6 791
Подписчики
-124 часа
-67 дней
+16830 день
Архив постов
አባቶች ለሰላም! 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹
Fathers for Peace!🕊
Peace for our Ethiopia! 🇪🇹
የሰላም ሚኒስቴር የ2019 በጀት ዓመት የመነሻ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄደ
ሐምሌ 4/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፤ በሰላም ሚኒስቴር የላቀ ውጤታማነትን እና የተቀናጀ ተቋማዊ ስኬትን ለማስመዝገብ ያለመ የ2019 በጀት ዓመት መነሻ እቅድ ላይ ከካዉንስል አባላት ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡
የውይይት መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ በ2018 በጀት ዓመት ተቋማዊ አቅምን ለመገንባት፣ የሰው ሃይልን ለማደራጀት እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን አቀናጅቶ ለመጠቀም የሚያስችሉ እጅግ የተሳኩ እና ተቋማዊ ግንባታን ያረጋገጡ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም የ2019 እቅዳችን አልቆ የመፈጸም አቅምን ማሳደግ 'አንድ እቅድ አንድ ሪፖርት' የሚለውን መርህ በመከተል የተቋሙን የሪፖርት እና የክትትል ሥርዓት ይበልጥ ማዘመን፣ የተጀመሩ አዎንታዊ የሰላም ግንባታ ሂደቶችን ማጠናከር፣ እንዲሁም የቴክኖሎጂ እና የዲጅታላይዜሽን ሥራን በማጎልበት በቀጣይም ቴክኖሎጂን በሰፊው የመጠቀም ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በአጽንኦት ተናግረዋል።
በሰላም ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድወሰን መኮንን እቅዱን አቅርበዋል። በቀረበው መነሻ እቅድ ላይ የካውንስሉ አባላት ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን በቀጣይ ሥራዎችን በጥራት፣ በፍጥነት እና በአሳታፊነት ማከናወን እንደሚገባ ተገልጾ ዕቅዱ ይበልጥ እንዲዳብር እና የተሟላ እንዲሆን በቀጣይም ከመላው የተቋሙ ሠራተኞች ጋር በእቅዱ ላይ ጥልቅ ውይይት እንደሚደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
ሰላም ለኢትዮጵያ!
ለምን እቺን ነጭ እርግብ? 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹
Why this Dove? 🕊
Peace for our Ethiopia! 🇪🇹
በሰላም ሚኒስቴር የፌደራሊዝም እና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ የነበሩት
ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ የፋና ሚዲያ ስራ አስፈፃሚ ሆነው ተሾመዋል።
ሚንስቴር መስሪያ ቤታችን መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ይመኛል።
ሰላም ለኢትዮጵያ!🕊️
#TheFeatureFriday
የሳምንቱ የሰላም ፕሮፋይል! 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹
-
The weekly Peace Profile! 🕊
Peace for our Ethiopia! 🇪🇹
እውቀታችንን ለሰላም፣ ለልማት እና ለሰው ልጆች ጥቅም! 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹
Our knowledge for peace, development and goodness of humanity! 🕊
Peace for our Ethiopia! 🇪🇹
“መንግሥት ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ከሚሠራቸው ሥራዎች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ ነው።”
የተከበሩ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር)
ሐምሌ 3/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፤ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የተከበሩ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) የብሔራዊ በጎ ፈቃድ የክረምት መርሐ-ግብርን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
የተከበሩ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማህበራዊ ትስስርን፣ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን፣ የህዝቦችን ትብብር እና አብሮነትን ለማጠናከር በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታዉሰው፡- ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሁሉም የዕድሜ ክልል የሚገኙ እንዲሁም ከሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ በጎ ፈቃደኛ ዜጎች የሚሳተፉበት ዘመኑን የዋጀ አርበኝነት እና የሀገር ፍቅር የሚገለጽበት ግዙፍ ሀገራዊ ጥሪ መሆኑን ገልፀዋል።
ፕሮግራሙ ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ተጀምሮ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም የሚጠናቀቅ መሆኑን ገልጸው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስተሩ ተጀምሮ በክልሎች ርዕሳነ-መስተዳድሮች እና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ፊታውራሪነት እየተመራ የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በ50 ከተሞች የሰላም ሚኒስቴር አስባባሪዎች ተሰማርተው ከክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች ጋር በቅንጅት እና በትብብር የሚከናወን መሆኑን አመላክተዋል።
የፕሮግራሙ ዓላማ በሕዝባችን ውስጥ ተጠብቆ የኖረውን የመረዳዳት፣ የመደጋገፍ እና የአብሮነት እሴቶችን እንዲሁም ማኅበራዊ ሀብቶችን መሳርያ አድርጎ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን እና አስተሳሳሪ ብሔራዊ ትርክትን መገንባት መሆኑን ገልፀዋል።
ፌዴራላዊ ሥርዓተ-መንግሥት በማዕከላዊ (የጋራ) እና በክልሎች (የራስ አስተዳደር) መንግስታት መካከል ሥልጣን በሕገ-መንግሥት ያካፍላል።
በኢትዮጵያ የፌደራል ስርዓት የፌደራሉ መንግስት የክልሎችን ሥልጣን ያከብራል፣ክልሎችም በተመሳሳይ የፌደራል መንግሥቱን ሥልጣን ያከብራሉ!
የፌደራል መንግስቱ ስልጣኑን ተግባራዊ በሚያደርግበት ወቅት የየክልሉን ልዩ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ይፈጽማል፤ በተመሳሳይም ክልሎች የየራሳቸውን ስልጣን ተግባራዊ በሚያደርጉበት ወቅት ከክልሉ ባሻገር ሀገራዊ ትልሞችን በሚያሳካ መልኩ ሚዛን በመጠበቅ መሆን ይኖርበታል።
ከዚህ አኳያ የሰላም ሚኒስቴር በፌደራል መንግስቱ እና በክልሎች እንዲሁም በክልሎች መካከል ጤናማ እንዲሁም የተቀናጀ ግንኙነት እንዲኖር
📍የመመካከሪያ፣
📍የልምድ መለዋወጫ እና
📍የመናበቢያ መድረኮች ሆነው የሚያገለግሉ ፎረሞች እንዲቋቋሙ በማድረግ ሚዛን በማስጠበቅ ሂደት ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊
በሰላም ሚኒስቴር የሴቶች ማህበር አባላት እና የተቋሙ ሠራተኞች ለአለም ፍሬ ፒንክሀውስ ካንሰር ፋወንዴሽን ድጋፍ አደረጉ
ሐምሌ 2/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ በሰላም ሚኒስቴር የሴቶች ማህበር አባላት እና የተቋሙ ሠራተኞች ከተለያዩ ክልሎች በካንሰር ተይዘው በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምናቸውን በመከታተል ላይ ያሉ ሴት ታካሚዎችን ተቀብሎ የነጻ መጠለያ፣ የምግብ እና የማማከር አገልግሎት በመስጠት ለሚንከባከባቸው አለም ፍሬ ፒንክሀውስ ካንሰር ፋወንዴሽን ድጋፍ አድርገዋል።
የተቋማችን የሴቶች ማህበር አባላት እና የተቋሙ ሠራተኞች በግል ተነሳሽነት በተሰበሰበ ገንዘብ የተለያዩ የምግብ ፍጆታ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ለግሰዋል፡፡
ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊️
#TheTrueThursday
የተኖሩ የሰላም ታሪኮች! 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹
-
#TheTrueThursday
Lived stories of peace! 🕊
Peace for our Ethiopia! 🇪🇹
በጋራ ለጋራ ቤታችን በሚል መሪ ሐሳብ ከተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ተወካዮች ጋር ውይይት ተካሄደ
ሐምሌ 2/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፤ በሀገራችን ህዝቦች መካከል አብሮነትን ለማጠናከር እና በዘላቂ ሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ያለመ ውይይት ከሃይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ተወካዮች ጋር ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የተከበሩ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) የሰላም ሚኒስቴር የተሰጠውን ተልዕኮ ማዕከል በማድረግ እና የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታ እና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸውን አይተኬ ሚና ታሣቢ በማድረግ የሃይማኖት አባቶች በስነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በመቅረጽ ሰላም እና አብሮነት እንዲያጎለብቱ ለማድረግ ከሃይማኖት ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
መንግሥስት የሃይማኖታዊ በዓላት በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው በ2019 ዓ.ም ሆነ በየአመቱ የሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት ከሀገራዊ ኩነቶች ጋር ሳይደራረቡ በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ተቀራርቦ መስራት ተገቢ መሆኑን ገልጸዉ፤ ይህን ሂደት ቀልጣፋ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።
መንግስት ከሃይማኖት ተቋማት ጋር ያለው ግንኙነት ሰላማዊ እንዲሁም በመከባበር እና የመንግስት-የሀይማኖት ግንኙነት መርህን የጠበቀ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው የሃይማኖት ተቋማት እርስበርሳቸው ያለው ሰላም ተሻሽሏል፣ በሃይማኖት ተቋማት መካከል ያለው ግንኙነት መልካም እንደሆነም ገልፀዋል። አንዱ የሃይማኖት ተቋም ከሌላው የሃይማኖት ተቋም ጋር በአብሮነት ችግሮቻቸውን ለመፍታት የሚያሳዩት አጋርነት እያደገ መምጣቱም የሚያስመሰግን ነው ብለዋል።
ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ለተከተዮቻቸው በአብሮነት፣ በጋራ ተከባብሮ መኖር እና በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የጀመሩትን ተቀራርቦ የመስራት በጎ ልምድ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የተገኙት የሃይማኖት መሪዎች በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ አንስተው ውይይት ተደርጓል፡፡ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ጋር በየወቅቱ ተቀራርቦ የመስራት ተግባሩ በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ አብሮ ለመስራት እድል መስጠቱን ገልፀው ሂደቱን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።
ዳይሮ ለሰላም! 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያ! 🇪🇹
Dairo for Peace! 🕊
Peace for our Ethiopia! 🇪🇹
የሚዲያ አጠቃቀም ግንዛቤ በማሳደግ የተሳሳቱ የመረጃ ስርጭቶችን መከላከል፤ ለጋራ ሰላማችን መጠበቅ ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡
🛜 መረጃን ከማጋራት በፊት የመረጃ ምንጮችን በማጣራት የተሳሳቱ መረጃዎችን መከላከል ተገቢ ነው፡፡
⚓️የሚዲያ ይዘትን በጥልቀት መረዳት፣
⚓️ ትክክለኛ መረጃን ከፕሮፓጋንዳ መለየት እና
⚓️ ሁከትን የሚቀሰቅሱ የውሸት ትርክቶችን በማጋለጥ ማህበራዊ ትስስራችን እና ዘላቂ ሰላማችን ልናሰፍን ይገባል፡፡
ሚዲያን
♟ ለልማት ሥራዎች
♟ ለሰላም ግንባታ እና
♟ ለማኅበራዊ ትስስር መሣሪያ አድርጎ መጠቀም ይገባል፡፡
⚠️ የሚዲያ ባለሙያዎች አንድነትን፣ መቻቻልን እና ገንቢ አመለካከቶችን የሚያበረታቱ ይዘቶችን በመፍጠር እና በማሰራጨት የጥላቻ ንግግር እና ከፋፋይ ትርክቶችን መከላከል ይኖርባቸዋል፡፡
✅ ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ በመጠቀም በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ የጥላቻ እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ሪፖርት ማድረግ እና ብሔራዊ ጥቅሞቻችን የሚያጎሉ መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊
#TheWorkWednesday
ቀጣይ ምን ክፍል በስራ ላይ እናሳያችሁ?
የሰላም ትጋታችን ከካሜራዉ በስተጀርባ! 🕊
ሰላም ለኢትዮጵያችን! 🇪🇹
ክረምትን በበጎ ፈቃድ፤ ሰላምን በተግባር!
ሰላም ለኢትዮጵያ ! 🇪🇹
Spend your summer volunteering. Build peace through action.
Peace for Ethiopia ! 🇪🇹
ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ወጣቱን በአመለካከት እና በሥነ-ምግባር እንዲታነጽ በማድረግ ብቁ ዜጋን ለማፍራት የሚያስችል ፕሮግራም ነው፡፡
ፕሮግራሙ ኢትዮጵያ ያሏትን መልካም እሴቶች፣ መርሆዎች፣ የሀገር እና የሕዝብ ፍቅር ለወጣቱ ትውልድ በማስተላለፍ የወጣቶችን
⚓️ ምክንያታዊነት
⚓️ የሥራ ባሕል
⚓️ የሕይወት መምራት ክሕሎት
⚓️ መልካም ሥነ ምግባርን በማጎልበት ሀገራዊ አንድነትን እና ብሔራዊ መግባባትን በማስረጽ ዘላቂ ሰላምን መገንባት የሚያስችል ነው፡፡
ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊
