር በገደሉጨ እየረገፉ ይገኛሉ። አላማ በሌለው ጦርነት ህይወታቸውን መሠዋት ያልፈለጉ የሠራዉት አባላት ከደቅ ከተማ ከመሸገው ጨፍ*ጫፊ ሰራዊት በመኮብለል ከእነ ሙሉ ትጥቃቸዉ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል። ክፍለጰጦሩን የተቀላቀሉ የአድማ ብተና አባላት :- 1.ይበልጣል መላኩ= አድማ በትን 2.ይመር አያና= አድማ ብተና 3.ሀብቴ ዘሪሁን=አድማ ብተና 4.ፈንታሁን ድረስ=አድማ ብተና 5.አበዉ ደሴ= አድማ ብተና 6.እንዳልክ=መከላከያ-ከፓዊ 7.ወርቁ አዲሱ= አድማ ብተና 8.አለኸኝ ግፉ=አድማ በተና 9.አስር አለቃ ሰለሞን አስማማዉ= መከላከያ _ከጃዊ ፈንድቃ አንድ የአድማ በተናን አባል ብቻዉን 3 ክላሽንኮቭ ይዞ በመዉጣት ከታሪክ ሰሪው የፋኖ ሰራዊት ጋር በመቀላቀል ታሪክ ሰርቷል ሲል የ66ኛ ክፍለ ጦር ከስፍራው ዘግቦታል። አፍብን ቴዎድሮስ ዕዝ የ105ኛ ኮር ሕ/ግንኙነት