Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ
Open in Telegram
መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አስተምህሮና ሙሉ የግእዝ ቋንቋ ሥልጠና ትምህርት ማስተማሪያ የቴሌግራም ገጽ። በመደበኛ መርሐ ግብር የግእዝ ቋንቋ ሥልጠናን መከታተል የምትሹ በኮሜንት መስጫው ጻፉልኝ።
Show more4 667
Subscribers
+3324 hours
+1987 days
+20530 days
Posts Archive
+2
ውስጣዊ መረጋጋትን ለማግኘትና ራስን ለመመልከት ምሽት ላይ ቤተክርስቲያን መገኘት ተመራጭ ነው።
ከአርባ አራቱ በአንዷ ቤተክርስቲያን ጎንደር
የምሽት ገጽታ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
የባስልዮስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰባ_ሦስት
💎 ማርያም ዘወትር ድንግል ናት
ካህኑ ይህንን ይጸልያል
➢ መሥዋዕት ያቀረቡትን በሰማይ ያለ ዋጋቸውን ስጣቸው። ከጥንት ጀምሮ ያለገሉህ ቅዱሳንህን እናስብ ዘንድ።
➢ ቅዱሳን አባቶቻችንን ፣ ሉቃነ ጳጳሳትን ኤጲስቆጶሳትን ፣ ነቢያትንና ሐዋርያትን ፣ ሰማዕታትንም ፣ ምእመናንን የቤተክርስቲያንህን ወገኖችን ወንጌልን የሚሰብኩ ፣በሃይማኖት ፍጹማን የሆኑ የጻድቃንን ነፍሳት ሁሉ እናስብ ዘንድ።
➢ ይልቁንም ሁልጊዜ ምሕረትን የተመላች ቅድስት ንጽሕት አምላክን የወለደች ድንግል ማርያምን እናስብ ዘንድ።
ይ.ሕ :- ወትረ ድንግል ማርያም ፤ ማርያም ዘወትር ድንግል ናት። ሦስት ጊዜ ደጋግመው ይላሉ።
ከዚህም በመቀጠል ካህኑ ከአበው ጀምሮ ነቢያትን ፣ ሐዋርያትን ፣ ሰማዕታትን ፣ ጻድቃን መነኰሳትን ስማቸውን እየጠራ ይጸልያል። ስለ እነዚህ ቅዱሳንም ሲል እንዲምረን ይቅር እንዲለን ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድም ይማጸናል።
✍️ የዓለሙን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ
ካህኑ ሠራዊት ከተባለ በኋላ ይህንን ይጸልያል
➢ የዓለሙን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ አማኑኤል ዛሬ ከኛ ጋራ በዚህች ማዕድ ላይ እነሆ አለ።
➢ የሰማይ መላእክት ፣ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ያመሰግኑታል። ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዕጣንን በተመሉ የወርቅ ማዕጠንት ከቅዱሳን ጸሎት ጋራ በፊቱ መሥዋዕት አድርገው ያሳርጋሉ።
➢ በበጉ ደም ልብሶቻቸውን ያጠቡ ንጹሓን ደናግል እሊኸውም ዐሥራ አራት እልፍ ከአራት ሺሕ አሸናፊ እግዚአብሔርን ያመሰግኑታል ያከብሩታልም እንዲህ እያሉ።
➢ አሜን ሃሉ ሉያ እግዚአብሔር አብ ቅዱስ ነው።
➢ ሃሌ ሉያ ጌታችን ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ነው።
➢ ሃሌ ሉያ መጽኛ የሚሆን ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ነው። አሜን።
➢ ሃሌ ሉያ አምላክን የወለደች ድንግል ማርያም የተቀደሰችና የተመረጠች ናት። አሜን።
➢ ሃሌ ሉያ ዳግመኛ ይህች መሥዋዕት የነጻች የተመረጠች ናት። አሜን።
➢ ስለዚህ መድኃኒታችን ይጮሃል እንዲህ እያለ ሥጋዬ እውነተኛ የጽድቅ መብል ነው። ደሜም እውነተኛ የሕይወት መጠጥ ነውና። ሥጋዬን የበላ ደሜንም የጠጣ ከእኔ ጋራ ይኖራል ዳግመኛም ከእርሱ ጋራ እኖራለሁ።
➢ በንጹሕ ልቡና ብርሃን በተመላች ነፍስ እንጠራህ ዘንድ ደፍረን በባለሟልነት ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ሆይ በሰማይ ያለህ አባታችን እንበል።
✍️ ካህኑ በአንብሮ እድ የሚጸልየው
➢ አቤቱ እሊህ ባሮችህ የሚገዙልህ ቅዱስ ስምህን የሚጠሩ ራሳቸውንም በፊትህ ዝቅ ዝቅ ያደረጉ ናቸው። አቤቱ በነርሱ ላይ እደር ከነርሱም ጋራ ሂድ። በበጎውም ሥራ ሁሉ እርዳቸው ልቡናቸውንም ምድራዊ ከሚሆን ከክፉ ሥራ ሁሉ አንጻላቸው።
➢ ይኖሩ ዘንድ መኖርን ስጣቸው። የዘላለም ሕይወትንም ያስቁ ዘንድ ደስ የሚያሰኙህንም ያውቁ ዘንድ። በዚህ በአንድ ልጅህ በጌታችንና በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እኛ ሁላችን ሕዝብህም ሁሉም መድኃኒታችን እግዚአብሔር ይቅር በለን ብለን ወደሱ የምንጮህለት እርሱ ነው ለዘላለሙ አሜን።
#የባስልዮስ_ቅዳሴ_ተፈጸመ።
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰባ_አራት
የጎርጎርዮስ ቅዳሴ
➜ ሰኔ / 22 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
የባስልዮስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰባ_ሁለት
💎 አገራችን ኢትዮጵያን አስባት
✍️ መግቢያ
ቅዱስ ባስልዮስ የቂሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ሲሆን አባቱ ኤስድሮስ የተባለ ካህን ነው። ለባስልዮስም አራት ወንድሞች ነበሩት። እሉህም
✔️ ጎርጎርዮስ :- በስሙ ቅዳሴ ያለው እና በኑሲስ ላይ ኤጲስቆጶስ ሆኖ የተሾመ ነው።
✔️ ጴጥሮስ :- በኤፌሶን አውራጃ በአንዲቱ ኤጲስቆጶስ ተሹሟል።
✔️ መካርዮን እና መካሪና :- እሊህ ንጹሐን ደናግላን ነበሩ።
የእመቤታችንን ውዳሴዋን ለደረሰ ቅዱስ ኤፍሬም በራዕይ በአምደ ብርሃን የታየው ይህ ቅዱስ ባስልዮስ ነው። ከሞተ በኋላም የኃጢአተኛዋን ኃጢአት አስተሠርይዋል (በእምነት ከአስከሬኑ ብትጥለው ከጻፈችው ብራና ላይ ተፍቆላታል)።
አንድ ሰው (የንጉሡ ሎሌ) የንጉሡን ልጅ ወዶ ከጠንቋይ ሂዶ ከሰይጣን ጋር ቃል ተጋብቶ በመስተፋቅር አገባት ከዛም ቤተክርስቲያን የማይሄድ ሆነ ሃይማኖቱንም ተወ። ይህንንም ሚስቱ ለባስልዮስ ነገረችው እሱም ጠርቶ ሲያናግረው እርሱም የንጉሡን ልጅ ከሰይጣን ጋራ ቃል እንደ ተጋባ ከጠንቋይ ያጻፈውንም አሳየው ባስልዮስም በጸለየ ጊዜ በአጋንንት እጅ የነበረውን ቃል የተጋቡበትን ወረቀት አጋንንቱ በአየር ላይ ጣሉለት። የተጋባውንም ቃል በጸሎቱ ናደው። ከዛም ቀኖና ሰጥቶ እንደ ቀድሞው በእምነቱ ጸንቶ ኖረ።
ቅዱስ ባስልዮስ መጽሐፈ ቅዳሴን ከመጽሐፉ በላይ የሰበሰበ ያስተጋባ እንዲሁም ከቅዳሴ መግቢያ እስከ መጨረሻው ድረስ ብዙ ጸሎቶችን አካቶ የጻፈ እና በሥርዓተ ቅዳሴው ላይ የሚጸለየው ጸሎት በብዛት እርሱ የደረሳቸው ናቸው።
በዚህ ቅዳሴ ውስጥ ተካተው የሚገኙ ጸሎቶችና ምስጋናዎች እነዚህ ናቸው።
➢ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለም ሳይፈጠር የነበረ መሆኑ ፣ ሰማይና ምድርን የፈጠረ መሆኑ።
➢ ቅዱስ እግዚአብሔር በደስታ ገነት ያኖረን መሆኑ።
➢ ካህኑ ሐዋርያት ስለ ሰበሰብዋት አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነት አስብ ይላል።
➢ ዲያቆኑም ሐዋርያት ስለ ሰበሰብዋት በእግዚአብሔር ዘንድ ስለ ቀናች ስለ አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን ጸልዩ ይላል።
➢ ካህኑም ቤተክርስቲያንህን ጠብቃት በማለት ይጸልያል።
➢ ዲያቆኑ ስለ ዝናብ መውረድ ስለ ሰማይ ነፋስ ስለ ምድር ፍሬ ስለ ዘርና እርሻ ስለ እንጨትና ስለ ወይን ፍሬ ጸልዩ ይላል።
✍️ ከዚህም በመቀጠል ካህኑ ይህንን ይጸልያል
➢ ምድርን ለዘርና ለመከር አዘጋጃት።
➢ የዚህችን ዓመት አክሊል (አዲሱን ዓመት) በቸርነትህ ባርክ።
➢ ስለ ድሆች ወገኖችህ ስለ ባልቴቶችና አባት እናት ስለሌለው ስለሚነግዱና ስለ ስደተኞች ወደ አንተ ተስፋ አድርገን ቅዱስና ክቡር ስምህን ስለምንጠራ ስለሁላችንም የሰው ሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋልና አንተ በጊዜው ምግባቸውን ትሰጣቸው ዘንድ እንደ ቸርነትህ ለእኛ በጎ ነገርን አድርግልን።
➢ ለሥጋዊ ሁሉ ምግብን የምትሰጥ አቤቱ በልቡናችን ተድላ ደስታ ሙላ። ለእኛ ሁልጊዜ በምንም በምን የሚበቃንን አስብ። በበጎ ሥራ ሁሉ እንበዛ ዘንድ።
➢ አቤቱ አገራችን ኢትዮጵያን አስባት።
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰባ_ሁለት
ማርያም ዘወትር ድንግል ናት
➜ ሰኔ / 22 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
የአትናቴዎስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰባ_አንድ
💎 ኑ ሰንበትን እናክብራት
የአትናቴዎስ ቅዳሴ ስለ ሰንበተ ክርስቲያን ክብር እና ታላቅነት በሰፊው የሚናገር ቀዳሚው ቅዳሴ ነው።
✍️ የሕፃናት ጽንሰት ሂደት
ይ.ካ :- ... የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ለጌትነትህ መጠን የለውም ለመንግሥትህም ፍጻሜ የለውም ላገዛዝህም ወሰን የለውም ለግዛትህም ዳርቻ የለውም።
ካህኑ በዚህ ጸሎቱ እነዚህን ያነሣል
➢ የመነለኮት አነዋዋሩ እንደማይታወቅ የሚገኝበት አለመመርመሩ።
➢ ቅድስናህ የሰው አሳብ አይደርስበትም ደኃራዊነትህንም የመላእክት ፍጥነት አያገኘውም አንተ ከሁሉ ዓይን የተሠወርህ ነህ።
➢ እግዚአብሔር ከሁሉ የራቀና የመጠቀ ሲሆን እርሱን ለሚፈሩት ግን የቀረበ ነው ከእነርሱም ጋር ይኖራል ፈቃዳቸውንም ያደርግላቸዋል።
➢ እግዚአብሔር የኃጢአተኛውን መመለስ እንጂ መሞቱን አይወድም።
➢ ሕፃንን ካባቱ ወገብ አውጥተህ ወደ ሴት ማኅፀን የምትልከው ሆይ በረቂቅ ሰፋድልም የምትጠቀልለው ውኃም ሲሆን በጥበብህ የምታረጋው። የሕይወት መንፈስንም እፍ ትልበታለህ። በሆነ ሁኖ በአርባ ቀን ትሾመዋለህ (ታድለዋለህ) ። ባለጸጋ ለመሆን ለመደህየትም ቢሆን ለመጽደቅም ለመኰነንም ቢሆን።
ዳግመኛም ከዚያ ታወጣዋለህ (እንዲወለድ ታደርገዋለህ) ዓይኑንም ትገልጣለህ ከዚያ የሚገባበትን ምድር ያይ ዘንድ ጒሮሮውን ከፍተህ ታስጮኸዋለህ። እጁንና እግሩን ታንቀሳቅሰዋለህ የእናቱን ጡት ያውቅ ዘንድ።
የምታሳድገውና የምታጎለምሰው እስከ እርጅናም የምታደርሰው አንተ ነህ።
➢ ነፋስን የምታነሣሣው ሳይታይ ጉምንም ያለ ድምፅ የምታስሄደው ሆይ።
➢ እንዳንተ ዙፋኑን በእሳት የጋረደ ማነው። በልብሱስ የውኃ ሥዕል ያደረገ ማነው። ተራራዎችንስ እንዳንተ በሚዛን የመዘናቸው የባሕርንስ ውኃ በእፍኙ የሚሰፍረው ማነው።
➢ እንዳንተ አዳራሹን በውኃ የሚታታ ዙሪያውንስ በእሳት የሠራ ማነው። በላይ ያለው የውኃው ጠፈር በጥበብህ ወደ እሳት ግርግዳ አይወርድም። በታች ያለው የውኃው ግርግዳም በአናንዋርህ በላይ ወዳለው ወደ ውኃው ጠፈር አይወጣም።
➢ ይህ ነገር የሚያስደንቅ ዕፁብ ነው ድንቅ ነው። ማናቸውን አስቤ አደንቃለሁ? በአርምሞና በቅድስና ካባትህ ጋራ መኖርህን ነውን? ወይስ እንደ ሕፃን በናትህ ክንድ መያዝህን ነውን?
➢ ማናቸውን አስቤ አደንቃለሁ? ከሱራፌል ዘንድ እንደ ባሕር ማዕበል የሚቀርብልህን (የሚመጣልህን) ምስጋና ነውን? ወይስ በዮርዳኖስ ባሕር መቆምህን?
➢ አቤቱ በላይ ሳለህ በታች ብቸኛ ትሆናለህ። በታች ሳለህም በላይ ሦስት ትሆናለህ።
#ማብራሪያ :- በላይ ሳለህ በታች ብቸኛ ትሆናለህ ማለት በላይ በልዕልና ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ሲሆን በተለየ አካል ግን ሥጋን የተዋሐደ ሰው የሆነ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ ብቻውን ወልድ መሆኑን ለመግለጽ ነው።
➢ እኛስ የተቻለንን ያህል ተናገርን። እስከ ሰማይም አደረስን። ከዚያ ማለፍም ግን አይቻለንም። ይሻገር ዘንድ ሕሊናችንን የማያሰናብተው የእሳት ባሕር ከዚያ አለና። አናንዋርህን አንተ ራስህ ታውቃለህ መለኮትህንም አንተ ራስህ ትረዳለህ።
✍️ ኑ ሰንበትን እናክብራት
ድርገት ካለቀ በኋላ ካህኑ ሐዳፌ ነፍስ የሚለውን ደግሞ ዲያቆኑ ጸልዩ ካለ በኋላ ካህኑ ይህንን ይጸልያል።
ይ.ካ :- ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት ኑ እናመስግናት ኑ እናክብራት ኑ በዓል እናድርጋት የበዓላትን መጀመሪያ ይህችውም ክብርት የምትሆን የክርስቲያን ሰንበት ናት።
ትላንት በመግባትዋ ደስ እንዳለን እንዲሁ በመውጣትዋ ደስ ብሎን እንሸኛት በርስዋ ሥጋችንን በማሳረፍ እየተጋን።
ዕረፍታችን ግን በደዌ እንደ ታመመ ሰው በመተኛት አይደለም ቀንና ሌሊት በመትጋት ነው እንጂ የዚህች ዕለት ወዳጆችዋ እንሆን ዘንድ።
ዳግመኛም እንደ እንስሳት ለሆነ ከእንስሳትም ለከፋን ለእኛ ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ለምኝልን ስለኛ አማልጂ እንበል።
ቅድስት ሆይ በየሳምንቱ ወደኛ ነዪ በአንቺ ደስ ይለን ዘንድ ለዘላለሙ።
አሜን።
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰባ_ሁለት
ቅዳሴ ባስልዮስ
➜ ሰኔ / 21 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
ቤተክርስቲያን እና ድንግል ማርያም
💎 ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካሉ ናት
እመቤታችንም ክርስቶስ ሥጋና ነፍስ የነሣባት አካሉ ናት
💎 ቤተክርስቲያን የክብሩ መገለጫ ናትተ
እመቤታችንም የእግዚአብሔር ክብር ነተገለጠባት አንድነት ሦስትነት የታወቀባት የክብሩ መገለጫ ናት።
💎 ቤተክርስቲያን መቅደሱ ናት።
እመቤታችንም የአካላዊ ቃል መቅደሱ ናት።
💎 ቤተክርስቲያን የክርስቶስ ሙሽራ ናት።
እመቤታችንም መርአተ አብ (የአብ ሙሽራ) ናት።
💎 ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት።
እመቤታችንም ቅድስት ናት።
💎 ቤተክርስቲያን አሐቲ (አንዲት) ናት።
እመቤታችንም አሐቲ ይእቲ ለእማ (ለእናቷ አንዲት ናት) እንደተባለ አንዲት ድንግል አንዲት የእግዚአብሔር እናት ናት።
💎 ቤተክርስቲያን ኵላዊት (በሁሉ በዓለም ያለች ለሁሉ የተሰጠች) ናት።
እመቤታችንም እናትነቷ ለሁሉ ነውና ፤ በአራቱ ማዕዘን የምትመሰገን ናትና።
💎 ቤተክርስቲያን ምዕራገ ጸሎት (ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የሚያርግባት) ናት።
እመቤታችንም የቅዱሳን ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት ምዕራገ ጸሎት ናት።
💎 ቤተክርስቲያን አንድነትን ሦስትነትን ትሰብካለች።
እመቤታችንም አንድነት ሦስትነት የተገለጸባት አንድነትን ሦስትነትን የምታስተምር ናት።
💎 ቤተክርስቲያን የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ናት።
እመቤታችንም የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ብቻ ሳይሆን እሷም ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ናት።
💎 ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር መንበሩ ናት።
እመቤታችን የእግዚአብሔር መንበር ናት።
💎 ቤተክርስቲያን ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገሪያ ድልድይ ናት።
እመቤታችንም ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገርንባት መርከባችን ናት።
💎 ቤተክርስቲያን የወንጌል ማዕድ የሚዘጋጅባት የምሕረት አደባባይ ናት።
እመቤታችንም ወንጌል የተገለጸባት የተጀመረባት ወንጌልን የወለደች ፊደል ናት።
💎 ቤተክርስቲያን ውኃው ወደ ወይን መለወጡን ታስተምራች።
እመቤታችን ውኃው ወደ ወይን እንዲለወጥ አደረገች።
💎 ቤተክርስቲያን የምእመናን ሁሉ እናት ናት።
እመቤታችንም የምእመናን ሁሉ እናት ናት።
💎 እመቤታችን በዕለተ ዐርብ ከመስቀሉ ስር በነበረችበች ቤተክርስቲያን ተመሠረተች።
💎 ቤተክርስቲያን ዕለት ዕለት ለምእመናን የምታድለው ሥጋውና ደሙ ከእመቤታችን የነሣው ነው።
💎 ቤተክርስቲያን የጰራቅሊጦስ እመቤታችን ባለችበት ተወለደች።
💎 ቤተክርስቲያን በቂሣርያ በእመቤታችን ስም ተመሠረተች።
ከቤተክርስቲያን ኅብረት ከእመቤታችን ልጅነት አይለየን።
➜ ሰኔ / 21 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
+2
ተወዳጁ ወንድሜ መምህር ኤርምያስ አበበ
በጽናት ተጉዘህ ካሰብከው ደርሰኻልና እንኳን ደስ ያለህ Congratulations
ለዓመታት ከኢንጂባራ ዩኒቨርስቲ ስትከታተል ቆይተህ ለምርቃት በመብቃትህ ደስ ብሎናል።
የተጓዝክበት መንገድ ለብዙዎች አርአያና አስተማሪ ነው።
የአትናቴዎስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰባ
💎 ዕለተ ምጽአት
✍️ሦስት ልደት
ዲያቆኑ :- ንነጽር (እናስተውል)
ካህኑ :- ይህንን ይጸልያል
➢ ለእኛ ከዚህ በአሸዋ የተሠራ ነፋሳት የሚነፍሱበት ፈሳሾች የሚገፉት ቤት ያለን አይደለም። በላይ ያለች ነጻ የምታወጣ ኢየሩሳሌም ናት እንጂ።
➢ በሥጋ ተወልደን ሦስት ልደቶች አሉን።
አንዲቱ ክርስቶስን የምታስመስለን ጥምቀት ናት።
አንዱም በደልንና ኃጢአትን የሚያስተሠርይ የክርስቶስ ሥጋውና ደሙ ነው።
አንዱም ንጹሕ አድርጎ ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብ ከሰውነት ውስጥ በዮርዳኖስ አምሳል የሚወጣ በንስሓ ያለ ዕንባ ነው።
➢ ሰምስጋና ቃል እግዚአብሔርን እንደሚያመሰግኑት መላእክት እንሁን።
✍️ ዕለተ ምጽአት
ዲያቆኑ :- ተሰጥዎውን መልሱ። ይላል
ካህኑ :- የበዓላትን በኵር ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት። ኑ እናመስግናት። ኑ እናክብራት። ኑ በዓል እናድርጋት። ይህችውም ቅድስት ሰንበተ ክርስቲያን ናት። ይህች ቀን እግዚአብሔር ሥራ የሠራባት ናት እንበል። በእርሷም ደስ ይበለን ሐሴትንም እናድርግ።
ከዚህም በመቀጠል በሚጸልየው ጸሎቱ ይህን እናገኛለን።
➢ ወንጌልን እንያዝ ፣ ትሕትናና ፍቅር ያለበትን ሁለተኛ ሕገ ኦሪትን ግን አንተው።
➢ በገና ከመሰንቆ ጋራ የተስማማ እንደሆነ የወንጌልም ትእዛዝ ከመሠራቱ ጋራ የተስማማ ነው። መሰንቆ ሰማዕታት የያዟት ሃይማኖት ናት።
ከዚህም በመቀጠል ስለ ክብረ ሰንበት ይናገራል
➢ እግዚአብሔር ሥራውን ይሠራ ዘንድ የጀመረባት ናት
➢ ይቺ ዕለት ለአብርሃም ፣ ለሙሴ ፣ ለነቢያት የታወቀች የተገለጠች ናት።
➢ አብ የቀደሳት ወልድ የባረካት መንፈስ ቅዱስ ከፍ ከፍ ያደረጋት ናት።
➢ ኑ ከፍ እናድርጋት በእርሷ ደስ ይበለን የበዓላት በኵር ሰንበተ ክርስቲያን ናት።
➢ ወዮ ይቺ ዕለት ያረጀችዋ ያለፈችባት አዲሲቱ የጸናችባት ናት። እስረኞች የተፈቱባት ባሮች ነጻ የወጡባት ናት።
➢ ወዮ ይቺ ዕለት የፈረሰ የታነጸባት ሰይጣንም የጠፋባት ናት።
✍️ ዕለተ ምጽአት
➢ ያን ጊዜ የፀሐይ የጨረቃ የከዋክብት ብርሃን የለም። በጋና ክረምት የለም።
➢ ያን ጊዜ መቃብራት ይከፈታሉ ሙታን እንደ ዓይን ቅጽበት ይነሣሉ። አብ መንግሥቱንና ፍርዱን ለልጁ ይሰጣል። የነጎድጓድ ድምፅም ይሰማል።
➢ ያን ጊዜ መላእክት በፊቱ ይቆማሉ። የእሳት ባሕር ይገለጣል።
➢ ያን ጊዜ መጻሕፍት ይገለጣሉ ሥራም ይገለጣል አንደበትም ዝም ይላል የተከፈተ አፍም ድዳ ይሆናል።
➢ ያን ጊዜ ጥቁርና ቀይ አጭርና ረጅም የለም አንድ አካል አንድ መልክ ነው እንጂ።
➢ ያን ጊዜ የነፍስ ቤዛ የለም ወንድ በሚስቱ አባት በልጁ እናት በልጇ መለወጥ የለም ሁሉም የሥራውን ፍዳ ይቀበላል እንጂ።
➢ ባለ ጸጋውን ስለ ባለጸግነቱ አያፍረውም። ድኃውንም ስለ ድኅነቱ አይራራለትም እርሱን ደስ ካላሰኘው።
➢ ያን ጊዜ ጻድቃን ደስ ይላቸዋል በሕይወታቸው አልቅሰዋልና። ኃጥአን ግን ያለቅሳሉ በምድር ላይ ሳቅና ስላቅን አብዝተዋልና።
➢ ያን ጊዜ ባለጸጎች ይደኸያሉ ተድላ ደስታቸውን በአመጽ ጨርሰዋልና። ነዳያንም ባለጸጎች ይሆናሉ ድኅነታቸውን በምስጋና ተቀብለዋልና።
➢ ያን ጊዜ ተርበው የነበሩ ይጸግባሉ በሕይወታቸው ስለ ሃይማኖት ተቸግረው ነበርና።
➢ ያን ጊዜ ተናጋሪዎች የነበሩ ዝም ይላሉ ከንቱንና ብላሽን ነገር ተናግረዋልና። ትዕግሥተኞች የነበሩ ይናገራሉ። አንደበታቸውን ወደ ሐሜት ይሮጥ ዘንድ አልተውትምና ባልንጀሮቻቸውንም ፈጽሞ አላሳዘኑምና።
➢ ያን ጊዜ ጽኑዓን የነበሩ ዬደክማሉ ሥጋቸውን በዝሙት አድክመዋልና። ደክመው የነበሩት ይጸናሉ ኃይላቸውን በሰጊድ በመዓልትና በሌሊትም በመትጋት አድክመዋልና።
➢ ያን ጊዜ ኃያላን ልምሾ ይሆናሉ እጃቸውን ለመቀማት ዘርግተዋልና። ባልቴትንና አባት እናት የሞቱበትን አስለቅሰዋልና።
➢ ያን ጊዜ የተናቁት እንደ አንስርት ይበራሉና ክንፎቻቸውም ይወጣሉ ጎልማስነታቸውም ይታደሳልና።
➢ ያን ጊዜ ትዕቢተኞችና ኩሩዎች ይገለጻሉ ኀፍረታቸውም ይገለጻል።
➢ ያን ጊዜ የታረዙት ይለብሳሉ የዝናምና የጠል ካፊያ አርሷቸዋልና ብርድና ውርጭ አስቸግሯቸዋልና የፀሐይ ሐሩርም አቃጥሏቸው ነበርና።
➢ ያን ጊዜ ጦርና ጋሻ ቀስትና ፍላፃ የለም በምድር የነበረ ሁሉ ተሽሯልና።
➢ ያን ጊዜ ንጉሥ አድልዎ በሌለበት በቅን ፍርድ ይፈርዳል።
➢ ያን ጊዜ ኃጥአን ከጻድቃን መካከል ይለያሉ ርኩሳንም ከንጹሓን መካከል ይለያሉ።
➢ የዚያን ጊዜ አውያት የዚያን ጊዜ ጩኸት የዚያን ጊዜም ልቅሶ ምን ያህላል እርሱ ቅሉ ፈጣሪ ወደ ጥፋት መንገድ ሲሄዱ ባያቸው ጊዜ እጁ ስለ ፈጠራቸው ፍጥረቶቹ እስኪያለቅስ ድረስ።
➢ ያን ጊዜ ኃጥአን ስለ ራሳቸው ያለቅሳሉ ጻድቃንም ስለ ዘመዶቻቸው ያለቅሳሉ የሰማይ መላእክትም ስለ ሰው ፍጥረት ያዝናሉ።
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰባ_አንድ
ዕለተ ምጽአት
➜ ሰኔ / 18 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
የአትናቴዎስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ስልሳ_ዘጠኝ
💎 አዳምና ሔዋን ምን አደረግናችሁ
ዲያቆኑ :- እግዚአብሔርን በመፍራት ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ። ካለ በኋላ
ካህኑ :- ይህንን ይጸልያል። በዚህ የጸሎት ክፍልም
የሰው ልጅን መውደቅ የአዳምና የሔዋንን መሳሳት በሰፊው ያትታል።
➢ ሰው ግን ክቡር ሲሆን አላወቀም። ልብ እንደሌለው እንደ እንስሳም ሆነ መሰላቸውም።
➢ ሰውስ ንጉሥ ሲሆን አላወቀም በፈቃዱ ራሱን አዋረደ ባርያም ሆነ ጌቶች ያልሆኑትም ገዙት።
➢ ሰውስ ባለጸጋ ሲሆን አላወቀም በፈቃዱ ራሱን ነዳይ አደረገ ሆዱን አስራበ ነፍሱንም አስጠማ።
✍️ ከዚህም በመቀጠል የእግዚአብሔርን ቸርነትና መግቦት ያመጣል
➢ እግዚአብሔር ለሰው ያደረገለት ብዙ መሆኑ ፣ ሰማይን አይቶ እንዲያደንቅ በምድር እንዲመላለስ ሰማይና ምድርን ዘረጋ።
➢ ዝናምን ማዝነቡ ፣ በቀን ፀሐይን በሌሊት ጨረቃን ያበሩ ዘንድ መፍጠሩ። ሰው የጣቶቹን ሥራ ያውቅ ዘንድ የከዋክብትን ብርሃን አበራ። ዘመናትን ዕለታት ሰጠኸው።
✍️ ሰው አትብላ የተባለውን መብላቱና የመጣበት ፍዳ
➢ ሰውስ የብርሃን ልብስ የለበሰ ሲሆን ሰውነቱን አራቆተ። የዳባ ልብስን ለበሰ።
➢ ሰውስ ከእግዚአብሔር በታች ገዥ ሲሆን ካልታዘዘለት ዕፅ ሰርቆ በላ።
✍️ ስለ አዳምና ሔዋን
የአትናቴዎስ ቅዳሴ ከሌሎቹ የሚለየው ስለ አዳምና ሔዋን በተጻፈው ነው።
➢ አዳም ሆይ የሞትን ፍርድ ያመጣህብን ምን አደረግንህ። አዳም ሆይ ደስታ ባለበት በእግዚአብሔር ማደሪያ ያልተውኸን ምን አደረግንህ።
➢ ሔዋን ሆይ ምን አደረግንሽ። እነሆ ሥጋችን ጠቆረ በሰማያውያን አምሳል በኖርነ ነበረ።
➢ ሔዋን ሆይ ምን አደረግንሽ። እነሆ ልጆችሽ በጭንቅና በሕማም በወለዱ ጊዜ ያለቅሳሉ አንቺ ያችን በገነት ያለችውን ዕንጨት እንዳደማሻት ይደማሉ።
➢ አዳምና ሔዋን ሆይ እናንተን እንነቅፍ ዘንድ የማቻል አይደለም እኮ አንደበትን እየተናገሩበት ሊሰድቡትና ሊነቅፉት እንዳይቻል እንደዚህም እናንተ እኛን ናችሁ እኛም እናንተን ነን።
➢ አዳምና ሔዋን ሆይ እናንተስ ይቅር ባይ በሆነ ጌታ ንስሓ ገብታችኋል። እናንተስ ድናችኋል በጌታ ደምም ወደ ቀደመ ቦታችሁ ገብታችኋል። በጌታ ያላመኑት ልጆቻችሁ እንጂ።
➢ እነሆ ልጆቻችሁን ኃጢአት እንደ እሳት በላችን። ፍትወትም አቃጠለችን።
➢ እንግዲህስ የደስታ ገነት ሰላም ላንቺ ይሁን እንበል። ከዚም ላይ በጽድቅ እንጂ በኃጢአት ገነት እንደማንገባ። በመጨከን እንጂ በመስነፍ እንደ ማንወርሳት ይናገራል።
➢ በዚህ ጸሎቱ መጨረሻም የገነትን ጠባቂ ሱራፊ መልአክን እንዲህ እያለ ይማጸናል። ሱራፊ ሆይ ወደ ገነት እንገባ ዘንድ ተወን አትከልክለን።
በመዓዛ እንደሰት ዘንድ እርሷን የሚያጠጡ አራቱን ወንዞቿን (ጤግሮስ ፣ ኤፍራጥስ ፣ ግዮን ፣ ኤፌሶን) እናይ ዘንድ ተወን። እያለ በመማጸን ምስጋናውን ይጨርሳል።
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰባ
ዕለተ ምጽአት
➜ ሰኔ / 16 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
የአትናቴዎስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ስልሳ_ስምንት
💎 የእግዚአብሔር ዓይኖች ካህናት
✍️ መግቢያ
የአትናቴዎስ ሐዋርያዊ ታሪክ
ቅዱስ አትናቴውስ በእስክንድርያ ከመምህሩ እለእስክንድሮስ ቀጥሎ የተሾመ ደግ አበት ሲሆን ክብሩም እንደ ሐዋርያት በመሆኑና ሐዋርያት ያስተማሩትን በማስተማሩ ሐርያዊ ተብሏል።
ቅዱስ አትናቴዎስ አስቀድሞ ከማያምኑ አረማውን ወገን ነበረ። ከዕለታት በአንዳቸው ቀንም የክርስቲያን ልጆች ተሰብስበው ሲጫወቱ (በክህነት አገልግሎት ካህን ዲያቆን ጳጳስ እየሆኑ ሲጫወቱ) አትናቴዎስ አጫውቱኝ አላቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ስለሆንክ አናጫውትም አሉት።
እሱም አጥምቁኝና ልጫወት አላቸው። ሕጻናቱ አትናቴዎስን የጨዋታ ጥምቀት አጥምቀው ጵጵስና ሹመው ከወንበር አስቀምጠው ሲጫዎቱ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳ እለእስክንድሮስ ከተኸታዮቹ ጋር በመንገድ ሲያልፉ አይዋቸውና ሊቀ ጳጳሱ ጨዋታቸውን ቁሞ ይመለከት ጀመር። አብረውት ያሉትም አባታችን ከእነዚሕ ሕፃናት ምን ቁም ነገር ይገኛል ብለህ ነው ቁመህ የምታያቸው ሲሉት እግዚአብሔር በእኔ አድሮ በኋላ የሚሠራውን እያየሁ ነው አላቸው። ይሄ ሕፃን አባቱ በሞተ ጊዜ እናቱ አምጥታ ለኔ ትሰጠኛለች እኔም አሳድጌ አስተምረዋለሁ። ከእኔ ቀጥሎም ሊቀ ጵጵስና ይሾማል በማለት ወደ ፊት የሚሆነውን ነገራቸው።
የተባለው አልቀረም አባቱ ከሞተ በኋላ ዘመነ ረኃብ ሲሆን እናቱ አድነውም ግደለውም ብላ ወስዳ ለሊቀ ጳጳሱ ሰጠችው እሱም እያስተማረው አደገ።
ሊቀ ጳጳሱ እለ እስክንድሮስም በአረፈ ጊዜ የእስክንድርያ 20ኛ ሊቀ ጳጳስ ሁኖ በመንበረ ማርቆስ ተሾመ።
ተሹሞ ሳለም ብዙ ድርሳን ደርሷል ብዙ ተግሣጽ ጽፏል ከጻፋቸውም ውስጥ አንዱ ይህ ቅዳሴው ነው።
✍️ አኰቴተ ቍርባን ዘቅዱስ አትናቴዎስ ሊቀ ጳጳሳት ዘሀገረ እስክንድር ... በእስክንድርያ ላይ የተሾመ ቅዱስ አትናቴዎስ የተናገረው የቍርባን ምስጋና ጸሎቱና በረከቱ ከእኛ ጋራ ይሁን ለዘላለሙ ይኑር።"
ይ.ዲ "ዮም በዛቲ ዕለት ... ዛሬ በዚህች ቀን በዚህች ቤተክርስቲያን ውስጥ የተሰበሰባችሁ ምእመናን ክብርት የምትሆን የክርስቲያንን ሰንበት ቅዳሴ ስሙ።"
✍️ ካህናት ሆይ ብሩሃት የእግዚአብሔር ዓይኖች እናንተ ናችሁ
ይ.ካ "ሰማያትን አዳኝባችኋለሁ ምድርንም አዳኝባችኋለሁ። ያለ መታወክ በመንቀጥቀጥና በመፍራት ትቆሙ ዘንድ። "
በዚህ ጸሎት እነዚህን ነገሮች ያነሳል
➢ እንደ ቃኤል በቀለኛ ሆኖ ወንድምን አለመጣላት
➢ ሙሴን እንደ ተጣሉት ዳታንና አቤሮን አለመሆን
➢ ሔዋንን እንዳሳታት እባብ ወንድምን አለመሸንገል
በቀጠልም ካህናትን የእግዚአብሔር ዓይኖች እያለ እንዲህ ያዛቸዋል
➢ ካህናት እስር በእርሳችሁ ተመለካከቱ ከወገናችሁ መርምሩ ከእናንተ ጋራም እንዳይቆምና እንዳይተባበር እነዚህን አምስቱ ውሾች የተባሉትን ለዩ። #ለዩ ማለቱ በንስሓ ሳይመለሱ ከቍርባን እንዳይሳተፉ አስተምሩ ገስጹ በቀኖና ለዩ ማለቱ ነው።
#አስምቱ_ውሾች_ያላቸው
✔️ ሴሰኛ (ዝሙተኛ)
✔️ ነፍሰ ገዳይ
✔️ ጣዖት አምላኪ
✔️ ሌባ
✔️ ሐሰተኛ ናቸው። እኒህ ከመንግሥተ ሰማይ በአፍኣ (ውጭ) ናቸው። ስለ ግብራቸው ውሻ ይላቸዋል።
➢ ካህናት ሆይ ኃጢአተኛውን እንደ ወንድማችሁ ገስጹት የበደለውንም ምከሩት
➢ የቤተክርስቲያን መብራት አገልጋዮች የምትሆኑ ዲያቆናት ተኵላ ከበግ ጋራ ጭላት (ጭልፊት) ከርግብ ጋራ እንክርዳድ ከስንዴ ጋራ እንዳይኖር በውስጧ ንቀሉ።
እናንተስ የውስጡን ያይደለ የውጩን መርምሩ የውስጡን ግን እግዚአብሔር ያውቃል በእርሱ መብራትም ይመረምራል።
#ማብራሪያ :- ተኵላ ከበግ ጋራ ጭላት (ጭልፊት) ከርግብ ጋራ እንክርዳድ ከስንዴ ጋራ እንዳይኖር ማለቱ አማኝ ከመናፍቅ ጻድቅ ከኃጥእ ጋራ በቤተክርስቲያን ኅብረት እንዳያደርጉ ማለቱ ነው።
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ስልሳ_ዘጠኝ
አዳምና ሔዋን ምን አደረግናችሁ
➜ ሰኔ / 15 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
አኰቴተ ቍርባን ዘ፫፻፲ወ፰ቱ ርቱዓነ ሃይማኖት ... ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ አስራ ስምንቱ ሊቃውንት የተናገሩት የቍርባን ምስጋና። ጸሎታቸው በረከታቸው ከእኛ ጋራ ይሁን ለዘላለሙ አሜን።"
ለተራቡት ወገኖቻችን (ሙሉ የቤተሰብ አባት) ባለሁበት አካባቢ እና ለማቃቸው ሰዎች ሼር በማድረግ እኔ አስተባብራለሁ የምትሉ ቤተሰቦቼ
እዚህ ላይ ጻፉልኝና ስለ ሰዎቹ መረጃዎችን ላጋራችሁ።
የቄሣርን ለቄሣር ሰጥተን እግዚአብሔርን ግን ቀማነው።
መቼ ይሆን እንደ ቄሣር ለእግዚአብሔርስ የምንገዛው?
ቤቱን በሙስና በብሔር በፓለቲካ ሸጥንበት
