en
Feedback
Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ

Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ

Open in Telegram

መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አስተምህሮና ሙሉ የግእዝ ቋንቋ ሥልጠና ትምህርት ማስተማሪያ የቴሌግራም ገጽ። በመደበኛ መርሐ ግብር የግእዝ ቋንቋ ሥልጠናን መከታተል የምትሹ በኮሜንት መስጫው ጻፉልኝ።

Show more
4 667
Subscribers
+3324 hours
+1987 days
+20530 days
Posts Archive
የሠለስቱ ምእት ቅዳሴ መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ #ክፍል_ስልሳ_ሰባት 💎 ያ ቃል ቀዳማዊ ነበረ ✍️ የጌታችን ሕማሙና ሞቱ ይ.ካ :- "አሜሃ ኢየሱስ ይቤ ተከዘት ነፍስየ ዘውእቱ መስተፍሥሔ ትኩዛን ... ፤ ያን ጊዜ ኢየሱስ ነፍሴ አዘነች አለ (በዕለተ ዐርብ)። ይኼውም ያዘኑትን ደስ የሚያሰኛቸው ነው (የጌታ ማዘን የሰውን ልጆች ሐዘን ለማራቅ ነውና)።" በዚህም ጸሎት ሕማሙና ሞቱን ያዘክራል። ይኼውም ➢ በሌሊት መያዙንና ሲነጋ በፍርድ አደባባይ በሸንጎዎች ፊት መቆሙን ➢ የኋሊት ማሰራቸውን ፣ የመላእክት ሠራዊት በመፍራት የሚቆሙለትን በፊታቸው አቆሙት። ➢ ፊቱን በጥፊ መምታታቸውን ፣ የሾኽ አክሊል እንደደፉበት ፣ ልብሱን ገፈው ቀይ ግምጃ ማልበሳቸውን ➢ መስቀል ተሸክሞ ወደ ሚሰቀልበት መሄዱን ፣ ከወንበዴዎች ጋር መሰቀሉን ➢ አዳምን የፈጠሩ እጆቹ ፣ በገነት የተመላለሱ እግሮቹ በችንካር መቸንከራቸውን ➢ ሐሞት መጠጣቱን ፣ ነፍሱን ከሥጋው መለየቱን ፣ በጦር ጎን መወጋቱን ፣ በአዲስ በስደተኞች መቃብር መቀበሩን ይናገራል። ✍️ የመፈተት ጸሎት ካህኑ በመፈተት ጊዜ ይህንን ይጸልያል። በዚህ ጸሎቱም ከቅድስት ድንግል የነሣው ሥጋ እያነሳ ይጸልያል። "ዳግመኛም ዓለምን የያዘውን ከኃጢአታቸውም ቤዛ የሆናቸውን እርሱን እንማልደዋለን። " "ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ ፤ የኛ ሥጋ እንደሆነ ከሰማይ ያላወረድከው እንደሆነ አስብ።" "ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ የኛ ሥጋ ፤ በጲላጦስ ፊት የቆመ እንደሆነ አስብ።" "ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ የኛ ሥጋ ፤ የማሠሪያ መዘጋትን የተሸከመ እንደሆነ አ፨ስብ።" #ማብራሪያ :- ማሠሪያ መዘጋት (ዝግሐታተ መዋቅሕት) ማለት ጌታ በመከራው ጊዜ በጨለማ እሥር ቤት ዘግተውት አድረው ነበርና ያንን ነው። "ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ የኛ ሥጋ ፤ የታመመው የሞተው እንደሆነ አስብ።" "ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ የኛ ሥጋ ፤ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ የተነሣው ሥጋ እንደሆነ አስብ።" "ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ የኛ ሥጋ ፤ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ያረገ በአባቱም ቀኝ የተቀመጠው እንደ ሆነ አስብ። ዳግመኛም አምላካችን እግዚአብሔር በዚህ ሥጋ ከመለኮቱ ኃይል ጋራ ይመጣል።" ✍️ ያ ቃል ቀድሞ የነበረ ነው ካህኑ ድርገት ወርደው ከተመለሱ በኋላ በኀዳፌ ነፍስ ጸሎቱ ይህንን ይጸልያል "ያ ቃል ቀድሞ የነበረ ነው። ያ ቃል የእግዚአብሔር ቃል ነው። ያ ቃል ሥጋ ሆነ በኛም አደረ። ለአባቱ እንደ አንድ የሚሆን ክብሩን አየን። ያ ቃል ወደ ወገኖቹ መጣ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም።" #ማብራሪያ :- ይሄ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ላይ ያለ ነው። ወገኖቹ ያላቸው አይሁድን ነው። አይሁድ በእሱ ሳያምኑ ቀንተው ተመቅኝተው ሰቅለው ገለውታልና። "የተቀበልነው እኛ ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ነን። ሃይማኖትን ያቀናን ሙሽራዋ አምላካችን እግዚአብሔር የሆነ የቤተክርስቲያንን ሕግ የሠራን።" #ማብራሪያ :- የተቀበልነው ማለታቸው የቃልን ቀዳማዊነት እነ አርዮስ ፍጡር ብለው ሲክዱ ተከራክረው ያወገዙት እነሱ ናቸው በዚህም ሃይማኖትን ያቀኑ ይባላሉ። የቤተክርስቲያንንም ሕግ ሠርተዋል። ✍️ አንብሮ እድ ካህኑ በቤተመቅደስ በዝቅታ ድምፅ የሚጸልየው የቅዳሴው የመጨረሻ ጸሎት ነው። "አቤቱ ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ባርከን ቀድሰን። ያለ ኃጢአት ያለ ርኵሰት በፍጹም ደስታ ወደ ቤታችን ለመሄድ የበቃን አድርገን። ከክብርት ማዕድህ የተቀበልነው ሥጋህና ደምህ የሚያድነን ይሁንልን። አቤቱ ቅዱስ መንፈስህንም ላክልን ወደ ሕይወትና ወደ ጽድቅ ጎዳና ይመራን ዘንድ። የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ሥጋውና ደሙን በዚህ ዓለም ሠራ ከርሱ በልተን ከርሱ ጋራ እንኖር ዘንድ። .... በየጊዜው ሁሉ በየሰዓቱም ሁሉ ጸሎትንና ልመናን በሚያሳርጉ በካህናት እጅ የተቀበልነው ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ለሕይወት ለተስፋ ለመድኃኒትና ለኃጢአት ማስተሥረያ ከሙታንም ተለይቶ ለመነሣት ይሁነን ለዘላለሙ አሜን።" ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ስልሳ_ስምንት የአትናቴዎስ ቅዳሴ ➜ ሰኔ / 12 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

"... ሶበ እጼውዕ ስመከ ከሲትየ አፈ። ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ። ለረዲኦትየ ነዓ ሰፊሐከ ክንፈ።" እንኳን ለታላቁ ተራዳኢ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ። በአማላጅነቱ
"... ሶበ እጼውዕ ስመከ ከሲትየ አፈ። ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ። ለረዲኦትየ ነዓ ሰፊሐከ ክንፈ።" እንኳን ለታላቁ ተራዳኢ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ። በአማላጅነቱ የታመን የጥምቀት ልጆችን በክንፈ ረድኤቱ ይጠብቀን። አሜን 🙏🙏🙏 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

የሠለስቱ ምእት ቅዳሴ መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ #ክፍል_ስልሳ_ስድስት 💎 እንደ ማይሰጥ ያዘገያል ይ.ዲ :- አሳባችሁ ወደ ላይ ይሁን። ልቡናችሁ በሰማይ ይኑር። የምትቆሙበትን ዕወቁ። ይ.ሕ :- በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ። ይ.ካ :- መዓቱ የራቀ ምሕረቱም የበዛ እውነተኛ የታገሠበት ጊዜ የለም። ያልታገሠበትም ጊዜ የለም ። የበደለውን ፈጽሞ ወደርሱ እስኪመለስ ድረስ ይታገሣል። በተቈጣ ጊዜም ኃጥኣንን በጥፋት ውሃ አጠፋ (የሰብአ ትካቱን መናገር ነው)። ቃሉን የጠበቁ ስምንት ሰዎችንም አተረፈ (ኖኅና ቤተሰቦቹ ናቸው)። ከዚህ በመቀጠልም ➢ ዙፋኑ በእሳት መከበቡን ፣ ዙሪው መብረቅ መሆኑ ፣ ስለ አራቱ እንስሳ ስለ ሀያ አራት ካህናተ ሰማይ በመንበሩ መኖራቸውን ፣ በራዕየ ዮሐንስ እንደተቀመጠ ለበጉ መስገዳቸውን በዚያም ከአባታችን አዳም ጀምሮ የነበሩ አበው ቅዱሳን ፣ ነቢያት ሐዋርያት ፣ ጻድቃን ሰማዕታት መኖራቸውን ይናገራል። ➢ "ባለጸጋውን ይጠብቃል ከድሃም ጋራ ይኖራል ትሑትን ሰው ይወዳል ትዕቢተኛን ግን ቸል ይላል። ቢፈቅድ ያጸድቃል ቢወድም ያድናል እንደማይሰማ ቸል ይላል እንደማያይ ዝም ይላል እንደማያውቅ ይታገሣል። #እንደማይሰጥ_ያዘገያል። እያለ ስለ ሀብቱ ስለ ትዕግሥቱ ሁሉን በጊዜው እንደ ሚያከናውን ይናገራል። ይ.ዲ :- በእንተ ብፁዕ ይ.ካ :- ጸሎተ ቡራኬ ይ.ካ :- " እግዘብሔር አብ አንድያ ልጁን የሰደደው ባል በማታውቅ በወለት ሥጋ ያድር ዘንድ ነው። ሕፃናትን የሚፈጥር እርሱ ሳይወሰን በማኅፀን ተወሰነ። አምላክ ሲሆን ሰው ሆነ። እሳተ መለኮትም ሲሆን ተወለደ። አደገ በጌጥና በክብር አይደለም። እንደ ድሆች ልጆች ለዘመዶቹ እየታዘዘ በብዙ ተግሣጽ አደገ እንጂ።" "ከኃጢአት ንጹሕ ሲሆን ባርያ ያጠምቀው ዘንድ ራሱን አዘነበለ። ወኃን ጠጅ እስከማድረግ ድረስ ተአምራት አደረገ በምድረ በዳም ብዙ ሰዎችን አጠገበ።" ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ስልሳ_ሰባት ያ ቃል ቀዳማዊ ነበረ ➜ ሰኔ / 11 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

በቅርበት የምታውቋቸው ክርስቲያኖች የሚበሉት አጥተው በረኃብ ሲሰቃዩ ማየት እጂጉን ያማል። ሁለቱም እጂግ የሚዋደዱና በጉልበታቸው ሠርተው የሚተዳደሩ ነበሩ ቀን ዘንብሎባቸው የቤቱ ምሰሶ የሆነው ባልየው
በቅርበት የምታውቋቸው ክርስቲያኖች የሚበሉት አጥተው በረኃብ ሲሰቃዩ ማየት እጂጉን ያማል። ሁለቱም እጂግ የሚዋደዱና በጉልበታቸው ሠርተው የሚተዳደሩ ነበሩ ቀን ዘንብሎባቸው የቤቱ ምሰሶ የሆነው ባልየው በሥራ ላይ ወድቆ እግሩ ፈጽሞ ተሰበረ ጭንቅላቱም ተጎዳ ለዓመታት ፓራላይዝድ ሆነ በእርሱ መታመም ሁሉም እያዘነ ሳለ ባለቤቱም ምንም አይነት የጉልበት ሥራ እንዳትሠራ በጠና ታማ የመታከሚያም አጥታ ትሰቃያለች። በእኒህ ባልና ሚስት የተወለዱት ሁለቱ ሕፃናትም ገና ቦርቀው ሳይጨርሱ እናትና አባታቸውን በጽኑ ደዌ ታመው ማየቱ ሳቃቸውን ወደ እለቅሶ ቀየረው። ይባስ ብሎ በቤታቸው ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ አለመኖሩ ለሕፃናቱ ሌላ ሕመም ነው ለታመሙት ወላጆችም ሌላ ስቃይ ነው ልጅን ያክል ነገር በርኃብ ሲቀጡ ማየቱ 😭😭😭 ክርስቲያኖች ወገኖቻችን እባካችሁን ይህንን መልእክት ሼር በማድረግ አዳርሱት (ለበጎ አድራጊ ምእመናንና የሚዲያ ሰዎችም ላኩላቸው) "በእውኑ እኛም ተባብረን ብናግዛቸው በምድር በረከቱን በሰማይ መንግሥቱን እንወርሳለን።" ✍️ ማሳሰቢያ :- የሰዎቹን አድራሻና የባንክ አካውንት ያላስቀመጥኩት መጀመሪያ መረጃውን አይታችሁ ሃሳባችሁን ለመስማትና ምን እናድርግላቸው የሚለውን እንድንመክርበት ነው። ሀሳባችሁን በኮሜንትና በውስጥ መስመር ጻፉልኝ። 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21

የሠለስቱ ምእት ቅዳሴ መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ #ክፍል_ስልሳ_አምስት 💎 ሰውን ሳይፈጥረው ገነትን አዘጋጀተ ይ.ዲ :- "እናስተውል" ይ.ካ :- "አባታችንን አዳምን በፈጠረው ጊዜ መሬትንና ውኃን ነፋስንና እሳትን ያመጣ ዘንድ የተመላለሰ አይደለም። ከዙፋኑ ሳይነቃነቅ ፈጽሞ ሳይነዋወጽም ነው እንጂ።" በዚህም ይህንን የመሰለ ምሥጢር ያለበት ምስጋና ተካቷል። ➢ አዳምን ለመፍጠር አራቱን ባሕርያት ነሣ። ሁለቱን ከሚዳሰስ (መሬትና ውሃ) ፣ ሁለቱን ከማይዳሰስ (እሳትና ነፋስ) ፣ ሦስቱን ከሚታይ (መሬት ፣ ውሃ ፣ እሳት) ፣ አንዱን ከማይታይ (ነፋስ)። ➢ ቅዱሳት በሚሆኑ እጆቹ በእርሱ አምሳል ፈጠረው። የሕይወትንም እስትንፋስ በእርሱ ላይ እፍ አለበት። #ማብራሪያ :- የሕይወትንም እስትንፋስ እፍ አለበት ማለት ሥጋ መጀመሪያ ተፈጥሮ ነፍስ ቆይቶ ተፈጠረ ማለት አይደለም ነፍስና ሥጋ ተፈጥሯቸው እኩል ነውና። ልጅነትን አሳደረበት ሲል ነው እንጂ። ➢ በላይ ላሉት ድምፅን አሰማ ፣ ማለት (እንደ ዲያብሎስ ላልካዱት ለጸኑት መላእክት ብርሃን ይሁን ብሎ አሰማቸው)። በታች ያሉትንም አንቀጠቀጠ ፤ ማለት(ዲያብሎስና ሠራዊቱን እንጦረንጦስ አወረደ)። ደመናትንም ረገጠ። ያለ እሳት አቃጠለ ያለውኃም አቀዘቀዘ። ➢ ፀሐይና ጨረቃን መፍጠሩ ጨልሞት ሊያበሩለት አይደለም። ከርሱ ብርሃንነት የስንዴ ቅንጣት ያክል ሰጣቸው እንጂ። ስለዚህም በሰው ላይ አበሩ። ➢ ሰውን ሳይፈጥረው ገነትን አዘጋጀ የወደደውን ወደ እርስዋ ያገባ ዘንድ። የሲኦልንም እሳት አዘጋጀ የገላውን ወደ እርስዋ ያገባ ዘንድ። ከዚህ በቀጠለም የአብና ወልድ የመንፈስ ቅዱስን ሕልውና አንድነት ሦስትነት ሐዋርያት እንደ ተናገሩ ይናገራል። ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ስልሳ_ስድስት እንደ ማይሰጥ ይዘገያል ➜ ሰኔ / 10 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

ንስሓ አባታቸው መነኵሴ ካልሆነ የሚጸድቁ የማይመስላቸው ምእመናን ግን የጤናቸው ነውን? ለምንኵስና መበላሸት ተጠያቂዎቹ ስንቅ የሚቋጥሩና ቀሚስ የሚያጥቡ ምእመናንም ናቸው።

ቀሲስ ጌትነት አይተነው ከእስር ተፈትተዋል። እውነቱን ከመናገር ወደ ኋላ የማይሉት ወጣቱ ካህን እንኳን ተፈቱልን በዛውም አሳሪዎቹን በሰማያዊ ስልጣንዎ ይሰሩሉልን። 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ http
ቀሲስ ጌትነት አይተነው ከእስር ተፈትተዋል። እውነቱን ከመናገር ወደ ኋላ የማይሉት ወጣቱ ካህን እንኳን ተፈቱልን በዛውም አሳሪዎቹን በሰማያዊ ስልጣንዎ ይሰሩሉልን። 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21

የሠለስቱ ምእት ቅዳሴ መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ #ክፍል_ስልሳ_አራት ቅዳሴ ሠለስቱ ምእት 💎 ከሰማያት ይልቅ ከፍ ያለ ነው "አኰቴተ ቍርባን ዘ፫፻፲ወ፰ቱ ርቱዓነ ሃይማኖት ... ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ አስራ ስምንቱ ሊቃውንት የተናገሩት የቍርባን ምስጋና። ጸሎታቸው በረከታቸው ከእኛ ጋራ ይሁን ለዘላለሙ አሜን።" ወልድ ዋሕድ በመለኰቱ ዘእሩይ ምስለ አብ ብለው ሃይማኖትን አቅንተው ከኃድያንን ለይተዋልና ሃይማኖታቸው የቀና አላቸው። ይ.ካ "ግሩም በውስተ ደመናት ወልዑል እምሰማያት እግዚአብሔር ... ፤ በደመናት ግሩም ነው ከሰማያት ይልቅ ከፍ ያለ ነው። እግዚአብሔር መንገዱ ሁሉ ምስጉን ነው የአማልክት አምላክ ፍጹም አሸናፊ ነው። የሌለበት ጊዜ የለም የታጣበትም ጊዜ የለም በመለኮቱ ግን ፈጽሞ የታየበት ጊዜ የለም። እርሱን ማየት የሚችል የለም አነዋወሩም እንደምን እንደሆነ የሚያውቅ የለም። ሰማይና ምድር ከዓለማቸው ሁሉ ጋራ ባሕርና ወንዞች በውስጣቸውም ያሉ ሁሉ እነርሱን የሚያመሰግኑ። ጸጋው ሁሉ የተፈጠረ በቸርነቱም ሁሉ የሚያድር። ይኸውም አንድ የሚሆን ያንድ አባት የጌታ አባት ከልጁ ጋራ እውነተኛ ብርሃን የሚሆን የመሢሕ አባት ነው።" ይ.ዲ "ተሰጥዎውን መልሱ።" ይ.ሕ "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ።" ✍️ይ.ካ የአብን ከልጁ ጋራ አነዋዋሩን እንናገራለን በዚህ የንባብ ክፍል ተካቶ የሚገኙት የሚከተሉት ናቸው። ➢ ከፍጥረት ሁሉ በፊት ሰማያትና ምድር ሳይፈጠሩ አብ ከወልድ ጋር ነበረ። ➢ ተራራዎችና ኮረብቶች ሳይቆሙ የአየርም ርዝመት ሳይታይ የነፋስም ኃይል ሳይነፍስ አብ ከወልድ ጋር ነበረ። ➢ ብልጭልጭታ ሳመላለስ የመብረቅ ፍጥነት ሳይታይ ደመናት ሳይዘረጉ አብ ከወልድ ጋር ነበረ። ➢ ከመላእክት መፈጠር በፊት ከሰማይ በታች ከሚጠራ ስም ሁሉ በፊት (በምድር ያሉ ሳይፈጠሩ በፊት) ፤ አብ ከወልድ ጋር ነበረ። ➢ ማንም ወደ ሰማይ ቢወጣ ወደ ምድር ቢወርድ ወደ ዳርቻወት ቢመላለስ አነዋወሩን ማግኘት ማወቅ አይችልም። ይ.ዲ "የተቀመጣችሁ ተነሡ" ✍️ ይ.ካ "አነዋወሩ እንዴት እንደ ሆነ ያውቅ ዘንድ በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስም መካከል ሊገባ አይችልም። አብ ልጁን ወለደው በዚህ ጊዜ እንዲህ ባለ ዘመንም ወለደው አይባልም። ከአብ መወለዱ አይታወቅም ጭንቅ ነውና። አነዋወሩም አይታወቅም የተሠወረ ነውና ላባቱ ቀኙ ነው ክንዱ። ልጁ ወዳጁም እንደርሱ የሚሆን የሚመስል ነው። ይ.ዲ "ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ።" ✍️ይ.ካ "አብ ልጁን ወለደው። እንደ ተቸገረ ሰው ያገለግለው ዘንድ ለሥራ እርዳታ በምክንያት የወለደው አይደለም። ሰማይና ምድርን በፈጠረም ጊዜ የረዳው የለም ከሃሊ ነውና።" በዚህም ይህንን የመለሰ ተጽፏል ➢ ፍጥረትን ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ማረፉ እንደ ሰው ደክሞት ያረፈ አይደለም። ➢ የእሳት ሰይፍ ከአፉ ይወጣል። የተናገረውን በዚያው ጊዜ ያደርጋል። ያሰበው በቅጽበት ይሆንለታል። የሕሊናት ሕሊና ጥበበኛም ብልሃተኛም እርሱ ነው። ➢ እንደ እርሱ በቀመር የሚቀመጥ መሠረትን የሚሠራ መሠረትን ተሸክሞ በጠፈር የማኖር ማነው። በውኃ ላይ ይመሠርታል በጥቃቅን ይሠራል በረቂቅ ይጠቀልላል በአሸዋ ይወስናል። በነፋስ ያጸናል ውኃውን ሰቅሎ ሰማይ ይለዋል። ➢ ስለ ሰው አፈጣጠሩ ፤ "ውኃን በማኅፀን ይቋጥራል ሥጋም ይሆን ዘንድ ያረጋዋል በሥር ያሥረዋል በጅማትም ያጸናዋል ጠጕርን ይቆጥራል። ልብን ይመረምራል ኵላሊትንም ያውቃል።" ➢ አብ ልጁን ወለደው ዕለት ግን የለም ሰዓትም የለም ። በወለደውም ጊዜ አባቱ ከእርሱ ብቸኛ አልሆነም። #ማብራሪያ :- ዕለት የለም ሰዓት የለም ማለት በዚህን ዕለት በዚህን ሰዓት ወለደው ተብሎ አይነገርም። አብም ያለ ወልድ የኖረበት ጊዜ የለም። ➢መላእክትንም ለምስጋና ሳይፈጥር ምስጋናው የተቋረጠ አይደለም። የአብ እና የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምስጋና የመላ ነው እንጂ። #ማብራሪያ :- መላእክት ሳይፈጠሩ ምስጋናው እንዴት የመላ ነው ይባላል ማን እያመሰገነው ነው ቢሉ ባሕርይው ባሕርይውን እያመሰገነው። ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ስልሳ_አምስት ሰውን ሳይፈጥረው ገነትን አዘጋጀ ➜ ሰኔ / 9 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

የሠለስቱ ምእት ቅዳሴ መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ #ክፍል_ስልሳ_ሦስት ቅዳሴ ሠለስቱ ምእት 💎ጸሎተ ሃይማኖት ✍️ መግቢያ ሠለስቱ ምእት በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዘመን በጉባኤ ኒቅያ አርዮስን ለማውገዝ የተሰበቡ ናቸው። በጉባኤው አርዮስን ካወገዙ ሃይማኖትን ከመለሱ በኋላ የሠራቸው ሥራዎች ብዙ ናቸው። ከእነዚህም ውስጥ:- ✔️ የቤተክርስቲያንን ሥርዓት ሠርተዋል ✔️ የመጻሕፍትን ቀኖና አስቀምጠዋል ✔️ ለመጻሕፍት አርእርስት ሰጥተዋል ✔️ መጽሐፈ ቅዳሴና ሌሎችንም መጻሕፍት ጽፈዋል ✔️ ጸሎተ ሃይማኖትን ደርሰዋል። ከድርሰታቸው ውስጥ ጸሎተ ሃይማኖት ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ (በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን) እስከሚለው ድረስ ሲሆን ፤ ከዛ በኋላ ያለውን የደረሱት በቁጥንጥንያ የተሰበሰቡት መቶ አምሳው ሊቃውንት ናቸው። መጽሐፈ ቅዳሴም አንዱ ድርሰታቸው ሲሆን ዛሬ ላይ በቤተክርስቲያናችን ከሚቀደሱት አሥራ አራት ቅዳሴዎች መካከልም አንዱ ነው። ✍️ ጸሎተ ሃይማኖት ነአምን በአሐዱ አምላክ ፤ የሚለው በቅዳሬ ጊዜ የሊቃውንት ቅዳሴ መግቢያ ነው። ✍️ የጸሎተ ሃይማኖት ይዘትና ምሥጢር ጸሎተ ሃይማኖት በውስጡ አምስቱ አእማደ ምሥጢር ✔️ ምሥጢረ ሥላሴ ✔️ ምሥጢረ ሥጋዌ ✔️ ምሥጢረ ጥምቀት ✔️ ምሥጢረ ቍርባን ✔️ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ያለበት ነው። ✍️ ምሥጢረ ሥላሴ ➢ "ሁሉን በያዘ ሰማይና ምድርን የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።" ብሎ አብን እና አንድ አምላክ ብቻ መኖሩን ይነግረናል። "ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋራ በነበረ የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን።" ብሎ ወልድን ፤ ወልድ በቅድምና ከአብ ጋር እንደነበረ ሥጋ የለበሰው ኢየሱስ ክርስቶስም ልጁ እንደ ሆነ ያስረዳል። "ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ የተፈጠረ ያይደለ የተወለ በመለኮቱ ከአብ ጋራ የሚተካከል። ሁሉ በእርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምንም የሆነ የለም። በሰማይም ካለው በምድርም ካለው።" ብሎ የወልድና የአብን እሪና (አንድነት) ወልድም ፍጥረትን የፈጠረ አምላክ መሆኑን ያስረዳል። ✍️ ምሥጢረ ሥጋዌ "ስለ እኛ ስለ ሰው ስለመዳናችን ከሰማይ ወረደ። ከመንፈስ ቅዱስ የተነሣ ከቅድስት ድንግል ማርያም ፈጽሞ ሰው ሆነ።" ብሎ ሥጋዌውን ስለ ሰው ልጆች መዳን በድንግልና ተጸንሶ በድንግልና መወለዱን ይናገራል። ✍️ ምሥጢረ ቍርባን እና "ሰው ሁኖ በጰንጤናዊ በጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ። ታመመ ሞተ ተቀበረ።" ብሎ ምሥጢረ ቍርባንን ያጠይቃል። ቍርባን የክርስቶስ ሕማሙ ሞቱ የሚታሰብበት ነውና። እንዲሁም ቍርባንን የሰጠን ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ ነውና። ✍️ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን "በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተጻፈ። በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ። ዳግመኛም ሕያዋንን ሙታንንም ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል። ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም።" ብሎ ክርስቶስ የትንሣኤያችን በኵር መሆኑን ይናገራል። ጸሎቱም የሚጨርሰው በምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ነው። "የሙታንን መነሣትም ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ።" በማለት። "ጌታ ማሕየዊ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት የተናገረ።" ይሄ ምሥጢረ ሥላሴ ነው መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋራ አንድ መሆኑን ያጠይቃልና። ✍️ ምሥጢረ ጥምቀት "ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰብዋት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያንም እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተሥረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን።" ብሎ የቤተክርስቲያንን ነገርና የጥምቀትን ነገር ይናገራል። ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ስልሳ_አራት ከሰማያት ይልቅ ከፍ ያለ ነው ➜ ሰኔ / 8 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

"ክርስቲያን መወለድ የለበትም" የአክራሪዎቹ አነጋገር በአርሲ ምድር የ9 ወር ነፍሰ ጡር እናትን ሆዷን ተርትረው የገደሏት ከዚህ በላይ የክርስቲያኖችን ሞት ምን ማሳያ አለ ምን እስከሚፈጠር ነው ዝምታችንስ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21

ሐሳባችንና ምልከታችን ከአርሲ ሳይርቅ የቅዳሴ ማብራሪያ ትምህርታችን ነገ ይጀመራል። በቴሌግራም https://t.me/MEBspiritualtraining21
ሐሳባችንና ምልከታችን ከአርሲ ሳይርቅ የቅዳሴ ማብራሪያ ትምህርታችን ነገ ይጀመራል። በቴሌግራም https://t.me/MEBspiritualtraining21

እንደ ሀገር ከፍ ሲልም እንደ ዓለም ኦርቶዶክሳዊ ኅብረታችንን ማጠናከር አለብን ለመንግሥቱ የሚያበቃንም ይሄ ነው። በተለይ የተማረው አካል ሊያስብበት ይገባል።

አንድነት ኃይል ነው የምእመናን ኅብረት መምህራንን ማስፈታት ችሏል። ዲያቆን ዘላለም ታየ ተፈትቷል
አንድነት ኃይል ነው የምእመናን ኅብረት መምህራንን ማስፈታት ችሏል። ዲያቆን ዘላለም ታየ ተፈትቷል

የኔታ በትረ ማርያም አበባው ተፈትተዋል ለጎንደርና አካባቢው ምእመናን ስላደረጋችሁልን መልካም ነገር እናመሰግናለን። በሌላ ቦታ የታሰሩ መምህራንንም በሰላም ያስፈታልን
የኔታ በትረ ማርያም አበባው ተፈትተዋል ለጎንደርና አካባቢው ምእመናን ስላደረጋችሁልን መልካም ነገር እናመሰግናለን። በሌላ ቦታ የታሰሩ መምህራንንም በሰላም ያስፈታልን

ሀገርን የመሠረተችውን ቤተክርስቲያን ከሀገሯ ሊያስወጧት ጠላቶቿ ተበረታቱባት የዘመናችን ባለጊዜዎች ታሪካችሁን በጥቁር ሰሌዳ እየጻፍን ነው። አምላከ ኃይል ውድቀታችሁን ያሳየን። ዓይኖቻችን አርሲ ላይ
ሀገርን የመሠረተችውን ቤተክርስቲያን ከሀገሯ ሊያስወጧት ጠላቶቿ ተበረታቱባት የዘመናችን ባለጊዜዎች ታሪካችሁን በጥቁር ሰሌዳ እየጻፍን ነው። አምላከ ኃይል ውድቀታችሁን ያሳየን። ዓይኖቻችን አርሲ ላይ ናቸው።

አርሲን መርሳት ክርስትናችንን እንደ መርሳት ነው።