ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Open in Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Show more2 808
Subscribers
+18124 hours
+2277 days
+23430 days
Posts Archive
የአርበኞች ጦር በተሬ ክላስተር ወደ ዘመናዊ የክፍለ ጦር አደረጃጀት እየተሸጋገረ ነው
ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ተሬ ክላስተር የአርበኞች ጦር ሠራዊቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጠንካራና ዘመናዊ አደረጃጀት እየሠራ እንደሚገኝ የዕዙ የስምሪት አመራሮች ገለጹ።
የአማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለማስከበርና የትውልዱን ነፃነት ለማረጋገጥ አደረጃጀቱን ማዘመን፣ ጠንካራ ተቋም መፍጠርና ቆራጥ አመራር መሰየም ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማጠናከር ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል በብርጌድ ደረጃ ተደራጅቶ ሲንቀሳቀስ የቆየው የተሬ ሕዝብ ድሉን ለማፋጠንና ቀጠናውን ለማስተሳሰር ብርጌዶችን ወደ አርበኞች ክፍለ ጦር በማዋሃድ ለመዋቀር ተዘጋጅቷል። በቀጠናው ታላላቅ ወታደራዊ ጀብዶችን ሲያስመዘግቡ የቆዩት ብርጌዶች ጥልቅ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግምገማ በማድረግ ውስጣዊ አንድነታቸውን በመፈተሽና ክፍተቶችን በመሙላት አወቃቀራቸውን በማዘመን ላይ ናቸው።
በዚህ የግንባታ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የድርጅት አመራሮች፣የቀጣናው ስምሪት አካል የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ የአፋብን ተቀዳሚ ም/ል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ ድርጅቱ ወጥ አሰራሮችን በመተግበር ለማይቀረው የነፃነት ጉዞ መዋቅሮቹን እያጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።በዚህም ሁሉም በየደረጃው ለትግሉ የሚጠበቅበትን አበርክቶ በማድረግ ሁልጊዜም ንቁና ቆራጥ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።
በዚህም መሐመድ ስንዴው ብርጌድ እና ታደለ ወርቁ ብርጌድ አመራሮቻቸውን በማዋሃድ አንድ ታላቅ ክፍለ ጦር እንዲመሰርቱ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ለአዲሱ አርበኞች ክፍለ ጦር በውጊያ ሜዳ ብቃታቸው የተመሰከረላቸው ቆራጥ መሪዎች የተሰየሙ ሲሆን፣ በተደራጀ ሁኔታ ወደ ሥራ በመግባት የሕዝቡን ሰቆቃ ለመታደግ መዘጋጀታቸው ተገልጿል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ፋሽስቱ የአብይ አህመድ ስርዓት ያሰማራት የስለላ መረጃ በቁጥጥር ዋለች!!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ምንልክ 1ኛ ዕዝ 101ኛ ኮር 15ኛ ክፍለጦር ባደረገው ጥብቅ ክትትል አገዛዙ በስለላ ስራ አሰልጥኖ ያሰማራትን መረጃ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል።
በደቡብ ወሎ ዞን ኩታ በር ወረዳ 014 ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሪት ከድጃ መሀመድ ካሴ የተባለችው ግለሰብ ከፋሽስቱ የብልፅግና ስርዓት በተሰጣት ስምሪት የስለላ ስራ ለመስራት በእንቅስቃሴ ላይ እያለች በ101ኛ ኮር 15ኛ ክፍለ ጦር ቃኞች ተለያየን በተባለ ቦታ በቁጥጥር መዋል ችሏልች።
ጉልበቱን ምላሱ ላይ ብቻ ያደረገው የፋሽሽቱ ስርዓት ሽንፈቱን ላለመቀበል ሲል በተለያየ መንገድ እየተጋጋጠ ቢገኝም ከክንደ ነበልባሎቹ የ101ኛ አናብስቶች ማምለጥ አልቻለም።
ግለሰቧ ከ45ኛ ክፍለ ጦር ጋር ግሸን ተቀምጣ የተለያዩ ስራዎችንም ትሰራ እንደነበር ማረጋገጥ ችለናል ሲል 101ኛ ኮር ሚድያና ኮሙኒኬሽን ክፍል መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ጳጉሜ 1 /2018 ዓ.ም
6 የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚኒሻ አባላት በ64ኛ ክ/ጦር በቁጥጥር ስር ሲውሉ 2 የሚኒሻ አባላት ክ/ጦሩን ተቀላቅሏል።
64ኛ ክ/ጦር ጶጉሜ 01/2018 ዓ.ም
~~~~~~
በሸበል በረንታ ወረዳ የሚገኘው አገዛዝ ወደ ትግራይ ክልል ለግዳጅ ዝግጁ እንዲሆኑ ትዛዝ ማስተላለፉን ተከትሎ የሚሊሻ አባላቱ እየተተራመሰ እና እየፈራርሰ ይገኛል።
የአማራ ህዝብን ለአብይ አህመድ አገዛዝ አሳልፈው የሰጡት የሚኒሻ ተቋም አባል የነበሩ ከአገዛዙ ኃይሎች ጋር ከፍተኛ ውዝግብ ላይ የነበሩ ሆድአደር የሚኒሻ አባላት ወደ ትግራይ ክልል አንዘምትም የትግራይ ህዝብ ወንድማችን ነው የአገዛዙን ትዛዝ አንቀበልም በማለት በሸበል በረንታ መርገጭ ንዑስ ወረዳ ሌዲ እና አካባቢው ቀበሌ እያሱ ጎጥ ተደብቀው የነበሩ ቢሆንም በአካባቢው ማህበረሰብ ጥቆማ መሰረት ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም በአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በቁጥጥስ ስር ከዋሉት የሚኒሻ አባላት ውስጥ:-
1ኛ.መኳንት ወረቅነህ ሚኒሻ
2ኛ.አባይ እሸቱ ሚኒሻ
3ኛ.ባንታምላክ አያሌው ሚኒሻ
4ኛ.ገበየሁ ድረስ ሚኒሻ
5ኛ.አብዩ እያሱ ሚኒሻ
6ኛ.ቢረስ ውዱ ሚኒሻ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ቢወጣ ወርቁ ሚኒሻ የዕድውኃ ወረዳ እነቦርኪት ቀበሌ እና አዳርጋቸው ቦራ እነማይ ወረዳ አንስላል ቀበሌ ተወላጅ የሆኑ አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ጶጉሜ 01/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርና የካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በመርሀቤቴ አውራጃ በቅንጅት በነበረ ውጊያ ድል መቀዳጀታቸው ተገለፀ!!
ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በተደረገ የጨበጣ ውጊያ በ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ፣ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለጦርና ካራ ምሽግ አርበኞች ጦር ድል መቀዳጀታቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ።
ቅዳሜ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡30 ጀምሮ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከሚዳ ሬማ ወረዳ በመነሳት በሶስት አቅጣጫዎች ማለትም በሰንቀሌ ቆፌ፣ በቃራመጅት ሸንኮራ እና በሬማ ከተማ ቢራባ መስመሮች ወደ ፋኖ ቀጠና በማንቀሳቀስ ከበባ ለመፈፀም ሙከራ አድርጎ በነበረ ጠላት ላይ መሆኑን ገልጿል።
ነገር ግን በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሃዶች እና በካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በተደረገ የተቀናጀ የጨበጣ አፀፋዊ ውጊያ ''ወደይላ'' በተባለው ልዩ ቦታ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ ታላቅ ድል መቀዳጀት እደቻሉ አብራርቷል።
እስከ ቀኑ 8:00 ድረስ በቆየው በዚህ አውደ ውጊያ፡ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥን ጨምሮ ከስምንት(8) የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ጋር የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ መቁሰላቸውን አክሏል።
የቆሰሉት የጠላት አባላት በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ፣ በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ካምፕ እና በአለም ከተማ አናት ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙ አረጋግጦ ተጠቅሶ፡ የሟችና የቁስለኛ ትክክለኛ ማንነት በመረጃ አጣርተን የምንመለስ ይሆናል ሲል ገልጿል።
በዚሕ የአፀፋ ውጊያ ሽንፈት የተበሳጨው ጠላት የቃራ መጅት ነዋሪ የሆኑትን አርሶ አደር አቶ አቡሽ ሰጠኸኝን በጥይት ደብድቦ መግደሉ ሲረጋገጥ፤ ከ13 በላይ የሚሆኑ ወጣቶችን በአስገዳጅ ሁኔታ አፍኖ በመውሰድ "የተማረኩ ፋኖዎች ናቸው" በሚል ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተረጋግጧል ብሏል።
በተጨማሪም የአርሶ አደሮችን የሶላር ንብረቶች ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶች በመዝረፍ ሙትና ቁስለኞቹን በሸራ ሸፍነው ወደ ሬማ ከተማ ከነ ሽንፈቱ መመለሱን ጠቅሷል።
👉 በመጨረሻም፣ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች ከግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እራሳቸውን እንዲጠብቁ እያሳሰበ፣ አቅምና ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ትግሉን በመቀላቀል ራሳቸውንና ህዝባቸውን እንዲታደጉ ጥሪ አስተላልፏል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አዲስ አመትን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማክበር #የወሰኑ የአምባገነኑ ስርዓት ጠባቂ ሰራዊቶች አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝን ተቀላቀሉ።
=====================
ነሐሴ : 30/2018 ዓ/ም
ከሞት ተርፈው ደጋ ዳሞት ከገቡት የአገዛዙ ሃይል በእየቀኑ እየከዳ ይገኛል።
ከነዚህም መካከል :-
1ኛ. አብዲ ምስጋናው --ጥቁር ክላሸንኮቭ
2ኛ ሳሊሞ ምሀመድ-- ጥቁር ክላሽንኮቭ
3ኛ. አብዱ ሰይድ-- ጥቁር ክላሽንኮቭ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክ/ጦር ደጋዳሞት ሻለቃን የተቀላቀሉ ሲሆን፤ በሻለቃ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
አፋብን|ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ
💢ሁለት ቲም መሪወችን ጨምሮ 3 የመከላከያ አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ❗️
የስርዓቱን መውደቅ 11ኛው ሰዓት ላይ መሆኑን ቀድመው ያወቁ የአገዛዙ ጦር ሰራዊት አባላት በየቀኑ እየፈረሱ ወደ ፋኖ መቀላቀላቸውን በቀጠሉበት በዚህ ሰዓት የሰራዊቱ የተዋረድ አመራሮችና አባላት ከስምሪት ቀጠናቸው ከነሙሉ ትጥቃቸው በቡድን እና በተናጥል በመውጣት አንድያ ህይወታቸው እያተረፉ ይገኛል።
በሰከላ ከተማ ግሽ ተራራ ላይ ከሰፈረው የምስራቅ ዕዝ 73ተኛ ክፍለ ጦር 3ኛ ሬጂመንት ፣ 2ኛ ሻምበል ፣ 1ኛ ጋንታ ውስጥ የቆዩት የቲም መሪ ፣ ምክትል ቲም መሪ እና አንድ አባል በመሆን ዛሬ ነሃሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 2(ሁለት) ጥቁር ክላሽ እና አንድ(1) ባለሁለት እግር ክላሽ ፣ ከ600 መቶ ተተኳሽ ጋር በመያዝ ከነሙሉ ትጥቃቸው በመውጣት የፋኖ ሰራዊትን ተቀላቅለዋል።
ዛሬ ነሃሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰከላ ግሽ ተራራ ላይ ከሰፈረው የአገዛዙ ጦር መካከል ወደ ህዝባችን አንተኩስም በማለት ፋኖን በመቀላቀል ህይወታቸውን ያተረፋት የመከላከያ አባላት
1, ኢሳያስ - ቲም መሪ
2, ገዲሳ - ም/ቲም መሪ
3, ሸጋው - አባል ሲሆኑ በአፋብን የቴወድሮስ 2ኛ ዕዝን ተቀላቅለዋል።
(ነሃሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም)
በምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ተራራዎች ጉልላት ሥር፣ ደመናን በሚዳስሱ ሰማይ-ጠቀስ ጫፎችና በዓባይ ወንዝ ጥልቅ ሸለቆዎች መካከል፣ ተፈጥሮ በራሷ ውብ እጆች አብርታ የሰራችውና ድንቅ አድርጋ የፈጠረችው አንድ አስደናቂ ሕዝብ ይኖራል እሱም የአማራ ሕዝብ ነው።
ተፈጥሮ ይህንን ሕዝብ ስትቀርፀው ከተራራዎቹ ግርማ ሞገስንና ጽናትን፣ ከወንዞቹ ጥልቅ መንፈሳዊነትን፣ ከለምለም ምድሩ ደግሞ የዋህነትን፣ እንግዳ ተቀባይነትንና አብሮነትን አድላዋለች።
ይህ ሕዝብ የታሪክ ተራ ተራኪ አይደለም፤ እሱ ራሱ የሺዎች ዓመታት የሰው ልጅ ጥበብ፣ ፍልስፍና እና ስልጣኔ የሚተነፍስበት ህያው መዛግብት ነው። የራሱ ፊደል፣ የራሱ የቀን አቆጣጠርና የጠለቀ የማኅበረሰብ መዋቅር ባለቤት የሆነው ይህ ሕዝብ፣ የመላውን ዓለም አእምሮና ልብ የሚያስደምም ተፈጥሮአዊ ማራኪነት አለው።
የእነዚህን ሰዎች ምድር አቋርጠህ ብታልፍ፣ በመንገዱ ዳር በቆሙት የድንጋይ ተአምራት አእምሮህ ይመሰጣል። ከአንድ ግዙፍ ድንጋይ ወደ ታች ተፈልፍለው የተሰሩት የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ሲገለጡ፣ የሰው ልጅ እጅና የእምነት ፍቅር ያነጸው ታላቅ ተአምር እንደሆነ ትረዳለህ።
የሽዋ ቅዱስ የሆኑ ገዳማትን የጎንደር የፋሲለደስ ግንቦች በፀሐይ ብርሃን ሲያንጸባርቁ፣ የመካከለኛው ዘመን የንግድና የከተማ ግርማ ሞገስ በዓይንህ ፊት ይቆማል። በጣና ሐይቅ ማዕበል መካከል በተሸሸጉት ደሴቶችና በወሎ ተራራዎች ሥር ያሉ ጥንታዊ ገዳማትና መስጊዶች ደግሞ፣ የዘመናት የታሪክና የሃይማኖት ምስጢራትን በጸጥታ ይጠብቃሉ።
በየአደባባዩና በየአድባራቱ የሚሰማው ቋንቋ ደግሞ የቅኔና የፍልስፍና ጥግ ነው። ከላይ እንደ «ሰም» ቀሎ የሚታይ፣ በውስጡ ግን የረቀቀ «ወርቅ» ያዘለ የቅኔ ውበት፣ የማኅበረሰቡን ጥልቅ የማሰብ ጥበብ ያሳያል። በ፮ኛው ክፍለ ዘመን የተፈጠሩት የቅዱስ ያሬድ የዜማ ምልክቶች ደግሞ እስከ ዛሬ ድረስ የመንፈስን እርካታና የዓለምን ሙዚቃ ሀብት ይሞላሉ።
ይህ ምድር የኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥት መሠረትና ማዕከላዊ አምድ ነው። ለዘመናት የኢትዮጵያውያን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቁርኝት እንዲጠናከር ያደረገውን የአማርኛ ቋንቋ በማበልፀግ፣ የፍትሐ ነገሥት ሕግጋትንና የመንግሥት መዋቅሮችን በመቅረጽ የዛሬዋን የአብይ አህመድ በስለት ሰንሰለት የሚበጣጥሳትን ኢትዮጵያ መሠረት ጥሏል።
በአንድ በኩል የጎንደሩ ጥምቀት፣ በሌላ በኩል የወሎው መውሊድ በደመቀ ሁኔታ ሲከበር፣ ክርስትና እና እስልምና በሰላምና በወንድማማችነት አብረው የኖሩበትን የጥልቁ መንፈሳዊነትና አገራዊ አንድነት ውበት ታያለህ።
ነገር ግን ይሄ ሕዝብ የጥበብና የሰላም ብቻ አይደለም ወረራና በደል ሲደቅንበት ከፍ ብሎ የሚነሳ የጽናትና የነጻነት አርበኛ ነው። የመሬቱንና የማንነቱን ሉአላዊነት ለማስከበር የሚቆም ህያው የወታደራዊ ወኔና የፍትህ ዘበኛ ነው። ከዓድዋ የነጻነት ሜዳ እስከ ዘመናዊው ታሪክ ድረስ፣ የአማራ ሕዝብ ለሀገሩና ለነጻነቱ ዋጋ ለመክፈል የማይወላውል የጽናት ዋስትና ሆኖ ኖሯል።
ተፈጥሮ በጥንታዊ ስልጣኔው፣ በቅኔው፣ በነጻነት መንፈሱና ለኢትዮጵያ ባበረከተው ታላቅ አስተዋጽዖ አጋጣጥማ የሰራችው የአማራ ሕዝብ፣ የሰው ልጅ ልቅናና የጽናት ህያው ተአምር ሆኖ ይኖራል።
ክብር ለአራሽ ለቀዳሹ ደግሞ ለተኳሹ ውድ የአማራ ህዝብ !! የአርበኛ አርቲስ አስገደ መኮንን ልጅ አርበኛ ይሳቅ #Dave #Amhara
7/70 ክፍለ ጦር በአጣዬ ዙሪያ ድል ሲቀናው፣ "የአርሶ አምባ አርበኞች ጦር" በአላላ ታላቅ ገድል ፈፀመ!!
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/70 ክፍለ ጦር በአጣዬ እና በአላላ ከተማ በተለያዩ ሁለት አቅጣጫዎች በተፈፀመ ልዩ ኦፕሬሽን ውጤታማ ድል መቀናጀቱ ተገለፀ።
በላይኛው አጣዬ ቀበሌ ምሽትን ሽፋን ተደርጎ በተካሄደው ኦፕሬሽን፣ በማታ ኬላ ዘርግተው አሽከርካሪዎችን በማስቆም ህገ-ወጥ የገንዘብ ምዝበራ ሲፈጽሙ በነበሩ የታጠቁ ሚሊሻዎች ላይ ጥቃት መፈፀሙ ተረጋገጠ።
በዚህም ታዬ ገብሬ (የመንገድ ትራንስፖርት ባልደረባ)፡ በከፍተኛ ጽኑ ቆስሎ ወደ ሪፈራል ሆስፒታል ሲላክ፣ አሳልፍ አድሴና ኮማንደር የሱፍ ሙሔ፡ በጽኑ የቆሰሉ የሚሊሻ አባል መሆናቸው ተረጋግጧል።
በተወሰደባቸው እርምጃ የተበሳጩት የአገዛዙ የጸጥታ አካላት፤ መረጃ ለፋኖ ሰጥተሃል በሚል ጌታዬ ሀይሉ የተባለን አንድ ወጣት በግፍ እርምጃ እደተወሰደበት ተሰምቷል። ወጣቱ ቀደም ሲል አባቱ ከብልፅግና መዋቅር ስራ እንዲወጣ ሲለምነው የነበረ ሲሆን፣ ይህንኑ ምክንያት በማድረግ መረጃ ሰጥተሃል በሚል ሰበብ በግፍ ተረሽኗል።
በሌላ አቅጣጫ በአላላ ቀበሌ በተካሄደው ሁለተኛው ኦፕሬሽን ደግሞ፤ የሚሊሻ ጠርናፊ በሆነው ተሾመ ጌቶ በተባለው ግለሰብ ላይ በአላላ ከተማ እርምጃ ተወስዶ እስከወዲያኛው እንዲሸኝ ተደርጓል።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰ይሕ በእንዲሕ እንዳለ የአርሶ አምባ ዘንቦ ቀበሌ ሕዝብን ለመዝረፍ በሰንበቴ የሚንቀሳቀሰው የስርዓቱ አገልጋይ ሚሊሻ፡ በአርሶ አምባ አርበኞች ጦር" ቀኑን ሙሉ ሲወቃ ውሎ ከባድ ኪሳራ መከናነቡ ተገለፀ።
የአርሶ አምባ ገበሬን ንብረትና ሀብት ለመዝረፍ ከኬሚሴና ሰንበቴ ሲግተለተል የመጣው ሚሊሻ፡ እንዳመጣጡ ሲያናግሩት ውለው፣ በርካታ አባላቱን ሙትና ቁስለኛ አድርገውበታል።
በዚሕ አውደ ውጊያ የደረሰው የንብረትና የሰብዓዊ ኪሳራ ከባድ ሲሆን፣ በጠላት ላይ የደረሰውን ኪሳራ፣የሙትና ቁስለኛ ቁጥር ለመግለፅ በመረጃች አጣርተን፡ በቀጣይ የምንገልፅ ይሆናል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር ዜና
በሳንቃ ከተማ ግንባር በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከባድ ጥቃት ተፈፀመ።
የከማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት ትናንትና ነሃሴ 29/2018ዓ/ም በጉባላፍቶ ወረዳ ከወልዲያ ከተማ በቅርብ ርቀት ሳንቃ ከተማ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ያልተጠበቀ መብረቃዊ ጥቃት ወሰዱ።
አገዛዙ በሳንቃ ከተማ ግንባር በሌሊት ጥቃት ሊከፍት እንዳሰበ የ102ኛ ኮር ወታደራዊ አመራሮች ባገኙት መረጃ መሰረት የ49ኛ ክፍለጦር ቃኝ በሳንቃ ጌሾ በር ከምሽቱ አስራ አንድ ሰዓት ተስበው ቀድመው ቦታዎችን በመያዝ ጠላት ባልጠበቀው እና ባለአቀድው መንገድ እርምጃ ወሰዱበት።
ጠላት ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ከሳንቃ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መነሻውን በማድረግ ወደ ጌሾ በር እና ጤና ጣቢያ ሰፈር የዘረጋ ቢሆንም በ49ኛ ክፍለጦር ነበልባሎች ከበባ ውስጥ መሆኑን ጦርነቱ እስኪጀመር ድረስ በቂ መረጃ አልነበረውም።
በመሆኑም የ102ኛ ኮር ትንታጎች የ49ኛ ክፍለጦር ቃኝ በወሰዱት ድንገተኛ የፊት ለፊት የጨበጣ ማጥቃት 30 የመከላከያ ሰራዊት ሲደመሰሱ ቁጥሩ ያልታወቀ በርካታ የጠላት ሰራዊት ቆስለኛ ሆኗል።
የተደመሰሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሳንቃ ከተማ ከጌሾ በር እስከ መነሐሪያ ዛሬ ነሃሴ 30/2018ዓ/ም በየ መንገዱ አስከሬናቸው ወድቆ በአደባባይ ይታይ እንደነበር ማህብረሰቡ ገልፃል።
ልማደኞቹ ዙ-23 ማራኪዎቹ ከጠላት ስምንት ጥቁር ክላሽን ኮፍ መሳሪያ እና ስድስት ሬን ኮት እንድሁም ሶስት የወገብ ትጥቅ በሞርኮ በ49ኛ ክፍለጦር እጅ ገብቷል።
ጨፍጫፊውና እብሪተኛው የብልፅግና አገዛዝ በመላው አማራ ህዝብ በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ከፍተኛ ውዝግብ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
በመሆኑም አውደ ውጊያው እስከ ምሽቱ እንድ ሰዓት ደረስ የቀጠለ ሲሆን አገዛዙ የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለጦር ቃኝ ጀግኖችን ክንድ መቋቋም ባለመቻሉ በሁሉም አቅጣጫ ሳንቃ ከተማን ሙሉ በሙሉ አሰረክቦ ወደ መጣበት ፈርጥጧል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በወታደራዊ ጠበብቶችና ፓለቲካዊ ልምድን ባካበቱ አርበኞች የሚመራው ጀብደኛዉ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ከወታደራዊ ድሎች ጎን ለጎን ህዝባዊ ዉይይቶች ተጠናክረዉ ቀጥለዋል!
የአናብስቶቹ ስብስብ 15ኛ ኮር 156ኛ ታቦር ተራራ ክፍለጦር ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች የህዝብ አስተዳደራዊ እና መዋቅራዊ ለውጦችን በማካሄድ ጥልቅ ሕዝባዊ ውይይት አካሄደ!
የ156ኛ ታቦር ተራራ ክፍለጦር በ019 ቀበሌ የሚገኙ ማህበረሰብን በመሰብሰብ የተለያዩ አጀንዳዎችን በማንሳት ውይይቶችን በማድረግ ከማህረሰቡ ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል። በመድረኩ የተለያዩ አጀንዳዎች የተነሱ ሲሆን ከነዚህም መካከል በትግሉ ሂደት ውስጥ የተፈጠሩ ችግሮችን ምን ነበሩ? ፣የፋኖና የህዝባችን የግንኙነት መስመሩ ምን መምስል አለበት? እንዲሁም አሁናዊ የትግሉ ቁመና ምን ይመስላል?በሚሉ ሃሳቦች ላይ ሰፊ ትንተና እና ውይይት በማድረግ ከማህበረሰብ የተነሱ ጥያቄዋችን ተቀበለው ምላሽ ሰጥተዋል። ከቀበሌው ማህበረሰብ የተለያለዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በክፍለጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ሰፊና አጥጋቢ ምላሽ ተሰጥቷል።
በመጨረሻም የ156ኛ ታቦር ተራራ የክፍለ ጦር አመራሮችም ማህበረሰቡ ላነሳቸው ጥያቄዎች ምላሹን በመስጠት የአምሃራ ሳይንት ቀጠና ለጠላት አስፈሪ የሆነ ኀይልን በመፍጠር የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ በጋራ በመመከት ህዝባችን ከደጋፊነት ወደ ባለቤትነት መሽጋገር እንዳለበት በስብሰባው የተገኘው ማህበረሰብ ጋር የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ውይይቱ ተጠናቋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም
