1 073
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-2030 days
Posts Archive
የዲጂታል ትምህርት
ኢትዮጵያ ተማሪዎችና ወጣቶች በቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርትና ክህሎት እንዲያገኙ ለማስቻል የዲጂታል ስርዓት ትምህርትን በዋነኛነት እያስፋፋች ትገኛለች። የኢንተርኔት ትስስር መንገዶቸን በማመቻቸት እንዲሁም የዲጂታል መሣሪያዎችን እና የኢ-ለርኒንግ (E-learning) ግብዓቶችን በትምህርት ቤቶችና በስልጠና ማዕከላት ውስጥ በማካተት እነዚህ መርሃ ግብሮች የመማር ዕድሎችን ያሰፋሉ፤ የትምህርት ክፍተቶችን ይደፍናሉ፤ እንዲሁም ተማሪዎችን ለዘመናዊው የሥራ ዓለም ዝግጁ ያደርጋሉ። ዲጂታል ትምህርት ተማሪዎችን በቴክኖሎጂ፣ በችግር አፈታት እና በፈጠራ ረገድ አስፈላጊ የሆኑ ክህሎቶችን የሚያስታጥቅ ሲሆን፤ ይህም በትምህርታቸውና በሙያቸው ስኬታማ እንዲሆኑ እንዲሁም ለሐገሪቱ አጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ልማት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ይረዳቸዋል።
DIGITAL LEARNING
Ethiopia is advancing digital learning to give students and young people greater access to technology-driven education and skills development. By integrating online platforms, digital tools, and e-learning resources into schools and training centers, these programs enhance learning opportunities, bridge educational gaps, and prepare learners for the demands of the modern workforce. Digital learning equips students with critical skills in technology, problem-solving, and innovation, helping them succeed academically and professionally while contributing to the country’s broader economic growth and development.
#PMOEthiopia
#VisionOfProsperity
#የኢትዮጵያብልጽግናራእይ
ሰሌክት አካዳሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሀነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሠላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡
#Selectacademy #Ephiphany
የሰሌክት አካዳሚ ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን ይከተሉ፣ ለሌሎችም ያጋሩ
👇👇👇
www.selectacademy.edu.et
https://t.me/select_academy
እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
Wishing you Merry Christmas & Happy New Year!
መልካም ገና!
የሰሌክት አካዳሚ ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን ይከተሉ፣ ለሌሎችም ያጋሩ
👇👇👇
www.selectacademy.edu.et
https://linktr.ee/selectcollege
https://www.tiktok.com/@select_college?_t=ZM-8sprqR3Wds5&_r=1
#Selectacademy #ገና #Christmas
+5
ለቂርቆስ ክ/ከተማ ከትምህርት አመራር እና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ር/መምህራን ስለ ሰሌክት አንላይን አካዳሚ የተሰጠ ስልጠና።
ጥቅምት 11/2/2018
+8
ለቂርቆስ ክ/ከተማ ከትምህርት አመራር እና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ር/መምህራን ስለ ሰሌክት አንላይን አካዳሚ የተሰጠ ስልጠና።
ጥቅምት 12/2/2018
+9
ለቀለም ወላጋ ዞን ከትምህርት አመራር እና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርትቤት ር/መምህራን ስለ ሰሌክት አንላይን አካዳሚ የተሰጠ ስልጠና።
ጥቅምት 1/2/2018
ደምቢዶሎ
Baga Ayaana Irreecha geessan.
Ayyaana gaarii!
Akkaadaami Barnoota Onlaayiinii Sellekti.
Baga Ayaana Irreecha geessan.
Ayyaana gaarii!
Akaadaamii Barnoota Onlaayinii Selleekti
በትምህርት ዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት የትምህርት ተቋማት፣ መምህራን እና ባለድርሻ አካላት ሀላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ
መስከረም 21/2018 ዓ.ም — በሰሌክት ኮሌጅ አዘጋጅነት በድሬዳዋ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ከትምህርቱ አመራር፣ ከI C T መምህራን ከሱፐርቫይዘር እና በዘርፉ ከሚመለከታቸዉ ባለ ድርሻ አካላት ጋር የኦንላይን የበይነ መረብ የትምህርት አሰጣጥ ዙሪያ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የትውውቅ መድረክ ተካሄደ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ እና የስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አቡበከር አዶሽ እንደተናገሩት፦ ትምህርት የብዙ ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነትና ርብርብን የሚጠይቅ በመሆኑ ተቀናጅቶ በመስራት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል።
አክለውም ከአለም ጋር አብሮ ለመራመድ ዘመኑ የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሃገርና ትዉልድን ማበልፀግ እና ማሻገር የሚቻለዉ የትምህርት አመራሩ እና ትምህርት ቤቶች የተጣለባቸዉን ኃላፊነት በአግባቡ ጊዜ ሰተው ሲሰሩ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።
የሰሌክት ኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ ሄኖክ ሀ/መስቀል እንደገለፁት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤት ማሽቆልቆል ምክንያት በማድረግ ችግሩን መደጋገም ሳይሆን ለችግሩ መፍትሄ ለማበጀት ጥረት የጀመርን ሲሆን ለነዚህም ጥያቄዎች ለመመለስ የተለያዩ ስራዎች እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
በትምህርት ዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ከመንግስት ጋር በመሆን የጋራ ጥረት ለማድረግ ስራዎችን ጀምረናል ያም የትምህርት ተቋማት፣ መምህራን እና ባለድርሻ አካላት ሁላችንም የተጣለብንን ሀላፊነት በአግባቡ መወጣት ስንችል በጊዜ ሂደት የምንፈልገው ውጤት ይመጣል ሲሉ ተናግረዋል።
በማስከተል ደግሞ በበይነ መረብ ከ9-12ኛ ክፍል ትምህርት እና የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ዝግጅት የሚያደርጉበት የ6 ዓመታት ፈተናዎች ላይ መሰረቱን ባደረገ መልኩ ተዘጋጅቶ የዚህ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን የኦላይን ትምህርት አካዳሚ ዳሬክተር የሆኑት ዶ/ር ጎሳዬ አልዪ ስለፕሮግራሙ በሚያስተዋውቁበት ጊዜ ገልፀዋል።
ይህ ለተማሪዎቻችን ውጤት መሻሻል አይነተኛ ሚና የሚጫወት ነው ሲሉ የተናገሩት ደግሞ በትውውቅ መድረኩ ተሳታፊዎች የሆኑ አካላት ናቸው።
+7
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ከሰሌክት ኦን ላይን አካዳሚ ጋር በመተባበር በስሩ ለሚገኙ የመንግስትና የግል የትምህርት ተቋማት አመራሮች ስልጠና ሰጠ::
(መስከረም 20/2018 ዓ.ም) የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ለመንግስትና የግል የ2ኛ ደረጃ የትምህርት አመራሮች ከሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ ጋር በመተባበር በE-Lernning ሲስተም ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::
የክ/ከተማው የስርዓተ ትምህርትና የትምህርት መረጃ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ባህይሉ ቅጣው በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር በሰሌክት የኦንላይን አካዳሚ የለማው የበየነ መረብ ትምህርት ሲስተም የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎችን ውጤት በማሸሻል ረገድ የራሱ የሆነ በጎ ሚና እንዳለው አንስተው የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቅምና የዕውቀት አድማስ በእጅጉ እንደሚያሻሽል አንስተው ቴክኖሎጂን ለአውንተዊ ሚና መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
🌐 በስልጠናው ላይ ከሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ የመጡ ባለሙያዎች የበለጽግው የተማሪዎች የE-Learning ሲስተም አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ የተዘጋጀና ከ9-12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አንስተው ለዚህም ትምህርት ሚኒሲቲርና የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሲስተሙ በተማሪዎች ውጤት ላይ የሚኖረውን ሚና በቴክኖሎጂና ሰርዓተ ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያዎች በጥልቀት በመፈተሽ ዕውቅና የተሰጣቸው መሆኑን ገልጽው በቀጣይ በክ/ከተማው ስር የሚገኙ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የግልና የመንግስት ሴክተሮችና የህብረተሰቡን ተሳትፎ እንደሚፈልግ አንስተው ከክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩና በትምህርት ሴክተሩ የተጣለባቸውን ማህበራዊ ሃላፊነት የሚወጡ መሆኑን ለስልጠናው ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል፡፡
እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሰዎ! በዓሉ የሰላም እና የደስታ እንዲሆንልዎ እንመኛለን!
ሴሌክት ኦንላይን አካዳሚ
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
+4
የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ለመንግስትና ለግል አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ርዕሰ መምህራን ስልጠና ሰጠ።
መስከረም 15/2018 ዓ.ም
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴን ጨምሮ የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ አመራሮች የትምህርት ጽ/ቤት የሥርዓተ ትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች፣በክፍለ ከተማው ሥር የሚገኙ የመንግስት እና የግል አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ተሳታፊ ሁነዋል።
በአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው ላይ ተገኝተው ለተሳታፊዎች መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ገነነ ዘውዴ እንዳሉት የትምህርት ተቋሞቻችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ከአለም እኩል መራመድ ያስፈልጋቸዋል ያሉት ኃላፊው ለዚህም መንግስት በራሱ አቅም እና በባለሀብቶች ድገጋፍ የተማሪዎችን ውጤት የሚያሻሽሉ እና የማለፍ ምጣኔን የሚጨምሩ ሥራዎችን በትኩረት እንደሚሰሩ ገልፀዋል። ኃላፊው አክለው እንዳሉት በዛሬው ዕለት የሁለተኛ ደረጃ የተማሪዎች የኦላይን ትምህርት እና የምዘና አተገባበር በሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ መሰጠቱን በቀጣይ ለምንሰራቸው ዘርፈብዙ ሥራዎች ጥሩ ጅማሮ መሆኑን ገልፀዋል።
የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ ከፍተኛ ባለሙያዎች በኦንላይን ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ሰፉ ያለ ስልጠና አቅርበዋል።
የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተሰጠው ስልጠና የተማሪዎችን አቅም እንደሚያጎለብት ገልፀው ሆኖም ግን ቀጣይነት ያለው ስልጠና እና እስከታችኛው እርከን ወርዶ ማስረጽ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል።
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
+4
የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ለመንግስትና ለግል አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ርዕሰ መምህራን ስልጠና ሰጠ።
መስከረም 15/2017 ዓ.ም
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴን ጨምሮ የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ አመራሮች የትምህርት ጽ/ቤት የሥርዓተ ትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች፣በክፍለ ከተማው ሥር የሚገኙ የመንግስት እና የግል አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ተሳታፊ ሁነዋል።
በአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው ላይ ተገኝተው ለተሳታፊዎች መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ገነነ ዘውዴ እንዳሉት የትምህርት ተቋሞቻችን ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ከአለም እኩል መራመድ ያስፈልጋቸዋል ያሉት ኃላፊው ለዚህም መንግስት በራሱ አቅም እና በባለሀብቶች ድገጋፍ የተማሪዎችን ውጤት የሚያሻሽሉ እና የማለፍ ምጣኔን የሚጨምሩ ሥራዎችን በትኩረት እንደሚሰሩ ገልፀዋል። ኃላፊው አክለው እንዳሉት በዛሬው ዕለት የሁለተኛ ደረጃ የተማሪዎች የኦላይን ትምህርት እና የምዘና አተገባበር በሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ መሰጠቱን በቀጣይ ለምንሰራቸው ዘርፈብዙ ሥራዎች ጥሩ ጅማሮ መሆኑን ገልፀዋል።
የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ ከፍተኛ ባለሙያዎች በኦንላይን ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ሰፉ ያለ ስልጠና አቅርበዋል።
የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተሰጠው ስልጠና የተማሪዎችን አቅም እንደሚያጎለብት ገልፀው ሆኖም ግን ቀጣይነት ያለው ስልጠና እና እስከታችኛው እርከን ወርዶ ማስረጽ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል።
+9
የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለከተማ ስር የሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን ጋር የተደረገ የግንዛቤ መስጫ መድረክ በዛሬው ዕለት 15/01/2018 በክፍለከተማው አስተዳደር ቢሮ ተደርጓል። በመድረኩ ላይ የክፍለከተማው የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ገነነ የድጋፍ መልክታቸውን አስተላልፈዋል። በመድረኩ ላይም የተለያዩ የክፍለከተማው የትምህርት ካሪኩለም ፣ የ አይሲቲ ባለሙያዎች እና ዳይሬክተሮች ተሳትፈዋል።
የሰሌክት ኦንላይን አካዳሚ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለከተማ ስር የሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን ጋር የተደረገ የኝዛቤ መስጫ መድረክ በዛሬው ዕለት 15/01/2018 በክፍለከተማው አስተዳደር ቢሮ ተደርጓል። በመድረኩ ላይ የክፍለከተማው የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ገነነ የድጋፍ መልክታቸውን አስተላልፈዋል። በመድረኩ ላይም የተለያዩ የክፍለከተማው የትምህርት ካሪኩለም ፣ የ አይሲቲ ባለሙያዎች እና ዳይሬክተሮች ተሳትፈዋል።
