en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 936
Subscribers
-324 hours
+3667 days
+38130 days
Posts Archive
የድሮው መከላከያ ሠራዊት መልዕክት እንደወረደ# እኝህ መኮነን #ከንጉስ  ዘመን መጨረሻ እስከ #ኢህአዴግ መጀመሪያወች በተለያዩ ግንባሮች #በጦር መሪነት ያገለገሉ ናቸው። ምክራቸውም:- ""1)ሰራዊቱን #በዲሲፕሊን እና# በአላማ መቅረጽ።ይህም ማለት ሰራዊቱን የአማራ ህዝብ እየደረሰበትን ያለወን ግፍ እና መከራ እንዲሁም  የቀጣይ  የኢትዮጵያን መጻኢ እድል ማስረዳት።ይህ ከሆነ አመራሮች ቢያጠፉ እንኳን ለምን ብሎ እንዲጠይቅ እና መስመሩን እንዳይለቅ ያግዛል ። ለግላቸው ሀብት የሚያካብቱ ሰርጎ ገቦችን ይከላከላል ።ሲያጠፊም ገምግም ያወርዳል። 2)ሰርጎ ገብን ማጽዳት:-ሰርጎ ገብ ማለት አመራር ይሁንም ተዋጊ #የጠላት  ግብ ለማሳካት የተሰለፈ ሲሆን በሰራዊቱ መካከል ክፍፍልና አለመግባባት መፍጠር ለግዳች ዝግጁ እንዳይሆን ማድረግን  ያካትታል ። እነዚህን ቡድኖች ከሀላፊነት ማንሳት ካልተቻለ  አሰራሩ መሠረት እርምጃ መውሰድ ። 3)የውጊያ ግንባሮችን ማስፋት፦ ሀ)ጠላት አንድን አካባቢ (ወረዳ)ሊያጠቃ ሲሞክር ከኋላ ያለ ደጀን ሀይል የጠላትን ማዘዣ  ላይ ጥቃት በመሰንዘር ጠላት ያሰበውን ግዳጀ ሳያሳከ እንዲመለስ ማድረግ።ይህንን የማይፈጽሙ ሻለቃወችን መገምገም ። ድክመታቸውን መለዬት ፤የባንዳነት ነው ወይስ አቅም ማነስ?በሌላኛው ሻለቃ ወይም ክፍለ ጦር  ላይ ጠላት ሲከብ  ለምን ዝም አለ? ለምሳሌ የደጋዳሞቱን ውጊያ ያነሳሉ ። ጠላት ወደ ደጋዳሞት ሲሄድ #አዴት-ፍኖተ ሰላምና #ደብረማርቆስ ላይ ያለን ማዘዣ ጣቢያ መምታት ነበረበት። የአፋብን አመራሮች በችግር ያለባቸውን ክፍለ ጦር እና ሻለቃአመራሮች መገምገም ብሎም እስከ ቅጣት ድረስ  መወሰን አለባቸውይላሉ። ይሄን ሀሳብ አንድ #የተማረከ  የስርዐቱ ወታደር #ከመቶ አለቃ አበበ ሰውመሆን ጋር  ባደረገው የስልክ ልውውጥ ሰምቸዋለሁ ፤መኮነኑ ጋሉኝ ጋር ተመሳሳይ ነው። ለ)ሌላው የጠላትን ሀይል ከክልሉ ውጭ ማለትም# በአፋር -መተሀራ መስመር እና #በአሶሳ_ወለጋ በኩል መወጠር እና ከመሃል ያለውን ሀይል ቀንሶ ወደ እነዚህ ግንባሮች ስለሚበትን  #በሸዋ፤ናዝሬትና ሞጆ  እንዳሁም በጎጃም በኩል ወደ ሰላሌ በኩል ሀይል ለማንቀሳቀስ ይጠቅማል። "" ብለዋል። በዬትኛውም ቀጠና ያለ ፋኖ ይጠቀምበት።

ህዝብ ይፍረድ!! ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም ~~~ በትናትናው ዕለት በተደረገው የመድፍ ጥቃት አንድ እግሯን ያጣችው የ79ኝ አመቷ "እማሆይ ውዴ አስረስ" በዛሬው ዕለት ህይወቷ አልፏል።ስርዓተ ቀብሯም ተፈፅሟል። የደባይ ጠላት ግን ወረዳ ሚኒሻ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆነው አበጀ አከለ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ከየትኖራ ወደ ቁይ ከተማ የመጡ የ602ኛ ኮር አባል ለሆኑት 9 የመድፍ ምድብተኞች፣ 56 የመድፍ አጃቢዎች እና  አመራሮች በ ሔለን ሆቴል ቁርጥና ጃቦ ጋብዞ የተወለደበትን መንደር በገበያ ዕለት ከቀኑ 9:50  በመድፍ ሲያስደበድብ፤ የሚስቱን በትዕግስት እንቻለው ታናሽ እህት ሰራዊት አወቀ እና የአያቷን እማሆይ ውዴ አስረስን ሕይወት ቀጥፎ ቤታቸውን አውድሞታል። በቁይ ከተማ 01 ቀበሌ በሚኒሻ ጽ/ቤቱ ኃላፊ አበጀ አከለ መኗሪያ ቤት ድንኳን ተጥሏል ካድሪውም ተሰብስቧል። ሞትስ ሞት ነው ምን ተብሎ ይለቀሳል ? ሀዘንተኞችንስ በምን ቃል ማጽናናት ይቻላል? የሚሉት ደግሞ የካድሬዎች ነውረኝነትና ግፍ የራሳቸውን ቤተሰብ ሰለባ ማድረጉ ባይጠፋቸውም አማራዊ ስነ - ልቦና የፈተናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች በጉዳዮ ግራ ግራ ተጋብተዋል ። ደብር ከተማ የተወረወረው መድፍ የሚኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊውን የሚስት ቤተሰቦች ህይወት ቀጥፏል መከራውም በቤቱ ገብቷል። በቤቱ አጠገብ ሲጫዎት የነበረው ህፃን አብርሃም ጌታቸው እጁን ቆስሏል። የገጠመን ጠላት ይሕ ነው ። ከስነ-ልቦናችን እጅግ የዘቀጠ ሁኖ ተቸገርን። ፍርዱን ለህዝብ ሰጠናል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

#ደጋዳሞት‼️ በዛሬው ዕለት ከሐሙስ ገቢያ ቀበሌ ወደ ጫትዋርካ ቀበሌ ለአሰሳ ብሎ የላካትን አንድ ሬጅመንት በጠዋቱ "#ፉት" የተደረገች ሲሆን ምርኮ ተገኝቷል‼ 👉 ሰራዊት 👉 ብሬን 👉 ክላሽ 👉
+1
#ደጋዳሞት‼️ በዛሬው ዕለት ከሐሙስ ገቢያ ቀበሌ ወደ ጫትዋርካ ቀበሌ ለአሰሳ ብሎ የላካትን አንድ ሬጅመንት በጠዋቱ "#ፉት" የተደረገች ሲሆን ምርኮ ተገኝቷል‼ 👉 ሰራዊት 👉 ብሬን 👉 ክላሽ 👉 ሽጉጥ 👉 ቦንብ እና የደረት ትጥቅ ገቢ ተደርጓል። ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም 12/11/2018 ዓ.ም

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝ አውራጃ በብልፅግና ጦር ላይ ድንገተኛ ጥቃት መፈጸሙን ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር አስታወቀ!! ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመ
+1
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝ አውራጃ በብልፅግና ጦር ላይ ድንገተኛ ጥቃት መፈጸሙን ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር  አስታወቀ!!      ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር በብልፅግና ጥምር ጦር ላይ በቀን 11/11/2018 ዓ.ም መብረቃዊ እርምጃ ወሰደ።  ኮሩ ከግንባር ባደረሰን መረጃ መሠረት የወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃ ቃኘዎች ከሞላሌ ወደ መሀል ሜዳ በመንቀሳቀስ ላይ በነበረው የብልፅግና ኮማንዶ ጦር ላይ  «አግዎ» በተባለ ስፍራ ሲሆን፣ በተጠና ወታደራዊ ስልት በተመራው ድንገተኛ ወታደራዊ እርምጃ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ የሙትና ቁስለኛ ጉዳት ማድረስ መቻሉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ !!

ከነ መገናኛ ራዲዮው አፈፍ የተደረገ የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት አዛዥ ነው። ወግዲ-ወሎ ቤተ አማራ! (በምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 45ኛ መብረቅ ክፍለጦር አርበኞች ቅጥጥር ስር የዋለ)
ከነ መገናኛ ራዲዮው አፈፍ የተደረገ የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት አዛዥ ነው። ወግዲ-ወሎ ቤተ አማራ! (በምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 45ኛ መብረቅ ክፍለጦር አርበኞች ቅጥጥር ስር የዋለ)

የጀግኖች ምድር ፈርስቤት የአምባገነኑን መዋቅር ሰባብራለች!" ​የአማራ እናት ማኅፀን ዛሬም ፍትሕና ነፃነትን የሚያስከብሩ የቁርጥ ቀን ጀግኖችን ማፍራቷን ቀጥላለች። ​በፈርስቤት ደጋ ዳሞት ወረዳ በተ
+2
የጀግኖች ምድር ፈርስቤት የአምባገነኑን መዋቅር ሰባብራለች!" ​የአማራ እናት ማኅፀን ዛሬም ፍትሕና ነፃነትን የሚያስከብሩ የቁርጥ ቀን ጀግኖችን ማፍራቷን ቀጥላለች። ​በፈርስቤት ደጋ ዳሞት ወረዳ በተደረገው ከፍተኛ ተጋድሎ፣ የአምባገነኑ የአብይ አህመድ ታማኝ አገልጋይና በሕዝባችን ላይ ግፍ ሲፈጽም የነበረው መሐመድ ተሰማ፣ በጀግኖች ክንድ ቅንድብ ቅንድቡን ተመትቶ የሚገባውን ቅጣት አግኝቷል። ​ይህንን ታሪካዊ ድል ተከትሎ፣ የሥርዓቱ የፕሮፓጋንዳ ማሽን የሆነው የፌደራል መከላከያ ሠራዊት የደረሰበትን የሞራልና የወታደራዊ ውድቀት ለመሸፈን የለመደበትን የውሸት ድራማ እየሰራ ይገኛል። የፒክአፕ (ፒጁ) ተሽከርካሪዎችን ፎቶግራፍ በሰው ሰራሽ አስተዋፅኦ (AI) እያቀናበረ በማኅበራዊ ሚዲያ መልቀቁ፣ የሥርዓቱ መፈራረስና የመጨረሻው የውድቀት ምልክት ማሳያ ነው። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምክትል አዛዥ ለወታደራዊ አስተዳደር አርበኛ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው እና የአፋብን ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድርስ ዕዝ ዘመቻ መመሪያ መሪ አርበኛ መቶ አለቃ ሰመሆን ባደረጉት የተቀናጀ ወታደራዊ አመራር፣ የጀግናው ፋኖ ክንድ ምን ያህል በመማረክና ማሸነፍ እንደሚችል በተግባር አሳይተዋል። ​የአማራ ልጅ ፋኖ ያሸንፋል፤ ጀግንነቱን ቃላት አይገልጹትም! ​ድል ለፋኖ! ድል ለአማራ ሕዝብ! Dave Amhara

ተጠናክሮ በቀጠለው ስቦ ማስከዳት ሁለት የአገዛዙ ሰራዊት አመራሮች ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀሉ። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር በሚንቀሳቀስባ
ተጠናክሮ በቀጠለው ስቦ ማስከዳት ሁለት የአገዛዙ ሰራዊት አመራሮች ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀሉ። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናወች ሁለት የአገዛዙ የሰራዊት አመራሮች  ከነ ሙሉ ትጥቃቸው 19ኛ (ተፈራ ማሞ) ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል። መነሻቸውን ከዋግ ህምራ ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ 09  ላልኪው ቀበሌ ከተከማቸው የአገዛዙ ጦር 204ኛ ኮር በኮሌኔል እባቡ ከምትመራው 38ኛ ክፍለጦር 6ኛ እሬጅመንት በመነሳት ፋኖን ተቀላቅለዋል። ፋኖን የተቀላቀሉት የአገዛዙ ሰራዊት አመራሮችም ደሳለኝ ክንዱ የሬጂመንቷ የሰው ሃይል ሌላኛዉ አመራር ብሩክ አባይ የረጅመንቷ ፋይናስ መምሪያ ሃላፊ መሆናቸዉ ታዉቋል። አመራሮቹም ወደ ፋኖ ሲቀላቀሉ ሁለት ጥቁር ክላሽ፣ 480 የክላሽ ተተኳሽ፣አራት ኤፍዋን የእጅ ቦንብ እና ሁለት የደረት ትጥቅ በመያዝ ነዉ የተቀላቀሉት። የአገዛዙ የሰራዊት አመራሮቹም ወደ ፋኖ ሲቀላቀሉ  በክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸዉ ሲሆን በተደረገላቸዉ አቀባበል እና እንክብካቤ በጣም እንደተደሰቱ ተናግረዋል  ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!! ሐምሌ 12/11/2018 ዓ'ም

​በሸዋ ጠቅላይ ግዛት 5 የጉድኝት ክላስተሮችን ያሳተፈ ታሪካዊ መድረክ ተካሄደ! ​በቀን 11/11/2018 ዓ.ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ በተሬ ክላስተር በተደረገው ታሪካዊ መድረክ ላይ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአባት አርበኞች መምሪያ አመራሮች፣ በቀጠናው የሚገኙ የፖለቲካ መምሪያ አስተባባሪዎች እንዲሁም የኮር እና ከ5ቱም ክላስተሮች የተውጣጡ አመራሮች በተገኙበት የትግሉን እድገት የሚመጥን የ6 ወር የሥራ ሪፖርትና ውይይት ተደርጓል። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኙትን አምስት (5) የጉድኝት ክላስተሮች፣ እነሱም፦ 1.የተሬ ክላስተር 2.መዘዞ ክላስተር 3.የባሽ ክላስተር 4.የኤፍራታና ግድም ክላስተር 5.የአሎሎ ክላስተር ​የእነዚህን ክላስተሮች አስተዳደሮች ወደ አንድ መድረክ በማምጣት የ6 ወር የሥራ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ተደርጓል። በዚህ ውይይት ላይ በክላስተሮቹ የተሰሩ ስራዎች ቀርበው፤ በሕዝብ አስተዳደር፣ በፍትህ፣ በሰላምና ደህንነት እንዲሁም በአባት አርበኛ ታጋዮች መጠርነፍና ማደራጀት ዙሪያ ውጤታማ ስራዎች እንደተከናወኑ ተገልጿል። በተጨማሪም በየክላስተሮቹ የነበሩ የአሰራር እቅፋቶችና የሕዝብ ጥያቄዎች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ​በሁሉም ወገን ከሕዝብና ከመሪዎቹ ለተነሱት ጥያቄዎች የአባት አርበኞች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ማሞ ማስረሻ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ዮናስ ባባው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመድረኩ የሙሐመድ ቢሆነኝ ኮር ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ ምናሉ ከበደ በመገኘት በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ የሕዝብ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥቷል። ​በመጨረሻም፣ የፖለቲካ መምሪያ የቀጠናው አስተባባሪዎች መድረኩን በመምራትና በማስተባበር፣ ለቀጣይ የትግል እንቅስቃሴ አቅጣጫ በመስጠት እንዲሁም ለአምስቱ ክላስተሮች መልካም አፈፃፀምና የትግል ንቅናቄን በበሰለ መልኩ በመምራታቸው የዕውቅና ምስክር ወረቀት እና የአርበኞች ምስል በሽልማት መልክ ተበርክቶላቸው መድረኩ በስኬት ተጠናቋል። ​ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ታሪካችን ረጅም ነው፣ ህመማችንም እንዲሁ፣" ሰንደቋን በደረታችን ላይ አጥብቀን የአማራ ህዝብ ነፃ የምናወጣበት የድል ቀናት ከፊታችን ናት። "ነገር ግን አማራነት ኢትዮጵያን የመሸከም እንጂ የማውረድ ትከሻ የለውም። ለዚህች ሀገር ማስተማር ማለት ከራስ በፊት ሀገርን ማስቀደም፣ ፍቅርን በትዕግስት መዝራት፣ እና ነገን በብርሃን መቃኘት ማለት ነው። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ወታደራዊ እቅድና እስትራቴጂ ዋና መምሪያ መቶ አለቃ ልመነው ሻወል ደመቀ Dave Amhara

በሸዋ በተፈጠረው የሁለቱ እዞች አለመስማማት ውስጡ ያርር ነበር። ትግሉ እንዳይቀጭጭ በማሰብ፣ ህይወቱን ለአደጋ አጋልጦ ለ15 ቀናት የፈጀ ውይይት ቢያደርግም፣ ነገሮች ሳይሳኩ ቀርተው ለስምንት ወራት በእስራት እንዲቆይ ተደረገ። ​ከተፈታ በኋላ ግን "ይህ ግፍ ደረሰብኝ" ብሎ በሚዲያ አልጮኸም። ይልቁንም የሸዋን አንድነት ለማምጣት ድጋሚ በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀመጠ። የአስራት ወልደየስን ፅናት፣ የአክሊሉ ሀብተወልድን ዲፕሎማሲ፣ የእሸቴ ሞገስን የትግል አርማነት አንግቦ፣ ለ3 ዓመታት እርስ በርሳቸው ይቃረኑ የነበሩትን የታሪክ ልጆች በአንድ ማዕድ አቀረባቸው። የሸዋን ታሪክ በወርቅ ቀለም አደሰው። ​በአሁኑ ሰዓት እርሱ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ወታደራዊ እቅድና እስትራቴጂ ዋና መምሪያ ሆኖ በፅናት እያገለገለ ይገኛል።

ምንጃር ላይ የበቀለውን ሀሞተ መራሩን ኮማንዶ ላስተዋውቃችሁ!! ነገሩ እንዲህ ነው ​በ1983 ዓ.ም የመስከረም ወር መባቻ ላይ፣ የምንጃር ሸንኮራ ሰማይ የክረምቱን የጭጋግ ካባ አውልቆ በወገግታ ተሞልቶ ነበር። አርባራቱ ታቦታት የጥምቀትን እድር አድረው ወደ መንበራቸው በሚመለሱባት፣ የእምነትና የፅናት መናገሻ በሆነችው በዚያች ታሪካዊት የገጠር ከተማ እራንቡቲ አንድ ጨቅላ ህፃን የዚህችን ምድር አየር ለመጀመሪያ ጊዜ ተነፈሰ። ​ወላጅ እናቱ፣ ይህ ቀይ ደማም ልጇ ወደፊት እስከ ሞት ድረስ ለህዝቡ ታማኝና እውነተኛ መከታ እንደሚሆን በልቧ የተገለጠላት ይመስል፣ አይኖቹን እያየች ስሙን "ልመንህ ሻወል ደመቀ" ስትል ሰየመችው። ለአለም ያስተዋወቀችው በልመና ሳይሆን፣ በፅኑ እምነት ነበር። ​እድሜው ለትምህርት ደርሶ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት፣ በአካባቢው የተለጠፈውን የመከላከያ ውትድርና ምልመላ ማስታወቂያ ተመለከተ። ያኔ በብላቴናው ልብ ውስጥ የአገር ፍቅር እሳት ተቀጣጠለ። ለመመዝገብ ቢሮው ድረስ ቢገሰግስም፣ ፈታኞቹ እድሜው ገና እንዳልደረሰ ነገሩት። ነገር ግን ወታደር መሆን ህልሙ ብቻ ሳይሆን እጣ-ፈንታው በሆነው በዚህ ህልመኛ ወጣት ፊት የሚቆም ምድራዊ ሃይል አልነበረም። ታሪኩን አዛብቶ፣ ፅናቱን አሳይቶ የሁርሶ ኮንቲኔጀንት ማሰልጠኛ ተቋም በርን ረገጠ። ለስምንት ወራት የሚፈጀውን፣ ብረትን እንደ ሰም የሚያቀልጠውን ከባድ ስልጠና በብቃት አጠናቆ መሰረታዊ ወታደር ሆነ። ​መቶ አለቃ ​ልመንህ ሻወል ደመቀ በሰራዊቱ ውስጥ ባሳየው እፁብ ድንቅ ብቃትና ታማኝነት፣ በልጅነቱ አቋርጦት የነበረውን ትምህርት። እንዲቀጥል እድል ተሰጠው። በ2007 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናውን በስኬት አጠናቆ፣ በ2010 ዓ.ም በወታደራዊ ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪውን በከፍተኛ ማዕረግ ተመረቀ። ​ሁሌም ራሱን ለማነፅ የሚተጋው ይሄው ታላቅ ወታደር፣ በ2012 ዓ.ም አለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ጦርን ተቀላቅሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ጁባ አቀና። በጁባ ለሁለት ዓመታት በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ሳለ ግን፣ በሀገሩ ምድር የጥፋት ደመና አጠላ። በስተሰሜን በኩል የጦርነት እሳት ተቀሰቀሰ። ጦርነቱ የአማራንና የአፋርን ህዝብ እንደ ቅጠል የሚያረግፍበት ያ ክፉ ቀን በጠባብ ሴራ ተተብትቦ መጣ። ​መንግስት አጣብቂኝ ውስጥ ሲገባ፣ የሰላም አስከባሪውን ጦር ያለምንም እረፍት ከጁባ አለም አቀፍ ኤርፖርት በቀጥታ ወደ ራያ ግንባር አዘመተው። በዚያ የወንድም እልቂት በበዛበት ምድር ላይ፣ መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ ያላሰበውንና ያልጠበቀውን ክህደት በዓይኑ አየ። አብረውት ያደጉ፣ የመከላከያ ልብስ የለበሱ ከፍተኛ ጀነራሎችና ሹማምንቶች በውስጣቸው በበቀለው የዘር ጥላቻ ተገፋፍተው፣ የገዛ ወታደሮቻቸውንና ወንድሞቹን በሴራ ሲያስገድሏቸው በብረቱ ዓይኑ ተመለከተ። ​የጦርነቱ ማዕበል ወደ ወሎ አንባሰል ተራራዎች ሲገፋ፣ ገንፎ ጨፌ በተባለ ቦታ ላይ የጠላት ጥይት አገኘውና ቆሰለ። በዚያች ሰዓት አካሉ ብቻ ሳይሆን ነፍሱም ቆሰለች። ወጣትነቱን፣ ህይወቱንና የውትድርና ስነ-ምግባሩን የሰጠለት "ኢትዮጵያዊነት" እና "ህዝባዊነት" በሴረኞች እጅ አፈር ድሚ ሲበላ ሲያይ ውስጡ ተሰበረ። ልፋቱ ሁሉ መና የቀረ መሰለው፤ አፈረ፣ ተሸማቀቀ፣ በከንቱ በፈሰሰው እድሜው አዘነ። ስነ-አእምሮው በሃዘን ታወከ። ነገር ግን ይሄ የቀይ ዳማው መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ በቀላሉ የጠላቶቹ መጫወጫ ሊሆን አልፈቀደም። ​ከቀሩት የሰላም አስከባሪ ወንድሞቹ ጋር በምስጢር ተመካከረ። ከሸዋና ከወሎ ነፍጠኛ ገበሬዎች፣ ከፋኖና ከአባት አርበኞች፣ እንዲሁም ከአማራ ልዩ ሃይል ጋር ጥምረት ፈጥሮ የጠላትን ጦር በሸዋ ተራሮች ላይ ሙሉ በሙሉ እንዲቀበር አደረገ። ያኔ ነበር በድጋሚ በስናይፐር ጥይት ተመትቶ የቆሰለው። ​ከዛም ​ከጦርነቱ ማብቂያ በኋላ መንግስት የኦነግን ጦር እንዲወጋለት ወደ ወለጋ አንገር ጉትን ላከው። ነገር ግን በወለጋ ምድር ያየው ትዕይንት ከቀደመው የከፋ ሆነ።የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ከመከላከያው ጋር እየተመሳጠረ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚፈፅመውን የዘር ማጥፋት በተመለከተ ጊዜ፣ ልቡ በሃዘን ደማ። መቶ አለቃ ​ልመንህ ሻወል ደመቀ ያንን አስከፊ ቀን ሁሌም በምሬት ያስታውሰዋል፦ አንድ የአማራ አርሶ አደር ገበሬን ገድለው፣ አንገቱንና ብልቱን ቆርጠው በውጪው የበራፍ አጥር ላይ በእንጨት ሰክተውት ተመለከትኩ። ታዲያ ያኔ አንድ ነገር ትዝ አለኝ... እኔም እኮ የተወለድኩበት ዘር፣ ወገን አለኝ! ​የቆሰለለት አላማ ግቡን አለመምታቱን ያረጋገጠው መቶ አለቃው፣ ለአስራ አምስት ዓመታት የለፋበትን የጦር ሜዳ ዩኒፎርም በቦርድ ለማውረድ ወሰነ። ወደ አዲስ አበባ ሄዶ ሁለት ጊዜ የደረሰበትን የመቁሰል አደጋ በመጥቀስ ከሰራዊቱ ለመልቀቅ አመለከተ። ጀነራሎቹ ግን ሊያጡት ስላልፈለጉ፣ "በዚህ ሰዓት አንተን አንለቅም፤ ጀነራል ሆነህ መከላከያውን የምትመራበት ቀን ደርሷል" እያሉ በሽልንግ ሊያታልሉት ሞከሩ። መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ ግን በቁርጠኝነት ሞገታቸው፦ "እኔ የጠየቅኩት መብቴን ነው፣ ሀኪሞች ቦርድ መውጣት እንዳለብኝ አረጋግጠዋል!" አላቸው። በመጨረሻም በመደንገጥ መብቱን አስከበሩለትና ወደ ትውልድ ቀየው ወደ ምንጃር ሸንኮራ ተመለሰ።፣ ​ የሪንጀሩ ቃልኪዳንና የሸዋ አንድነት ​ወደ ትውልድ መንደሩ የተመለሰው መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ፣ ገና የቤተሰቦቹን ናፍቆት እንኳን ሳይወጣ የጦርነት ነጋሪት ተጎሰመ። የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ከኤጄሬ ከተማ ተነስቶ ምንጃር ሸንኮራን በመውረር፣ ሳማ ሰንበት በተባለ ቦታ ላይ ጥቃት መፈፀም ጀመረ። ​የቀዩ ኮማንዶ ደም ፈላ። የመከላከያ ሬንጀር ልብሱን እንኳን ሳይቀይር፣ ስናይፐሩን አንግቦ ገሰገሰ። የሸንኮራን ወጣቶች በአጭር ጊዜ አደራጅቶ፣ የኤጄሬን ከተማ በቆረጣ በመግባት የጠላትን ግንባር ግንባሩን በጥይት ይነድለው ጀመር። የወራሪውን ጦር መመለስ ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ የኮማንዶ ሃይሎችን አረገፋቸው። ​ይህንን የተመለከቱ ነባር የፋኖ ታጋዮች በአድናቆት እየተገረሙ፣ "ይህ ለምድር የከበደ እግረ-ዦቢራ ከየት የመጣ የእግዜር ስጦታ ነው?" አሉ። በዚያች ዕለት መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ ቤቱን፣ ኑሮውንና የወደፊት እጣ ፈንታውን ለጫካ ሰጠ። ስሙም ከመቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ ወደ "ፋኖ መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ" ተቀየረ። ​በፋኖ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ኃላፊነትን በመውሰድ በርካታ የጦር ግንባሮችን መራ። ከብዙዎቹ ገድሎቹ መካከል ሁለቱ ግን በታሪክ ማህደር የማይረሱ ሆኑ፦ ​የውርጌቻው ውጊያ፦ የመንግስት ጦር በመካናይዝድ ታጅቦ በከፈተው ከባድ ወረራ ላይ፣ መቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ ከነበልባል ክፍለ-ጦር አንዷን ሺ አለቃ በመያዝ የሰነዘረው የመልሶ ማጥቃት እርምጃ ጠላትን እስከ አዳማ (ናዝሬት) ድረስ አባሮ እንደ ቡሄ ግርፊያ የቀጣበት ዕለት ነበር። ​የጥር 10 የጉራንባ ውጊያ፦ የከተራና የጥምቀትን በዓል ለማስተጓጎል የመጣውን ወራሪ ሃይል፣ ከአምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁንና ከይርጋ ወንዳለ ጋር በመሆን በ3 ቀን አውደ ውጊያ ድባቅ የመቱበት ገድል ነው። ​ታዲያ የመቶ አለቃ ልመንህ ሻወል ደመቀ ትልቁ ገድል በጦር ሜዳ ብቻ አልነበረም።

ሰበር!! በምዕራብ አማራ ቀጠና ደባይ ጥላት ግን ወረዳ በደረሰ የመድፍ ጥቃት በመኗሪያ ቤት የነበሩ ንፁሐን ሕይወታቸውን አጡ። ቅዳሜ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም =========================
+4
ሰበር!! በምዕራብ አማራ ቀጠና ደባይ ጥላት ግን ወረዳ በደረሰ የመድፍ ጥቃት በመኗሪያ ቤት የነበሩ ንፁሐን ሕይወታቸውን አጡ። ቅዳሜ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም ================================== በደባይ ጠላት ግን ወረዳ ደብረ እየሱስ ታዳጊ ከተማ በደረሰ የመድፍ ድብደባ ሰራዊት በውቀት የተባለችው የ19 ዓመት ወጣት ህይወቷ ሲያልፍ ታናሽ ወንድሟ አማን በውቀት ከባድ ቁስለኛ ሁኗል። እናታቸው ወ/ሮ እታገኝ ገደፋው እና ጎረቢታቸው የ79 አመቷ መነኩሴ እንዲሁ ከባድ ቁስለኛ ሲሆኑ የ13 ዓመቱ ታዳጊ አብርሃም ጌታቸው በጨዋታ ላይ እያለ ቆስሎ ክሊኒክ ገብቷል። በዕለተ ቅዳሜ ከ10 ቀበሌ በላይ ህዝብ በአንድ አደባባይ በሚውልበት የገበያ ቀን በደብር ከተማ የመከላከያ የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር በደባይ ጥላት ግን ወረዳ በህዝብ ላይ በከፈተው ተኩስ የንፁሐንን ህይወት ቀጥፏል። ከቁይ ከተማ  ደብረ እየሱስ ታዳጊ ከተማ የንፁሐን መኖሪያ በሆኑ መንደሮች ላይ በአስወነጨፈው መድፍ መኗሪያ ቤቶች ወድመዋል። አዲስ ትውልድ ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

አንድ ሻለቃ በአራት ጀነራሎችና በሰባት ኮሎኔሎች ላይ!! "የጎልያድና የዳዊት ትንቅንቅ" ​የጀግንነት መፍለቂያ በሆነችው በደጋ ዳሞት ምድር፣ ዛሬ ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ነው! የአራት ኪ
አንድ ሻለቃ በአራት ጀነራሎችና በሰባት ኮሎኔሎች ላይ!! "የጎልያድና የዳዊት ትንቅንቅ" ​የጀግንነት መፍለቂያ በሆነችው በደጋ ዳሞት ምድር፣ ዛሬ ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ነው! የአራት ኪሎው አገዛዝ ያለ የሌለ ኃይሉን አሰባስቦ፣ በርካታ መድፎችንና ከባድ መሣሪያዎችን አስታጥቆ የላካቸውን 4 ጀነራሎች እና 7 ኮሎኔሎችን (በአጠቃላይ 11 የጦር መኮንኖችን) የአማራ ፋኖ ኩራት በሆነው በጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የሚመራው የቴዎድሮስ ዕዝ ጀግኖች እያንቀጠቀጧቸው ይገኛል። ​የጦር ሳይንስንና መደበኛ ውትድርናን ብቻ ሳይሆን፣ የሕዝብን እውነተኛ የነጻነት ስሜትና ወኔ አንግቦ የተነሳው ሻለቃ ዝናቡ፣ በደጋ ዳሞት ቆራጥ ሕዝብ ደጀንነት የታገዘ ተአምረኛ አመራሩን በተግባር እያሳየ ነው። አራት ጀነራልና ሰባት ኮሎኔል ተደምረው በአንድ የፋኖ መሪ ፊት መቆም አቅቷቸው ሲጨነቁና ሲጠበቡ ማየት፣ የትግሉን የሞራል የበላይነትና የፋኖን ድል አድራጊነት በግልጽ ያሳያል። የደጋ ዳሞት ምድር ዛሬም ነገም የጀግኖች መቃብር እንጂ የፈሪዎች መፈንጫ አትሆንም፤ የጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ክንድ ነገም ታሪክ መስራቱን ይቀጥላል!! ​ድል ለአማራ ፋኖ! ክብር ለደጋ ዳሞት ጀግና ሕዝብና ለሻለቃ ዝናቡ ልንገረው!!

ሰበር  ዜና❗❗ 7/ለ70 ክፍለ ጦር  በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የአገዛዙን ታማኝ መረጃ አቀባይ  እስከወዲያኛው ማሰናበቱን አስታወቀ!!          ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7ለ70 ክፍለ የኦፕሬሽን  ስራ በመስራት የጠላትን የመረጃ መረብ በመበጣጠስ ላይ ይገኛል።ክፍለ ጦሩ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ኤፍራታና ግድም ክላስተር አላላ ከተማ ላይ በልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙ መረጃ የነበረ ተከፋይን ማለትም  ''ሰይዶ'' በሚል ስም የሚታወቀው ባንዳ ላይ  እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ግለሰቡ በተደጋጋሚ በክ/ጦሩ ማስጠንቀቂያና ምክር ቢሰጠውም ሊሰማ ባለመቻሉ፣ በናሁሰናይ ሻለቃ የቅኝት ቡድን አማካኝነት ዘልቆ በመግባት  እስከወዲያኛው ሊሰናበት እንደቻለ የክ/ጦሩ ሪፖርተር ከግንባር በላከው መረጃ አመልክቷል። አክለውም የአገዛዙ አስገዳይ ተከፋይ ባንዳ ላይ እንድህ አይነት የማያዳግሙ እርምጃዎች ተጠናክረው ስለሚቀጥሉ ሌሎች ተላላኪዎች ከዚህ ተማሩ ብሏል ። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ