Wolkite city Administration Government Communication Affairs Office
Open in Telegram
671
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+330 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+1
in 0 channels
August '26
+20
in 0 channels
Get PRO
July '26
+35
in 0 channels
Get PRO
June '26
+8
in 0 channels
Get PRO
May '26
+18
in 0 channels
Get PRO
April '26
+20
in 0 channels
Get PRO
March '26
+12
in 0 channels
Get PRO
February '26
+13
in 0 channels
Get PRO
January '26
+16
in 0 channels
Get PRO
December '25
+65
in 0 channels
Get PRO
November '25
+45
in 0 channels
Get PRO
October '25
+45
in 0 channels
Get PRO
September '25
+41
in 0 channels
Get PRO
August '25
+45
in 0 channels
Get PRO
July '25
+13
in 0 channels
Get PRO
June '25
+26
in 0 channels
Get PRO
May '25
+34
in 0 channels
Get PRO
April '25
+37
in 0 channels
Get PRO
March '25
+21
in 0 channels
Get PRO
February '25
+274
in 0 channels
Get PRO
January '250
in 1 channels
Get PRO
December '240
in 1 channels
Get PRO
November '24
+143
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 09 September | 0 | |||
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +1 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
Channel Posts
| 2 | የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት አስተባባሪነት “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ከየም ዞን እና ከቀቤና ልዩ ወረዳ ወጣቶች የ2018 ዓ.ም ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ ሥራ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የተለያዩ የበጎ ተግባራትን አከናወኑ።
በመርሀ -ግብሩ የየምም ዞንና የቀቤና ልዩ ወረዳ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በከተማ አስተዳደሩ የችግኝ ተከላ ፣ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት የቤት ጥገና፣ ፣የከተማ የጽዳት፣ የአይነት ድጋፍ፣ የአልባሳት ፣የተማሪዎች መማሪያ ቁሳቁስ እና የአንድ ማዕከል የመሶብ ጉብኝት ጨምሮ ሌሎችም የበጎ ፍቃድ የአገልግሎት ስራዎች አከናውነዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት አብዱ ዲንቁ በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ ወጣቶች የክልሉ ባህልና ቋንቋ እንዲሁም አኗኗር በማስተዋወቅ ችግሮች ሲኖሩ እርስ በእርስ በመቀራረብ ለጋራ መፍትሄ የሚሰሩበት ነው ብለዋል።
አብሮነት፣ እህትማማችነትና ወንድማማችነት በማጠናከር ቤተሰባዊነት በመፍጠር በአንድ አስተሳሰብ ለጋራ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።
በክልላችን በርካታ የበጎ ፍቃድ ተከናውነዋል ያሉት አቶ አብዱ በደም ልገሳ፣በአረንጓዴ አሻራ፣ የፅዳት ፣አቅመ ደጋማ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎች ፣ የቤት እድሳትና ጥገና ላይ ማከናወን መቻሉን አንስተዋል።
በክልሉ ከ98% በላይ ወጣት በበጎ ፍቃድ ተግባራት ላይ ተሳታፊ ሲሆኑ ከ90% በላይ የሚሆነ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ በማግኘት ተጠቃሚ መሆን መቻላቸው አንስተው ወጣቱ ሀይል ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ለማድረግ እያደረገ ያለው ያላሰለሰ ጥረት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መክረዋል።
የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ እንደተናገሩት የ2018 ዓ.ም የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች ስኬታማ ነው ብለዋል።
በክልላችን ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች የህዝባችን አንድነትና መቀራረብ ላይ ትኩረት በማድረግ በፅኑ መሠረት ለጋራ ውጤት የሚሳተፍበት ነው ሲሉ አንስተዋል።
ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር ተግባራት አፅንኦት በመስጠት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ውስጥ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ በማድረግ እንደ ክልልም ለሌላው አርዓያነት ያለው ስራ እየተሰራ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሀላፊና ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ታደለ በቀለ እንደተናገሩት አብሮነትና አንድነት በማጠናከር እና ወል ትርክትን የህዝባችን ሁለንተናዊ ብልፅግናና እድገት ልናስቀጥል ይገባል ብለዋል።
የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር ከሆኑ ተግባራት አንዱ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ስራዎች አንዱ መሆኑን ያነሱት አቶ ታደለ በጎነት ከፈጣሪና ከሰው ዘንድ የሚያስመሰግን ትልቅ የህሊና ስራ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል።
በወጣቱ ንቁ ተሳትፎ ማህበረሰባችንን በማገልገል በዓለን እውቀትና ሀብት አንድነትን የሚያጠናክር ክልላችንን የሚያሻግር ተግባር በማከናወን የብልፅግና ጉዞዋችንን በውጤት ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
የጉራጌ ዞን ወጣቶች ክንፍ ሀላፊ አቶ ሰፊዩ ቅባቱ በበኩላቸው የዞናችን ወጣት በበጀት ዓመቱ በበጎ ፍቃድ ስራዎች አደረጃጀት በማስፋት ሰፊ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
የክልሉ ሀብት በማስተዋወቅ እና 7 ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በማስቻል የወጣቱ ሚና ከፍተኛ እንደነበረ ገልፀዋል።
ወሰን ተሻጋሪ ወጣቶች በሰጠቱ አስተያየት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች በማጠናከር ህዝባችንና ማህበረሰባችን በዓለን አቅም ድጋፍ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
አንድነታችንን በማጠናከር አብሮ የመኖር እሴታችን በማሳደግ ልማትና እድገታችንን ልናስቀጥል ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል።
| 141 |
| 3 | No text... | 114 |
| 4 | በወልቂጤ ከተማ የግብር ሕግ ማስከበር ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
ወልቂጤ፤ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተጀመረው የግብር ሕግ ማስከበር ሥራ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል።
በተጠናከረው የሕግ ማስከበር ሥራ በተለይም የደረሰኝ አጠቃቀምና አሰጣጥ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ሲሆን፣ የግብር ሕግና ደንብን ተከትለው የማይሠሩ ተቋማትና ድርጅቶች ላይም በሕጉ መሠረት ተገቢው አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ ነው።
የደረሰኝ ሕግን መጣስ፣ ግብርን ለመሰወር የሚደረጉ ሕገወጥ ተግባራትና ሌሎች የግብር ሕግ ጥሰቶች በቸልታ እንደማይታዩ በማስገንዘብ፣ የቁጥጥርና የሕግ ማስከበር ሥራው በዞኑ ወልቂጤ ከተማ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የግብር ሕግ ማስከበር ሥራው ሁሉም ግብር ከፋይ ሕጋዊ ግዴታውን በወቅቱና በትክክል እንዲወጣ ከማድረግ ባለፈ፣ ፍትሐዊ የግብር ሥርዓትን ለማጠናከር፣ የገቢ መሠረቱን ለማስፋትና የገቢ ክፍተትን ለማስቀረት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገልጿል።
በተጨማሪም በነሐሴ ወር የታቀደውን የገቢ ግብ በሙሉ ለማሳካት የደረሰኝ ቁጥጥር፣ የግብር ከፋይ ክትትልና የግብር ሕግ ማስከበር ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ ይገኛል።
በክልሉ በሳምንቱ መጀመሪያ ቀናት የተጀመረው የግብር ሕግ ማስከበር ዘመቻም በሁሉም የገቢ መዋቅሮች ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን፣ በቀጣይም የግብር ሕግ ጥሰቶችን በመከላከልና በሕግ ማስከበር ሥራው ላይ በተጠናከረ መልኩ እንደሚሠራ ተገልጿል።
በመሆኑም ግብር ከፋዮች የግብር ሕግና ደንብን በመከተል፣ ለሚያከናውኑት ግብይት በትክክል ደረሰኝ በመስጠትና በመቀበል ሕጋዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ተገልጿል። | 115 |
| 5 | No text... | 79 |
| 6 | ጊዜው ያለፈባቸው ምርቶችን ከመግዛትና ከመጠቀም ህብረተሰቡ እንዲጠነቀቅ ጥሪ ቀረበ
ወልቂጤ፤ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈ፣ ከጥራት ደረጃ በታች የተመረተ እና ለሸማቾች ጤና ጉዳት ሊያስከትል የሚችል ምርት ወደ ገበያ እንዳይገባ የሚደረገው የቁጥጥርና የኢንስፔክሽን ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የወልቂጤ ከተማ ጤና ጽህፈት ቤት ከከተማው ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት፣ ከጉራጌ ዞን ጤናና ከዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጋር በመቀናጀት ባካሄደው የኢንስፔክሽን ሥራ በርካታ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈ ምርቶች መገኘታቸው ተገልጿል።
የጋራ የቁጥጥር ሥራው ከነሐሴ 25/2018 ዓ.ም ጀምሮ መካሄዱን የገለጹት ባለሙያዎች፣ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈ ምርቶችን፣ ከደረጃ በታች የተመረቱ ምርቶችን እንዲሁም በምርቶች ላይ ጎጂ ነገሮች እንዳይቀላቀሉ ለማረጋገጥ ቁጥጥር እያደረጉ እንደነበር አስረድተዋል።
የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈ የምግብ ወይም የመጠጥ ምርት በተለይ በአግባቡ ካልተከማቸ የምርቱ ጥራትና ደህንነት ሊጎዳ ይችላል።
እንደ ምርቱ ዓይነትና የአከማች ሁኔታ በምርቱ ውስጥ ጎጂ ተህዋስያን ሊበዙ የሚችሉ ሲሆን፣ ይህም የምግብ መመረዝን፣ የሆድ ሕመምን፣ ማቅለሽለሽን፣ ተቅማጥንና ሌሎች የጤና ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል።
በተለይም ለሕፃናት፣ ለአረጋውያንና የጤና አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ሰዎች ከጥራት ውጪ የሆነ ምርት መጠቀም የበለጠ የጤና ስጋት ሊያስከትል ስለሚችል፣ ሸማቾች ምርት ሲገዙ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልእክት ተላልፏል።
በቁጥጥር ሥራው የተገኙ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፉ ምርቶች ተሰብስበው በግብረሀይል በአግባቡ መወገዳቸውን ባለሙያዎቹ ገልጸዋል።
የተወገዱት ምርቶች ወደ ሸማቾች እንዳይደርሱ በማድረግም በሕዝብ ጤና ላይ ሊደርስ የሚችልን ጉዳት ለመከላከል ጉልህ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል።
በመሆኑም የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ማንኛውንም የምግብና የመጠጥ ምርት ከመግዛታቸው በፊት የመጠቀሚያ ጊዜውን፣ የማሸጊያውን ሁኔታና የምርቱን ጥራት በጥንቃቄ እንዲመለከቱ ተጠይቀዋል።
የተበላሸ፣ የተቀደደ፣ የተከፈተ ወይም አጠራጣሪ ሁኔታ ያለውን ምርት ከመግዛትና ከመጠቀም እንዲቆጠቡም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
እንዲሁም ነጋዴዎች የሸማቾችን ጤናና ደህንነት በማስቀደም የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈ፣ ጥራቱ የተጓደለ ወይም ከሕግና ከደረጃ ውጪ የሆነ ምርት ለሽያጭ እንዳያቀርቡ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል ።
በተመሳሳይ ጊዜው ያለፈ፣ ከጥራት ደረጃ በታች የሆነ ወይም ለሕዝብ ጤና አደገኛ ሊሆን የሚችል ምርት ከተመለከቱ ወይም ጥቆማ መስጠት ከፈለጉ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ማሳወቅ ይችላሉ፦
☎️ 011 330 1899 — የቢሮ ስልክ
📱 091 323 1033
📱 091 001 3774
የሸማቾች ጥንቃቄ የጤና ዋስትና ነው፤ ጥራት ያለው ምርት እንግዛ፣ ጤናችንን እንጠብቅ! | 81 |
| 7 | No text... | 85 |
| 8 | በክልሉ በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ወልቂጤ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል"ዘላቂ የትምህርት ጥራት ለላቀ የመማር ውጤት እና ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ ሲካሄድ የነበረው 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ ተጠናቋል
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉባኤው ማጠቃለያ በሰጡት የስራ መመሪያ እንደገለጹት በክልሉ በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል።
የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም መገንባት እንዲሁም መምህራን የሚያስተምሩትን ትምህርት መሰረት በማድረግ አቅማቸውን ማሳደግ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።
መምህራን ለተማሪዎቻቸው በቂ እውቀት መስጠት እንዲችሉ ጥረት ማድረግ ይገባል ሲሉም ጠቁመዋል።
የሁሉም የትምህርት ስራ ማጠቃለያ ተማሪ እና መምህራንን ፊት ለፊት በማገናኘት ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የመማር ማስተማር ስራው ውጤታማ እንዲሆን መስራት ተገቢ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ተማሪዎችን በውጤትም ሆነ በስነ ምግባር ብቁ እንዲሆኑ መስራት እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።
የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ በሁሉም መስክ የተጀመሩ ስራዎችን በግብአት ማሟላት ተገቢ ስለመሆኑም ተናግረዋል።
የትምህርት ቤት ሀብት በማጠናከር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ መፍጠር እንደሚገባም አመላክተዋል።
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ረገድ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።
ተማሪዎችን እና መምህራንን አቅም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ላይ ብቃት እንዲኖራቸው መስራት ይገባል ብለዋል።
የተማሪዎች ምዘና በማጠናከር ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ፈተና በማዘጋጀት ተማሪዎች በየ ጊዜው እንዲፈተኑ በማድረግ አቅማቸውን መለካት የሚቻልበትን ስርዓት መፍጠር ተገቢ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።
የተማሪዎች እና የመምህራንን የፈጠራ አቅም ለማጎልበት የአጫጭር ጊዜ ስልጠና በማዘጋጀት ስራቸውን ወደ ገበያ ማውጣት እንዲችሉ ማበረታታት ይገባል ብለዋል።
ለዚህም የለፈጠራ አቅምን ማሳደግ የሚያስችል ማዕከል ዝግጁ ማድረግ ተገቢ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
በአምስት ዓመታት ውስጥ 200 ብቃት ያላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆኑ ወጣቶችን ለመፍጠር መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ በሁሉም መስክ ውጤት ለማስመዝገብ ላደረገው የላቀ ጥረት ርዕሰ መስተዳድሩ እውቅና ሰጥተዋል።
በሀገሪቱ በምክክር ያገኘናቸው ነጥቦች ወደ ፖሊሲ፣ ወደ ህገ መንግስት እና መሰል ጉዳዮዮች ተሸጋግረው የኢትዮጵያን መጻኢ እድል ብሩህ የሚያደርጉበት ዓመት እንደሚሆን ርዕሰ መስተዳድሩ ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል።
ሰላማችን ላይ አጥልተው ያሉ ጉዳዮች የሚገፈፉበት ወደ ተሻለ እድገት የምንሸጋገር አመት ይሆናል ብለዋል።
2019 የበለጸገች ኢትዮጵያን የምናይበት፣የሰላም፣ የጤና የመከባበር አመት እንዲሆን ርዕሰ መስተዳድሩ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ እንደገለጹት የትምህርት ስራ ከፍተኛ ሀብት የአመራሩን ፣የባለሙያውን እና የባለ ድርሻ አካላትን ጥረት ይጠይቃል ብለዋል።
በቅድመ አንደኛ ላይ መስራት በዘርፉ ውጤት ለማስመዝገብ ያግዛል ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ውጤቱ ዓመታትን እንደሚፈጅ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።
በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ ከወላጅ እና ከማህበረሰብ ጋር መስተጋብር መፍጠር ተገቢ ነው ያሉት አቶ አንተነህ የመምህራንን ተነሳሽነት ማሳደግ እንደሚገባም ጠቅሰዋል።
የመምህራንን ጥቅማ ጥቅም እና መሰል ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባም አብራርተዋል።
የትምህርት ቤት አመራር እና የትምህርት ሪፎርም በማድረግ ዘርፉን ማሳደግ ተገቢ መሆኑንም ክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
የትምህርት ስራ እንዲሻሻል ጥናትና ምርምር ያሻል ያሉት አቶ አንተነህ በዚህም ችግሮችን በመለየት መፍትሄ ለማፍለቅ እንደሚያግዝም አብራርተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ መንግስት የሚመድበው ሀብት ብቻ በቂ አለመሆኑን የገለጹት አቶ አንተነህ ህብረተሰቡን በማስተባበር አማራጭ ገቢ መፍጠር ተገቢ ስለመሆኑም ተናግረዋል።
የትምህርት ስራ የአመራሩን ባለቤትነት ይፈልጋል ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠንካራ ክትትል እና ድጋፍ የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንደሚያስችልም መግለፃቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቦታል። | 81 |
| 9 | No text... | 74 |
| 10 | ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ በወልቂጤ ከተማ ተካሄደ
ወልቂጤ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ሳምንታዊ የጋራ የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ።
በዘመቻው የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙባሪክ ዘይኑን ጨምሮ የከተማው አስተባባሪ አካላት፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ የሴፍቲኔት ሰሪ ሀይሎች፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጪ ወጣቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በንቃት ተሳትፈዋል።
ምክትል ከንቲባና ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙባሪክ ዘይኑ በጽዳት ዘመቻው ላይ በመሳተፍ የጽዳት ሥራ የከተማ መንግሥት ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን የእያንዳንዱ ነዋሪ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አመላክተዋል።
ከተማዋን ንጹህ፣ ማራኪና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የሚከናወኑ የጽዳት ሥራዎች በዘመቻ ጊዜ ብቻ ሳይወሰኑ የዕለት ተዕለት ባህል እንዲሆኑ የሁሉም አካላት ተሳትፎ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
የጽዳት ዘመቻው ዋና ዓላማም የከተማዋን ንጽህናና ውበት ማስጠበቅ፣ ከቆሻሻ አወጋገድ ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮችን መቀነስ እና ነዋሪዎች በጋራ ኃላፊነት የሚሳተፉበትን የንጽህና ባህል ማጠናከር መሆኑ ጠቁመዋል።
በተለይም የከተማ አስተዳደሩ ከነዋሪዎች፣ ከወጣቶች፣ ከመንግሥት ተቋማትና ከሌሎች አካላት ጋር በትብብር የሚያካሂደው የጋራ የጽዳት ዘመቻ የከተማዋን ንጽህና ከማስጠበቅ ባለፈ የህብረተሰቡን የጋራ ተሳትፎ ለማጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑ ገልጸዋል።
በዘመቻው ላይም የዕለት ተዕለት የጽዳት ሥራዎችን እንዲሁም በየሳምንቱ የሚካሄደውን የጋራ የጽዳት ዘመቻ ከወትሮው በበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።
“ንጹህ ከተማ የጋራ ኃላፊነት፣ የጋራ ጥረትና የጋራ ባለቤትነት ውጤት ናት” የሚለውን መርህ በተግባር ለማስረጽ፣ ሳምንታዊ የወልቂጤ ከተማ የጽዳት እንቅስቃሴዎች በቀጣይም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ ተጠቁሟል። | 92 |
| 11 | No text... | 71 |
| 12 | ወሄም ሳረነም! ወሄም ሳረነም!
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ ያለን!
የወልቂጤ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ልዩ ተሸላሚ ሆነ
ወልቂጤ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ባስመዘገበው አመርቂ የሥራ አፈጻጸም በዞኑ ከሚገኙ መዋቅሮች መካከል ልዩ ተሸላሚ በመሆን የዋንጫና የምስክር ወረቀት ተሸላሚ ሆነ።
ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ የልማት ሥራዎችን በዕቅድና በትጋት በማከናወን፣ ለከተማው ነዋሪዎች የሚጠቅሙ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችን በማስፋፋት እንዲሁም ቀልጣፋና ውጤታማ የአገልግሎት አሰጣጥን በማጠናከር የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡ ተገልጿል።
የተገኘው እውቅናም ጽ/ቤቱ በልማት ሥራዎችና በአገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ያሳየውን ተግባራዊ አፈጻጸም ከፍ ብሎ የሚያሳይ ሲሆን፣ ውጤቱ የከተማው አመራሮች፣ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎችና ሠራተኞች እንዲሁም የማኅበረሰቡ የተቀናጀ ጥረት ውጤት መሆኑ ተመላክቷል።
ለጽ/ቤቱ በተሰጠው እውቅና መላው የወልቂጤ ከተማ አመራርና ማኅበረሰብ ደስታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ይህ ስኬት በቀጣይ የበለጠ ለመሥራት ተጨማሪ ማበረታቻ እንደሚሆን ተገልጿል።
ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤቱም የተጀመሩ የልማትና የአገልግሎት ሥራዎችን በተጠናከረ መልኩ በማስቀጠል፣ የከተማውን ነዋሪ ተጠቃሚነት ይበልጥ በማረጋገጥና ከዚህ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ የላቀ የአገልግሎት ተሞክሮን ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጧል።
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን! 🏆👏
የወልቂጤ ከተማ ስኬት ይቀጥላል! | 74 |
| 13 | No text... | 72 |
| 14 | የከተማን ውበትና የመንገድ ደህንነት ለማሳደግ የዚብራ መስመሮች በበጎ ፈቃደኞች ተቀብቷል
ወልቂጤ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት አካል የሆነው የከተማዋን የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገዶች የዚብራ መስመሮችን የመቀባት ሥራ ተከናወነ።
በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ተስፋ በጎ አድራጎት ክበብ ከከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት እንዲሁም ከከተማዋ መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ይህን በጎ ተግባር አከናውኗል።
የዚብራ መስመሮችን በግልጽና በተገቢው ሁኔታ መቀባት ለከተማዋ ውበት ከሚያበረክተው ጥቅም ባሻገር፣ እግረኛ ተጠቃሚዎች መንገድ በሚሻገሩበት ወቅት ተገቢውን የትራፊክ ጥንቃቄ እንዲያገኙ እና የመንገድ ተጠቃሚዎችም የእግረኞችን የመሻገሪያ ቦታ በግልጽ እንዲለዩ ያግዛል።
በተለይም በከተማ መሃል በሰውና በተሽከርካሪ ፍሰት የበዛባቸው መንገዶች ላይ የዚብራ መስመሮች ግልጽነት የእግረኞችን የመንገድ መሻገሪያ ሥፍራ በማመላከት ለትራፊክ ደህንነት የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል።
የአዲስ ተስፋ በጎ አድራጎት ክበብ ያከናወነው ተግባርም በጎ ፈቃድ ማለት በገንዘብ ወይም በቁሳቁስ ድጋፍ ብቻ ሳይሆን፣ የራስን ጊዜ፣ ጉልበትና አቅም ለማህበረሰብ ጥቅም በነፃ ማዋል መሆኑን ያሳያል።
በጎ ፈቃደኞች በሚኖሩበት አካባቢ የሚታዩ የማህበረሰብ ችግሮችን በመለየት በተግባር መፍትሔ ለማምጣት መሳተፋቸው የዜጎችን የከተማ ባለቤትነት ስሜት ከማጠናከር ባለፈ፣ የመንግስትና የማህበረሰብ ተቋማት በጋራ ሲሰሩ የሚፈጠረውን ውጤታማ ትብብርም ያሳያል።
የዚህ ዓይነቱ በጎ ተግባር በከተማዋ የንፅህና፣ የውበትና የደህንነት ሥራዎች ላይ ህብረተሰቡ በቀጣይነት እንዲሳተፍ የሚያነሳሳ ሲሆን፣ ወጣቶችም በአካባቢያቸው ልማትና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ሚና እንዲወጡ የሚያበረታታ ነው።
የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትም በከተማዋ በተለያዩ ዘርፎች የሚከናወኑ የበጎ ተግባራትን በማስተባበር የዜጎችን ተሳትፎ እያሳደገ ይገኛል።
በጎ ፈቃድ የሚጀምረው ከራስ ጊዜና ጉልበት ሲሆን፣ ውጤቱ ግን ለመላው ማህበረሰብ ስለሆነ ተሳትፏችን አጠናክረን እንቀጥል። | 72 |
| 15 | No text... | 134 |
| 16 | ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የደህንነት ካሜራ ተመርቆ ሥራ ጀመረ
ወልቂጤ፤ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የደህንነት ካሜራ በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
የደህንነት ካሜራው በከተማዋ የሚከሰቱ የወንጀል ተግባራትን አስቀድሞ ለመከላከል፣ ወንጀል ተፈጽሞ ሲገኝም የምርመራ ሥራን ለማጠናከርና ወንጀል ፈጻሚዎችን በሕግ አግባብ ለማስጠየቅ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በሥራ ላይ ማዋል ወሳኝ ነው።
በተለይም በባጃጅ ላይ የሚፈጸም ዝርፊያ፣ በተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ዝርፊያዎችና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶችን ከመከላከል አንጻር የደህንነት ካሜራዎች ጠቀሜታቸው ከፍተኛ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል።
የደህንነት ካሜራዎቹ በስማርት ፖል ቴክኖሎጂ በመታገዝ በተመረጡ የከተማዋ አካባቢዎች መተከላቸው፣ የወንጀል ተግባራትን በቅድሚያ ለመከላከልና የተፈጸመ ወንጀልን በፍጥነት ለመመርመር የሚያስችል የቴክኖሎጂ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
ከንቲባው አክለውም፣ ከተሞች እያደጉና የነዋሪዎች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ሊከሰቱ የሚችሉ የወንጀል አፈጻጸሞችን በብቃት ለመከላከል ዘመኑን የሚመጥን ቴክኖሎጂን መጠቀም እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
የደህንነት ካሜራዎችን በከተማዋ በተመረጡ ስፍራዎች በማስፋፋት ወንጀልን አስቀድሞ መከላከል፣ የፖሊስን የሥራ ጫና መቀነስና የምርመራ ሥራን በመረጃ ማጠናከር የሚያስችሉ ተጨማሪ ሥራዎች እንደሚከናወኑም አስታውቀዋል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ በቀለ በበኩላቸው፣ የደህንነት ካሜራ የስማርት ሲቲ አንዱ መለኪያ መሆኑን ገልጸው፣ ፖሊስ ይህንን የቴክኖሎጂ አቅም በአግባቡ በመጠቀም ለማኅበረሰቡ በሰላምና ደህንነት ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት ሊሰጥ ይገባል ብለዋል።
አቶ ታደለ አክለውም ከተሞችን ከስማራት ሲቲ እሳቤ ጋር በማስተሳሰር ከማዘመን እና ዘመኑ ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ አኳያ የደህንነት ካሜራዎች የትራፊክ ቁጥጥር፣ የፀጥታ ስራዎችን፣ ወንጀሎችን ለመከላከል ያግዛል ብለዋል።
በወልቂጤ ከተማ ማኅበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከል ስልት ተግባራዊ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ ፖሊስ ከነዋሪው ሕዝብ ጋር በመደጋገፍ ባከናወናቸው ተግባራት ከተማዋ ለነዋሪዎቿም ሆነ ለሚጎበኟት እንግዶች ሰላማዊና ምቹ ከተማ እንድትሆን አስተዋጽኦ ማድረጉን አቶ ታደለ ገልጸዋል።
የወልቂጤ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መንዚላ አህመድ በበኩላቸው፣ የደህንነት ካሜራው የከተማዋን የሰላምና ደህንነት ሥራ ከማጠናከር ባሻገር በተቋማት ውስጥ የሚሰጠውን አገልግሎት ግልጽ፣ ተጠያቂነት ያለውና ቀልጣፋ ለማድረግ የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።
አፈ ጉባኤዋ አክለውም፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሕዝብን ደህንነት ከማረጋገጥ ባለፈ ተቋማት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በተገቢው ሁኔታ እንዲወጡ የሚያግዝ የቁጥጥርና የተጠያቂነት መሣሪያ መሆኑን ጠቁመው፣ ቴክኖሎጂው ከሕግና ከሥነ ምግባር መርሆች ጋር ተጣጥሞ ለሕዝብ ጥቅም እንዲውል ተቋማት በኃላፊነት ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል።
የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጅን ይታገሱ ደሳለኝ እንደገለጹት፣ በከተማው የፖሊስ ጽሕፈት ቤት ሕንፃ ላይ የደህንነት ካሜራ ተተክሎ የተቋሙን ደህንነት ከመቆጣጠር ባሻገር በመደበኛ የሥራ ሰዓት ሠራተኞች ለአገልግሎት ፈላጊዎች በራቸውን ክፍት አድርገው ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆኑን ለመከታተልም እያገለገለ ነው።
የደህንነት ካሜራው በፖሊስ ጽሕፈት ቤት ውስጥ የሚከናወኑ የሥራ እንቅስቃሴዎችንና የሠራተኞችን የሥራ አፈጻጸም ለመከታተል እንዲሁም የተቋሙን ንብረትና ሕንፃ ደህንነት ለመጠበቅ ጠቀሜታ እያለው መሆኑን አዛዡ ገልጸዋል።
የተገጠሙት የደህንነት ካሜራዎች ወንጀልን ቀድሞ በመከላከል ዜጎች ደህንነት ተሰምቷቸው እንዲኖሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡
በከተማዋ በሁሉም አካባቢዎች በፖሊስና በሕዝብ ትብብር አስተማማኝ ሰላምን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የገለጹት አዛዡ፣ ማኅበረሰቡ ከፖሊስ ጎን በመቆም በወንጀል መከላከል ሥራ ላይ የሚያደርገውን ንቁ ተሳትፎ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በአጠቃላይ፣ የደህንነት ካሜራው በወልቂጤ ከተማ የሰላምና ደህንነት ሥራን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ወንጀልን በቅድሚያ ለመከላከል፣ የምርመራ ሥራን ለማጠናከር፣ የፖሊስን የሥራ ጫና ለመቀነስና ከተማዋን የበለጠ ሰላማዊ፣ ደህንነቷ የተጠበቀና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያግዝ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የከተማ የፊት አመራሮች፣ የካቢኔ አካላት፣ የከተማ የፀጥታ የዘርፍ አመራሮች፣ ተሳትፈዋል። | 108 |
| 17 | No text... | 151 |
| 18 | በወልቂጤ ከተማ የኮሪደር ልማትና የመሬት ጥበቃ ሥራዎች በመስክ ተጎበኙ
ወልቂጤ፤ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራና የከተማ መሬትን ከሕገ-ወጥ ወረራ የመጠበቅ ሥራዎች በመስክ ተጎብኝተው ተገምግመዋል።
የመስክ ጉብኝቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጨምር ሀይሌ፣ የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትብለጥ እስጢፋኖስ፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ በቀለ እንዲሁም የክልልና ዞን የዘርፉ ባለሙያዎች፣ የከተማው አስተባባሪ አካላትና የማዘጋጃ ቤት ማኔጅመንት አካላት አድርገዋል።
በጉብኝቱም በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማትና የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች በተቀመጠላቸው ዲዛይን፣ ደረጃና መስፈርት መሠረት እየተፈጸሙ መሆናቸው ተመልክቷል።
ቀሪ ሥራዎችም በፍጥነት፣ በጥራትና በተቀመጠላቸው ደረጃ እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጨምር ሀይሌ እንዳመለከቱት፣ በወልቂጤ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የከተማዋን የአገልግሎት አቅም፣ ውበትና የነዋሪዎችን የኑሮ ምቾት ከማሻሻል ባለፈ ዘመናዊ የከተማ ገጽታ ለመፍጠር ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው።
በተለይም የሁለተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ወልቂጤን ምቹ፣ ውብና ዘመናዊ ከተማ ከማድረግ ባለፈ የንግድ፣ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማነቃቃት የሚያስችል በመሆኑ፣ ሥራው በተቀመጠው ዲዛይን፣ ደረጃና ጥራት እንዲጠናቀቅ በትኩረት መሠራት እንዳለበት ጠቁመዋል።
የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትብለጥ እስጢፋኖስ በበኩላቸው፣ የከተማዋ የልማት ሥራዎች በዕቅድ እንዲመሩና በተወሰነላቸው ጊዜ፣ ጥራትና ደረጃ እንዲጠናቀቁ የቴክኒክ ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የከተማ መሬት ለታቀደለት የልማት ዓላማ እንዲውልና ከሕገ-ወጥ ወረራና ግንባታ እንዲጠበቅ በተቀናጀ መንገድ መሥራት የወልቂጤን የወደፊት የከተማ ልማት አቅም ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመስክ ጉብኝቱ ከተማ መሬትን ከሕገ-ወጥ ወረራ ለመጠበቅ እየተወሰዱ ያሉ የቁጥጥርና የሕግ እርምጃዎችም ተገምግመዋል።
በተለይ ለልማት የተያዙ መሬቶች እንዳይወረሩ፣ ሕገ-ወጥ ግንባታዎች እንዳይካሄዱና የከተማዋ የወደፊት የልማት አቅም እንዳይጎዳ የሚደረጉ ጥረቶች በትኩረት እንዲቀጥሉ ተጠቁሟል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ በቀለ እንዳሉት፣ የከተማዋ የልማት አቅም እንዲጠናከር የአመራር ትኩረት፣ የተቀናጀ አፈጻጸምና የሕዝብ ተሳትፎ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል።
አቶ ታደለ አክለውም፣ የከተማ መሬትን ከሕገ-ወጥ ወረራና ግንባታ መጠበቅ የአሁኑን የልማት ሥራ ብቻ ሳይሆን የወልቂጤን የወደፊት የከተማ ልማት አቅም ከመጠበቅ ጋር የሚያያዝ መሆኑን በመጥቀስ፣ አመራሩ፣ ባለሙያዎችና ማኅበረሰቡ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአጠቃላይ፣ የመስክ ጉብኝቱ የወልቂጤ ከተማን የልማት አፈጻጸም በተግባር ለመገምገም፣ የሚጠናከሩ አቅጣጫዎችንና የሚስተካከሉ ክፍተቶችን ለመለየት እንዲሁም ቀሪ ሥራዎችን በተቀናጀ አመራር፣ በተከታታይ ክትትልና ቁጥጥር በጥራትና በወቅቱ ለማጠናቀቅ አቅጣጫ የተቀመጠበት ሆኗል። | 145 |
| 19 | No text... | 145 |
| 20 | በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶች በዞኑ የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶች መጎብኘታቸው የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤውን በወልቂጤ ከተማ አካሄዷል
የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናስር ሀሰን በጉባኤው ተገኝተው እንዳሉት የዞኑ የባህል አምባሳደር በየጊዜው እጅግ አዳጊና አዳዲስ ስራዎች እየሰሩ ሲሆን ይህም ከዞኑ አልፎ ለክልሉ ጭምር ትላልቅና አስተማሪ ተውኔቶች በመስራት የጉራጌ ማህበረሰብ ቱባ ባህሎች በማውጣት ውጤታማ ስራዎች እየሰሩ መሆኑም ተናግረዋል።
የባህልና ቱሪዝም ቁርኝት አንዱ ለአንዱ የሚመግብ ሲሆን ህዝቦች ከቅርስ ጋር በማስተሳሰር ትልቅ ሚና ያለው ዘርፍ መሆኑም ተናግረዋል።
የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ መሰረት አመርጋ እንዳሉት መምሪያው በ2018 በጀት አመት 15 ግቦችን ይዞ በርካታ ስራዎች ሲያከናውን እንደነበረም አስረድተዋል።
የጉራጌ ማህበረሰብ በርካታ ጸጋዎች ያሉት ሲሆን በተለይ በባህሉ ዘርፍ ላይ ለዘመናት ማህበረሰቡ አበልጽጎ ያቆያቸውን ባህሎቻችን በዘመናት ሂደት ውስጥ ዘመናዊነት ተጭኗቸው እየደበዘዙ የነበሩ ባህሎች የነበሩ እንደሆነም ተናግረው እነዚህ ወደ ከፍታ እንዲመጡ ባለፈው አመት በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውም አመላክተዋል።
በበጀት አመቱ የበለጠ ጎልተው እንዲወጡ ከተደረጉ ባህሎች መካከል ነቆ የልጃገረዶች በዓል ሲሆን ይህ ባህል እየደበዘዘ መጥቶ የነበረ ሲሆን ዘንድሮ በሁሉም መዋቅሮች የበለጠ ጎልቶ እንዲወጣና እንዲከበር ተደርጓል ብለዋል።
ባህላዊ ምግቦች ፣መድሐኒቶች ፣ባህላዊ የዌጌሻ ስርአት ፣ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ ፣ባህላዊ የማዕረግ ስሞች ላይ መረጃዎች የማሰባሰብና የማደራጀት ስራ መሰራቱም አብራርተው ሀገር በቀል እውቀቶች ከማልማት አኳያ ባህላዊ መድሐኒቶች ምንድናቸው የሚለውን በሙህር አክሊል ወረዳ በምርጥ ተሞክሮ ደረጃ ተቀምሮ ተሰንዶ ተቀምጧል ብለዋል።
ባህላዊ የወጌሻ ጥበብ በተመለከተ እዣ ወረዳ የፈንቅር ቤተሰብ መነሻ በማድረግ በምርጥ ተሞክሮ ተሰንዶ የተቀመጠበት አግባብ መኖሩም ያመላከቱት ወይዘሮ መሰረት ባህላዊ ምግቦቻችን በሁሉም አካባቢዎች እንደየዜዬዎቻችን ተተንትነውና ተሰንደው ተቀምጠዋል ብለዋል።
ይህም ደራሲዎች ፣ተመራማሪዎች በትምህርት ሴክተሩ ላይ ለተጀመረው የጉራጊኛ ቋንቋ ትምህርት ለማጎልበትና በስርአተ ትምህርት ለማካተት እንደነዚህ አይነት ጥበቦች በተገቢው ተሰንደው ማስቀመጥ መሰረታዊ ጉዳይ አድርገው የሰሩበት እንደሆነ አመላክተዋል።
የጉራጌ ጀፎረ ከማስተዋወቅና ከማልማት ባሻገር በዩኒስኮ እንዲመዘገብ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን የጥናትና ምርምር ስራ መሰራቱም አመላክተው በዘንድሮ አመት ወደ 315 ኪሎ ሜትር ጀፈረ ማልማታቸውምና ወደ መረጃ ቋት በማስገባት አብዛኛዎቹ የይዞታ ማረጋገጫ እንደተሰጣቸውም አስረድተዋል።
ሌላው የጉራጌ ክትፎ በዩኒስኮ ለማስመዝገብ ወደ መጨረሻው ምዕራብራፍ ላይ መድረሱም ያስታወቁት ወይዘሮ መሰረት ከባህል አካያ ሰፋፊ ስራዎች መስራት የተቻለ እንደሆነ ጠቅሰው ከ139 በላይ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች በማሰባሰብ ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ስራ መሰራቱም አስረድተዋል።
መንግስት ለቱሪዝም ሴክተር ለሰጠው ከፍተኛ ትኩረት መነሻ በማድረግ በዞኑ ያሉ የቱሪዝም ጸጋዎች በተለያዩ ሚዲያዎች በማስተዋወቅ ረገድ ሰፊ ስራዎች የተሰራበት እንደሆነም ተናግረዋል።
የመስቀልና የአረፋ በዓል ፌስቲቫሎች ባለፉት 8 አመታት በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች በድምቀት ማክበር ተችሏል ብለው በዓሉን ተከትሎ ወደ ዞኑ የሚመጡ ቱሪስቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ብለዋል።
ባለፈው በጀት አመት 1ነጥብ 2 ሚሊየን ቱሪስቶች ወደ ዞናችን መጥተዋል ብለው በእነዚህም ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ እንደተገኘ መረጃዎች ያመላክታሉ ብለዋል።
በእደ ጥበብ ፣በክብረ በዓላት ፣በሽመና ፣ በስንደዶ ፣ በሸክላ ፣በተለያዩ ዘርፎች ላይ ጉራጌ ዞን የታደለ እንደሆነም አስረድተው እነዚህም ቱሪስቶች ሲመጡ በመግዛት በመልበስና በማስተዋወቅ እንዲሁም በአገልግሎት ዘርፍ ሙሉ ወርቅ ሪዞርትን ጨምሮ የቱሪስት መዳረሻ ሆቴሎች እየጨመሩ የመጡበት እንደሆነና በዞኑ የቱሪስቶች ፍሰት እየጨመረ መምጣቱም ተናግረዋል።
የማህበረሰቡ የዘመናት ጥያቄ የነበረው የጉራጊኛ ቋንቋ ለማበልጸግ ከመጥፋት ወደ ማንሰራራት የመጣበት እንደሆነም ተናግረው በዚህ ዘርፍ በባለፉት አመታት የስራ ፣የሚዲያና የትምህርት ቋንቋ እንዲሆን በምክር ቤት ጸድቆ እየተሰራበት እንደሆነም አብራርተው በዘርፍ ተቋሙ ግንባር ቀደም በመሆን እየሰራበት ይገኛል ብለዋል።
በመድረኩ የተገኙ አንዳንድ ባለ ድርሻ አካላቶች በሰጡት አስተያየት በዞኑ በቋንቋ ፣በባህልና በቱሪዝም ዘርፎች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል።
በመጨሻም የ2019 በጀት ዓመት የስራ እቅድ ግብ ስምምነት ከመዋቅሮች ጋር በመፈራረምና በ2018 በጀት አመት ስራ አፈፃፀም የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ በከተማ ደረጃ 1ኛ የእምድብር ከተማ አስተዳደር ፣2ኛ ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር 3ኛ የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በወረዳ ደረጃ 1ኛ የእኖር ወረዳ ፣2ኛ የቸሃና የእዣ ወረዳዎች 3ኛ የምሁር አክሊል ወረዳ እንዲሁም የጉመር ወረዳ ልዩ ተሸላሚ በመሆንና ለአጋር ተቋማቶች እውቅና በመስጠት ጉባኤው ተጠናቋል ሲል የዘገበው የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ነው። | 108 |
