fa
Feedback
Wolkite city Administration Government Communication Affairs Office

Wolkite city Administration Government Communication Affairs Office

رفتن به کانال در Telegram

ህዝብና መንግስትን ድልድይ ሆነን እናገለግላለን ‼️

نمایش بیشتر
644
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
-230 روز

در حال بارگیری داده...

کانال‌های مشابه
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+8
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+8
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+13
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+65
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+41
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+13
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+26
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+34
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+274
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '250
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '240
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+143
در 1 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
12 ژوئیه+3
11 ژوئیه0
10 ژوئیه0
09 ژوئیه0
08 ژوئیه0
07 ژوئیه+1
06 ژوئیه0
05 ژوئیه0
04 ژوئیه+1
03 ژوئیه+1
02 ژوئیه+1
01 ژوئیه+1
پست‌های کانال
2
ሁለተኛ ቀኑን የያዘው የሐምሌ ወር የገቢ ግብር አሰባሰብ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል!!! #ወልቂጤ|ሐምሌ 2/2018 ዓ.ም. ሁለተኛ ቀኑን የያዘው የሐምሌ ወር የገቢ ግብር አሰባሰብ በጉራጌ ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ተጠናክሮ ቀጥሏል። የግብር አሰባሰብ በስኬታማነት እንዲከናወን አጠቃላይ የአመራር አካላት ድጋፋዊ ክትትል እና የንግዱ ማህበረሰብ ቅንጅት የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገለጿል። የወልቂጤ ከተማ ፈጣን እድገት እና የልማት ጉዞ ለማስቀጠል ግብር መሰረታዊ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ተመላክቷል። በሶስቱም ክፍለ ከተሞች የአንድ ማእከል የአገልግሎት መስጫ ማእከል ተዘጋጅቶ ግብር ከፋዮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እየተሰጣቸው ይገኛል ። ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝባችንን የልማት ጥያቄዎች በራስ አቅም በብቃት ለመመለስ፣ ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ፣ ለሀገር ዘላቂ ልማትና ሁለንተናዊ ብልጽግና ስኬታማ ለማድረግ ቁልፍ ሚና አለው በዘንድሮው የደረጃ ለ የግብር አሰባሰብ ላይ የቴክኖሎጂ አቅምን በመጠቀም ለአሰራር ግልፅ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት በታቀደው መሰረት መፈፀም እንደሚገባም ተመላክቷል።
137
3
+6
بدون متن...
151
4
የተቋማችን ሥኬት የሚረጋገጠው በምንሰጠው ቀልጣፋና ተገልጋይ ተኮር አገልግሎት ላይ ነው:- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ ሐምሌ 1/2018ዓ.ም[ወልቂጤ] እንደ ሀገር ታማኝ ግብር ከፋይ የጉራጌ ማህበረሰብም መሆኑ የሚታወቅ ነው በዚህ ማህበረሰብ መካከል ተገኘቼ በማስጀመሬ ኩራት ይሰማኛል ሲሉ ጠቅሰዋል። ግብር ከፋዩ ፈጣንና ቀልጣፋ የሆነ አገልግሎት የሚያገኙበትን ምቹ ሁኔታዎች በመመቻቸቱ በተጠቀሰው ጊዜ በመገኘት ግብራቸውን በአግባቡ በመክፈል ካላስፈላጊ ቅጣት ልትጠበቁ ይገባልም ብለዋል። የክልላችን ግብር ከፋዮች እናንተ የምትከፍሉት ግብር ለተለያዩ የመሠረተ ልማት አገልግሎት የሚውል መሆኑን አውቃችሁ ግብራችሁን በተገቢው መክፈል ይጠበቅባችኋል ሲሉ ወይዘሮ ቀመሪያ አስገንዝበዋል። የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናስር ሀሰን እንደገለፁት የንግዱ ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ግብር በአግባቡና በወቅቱ በመክፈል የዜግነቱን በመወጣት የልማት ተሳታፊዎች መሆን ይገባል ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል። የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራር ከድር በማስጀመሪያወ መርሐግብር ላይ ተገኝተው እንደገለፁት ግብር የልማት መሰረት ነው የሰላም፣ የልማት የመልካም አስዳደር ቁልፍ ግብር ነው መሆኑን ገልጸው የገቢ አማራጮችን በማስፋፋት ከማህበረሰብ የሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ለማሳለጥ ከ2018 የተሻለ የገቢ አሰባሰብ በመዘርጋት የተሻለ ልማት ልናረጋግጥና ከተማችን ከአቻ ከተሞች ተወዳዳሪ እንድትሆን ግብርን በአግባቡ ሊከፈል ይገባልበ በየደረጃው የሚገኙት የገቢ እና የንግድና መዋቅር አመራር እንዲሁም ባለሙያዎች ስራው እንዲሳካ በቅንጅት መሥራት ይጠበቃልም ብለዋል። የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚነወር ሀያቱ እንደገለፁት ግብርን በአግባቡ ሰብስቦ ለልማት ለማዋል እንዲቻል ገቢ መሰብሰብ አስፈላጊ በመሆኑ ማህበረሰቡ ለሚከፍለው ግብር ቀልጣፋ አገልግሎት መሥጠት ይገባል ሲሉ ጠቅሰው አገልግሎቱን በአንድ ቦታ እንዲያገኙና ለአላስፈላጊ ወጪ እንዳይዳረግ እየተሰራ እንደሚገኘና የንግዱ ማህበረሰብ ግብሩን በአግባቡ ከፍሎ መንግሥትም ለታለመለት አላማ እንዲያውል በታማኝነት ግብር መክፈ እንደሚገባና እንደ ዞን 15 መዋቅሮች 57 የክፍያ ማዕከል በማዘጋጀት የግብር፣የንግድ ፈቃድ እድሳትና መሰል አገልግሎቶች እየተሰጡ ይገኛል ሲሉ አብራርተዋል። የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይድረሱ ተስፋዬ ሁለንተናዊ ብልፅግናችን ለማረጋገጥ በከተማችን የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግር ምላሽ ለመስጠት በወቅቱ የሚሰበሰብ ግብር አስፈላጊ ነው ያሉ ሲሆን ባሳለፍነው በጀት ዓመት በከተማችን በመደበኛና በማዘጋጃ የገቢ አርዕስቶች 1.2 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 1.18 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን ጠቅሰው በተሰበሰበው ገቢ ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች በሰራታቸው ጠቁመው በበጀት አመቱ የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን አስቀጥለን ድክመቶችን አርመን ያደገ ገቢ በመገንባት በከተማችን የተጀመሩ የልማት ስራዎችን እንደሚጠናከሩ አውስተው በተሻሻለው የክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 39/2018 መሰረት የደረጃ "ለ"ከፋይ በየግብር ዓመቱ ከሐምሌ ወር መጨረሻ ሊከፍሉ ከሚገባው ግብር ላይ በየሶስት ወሩ የከፈሉት እየቀነሱ ቀሪውን ግብር ለእያንዳንዱ በጀት ዓመት ከሐምሌ 01 እስከ ሐምሌ 30 እንደሚከፈልና የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋይ ደግሞ የግብር ዓመቱ ከተጠናቀቀበት ጊዜ አንስቶ ባሉት አራት ወራት ውስጥ የሂሳብ ሪፖርት በሚያቀርቡበት ወር መጨረሻ በሂሳብ ሪፖርቱ መሰረት ሊከፍሉ ከሚገባው ግብር ላይ በየሶስት ወሩ የከፈሉት ተቀንሶ ቀሪውን ግብር ከሐምሌ 01 እስከ ጥቅምት 30 ድረስ በተዘጋጀው የክፍያ ማዕከል በመገኘት የክያችሁን እንድትከፍሉና የንግድ ፈቃዳችሁን እንድታድሱ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ግብር ሲከፍሉ ያገኘናቸው የከተማው ነዋሪዎች አቶ ሚካኤል ዳዊትና ወይዘሮ ማረግነሽ ባዴ በሰጡት አስተያየት ግብር በመክፈል ክብር እንጂ ውድቀት እንደሌለው ጠቅሰው ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ባህል ተደርጎ መወሰድ እንዳለበትና ግብር በመክፈል የልማት ተጠቃሚ መሆን መቻል አለብን የምናየው ልማት እንዲቀጥል ግብርን በአግባቡ መክፈል ይጠበቅብናል ሲሉ ገልፀዋል። በማስጀመሪያው ወቅት ቀድመው ተገኘተው ግብር ለከፈሉ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።
144
5
+5
بدون متن...
123
6
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሱፐርቪዥን ቡድን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት በ2018 ዓ.ም በተቋሙ የተከናወኑ ተግባራት ምልከታ አደረጉ። ‎ ‎ሀምሌ 1/2018ዓ.ም [ወልቂጤ ] ‎ ‎የክልሉ ሱፐርቪዥን ቡድን በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት በ2018 ዓ.ም በኮሙዩኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፍ በተለያዩ ጊዜያት በተቋሙ የተከናወኑ ስራዎች ተመልክተዋል። ‎ ‎በህዝብ በመንግሥት ቀጥተኛ ግኑኝነት በመፍጠር ተዓማኒነት ያለው መረጃ ተደራሽ በማድረግ በህዝብ ግንኙነት ስራዎች ፣የማህበራዊ ሚዲያና የመረጃ ስርጭት ተግባራት እንዲሁም የህዝብ አስተያየት ላይ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ምክት ሀላፊና የመንግሥት የመረጃ ማዕከል የዲጅታል ሚዲያ አስተዳደር ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብርሃም አለሙ ገልፀዋል። ‎ ‎የመረጃ ጥራትና ቁጥጥር በመንግሥት በህዝብ ተሳትፎ የተከናወኑ የልማት ስራዎች በሀላፊነት በወቅቱ ተደራሽ በማድረግ ወቅቱ የደረሰበት የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባም አስገንዝቧል። ‎ ‎የመረጃና የቴክኖሎጂ ዘመን በመሆኑ ቀጣይ በበለጥና በተሻለ ትኩረት በመስጠት በዘርፉት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በልዩነት ተግባራትን አሳልጦ መስራት እንደሚገባም አስገንዝቧል። ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እስክንድር እንድርያስ እንደተናገሩ በበጀት አመቱ በሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን በከተማው የተሰሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ለቅሞ መረጃን ተደራሽ በማድረግ ፈጣንና ወቅቱን ያማከለ ስራ መሥራቱን ተናግረዋል። ‎ ‎ተቋሙ የተቀመጠለት ዓላማና ግብ በሚገባ በመረዳት ህዝብና ማህበረሰብ የሚጠቅም በልማቱ ተሳትፎ ከፍ በሚያደርጉ ተግባራት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መምራት መቻሉን አንስተዋል። ‎ ‎ቀጣይ የተሻለ ስራ በመስራት በኮሙዪኒኬሽን እና በሚዲያ ስራው ላይ በሚፈለገው ልክ የተቀመጠውን ግብ ከዳር ለማድረስ ጠንካራ የሚዲያው ሰራዊት በመፍጠር ማህበረሰባችንን ሊጠቅም የሚችል ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ‎ ‎የክልሉ ሱፐርቪዥን ቡድን በምልከታው ከተማ አስተዳደሩ ለተቋሙ የሚያደርገው ድጋፍን አቅም አንደፈጠረለት አመላክተው በቀሪ መሟላት የሚገባቸውን በማሟላት ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አመላክተዋል። በከተማው የተጀመሩ መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋት፣አፈፃፀም ብቃትን በማሳደግ ፣የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል ። ‎ ‎ለህብረተሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጧል።
101
7
+5
بدون متن...
90
8
ማእከሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ ለኅብረተሰቡ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ እና ግልጽ ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ መሆኑን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዮች ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ ገለጹ ሀምሌ 1/2018(ወልቂጤ)፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ፣ የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰንና የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች የወልቂጤ መሶብ አንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ተዘዋውረው ጎብኘተዋል የወልቂጤ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን እርካታ እያሳደገ መሆኑ በጉብኝቱ ተመላክቷል። የወልቂጤ መሶብ አንድ ማእከል የገቢ አሰባሰብ አገልሎትን ጨምሮ በውሰጡ በርካታ የመንግሥት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ስር በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ለዜጎች ፈጣንና ፍትሃዊ ምላሽ ለመስጠት የተዘረጋ ዘመናዊ አሰራር መሆኑንም ተገልጿል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ2030 ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተያዘውን ሀገራዊ ተልዕኮ ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው ተገልጿል። በጉብኝቱ ወቅት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ እንደገለፁት ማዕከሉ የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ በማቅረብ ተገልጋዮች ከተቋም ወደ ተቋም የሚያደርጉትን ውጣ ውረድ በመቀነስ ጊዜን፣ ወጪንና እንግልትን በመቀነስ የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ከፍ እንደሚያደርግም ገልጸዋል። የመሶብ አንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥን የለውጡ መንግስት ለማዘመን ባደረገው ጥረት ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ሲሆን፣ የተገልጋዮችን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ አገልግሎቶችን በመስጠት የተገልጋይ እርካታን እያጎለበተ መሆኑንም አመላክተዋል። ባጭር ጊዜ ስራ የጀመረው የወልቂጤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሁን እየሰጠ ያለው ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚያስደንቅ መሆኑ ገልጸዋል። የወልቂጤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሄኖክ፤ ባስጎበኙበት ወቅት እንዳሉት ቀደም ሲል በተለያዩ ቦታዎች ተበታትነው የነበሩ አገልግሎቶች በአንድ ቦታ መሰጠታቸው፣ ማኅበረሰቡ በርካታ አገልግሎቶችን በአጭር ጊዜ ማግኘት በመቻሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እየፈታ መሆኑን ገልጸዋል። በአገልግሎት ፈላጊውና በአገልግሎት ሰጪው መካከል የነበረውን የሦስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት በማስቀረት ማዕከሉ ዘላቂ መፍትሔ እየሰጠ መሆኑን አመልክተዋል። ለማእከሉ ሰራተኞችም ሆነ ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አካባቢ መፈጠሩን የጠቀሱት ስራ አስኪያጁ እጅጉን ባጠረ ግዜ ውስጥ ባገኙት አገልግሎት ረክተውና ተደስተው እየተመለሱ መሆኑን ገልፃለች። #የአንድ_ማዕከል_አገልግሎት #ወልቂጤ_ከተማ #መልካም_አስተዳደር
115
9
+8
بدون متن...
173
10
‎በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የክረምት ወራት የገቢ አሰባሰብና የ2019 ዓ.ም የንግድ ፈቃድ እድሳት ሥራዎችን በንቅናቄ ለማሳካት የጋራ የውይይት መድረክ መካሄዱ ተገለፀ። ‎ ‎ሰኔ 30/ 2018 [ወልቂጤ] ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት እና የወልቂጤ ከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ጽህፈት ቤት በጋራ በመሆን የ2019 ዓ.ም የንግድ ሥራ ፈቃድ አሰጣጥ፣ እድሳት እና የክረምት ወር ገቢ አሰባሰብ ሥራዎችን በተቀናጀ እንቅስቃሴ ለማሳካት የውይይት መድረክ አካሂደዋል። ‎ ‎በወቅቱ የ2017 ዓ.ም የገቢ አፈጻጸምና የ2018 ዓ.ም የገቢ አፈፃፀም እቅድ እንዲሁም የንግድ ፈቃድ እድሳት በተመለከተ በሁለቱም ተቋማት በኩል ቀርቦ ሰፊ ውይይት እንዲደረግበት ተደርጓል። ‎ ‎ የንቅናቄ መድረኩን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድርና የሁለቱ ተቋማት ሀላፊዎች በጋራ መርተውታል። ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር እንደገለፁት ግብር ከፋዩ ማህበረሰባችን ግብርን በወቅቱ ለመክፈል የነበረው መነቃቃትና የነበረው የአመራሩ የአፈፃፀም ሂደት አመስግነው ግብር ለሀገርና ለአካባቢ ልማት ወሳኝ በመሆኑ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠትም ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። ‎ ‎እንዲሁም የ2018 የግብር አሰባሰብና የንግድ ፈቃድ እድሳት ሥራዎች በተለይ ለደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች በተወሰነ ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቁ በትኩረት እንደሚሠራ አሳስበዋል። ‎ ‎በ2017 ዓ.ም አፈጻጸም ውስጥ የታዩ ድክመቶች በቀጣይ እንዳይደገሙ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሠሩም ጠይቀዋል። ‎ ‎አቶ ሙራድ አክለውም በአዲስ መንፈስ ወደ ስራ በመግባትና ልማትን በማስቀጠል ማህበረሰባችን ተጠቃሚ ለማድረግ በጊዜ የለኝም ስሜት ስንሰራ ነው ሱሉም ተደምጠዋል። ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ታደለ በቀለ በበኩላቸው የነበረው የ20 ቀን እቅድ አፈፃፀም መልካም እንደነበረ ገልጸው የገቢ አሰባሰብ እና ንግድ ፍቃድ እድሳት በተገቢውና በሚፈለገው ልክ ለማጠናቀቅ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎አምና የነበረው የአፈፃፀም ስልት እሰይ የሚባል ነበረ ያሉት አቶ ታደለ ዘንድሮም አጠናክሮ በማስቀጠል ዳግም ከተማችን ማስጠራት ይኖርብናልም ብለዋል። ‎ ‎የከተማው የገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይድረሱ ተስፋዬ በበኩላቸው ገቢ ማለት ከማንኛውም ምንጭ በጥሬ ገንዘብ ወይም በዓይነት የሚገኝ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መሆኑን ገልጸው በከተማው 6389 የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች መሆናቸውን አስረድተዋል። ‎ ‎ ሕገ-ወጥ ንግድ የሚያካሄዱ ነጋዴዎችን ሕጋዊ ለማድረግ በተቀናጀ መንገድ መሥራት እንዳለበት እና ግብርን እንደ ዕዳ ሳይሆን እንደ ሀገር ልማት መመልከት እንደሚገባ የከተማ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ጠቁሟል። ‎ ‎ እንደ ተሳታፊዎቹ ገለፃ በከተማው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየታየ ያለው የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የገቢ ግብርን በታማኝነት መክፈል ለራስም ጥቅም ያለው መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎በመድረኩ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ባለሙያዎች ፣ የከተማው አስፈፃሚ አካላት፣የከተማው አመራሮች፣ከቀበሌ የተወከሉ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የገቢዎችና የንግድ ልማት ጽ/ቤቶች ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል። ‎ ‎ተሳታፊዎች በሰፊው አስተያየት ከሰጡ በኋላ ለተነሱ ጉዳዮች በቂ ምላሽ ከመድረኩ ተሰጥቶ መድረኩ ተጠናቋል። ‎
136
11
+8
بدون متن...
128
12
የገቢ አቅምን በማሳደግ የአገልግሎት ጥራት የማሻሻል ስራ ቅድሚያ ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገለፀ። ‎ ‎ሰኔ 30/2018ዓ.ም [ወልቂጤ ] ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት አመት የተከናወኑ የእቅድ አፈፃፀም ስራዎች እና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ እቅድ ከከተማው የሴክተር መስሪያ ቤት ሀላፊዎች ጋር ገመገመ። ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር እንደገለፁት የከተማዋ እድገት እና ብልፅግና ለማረጋገጥ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረትና በህዝባችን ንቁ ተሳትፎ የተከናወኑ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ሁሉም በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል። ‎ ‎በነዋሪው የሚነሱ በመሠረተ ልማት ስራወች በመንገድ ስራ፣የመንገድ ከፈታና ጠረጋ፣የጠጠር መንገድ ዝርጋታ፣የመብራት መስመር ዝርጋታ እንዲሁም የንፁህ ውሃ አቅርቦት በከተማችን አንዳንድ አካባቢዎች ልየታ በማድረግ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተው ቀጣይ በተሻለ ለመስራት አጠናክረን በርብርብ ልንሰራ ይገባል ብለዋል። ‎ ‎በከተማ አስተዳደሩ በበጀት አመቱ ከ1.16 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ያነሱ ከንቲባው ከተማዋ ከአላት ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ እና ትልቅ ሀብት አንፃር ትኩረት ሰጥተን የምንሰራባቸው ስራዎች በመኖራቸው በ2019 በጀት ዓመት የግብር ስርዓታችን ፈትሸን ገቢያችንን ልናሳድግና ከተማዋን ከፍ በሚያደርጉ ተግባራት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አንስተዋል። ‎ ‎በመልሶ ማልማትና የመሬት ማኔጅመንት ስርዓታችን እንዲሁም ህገወጥነት ከመከላከል አንፃር ከባለፉት ጊዜያት ሲነፃፀር መልካም መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎ከተማዋ ተመራጭና ከሌሎች አቻ ከተሞች ተወዳዳሪ እንድትሆን ለማስቻል ፅዱና ከቆሻሻ የፀዳች ከተማ መፍጠር ሲቻል በመሆኑ የቆሻሻ ስርዓታችንን በሚገባ ፈትሸን በውጤት መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። ‎ ‎ተቋማት አገልግሎት በማዘመን ለማህበረሰቡ ከብልሹ አሰራር የፀዳ ስራ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ‎ ‎የልማት ፕሮጀክቶች ጥራት ክትትል ፣በስራ እድል ፈጠራ ፣የኑሮ ውድነት ከማረጋጋት አንፃር፣ህገወጥ የትራንስፖርት የታሪፍ ጭማሪዎች ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አንስተዋል። ‎ ‎ከተማዋ አሁን ያለችበት የልማት ጎዞ ለማስቀጠል የተጀመሩ የልማት ስራዎች በፍጥነትና በጥራት በማጠናቀቅ እና አዳዲስ የልማት ስራዎች ለማሳለጥ ከምንም ጊዜ በተሻለ ከከተማው ህብረተሰብ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አክለዋል ።ለዚህም ተግባር መሳካታ ተቋማት የራሳቸው ተልዕኮ እና ራዕይ በመረዳት ህዝቡን በታማኝነት ሊያገለግሉ ይገባል ሲሉ አቶ ሙራድ ተናግረዋል። ‎ ‎በግምገማ መድረኩ የተቋም ስራ ሀላፊዎች እንደተናገሩት በእቅድ ተይዘው የሚከናወኑ ተግባራት የህዝቡን የሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ቅድሚያ በመስጠት በቅንጅት መምራት ይገባል ብለዋል። ‎ ‎የህዝብና የመንግስት ሀብት ንብረት አያያዝ ላይ የሚስተዋሉ ውስንነቶች ለይቶ ከብክነት መታደግ እንደሚገባ አንስተዋል። ‎ ‎በመጨረሻም በ2018 በጀት ዓመት ያልተከናወኑ ተግባራት በቀጣይ 2019 በጀት ዓመት የእቅድ አካል በማድረግ ተግባራትን በውጤት መገምገም እንደሚገባ ተጠቁሞ መድረኩ ተጠናቋል።
131
13
+6
بدون متن...
183
14
የ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ18566 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ ። ‎ ‎ሰኔ 27/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) ‎ ‎ የጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ "በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሀ ግብርና የበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ መርሀግብር በጉብሬ ክፍለ ከተማ ኤዋንና ጭቋራ ቀበሌ በሙራ መንደር ተካሔደ ። ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕድሜና ፆታ ሳይገድበው የሰብዓዊነት መርህን ብቻ መሠረት በማድረግ የሚከናወን ተግባር ነው ብለዋል። ‎ ‎በከተማችን በባለፈው የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተከናወኑ የስምሪት መስኮችና አዳዲስ ኢንሼቲቮች በርካታ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ‎ ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ሀላፊና ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ታደለ በቀለ በመርሀ ግብሩ ላይ በአስተላለፉት መልዕክት በበጋው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች በርካታ በጎ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው አሁን በክረምቱ መርሀግብር በተሻለ ሰርተን ህብረተሰባችንን የምናገለግልበት ነው ብለዋል። ‎ ‎በጎ ተግባር ከሰውና ከፈጣሪ ዘንድ የሚያስመሰግን ስራ በመሆኑ በመንግሥት ልዪ ድጋፍና በህዝባችን ንቁ ተሳትፎ በጉልበት ፣በገንዘብ እና በሀሳብ ሁሉም የበኩሉን የሚወጣበት ትልቅ እድል ነው ሲሉ አቶ ታደለ አስረድተዋል። ‎ ‎የበጎ ፈቃድ ተግባር የመርሀ ግብርና የቁጥር አለመሆኑ የገለፁት የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ትብለጥ እስጢፋኖስ ሲሆኑ እጅግ በጣም ደስ የሚል የህሊና እርካታ ሊሰጥ የሚችል የመንፈስ እርካታ ያለው ነው ሲሉ ተናግረዋል። ‎ ‎የበጎ ፈቃድ ተግባር መከናወን ያለበት በከተማ ብቻ ሳይሆን በክፍለ ከተሞችና በቀበሌዎች ሰፋ ያለ እቅድ በማቀድ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል። ‎ ‎ ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቶፊቅ ጀማል በበኩላቸው በከተማው ዛሬ በሚጀመረው የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ በ17 ተግባራቶች ማለትም 6 አዳዲስና 6 የሚጠገኑ ቤቶች ጨምሮ ሌሎችም በርካታ ስራዎች ተግባራዊ እንደሚደረጉም ተመላክተው ‎ ‎በዘንድሮ የ2018 የክረምት ወራት የበጎ አገልግሎት ዕቅድ በተለያዩ መስኮች ከ8084 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ከ18566 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚሆኑና ይህም በገንዘብ ሲተመን ወደ 16,000,000ብር ይገመታል ብለዋል ። ‎ ‎በውይይቱ መድረኩ አስተያየት ሰጪዎች በሰጡት ሀሳብ ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር በሆኑ ተግባራት ላይ ህዝቡ ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል። ‎ ‎በክረምቱ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አቅመ ደካማ የማህበረሰባችን ክፍሎችን በልዩ ሁኔታ በማሰብ ሁሉም ባለው አቅም ድጋፍ ማድረግና መሳተፍ መቻል እንዳለበትም መክረዋል። ‎ ‎በመርሀ ግብሩ የከተማው አስተባባሪ አካላትና አመራሮች፣የመንግስት ሰራተኞች፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም የአካባቢ ሽማግሌዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል። ‎ ‎ ‎በመጨረሻም የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በጉብሬ ክፍለ ከተማ ኤዋንና ጭቋራ ቀበሌ በሙራ መንደር የአንዲት አቅመ ደካማ እናት አዲስ ቤት ግንባታ ሂደት ተካሔደ ። ‎ ‎
164
15
بدون متن...
108
16
+9
بدون متن...
165
17
በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ 2018 ዓመተ ምህረት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ይተከላል‼️ ‎ ‎ሰኔ27/2018ዓ.ም [ወልቂጤ ] ‎ ‎''ተስፋን እንትከል '' በሚል መሪ ሀሳብ በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብርየ ክፍለከተማ በኤዋንና ጭቋራ ቀበሌ ሙራ መንደር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ክፍለከተማ በይፋ ተጀመረ። ‎ ‎በዛሬው እለት በከተማ አስተዳደሩ የበጋ በጎ ፍቃድ ማጠቃለያ በማድረግ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በኤዋንና ጭቋራ ቀበሌ ሙራ መንደር ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል። ‎ ‎በከተማ አስተዳደሩ በአረንጓዴ አሻራ ባለፈው አመት የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበብትና ሁሉም በቅንጅት በልዩ ትኩረት የተከናወነ እንደነበረ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ተናግረዋል። ‎ ‎እንደከተማ በ2018 ዓ.ም ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቆ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል ። ‎ ‎በአንድ ጀምበር ከ5መቶ ሺ በላይ ችግኞችን ለመትከል የችግኝና የቦታ መረጣ በማድረግ እና የአፈር ጥበቃና የኢኮኖሚ ፋይዳ ሊያረጋግጡ የሚችል ስራ በቁርጠኝነት ይሰራል ሲሉ ጠቁመዋል። ‎ ‎በዚህም በችግኝ ተከላው የከተማ ነዋሪና ማህበረሰብ ተሳትፎ ከፍተኛ ሲሆን በትምህርት ቤቶች ፣በእምነት ተቋማት እና በተመረጡ የከተማዋ አካባቢዎች ላይ በስፋት ለመትከል እየተሰራ ነው ብለዋል። ‎ ‎ ‎ችግኞቹ ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ ሲሆኑ ለምግብነት የከተማው ማህበረሰብ ባለው ውስን ቦታ ተጠቅሞ እንዲተክልና የምግብ ዋስትናን እንዲያረጋግጥ ለማስቻል ከአቅርቦት አንፃር በልዩ ትኩረት ይከናወናል። ‎ ‎ለጥላና የአፈር መሸርሸር ለመከላከል የሚያስችሉ ችግኞችን በመለየት ቦታ በመምረጥ ከአለፉ ጊዜያት የተሻለና ውጤት ልናይበት የምንችል ስራ ህዝባችን አሳትፈን በሶስቱም ክፍለከተማ በቅንጅት ይከናወናሉ ሲሉ አቶ ሙራድ ተናግረዋል። ‎ ‎እንዲሁም ለከተማዋ ውበትና ገፅታን ከፍ የሚያደርጉ የውበት ችግኞች በተመረጡ አካባቢዎች የሚተከሉ መሆኑንም አስረድተዋል። ‎ ‎የምንተክላቸው ችግኞችን በተገቢው መከባከብና የሚፈለገውን አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል ይገባል ያሉት ከንቲባው ባለፉ ጊዜያ በአረንጓዴ አሻራ ስራ ውጤታማነት የተስተዋሉ ውስንነቶችን አርመን ለበለጠ ውጤት ልንሰራ ይገባል ሲሉ አቶ ሙራድ ተናግረዋል ።
99
18
+8
بدون متن...
118
19
በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በጉብርየ ክፍለከተማ በኤዋንና ጭቋራ ቀበሌ ሙራ መንደር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ፣የበጋ የበጎ ፍቃድ ስራ ማጠቃለያ እና የክረምት በጎ ፍቃድ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ ። ‎ ‎ሰኔ 27/2018ዓ.ም [ወልቂጤ ] ‎የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ታደለ በቀለ በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት በበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚከናወኑ ተግባራት የብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር አስተሳሰብና የልማት አቅጣጫ በተግባር የሚገለፅባቸው ስራዎች ናቸዉ ብለዋል። ‎ ‎ብልፅግና ፓርቲ የዜጎችን ሁለንተናዊ ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የተለያዩ ኢኒሼቲቭ ፕርግራም በማውረድ በልዩ ትኩረትና ክትትል እየሰራ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል ። ‎ ‎በክረምቱ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች መካከል የአካባቢ ፅዳት፣የዛፍ ተከላና የተተከሉ ችግኞች እንክብካቤ ፣ለአቅመ ደካሞች የቤት እድሳትና ጥገና፣በጤናው ዘርፍ ለእናቶች የደም ልገሳ ዘመቻ እንዲሁም የሀገር ባለውለታ የሆኑትን የሰራዊት የቤተሰብ አባላት ድጋፍና እንክብካቤ ስራዎች የከተማችን ማህበረሰብ ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት ለህዝባችን ፈጣን አገልግሎት የምንሰጠው መሆን አለበት ብለዋል። ‎ ‎ህዝብን ማገልገል የልማት መሠረት ነው ያሉት አቶ ታደለ በጎ ፍቃድ የብልጽግና ፓርቲ እሴት እና ማህበረሰባችንን በምንችለው አቅምና ሀብት የምንጠቅምበት ትልቅ አጋጣቢ በመሆኑ ሁሉም ሊሳተፍ ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል። ‎ ‎በክረምቱ በጎ ፍቃድ ተግባራት በከተማው በሁሉም ቀበሌ በተቀናጀና ሁኔታ የሚመራ ነው ያሉት ዋና ተጠሪው ለማህበረሰባችን ተጨባጭ ውጤት የምናስመዘግብበት ነው ብለዋል። ‎ ‎
89
20
+5
بدون متن...
131