en
Feedback
Ministry Of Peace Ethiopia-MOP

Ministry Of Peace Ethiopia-MOP

Open in Telegram

Peace for Ethiopia!

Show more
8 956
Subscribers
-424 hours
-717 days
-29430 days
Posts Archive
ጳጉሜ 5 | ነገ ነገን ዛሬ እንገንባ! 🕊️ ሰላም ለኢትዮጵያ!🇪🇹 - Pagumen 5 | Tomorrow Let’s build tomorrow today! 🕊️ Peace for our Ethiopia! 🇪🇹

ጳጉሜ 5 | የነገ ቀን ዛሬ የምንገነባው ነገ የምንኖረው ሕይወት ነው! 🕊️ ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹 - Pagumen 5 | Tomorrow The future we live tomorrow is built by what we do today!🕊️ Peace for our Ethiopia! 🇪🇹

በሰላም ሚኒስቴር ረጅም ዓመታትን አገልግለው በጦረታ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ሽኝት ተደረገ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የኅብር ቀንን  እና መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሰላም ሚኒስቴር ረጅም ዓመታትን አገልግለው በጦረታ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ሽኝት አድርጓል። የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ እንደተናገሩት ሀገርን በታማኝነት እና በቁርጠኝነት ያገለገሉ ሰራተኞች ሊከበሩ እና ዕውቅና ሊሰጣቸው ይገባል ያሉ ሲሆን ህዝብን ማገልገል ዕድለኝነት ነው ብለዋል። ሽኝት የተደረገላቸው በበኩላቸው ተቋሙ ላደረገላቸው ዕውቅና ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

photo content
+9

የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በዓል ላይ ከተናገሩት የተወሰደ.... ''ኅብረ-ብሔራዊ አንድነታችን እና አብሮነታችን የጥንካሬያችን መሠረቶች ናቸው''
የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በዓል ላይ ከተናገሩት የተወሰደ.... ''ኅብረ-ብሔራዊ አንድነታችን እና አብሮነታችን የጥንካሬያችን መሠረቶች ናቸው'' ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

የሰላም ሚኒስቴር የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ ሴት አመራሮች እና ሰራተኞቹ  ሽልማት አበረከተ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣  የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የኅብር ቀንን ምክንያት በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ ሴት አመራሮች እና ሰራተኞቹ የስልክ ቀፎ እና የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል። ሽልማቱ የተሻለ የሥራ መነሳሳትን ለመፍጠር ያለመ  መሆኑ ተገልጿል። ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

photo content
+3

photo content
+9

''ኅብረ-ብሔራዊ አንድነታችን እና አብሮነታችን የጥንካሬያችን መሠረቶች ናቸው''   ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ------------------------ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፤ ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የኅብር ቀን  የኢትዮጵያውያን ብዝሃነት፣ አብሮነት እና ወንድማማችነት የሚገለጽበት ልዩ ቀን በመሆኑን ያነሱ ሲሆን የጥንካሬያችን መሰረት የሆነውን ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ማጠናከሪያ ነው ብለዋል። ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን እና አብሮነታችን የጥንካሬያችን መሠረቶች ናቸው ያሉት ሚኒስትሩ መከባበርን እና ውይይትን ባህል በማድረግ ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሁላችንም ድርሻ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ሀገራዊ ሰላምን፣ መከባበርን እና ውይይትን ባህል በማድረግ ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ​ መጪው አዲስ ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የህብረት እና የመቻቻል ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

#TheWorkWednesday ቀጣይ ምን ክፍል በስራ ላይ እናሳያችሁ?‌‌ የሰላም ትጋታችን ከካሜራዉ በስተጀርባ! 🕊 ብሔራዊ የሰላም በጎ ፍቃድ አገልግሎት ወጣቶችን ከየክልል እና ከተማ አስተዳደሮች
#TheWorkWednesday ቀጣይ ምን ክፍል በስራ ላይ እናሳያችሁ?‌‌ የሰላም ትጋታችን ከካሜራዉ በስተጀርባ! 🕊 ብሔራዊ የሰላም በጎ ፍቃድ አገልግሎት ወጣቶችን ከየክልል እና ከተማ አስተዳደሮች በመቀበል ለሰላም እና ለሀገር ግንባታ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ የስልጠና ስምሪት የሚሰጠው ይህ የብሄራዊ በጎ ፈቃድ ሰልጠና ዴስክ የክትትል እና ድጋፍ ዴስክ ነው ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹 Which executive team would you like to see next? Our Peace efforts behind the Scene! 🕊 The National Volunteer Training, Monitoring, and Support Desk: Welcomes National Peace Volunteer Service youths from all regions and city administrations, equipping them through training and strategic deployments to contribute meaningfully to peace-building and nation-building. #TheWorkWednesday Peace for our Ethiopia! 🇪🇹

photo content
+9

''ኅብረ-ብሔራዊ አንድነታችን እና አብሮነታችን የጥንካሬያችን መሠረቶች ናቸው''   ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ------------------------ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፤ ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የኅብር ቀን  የኢትዮጵያውያን ብዝሃነት፣ አብሮነት እና ወንድማማችነት የሚገለጽበት ልዩ ቀን በመሆኑን ያነሱ ሲሆን የጥንካሬያችን መሰረት የሆነውን ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ማጠናከሪያ ነው ብለዋል። ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን እና አብሮነታችን የጥንካሬያችን መሠረቶች ናቸው ያሉት ሚኒስትሩ መከባበርን እና ውይይትን ባህል በማድረግ ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሁላችንም ድርሻ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ሀገራዊ ሰላምን፣ መከባበርን እና ውይይትን ባህል በማድረግ ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ​ መጪው አዲስ ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የህብረት እና የመቻቻል ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

ኅብረ -ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር ጠንካራ ሀገራዊ አቅምን ለመፍጠር የመደመር መንግስት በትኩረት እንደሚሰራ ተገለፀ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ የኅብር ቀን የሰላም ሚኒስቴር አመራሮች እና ሠራተኞች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የተለያዩ ሲቪክ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ኅብር የሀገራችን ጌጥ እና አቅም ነው ያሉት በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስስተላለፉት  የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ  የተከበሩ  ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) 2018 ዓ.ም በሀገራችን ሲንከባለሉ የመጡት የፓለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሀገራችን ህዝቦች ሀገራዊ ምክክር በማድረግ ለሀገር ጠቃሚ ምክረ ሀሳቦችን ተወያይተው ያቀረቡበት ስኬታማ ዓመት ነው ብለዋል። ብዝሀነትን በአግባቡ አለማስተናገድ የሀገራችን ትልቅ የፖለቲካ ስብራት ሆኖ ቆይቷል ያሉት ሚኒስትር ዴዔታው የመደመር መንግስት ኅብረ ብሄራዊ ማንነታችንን ሀገራዊ ድርጁ አቅም ለመገንባት እና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መንገድ ለመጠበቅ እና ለመንከባከብ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች  እየተከበረ ይገኛሉ። ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

photo content
+2

photo content
+9

photo content
+9

ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣  የሰላም ሚኒስቴር  ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ሀገር አቀፍ የኅብር ቀንን እና አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ ለሠራተኞች መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል። 2018 ዓ.ም እንደ ተቋም ብሎም እንደ ሀገር ትልልቅ ሥራዎችን ያከናወንበት ዓመት ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ በቀጣይ ዓመትም በአዲስ መንፈስ እና በአዲስ አስተሳሰብ የላቀ ሥራ እናከናውናለን ብለዋል። ሀገር አቀፍ የኅብር ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች  እየተከበረ  ይገኛሉ። ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

photo content
+4