Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ
Open in Telegram
መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አስተምህሮና ሙሉ የግእዝ ቋንቋ ሥልጠና ትምህርት ማስተማሪያ የቴሌግራም ገጽ። በመደበኛ መርሐ ግብር የግእዝ ቋንቋ ሥልጠናን መከታተል የምትሹ በኮሜንት መስጫው ጻፉልኝ።
Show more4 667
Subscribers
+3324 hours
+1987 days
+20530 days
Posts Archive
➖ ➖ ➖ ➖
🔹 ነ ብሂል ➢ ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ። ክርስቶስ ደዌያችንን ነሣ መከራችንንም ተሸከመ ማለት ነው
🔹 ኑ ብሂል ➢ ዛኅኑ ለባሕር። የባሕር ጸጥታ ማለት ነው፡፡.
🔹ኒ ብሂል ➢ ኮናኒ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ገዢ ነው ማለት ነው።
🔹ና ብሂል ➢ መና እስራኤል። የእስራኤል ምግባቸው ማለት ነው፡፡
🔹ኔ ብሂል ➢ መድኃኔ ዓለም። የዓለም መድኃኒት ክርስቶስ ማለት ነው።
🔹ን ብሂል ➢ መኮንን እግዚአብሔር። እግዚአብሔር ፈራጅ ነው ማለት ነው።
🔹ኖ ብሂል ➢ ኖላዊ እግዚአብሔር። እግዚአብሔር ጠባቂ ነው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ኀ ብሂል ➣ ኀብአ ርእሶ። ባሕርዩን ሰወረ ማለት ነው፡፡
🔹ኁ ብሂል ➢ እኁዝ አቅርንቲሁ። ሥልጣኑ የባሕርይ ገንዘቡ ነው ማለት ነው፡፡
🔹ኂ ብሂል ➢ ዘልማዱ ኂሩት። በጎነት፣ ቸርነት ልማዱ የሆነ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ኃ ብሂል ➢ ኃያል በኃይሉ እግዚአብሔር። እግዚአብሔር ኃያል ነው ማለት ነው።
🔹ኄ ብሂል ➢ ኄር እግዚአብሔር ቸር ነው ማለት ነው።
🔹ኅ ብሂል ➢ ኅብስት ለርኁባን። እግዚአብሔር ለተራቡት ኅብስት (ምግብ) ነው ማለት ነው።
🔹ኆ ብሂል ➢ ኆኅተ ገነት ወልድ። እግዚአብሔር ወልድ የገነት በር ነው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹አ ብሂል ➢ አአኲቶ ወእሴብሖ ለእግዚአብሔር። እግዚአብሔርን ፈጽሞ አመሰግነዋለሁ።
🔹ኡ ብሂል ➣ ሙጻኡ ለቃል። የቃል መገኛው ማለት ነው፡፡
🔹ኢ ብሂል ➢ ለሊሁ ተንሣኢ ወለሊሁ አንሣኢ። ክርስቶስ ራሱ ተነሺ ራሱ አንሺ ማለት ነው።
🔹ኣ ብሂል ➢ ኣሌፍ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ቀዳማይ ወደኃራዊ። ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር ፍጥረታትን የፈጠረ አግዚአብሄር ማለት ነው፡፡
🔹ኤ ብሂል ➢ አምጻኤ ዓለማት እግዚአብሔር። ዓለማትን ከአለመኖር ያመጣ የፈጠረ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹እ ብሂል ➢ እግዚአብሔር እግዚእ። እግዚአብሔር ጌታ ነው ማለት ነው።
🔹ኦ ብሂል ➢ እግዚኦ። አቤቱ ጌታ ሆይ ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ከ ብሂል ➢ ከሃሊ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነው ማለት ነው።
🔹ኩ ብሂል ➢ ዐርኩ ለመርዓዊ ፤ የሙሽራው ሚዜ ማለት ነው።
🔹ኪ ብሂል ➢ ኪያሁ ንሰብክ ፤ እርሱን ጌታን እናስተምራለን። አንድም ስለእርሱ እንሰብካለን ማለት ነው።
🔹 ካ ብሂል ➢ ካፍ ከሃሊ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነው ማለት ነው።
🔹ኬ ብሂል ➣ ሰባኬ ወንጌል ነዋ በማእከለ አኃው ፤ ወንጌልን የሚያስተምር እነሆ በወንድሞች መካከል አለ ማለት ነው።
🔹ክ ብሂል ➣ ክብሮሙ ለመላእክት ፤ የመላእክት ክብራቸው ማለት ነው።
🔹ኮ ብሂል ➣ ዘረዳእኮ ለአብርሃም ፤ አብርሃምን የረዳሀው እግዚአብሔር ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹 ወ ብሂል ➣ ወረደ እምሰማያት ፤ ከሰማያት ወረደ ማለት ነው።
🔹ዉ ብሂል ➣ ጼዉ ለምድር ፤ የምድር ጨው ማለት ነው።
🔹ዊ ብሂል ➣ ናዜራዊ ፤ ኢየሱስ ናዝራዊ ነው ማለት ነው።
🔹ዋ ብሂል ➢ ዋሕድ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር አንድ ነው ማለት ነው።
🔹ዌ ብሂል ➢ ዜናዌ ትፍሥሕት ፤ ደስታን የሚናገር ማለት ነው።
🔹ው ብሂል ➢ ሥግው ቃል ፤ ሰው የሆነ አምላክ ማለት ነው።
🔹ዎ ብሂል ➢ ቤዘዎ ለዓለም ፤ ዓለምን አዳነው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹 ዐ ብሂል ➢ ዐቢይ እግዚአብሔር ወብዙኅ አኰቴቱ ፤ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ምስጋናውም ብዙ ነው ማለት ነው።
🔹ዑ ብሂል ➢ በግዑ ለእግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር በግ ማለት ነው።
🔹ዒ ብሂል ➢ ለሊሁ ሠዋዒ ወለሊሁ ተሠዋዒ ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ መሥዋዕት አቅራቢ ራሱ መሥዋዕት ነው ማለት ነው።
🔹ዓ ብሂል ➢ ዓይነ ኲሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ ፤ ጌታ ሆይ የሰው ሁሉ ሰውነት አንተን ተስፋ ያደርጋል ማለት ነው።
🔹ዔ ብሂል ➣ ዔ ዐቢይ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ማለት ነው።
🔹ዕ ብሂል ➢ ብፁዕ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ብፁዕ ነው ማለት ነው።
🔹ዖ ብሂል ➢ ሞዖ ለሞት ወተንሥአ ፤ ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ ተነሳ ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ዘ ብሂል ➢ ዘኲሎ ይእኅዝ እግዚአብሔር ፤ ሁሉን የያዘ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ዙ ብሂል ➢ ምስጕዙ ለሐንካስ ፤ ለአንካሳ ምርኩዝ ነው ማለት ነው።
🔹ዚ ብሂል ➣ ናዛዚ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር የሚያረጋጋ ነው ማለት ነው።
🔹ዛ ብሂል ➢ ዛይ ዝኩር እግዚአብሔር ፤ አምላክ የሚያስብልን ነው።
🔹ዜ ብሂል ➢ አኃዜ ዓለም በእራኁ ፤ ዓለምን በመሐል እጁ የያዘ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ዝ ብሂል ➢ ሐዋዝ ሕገ እግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር ሕግ ያማረ ነው ማለት ነው።
🔹ዞ ብሂል ➣ አግአዞ ለአዳም ፤ አዳምን ነጻ አወጣው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹 የ ብሂል ➢ የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ፤ የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች ማለት ነው።
🔹ዩ ብሂል ➢ ዕበዩ ለእግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር ታላቅነት ማለት ነው።
🔹ዪ ብሂል ➢ መስተስርዪ ፤ ኃጢኣትን የሚያስተሰርይ ማለት ነው።
🔹ያ ብሂል = አንተ ኬንያሁ ፤ ጥበበኛው አንተ ነህ ማለት ነው።
🔹ዬ ብሂል ➢ ዐሣዬ ሕይወት ፤ ሕይወትን የሚያድል ማለት ነው።
🔹ይ ብሂል ➣ ሲሳይ ለርኁባን ፤ ለታራቡት ምግብ ማለት ነው
🔹ዮ ብሂል ➣ ዮድ የማነ እግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር ቀኝ ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ደ ብሂል ➢ ደመረ መለኮቶ ምስለ ሥጋነ ወሥጋነ ምስለ መለኮቱ ፤ እግዚአብሔር ወልድ ቃሉን ከሥጋችን ሥጋችንን ከቃሉ አዋሐደ ማለት ነው።
🔹ዱ ብሂል ➢ ፈዋሴ ዱያን ፤ ሕመምተኛን የሚፈውስ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ዲ ብሂል ➣ ቃለ ዓዋዲ፤ አዋጅ ነጋሪ ማለት ነው።
🔹ዳ ብሂል ➣ ዳሌጥ ድልው እግዚአብሔር፤ እግዚአብሔር ሁሉንም ይመዝናል ፣ ያዘጋጃል ማለት ነው።
🔹ዴ ብሂል ➣ ዐማዴ ሰማይ ወምድር፤ ሰማይና ምድርን የፈጠረ ማለት ነው።
🔹ድ ብሂል ➣ ወልድ ዋሕድ፤ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው እግዚአብሔር ወልድ ማለት ነው፤
🔹ዶ ብሂል ➣ ፈነወ ዋሕዶ ወተሰብአ እምኔኪ ፤ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ልጁን ልኮ ከእመቤታችን ሰው ሆነ።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ገ ብሂል ➢ ገባሬ ሰማያት ወምድር ፤ ሰማይና ምድርን የፈጠረ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ጉ ብሂል ➣ ለአስካለ ሕይወት ሐረጉ ፤ የሕይወት ፍሬ ሐረግ ማለት ነው።
🔹ጊ ብሂል ➣ ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ሥራውን የሚሰራበት ጊዜ አለው።
🔹 ጋ ብሂል ➣ ጋሜል ግሩም እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ድንቅ ነው ፣ ግሩም ነው ማለት ነው።
🔹ጌ ብሂል ➣ ጽጌ ቅዱሳን ፤ የቅዱሳን አበባ ወይም ክብር ፣ ውበት ማለት ነው።
🔹ግ ብሂል ➣ ሐጋጌ ሕግ ፤ ሕግን የሰራ ማለት ነው።
🔹ጎ ብሂል ➣ ሰርጎሙ ለሐዋርያት ፤ የሐዋርያት ጌጣቸው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ጠ ብሂል ➣ ጠቢብ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ጠቢብ ነው ማለት ነው።
🔹ጡ ብሂል ➣ ውስጡ ለሰብእ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ለሰው ውስጡ ነው።
ከሀ - ፐ ያሉ ፊደላት ትርጉም
ትምህርተ ልሳነ ግእዝ
ትምህርት አሐዱ ➛ ፊደል ወአኃዝ
ምዕራፍ ክልኤቱ ➛ ትርጓሜ ፊደል
#ክፍል_ሰመንቱ
ትርጓሜ ፊደላት
➜በዚህ ምዕራፍ ሁሉንም የግእዝ ፊደላት ትርጉም እናያለን።
🔷"ወዘኢያስተርኢ እግዚአብሔር እምፍጥረተ ዓለም ይትዐወቅ በፍጥረቱ በሐልዮ ወበአእምሮ ፤ የማይታየው የእግዚአብሔር ባሕርይ እርሱም የዘለዓለም ኃይሉና ጌትነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ የፈጠረውን ፍጥረት በማሰብና በበመርመር ይታወቃል።" እንዳለ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ። ሮሜ ፩:፳
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤ/ክ ሊቃውንት እናመሰግነው ዘንድ መግባቢያ ቋንቋን የሰጠን፣ ሀሳባችንን በጽሑፍ እንገልጽ ዘንድ ፊደላትን እንድናውቅ ያደረግንን አምላካችንን የሚጠቀሙባቸውን ሁሉንም የግእዝ ፊደላት ከእግዚአብሔር የባሕርይ አምላክነት ፣ የሰውን ልጅ ከማዳን ስራው ጋር አያይዘው ይረተጉማሉ።
ይኼውም እንደ ሚከተለው ነው።
🔹ሀ ብሂል ➣ ሀልወቱ ለአብ እምቅድመ ዓለም ፤ የእግዚአብሔር አነዋወሩ ከዓለም በፊት ነው ማለት ነው።
🔹ሁ ብሂል ➣ ኪያሁ ተወከሉ ፤ በእርሱ (በእግዚአብሔር) ታመኑ።
🔹ሂ ብሂል ➣ አስተይዎ ብሂዐ ፤ አይሁድ ጌታን ሖምጣጤ አጠጡት ማለት ነው።
🔹ሃ ብሂል ➢ ሃሌ ሉያ ፤ ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር ማለት ነው።
🔹 ሄ ብሂል ➢ በኲለሄ ሀሎ ፤ እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ እና ጊዜ አለ ማለት ነው።
🔹ህ ብሂል ➢ ህልው እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር አለ ማለት ነው።
🔹ሆ ብሂል ➢ ኦሆ ብሂሎ ወመጽአ ፤ እሺ ብሎ መጣ ማለት ነው ። ይኸውም አዳምን ለማዳን እግዚአብሔር በፈቃዱ ሥጋን መዋሐዱን ያመለክታል።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ለ ብሂል ➢ ለብሰ ሥጋ ዚአነ ፤ እግዚአብሔር የእኛን ሥጋ ተዋሐደ ማለት ነው።
🔹ሉ ብሂል ➢ ሣህሉ ለእግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር ይቅር ባይነት ማለት ነው።
🔹ሊ ብሂል ➢ ከሃሊ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነው ማለት ነው።
🔹ላ ብሂል ➢ ላሜድ ልዑል እግዙአብሔር ፤ እግዚአብሔር ልዑል ነው ማለት ነው።
🔹ሌ ብሂል ➢ መቅለሌ ዕጹብ ፤ ጭንቀትን (ጭንቅን) የሚያቀል እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ል ብሂል ➢ መስቀል ዘወልደ አብ ፤ የአብ ልጅ መስቀል ማለት ነው።
🔹ሎ ብሂል ➢ ዘሀሎ እምቅድም ፤ ቅድመ ዓለም የነበረ እግዚአብሔር ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ሐ ብሂል ➢ ሐመ ወሞተ በእንቲአነ ፤ ክርስቶስ ስለእኛ ሲል መከራን ተቀበለ ሞተ ማለት ነው።
🔹ሑ ብሂል ➢ ሰብሑ ለስመ እግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔርን ስም አመስግኑ ማለት ነው።
🔹ሒ ብሂል ➢ መንጽሒ ፤ ከበደል የሚያነጻ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ሓ ብሂል ➢ መፍቀሬ ንስሓ ፤ ንስሓን የሚወድ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ሔ ብሂል ➢ ሔት ሕያው እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ሕያው ነው ማለት ነው።
🔹ሕ ብሂል ➢ ሕያው እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር በባሕሪው ሞት በመንግሥቱ ሽረት የሌለበት ዘለዓለማዊ ነው።
🔹ሖ ብሂል ➢ ንሰብሖ ለእግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔርን እናመስግነው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹መ ብሂል ➢ መንክር ግብሩ ለእግዚአብሔር ፤ የእግዚአብሔር ሥራው ድንቅ ነው ማለት ነው።
🔹ሙ ብሂል = ሙጻእ ሕግ ፤ የሕግ መገኛ።
🔹ሚ ብሂል ➢ ዓለመ ኀታሚ ፤ ዓለምን የፈጠረ፣ ዓለምን የሚያኖር ዓለምን የሚያጠፋ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።
🔹ማ ብሂል ➢ ፌማ መንፈስ ቅዱስ ፤ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው።
🔹ሜ ብሂል ➢ ሜም ምዑዝ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ምዑዝ ነው ማለት ነው።
🔹ም ብሂል ➢ አምላከ ሰላም ፤ የሰላም አምላክ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ሞ ብሂል ➢ ሞተ በሥጋ ፤ በሥጋ ሞተ ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ሠ ብሂል ➢ ሠረቀ በሥጋ እምድንግል ፤ ቃል ከድንግል ማርያም በሥጋ ተወለደ ማለት ነው።
🔹ሡ ብሂል = መንበረ ንግሡ ፤ የንጉሥነቱ ዙፋን ማለት ነው።
🔹ሢ ብሂል ➢ ሢመተ መላእክት ፤ የመላእክት ሹመት ማለት ነው።
🔹ሣ ብሂል ➢ ሣህል ወርትዕ ፤ ይቅርታና ቅንነት ማለት ነው።
🔹ሤ ብሂል ➢ ሤሞሙ ለካህናት ፤ እግዚአብሔር ካህናትን ሾመ ማለት ነው።
🔹ሥ ብሂል ➢ ንጉሥ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ንጉሥ ነው ማለት ነው።
🔹ሦ ብሂል ➢ አንገሦ ለአዳም ፤ እግዚአብሔር አዳምን አነገሠው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹 ረ ብሂል ➢ ረግዓት ምድር በቃሉ ። ምድር በቃሉ ጸናች ማለት ነው።
🔹ሩ ብሂል ➢ በኲሩ ለአብ ። ወልድ የአብ አንድያ ልጁ ነው ማለት ነው።
🔹ሪ ብሂል ➢ ዘይሰሪ አበሳ ። በደልን ይቅር የሚል እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ራ ብሂል ➢ ጌራ መድኃኒት ፡፡
🔹ሬ ብሂል ➢ ሬስ ርኡስ እግዚአብሔር ። እግዚአብሔር አለቃ ነው ማለት ነው።
🔹ር ብሂል ➢ ርግብ መንፈስ ቅዱስ ። መንፈስ ቅዱስ ርግብ ማለት ነው።
🔹ሮ ብሂል ➢ ፈጠሮ ለዓለም ። እግዚአብሔር ዓለምን ፈጠረው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ሰ ብሂል ➢ ሰብአ ኮነ ከማነ ። እግዚአብሔር ወልድ እንደኛ ሰው ሆነ ማለት ነው።
🔹 ሱ ብሂል ➢ ፋሲልያሱ።
🔹ሲ ብሂል ➢ ዘይሤሲ ለኩሉ ሥጋ። ደማዊ ፍጥረታትን ሁሉ የሚመግብ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።
🔹ሳ ብሂል ➢ ሳምኬት ስቡሕ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ምስጉን ነው ማለት ነው።
🔹ሴ ብሂል ➢ ለባሴ ሥጋ ። ሥጋን የተዋሐደ እግዚአብሔር ቃል ማለት ነው።
🔹ስ ብሂል ➢ ልብስ ለዕሩቃን ። ለታረዘት ልብስ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።
🔹 ሶ ብሂል ➢ መርሶ ለአሕማር ። የመርከቦች ወደብ።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ቀ ብሂል ➢ ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ። በመጀመሪያ ቃል ነበር ማለት ነው።
🔹ቁ ብሂል ➢ ጽድቁ ለኃጥእ ።
🔹ቂ ብሂል ➢ ፈራቂሁ ለዓለም። ዓለምን የፈጠረ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ቃ ብሂል ➢ ቃልየ አጽምዕ ። አቤቱ ቃሌን ስማ ማለት ነው።
🔹 ቄ ብሂል ➢ ሰዋቄ ኃጥኣን ። ኃጥአንን በንስሓ የሚደግፋቸው።
🔹ቅ ብሂል ➢ ጻድቅ እግዚአብሔር ። እግዚአብሔር እውነተኛ ነው ማለት ነው።
🔹ቆ ብሂል ➢ ቆፍ ቅሩብ እግዚአብሔር ። እግዚአብሔር ቅርብ ነው ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹በ ብሂል ➢ በትሕትናሁ ወረደ ለቤዛ ኲሉ ዓለም። ዓለምን ሁሉ ለማዳን በትሕትናው ሰው ሆነ።
🔹ቡ ብሂል ➢ ጥበቡ ለአብ። የአብ ጥበቡ ማለት ነው።
🔹ቢ ብሂል ➢ ረቢ ነአምን ብከ። መምህር ክርስቶስ ሆይ በአንተ እናምናለን ማለት ነው።
🔹 ባ ብሂል ➢ ባዕድ እም አማልክተ ሐሰት። ከሐሰት አማልክት የተለየ እግዚአብሔር ማለት ነው።
🔹ቤ ብሂል ➢ ቤት ባዕል እግዚአብሔር እግዚአብሔር ባዕለጸጋ ነው ማለት ነው።
🔹ብ ብሂል ➢ ብርሃነ ቅዱሳን። የቅዱሳን ብርሃን ማለት ነው።
🔹ቦ ብሂል ➢ አልቦ ባዕድ አምላክ ዘእንበሌሁ። ከእግዚአብሔር በስተቀር ሌላ አምላክ የለም ማለት ነው።
➖ ➖ ➖ ➖
🔹ተ ብሂል ➢ ተሰብአ ወተሠገወ እማርያም እምቅድስት ድንግል። ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ ማለት ነው።
🔹ቱ ብሂል ➢ መዝራእቱ ለአብ።የአብ ክንዱ ማለት ነው።
🔹ቲ ብሂል ➢ ተአኳቲ እግዚአብሔር እግዚአብሔር ተመስጋኝ ነው ማለት ነው።
🔹ታ ብሂል ➢ ታው ትጉህ እግዚአብሔር። እግዚአብሔር ትጉህ ነው ማለት ነው።
🔹ቴ ብሂል ➢ ከሣቴ ብርሃን። ብርሃንን የሚገልጥ ማለት ነው።
🔹ት ብሂል ➢ ትፍሥሕት ወሐሴት። ፍጹም ደስታ ማለት ነው።
🔹ቶ ብሂል ➢ ነአምን ልደቶ ለክርስቶስ። የክርስቶስን መወለድ እናምናለን ማለት ነው።
➢➢➢የተቀያየሩ ታሪኮች...
✣ከመጀመሪያው እንጨት አዳምና ሔዋንን ከገነት አስወጣቸው ፤ እስከ ክርስቶስ መሰቀል ድረስም የወንበደኛ መቅጫ ነበር። ይህንን የተዛባ ታሪክ ያለውን እንጨት መድኃኔዓለም በቅዱስ መስቀል ሰይሞ የድኅነት የነጻነት የሕይ መንገድ አደረገው።
✣ወንበዴዎችና ቀማኞች በሕዝቡ ዘንድ የተጠሉ የረገሙ ነበሩ እንኳን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ወደ ገነት ሊገባሉ ተብሎ ሊታሰብ ይቅርና ከኃጥአን ፊታውራሪዎች ናቸው ይባሉ ነበር። ዕለተ ዐርብ በጌታ ቀኝ ጎን የተገኘውና መከራ መስቀልን የተሣተፈው ጥጦስ አንድ ቃል በመናገሩና በማመኑ ብቻ የጌታን ደመ ማኅተም
ይዞ ገነት መግባቱ ሳያንስ አዳምንና ደጋግ አባቶችን ቀድሞ መግባቱ ምን ይንቅ ምን ይረቅ።
✣እንጨትን ከእንጨት እያጣባቁ ለተለያየ ተግባር ይውሉ የነበሩ አምስቱ ረዣዥም ወፋፍር ሚስማሮች (ችንካሮች) እነርሱ የተሰሩባትን ዓለም የፈጠረ ጌታን ሰውነቱን በስተው ከእንጨት ጋር ማጣበቃቸው ሊያስወቅሳቸው ሲገባ ፤ የአምስቱ አእማደ ምሥጢር ፣ የአምስቱ ጾታ ምእመናን ምሳሌ መሆናቸው ምን ይደንቅ ምን ይረቅ።
✣ከተፈጠሩ ጀምሮ በሰማይ ላይ ተስዕለው ብርሃናቸውን ለዓለም የሚለግሱት ሦስቱ ታላላቅ ብርሃናት (ፀሐይ ፣ ጨረቃ ፣ ከዋክብት) የፈጣሪያቸውን እርቃን ለመሸፈን የጨካኞችን አይሁድ ልቡና ለማስደንገጥ ፤ መጨለም ፣ ደም መምሰል ፣ መርገፍ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
✣ኦሪታውያን የሚመኩበት የኦሪቱ ቤተመቅደስ መጋረጃ ቤተመቅደሳችንን ሊያፈርስብን ነው ብለው በቅናት ጌታን በሰቀሉት ጊዜ የሰው እጅ ሳይነካው ከሁለት መቀደዱ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
✣ውሃን ያስገኘ ፣ ፈሳሾችን የፈጠረ በዝናብ አብቆሎ በፀሐይ አብስሎ የሚመግብ አምላክ ተጠማሁ ብሎ ውሃ መለመኑ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
✣ከክፋታቸው ላለመተባበር ብሎ ተደብቆ የዋለው አንድ ዓይናው ለንጊኖስ ነፍሱ ከሥጋው ከተለየ በኋላ ጌታን ጎኑን በጦር ቢወጋው ደምና ውሃ ፈሶ ተበቅሎት ሊያጠፋው ሲገባ ዘልማዱ ሂሩት የሆነ አምላክ በቸርነቱ የታወረች ዐይኑን ማብራቱ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
✣ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላክ በመቃብር ተወስኖ መዋሉና ማደሩ እንዲሁም ሙታንን ወደ አፈርነት የምትቀይረው መቃብር ጌታን መሸከሟ እና መወሰኗ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
✣አምስት ሺህ ከአምስት መቶ ዘመን አዳምና ልጆቹን ተቆራኝቶ በሲዖል መከራ ያጸናባቸው የነበረ ዲያብሎስ መፍራቱ ፣ መንቀጥቀጡ ፣ ድል መነሳቱ ፣ ነፍሳትንም በነጻ መልቀቁ እንዲሁም ጌታ በመስቀል ትርክዛ ከሲዖል አዳምና ልጆቹን ከሲዖል ወደ ገነት ማሸጋገሩ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
✣ከኃያልነቱ የተነሣ ሥጋ በለበሱ የሰው ልጆች ዘንድ ይፈራ የነበረው ሞት በጌታ ሞት ድል ተነሥቶ የትንሣኤ መጀመሪያ የሕይወት መሸጋገሪያ መሆኑ ምን ይረቅ ምን ይደንቅ።
➜ መጋቢት / 27 / 2017 ዓ.ም
👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
© መ/ር ማኅቶት እሸቴ
+8
የመልካም ወጣት ዓላማው ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችን ከመልካሚቱ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን መለየት እንደሆነ ከመጀመሪያው ተናግረን ነበር።
እኼው ዛሬም መልካም ወጣት በመባል በነዮናታን የተቋቋመው በይፋ የፕሮቴስታንት ማዕከል አንዱ አካል ሁኗል።
እንደ ለመደው ወጣቶችን መስቀል አሳስሮ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ነው የመጣነ እያለ መወናበዱን ቀጥሎበታል።
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
+3
የመጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ ክፍል ሁለት በመጽሐፍ መልኩ በPDF ተለቀቀ።
ለአምስት ወራት ያክል የተማማርነው የቅዳሴ ማብራሪያ ሶፍት ኮፒ / PDF እነሆ በቴሌግራም ገጼ ተለቀቀ።
የማስተማሪያ ሚዲያዎቸን ለሌሎች በማጋራት የትምህርቱን ተደራሽነት እንዲሰፋ ያድርጉ።
የቀጣይ ትምርታችን
፩ ፡ በዕቅበተ እምነት ዙሪያ በጥያቄና መልስ መልኩ ሁሉንም የቤተክርስቲያናችን ትምህርቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በተከታታይ እንማማራለን።
፪ : የውዳሴ ማርያም ትርጉም እና ማብራሪያ
#የማስተማሪያ_ሚዲያዎች
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
🔷🔶🔷 ትምህርቱ ለሁሉም እንዲዳረስ
#ሼር እና #ሜንሽን በማድረግ ለሌሎች እንድታጋሩልኝ በትሕትና እጠይቃለሁ።
© መምህር ማኅቶት እሸቴ
የቀጣይ የትምህርት መርሐግብር
የመጽሐፈ ቅዳሴን ማብራሪያ ሙሉውን
ከዐቢይ ጾም ጀምሮ ማለትም ከየካቲት 11 እስከ ሐምሌ10 ቀን ድረስ በተከታታይ ለአምስት ወራት ያክል ስንማማር ቆይተናል።
ከዚህ በመቀጠልም የምንማማራቸው
፩ ፡ በዕቅበተ እምነት ዙሪያ በጥያቄና መልስ መልኩ ሁሉንም የቤተክርስቲያናችን ትምህርቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በተከታታይ እንማማራለን።
፪ : የውዳሴ ማርያም ትርጉም እና ማብራሪያ
#የማስተማሪያ_ሚዲያዎች
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
🔷🔶🔷 ትምህርቱ ለሁሉም እንዲዳረስ
#ሼር እና #ሜንሽን በማድረግ ለሌሎች እንድታጋሩልኝ በትሕትና እጠይቃለሁ።
መምህር ማኅቶት እሸቴ
አቋቋምን እና ማናቸውንም የአብነት ትምህርት ከምንጩ መማር ለምትፈልጉ
በጎንደር የአቋቋም ምስክር ጉባኤ ቤት ከሆነችው በአታ ለማርያም ካቴድራል እጩ ተመራቂ የሆኑት መምህር ሐመልማል በሚዲያ ለማስተማር ተዘጋጅተዋልና በተቀመጠው የስልክ አድራሻ እና በተቀመጠው የቴሌግራም ሊንካቸው ማግኘት ይችላሉ።
የሚያስተምሩት የትምህርት ዝርዝር
➢ ውዳሴ ማርያም
➢ ዜማ
➢ ንባብ
➢ ዳዊት
➢ ቅዳሴ
➢ አርባዕት ፣ ሠለስት ፣ አርያም ፣ ክስተት
➢ ዝማሬ እና መዋሥዕት
➢ አቋቋም
➢ ወረብ
➢ ክብረ በዓል ፣ ወርሐ በዓል
➢ ቅኔ ምራታ
ስልክ ቁጥር :- 0942856021
የቴሌግራም ሊንክ
👇👇👇
https://t.me/+xmPRo_yEgLc1YTg0
የመጨረሻው የቅዳሴ ማብራሪያ
የጎርጎርዮስ ካልዕ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰማንያ_ሦስት
💎 በቅዱሳን ላይ የምትኖር ነህ
✍️ መግቢያ
ቅዱስ ጎርጎርዮስ በሕፃንነቱ ብሉይ ሐዲስ ተማሯል ከዛም ይህ ዓለም እንደ ሚያልፍ ያኛው ዓለም እንደ ማያልፍ አውቆ መንኖ ገዳም ገባ። ከሄደበት ገዳም አንድ አረጋዊ ኤጲስቆጶስ ነበር እርዳኝ አለው ጎርጎርዮስም ውዳሴ ከንቱ አይሻምና አይሆንልኝም አለው።
ኤጲስቆጶሱ ሞተ። ማነን እንሹም እያሉ ሲጨነቁ "ሲምዎ ለጎርጎርዮስ ገዳማዊ ፣ ገዳዊ መናኙን ጎርጎርዮስን ሹሙት" የሚል ቃል ከሰማይ ሰሙ።
በየተራራው በየጫካው ቢፈልጉት ታጣ ከዚያም ተመልሰው ልብሰ ተክህኖውን ከወንበሩ ላይ አድርገው መጽሐፈ ሢመቱን ደግመው ፤ "ሤምናሁ ለጎርጎርዮስ ፣ ጎርጎርዮስን ሾምነው" አሉ። ካህናቱም ሕዝቡም ይደልዎ ይደልዎ ፣ ይገባዋል ይገባዋል ብለዋል።
የእግዚአብሔር መልአክ ወደ ጎርጎርዮስ ሂዶ ወጥተህ አስተምር አለው። ለማስተማር ወጥቶ በሄደ ጊዜ እንደገና መጽሐፈ ሢመቱን አንብበው ሹመውታል።
ተሹሞ ሳለ ብዙ ተአምራት አድርጓል። ከእነዚህም አንዱ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ ከመሬታቸው መሀል ባህር ነበራቸው ያን ተካፍለው ዓሣ እያሠገሩ ይኖሩ ነበር። በተጣሉ ጊዜ ወደ ጎርጎርዮስ ሄዱ። አንድ ቀን አንዳችሁ አንድ ቀን አንዳችሁ በየተራ እያሠገራችሁ ተጠቀሙ አላቸው። በአንተ ቀን ብዙ በእኔ ቀን ትንሽ ዓሣ ሆነ እያሉ የሚጣሉ ሆነ። በኋላ ጎርጎርዮስ ባህሩን በጸሎቱ አድርቆት መሬቱን ተካፍለው እያረሱ በሰላም ኑረዋል።
ካህኑ :- አኰቴተ ቍርባን ጸሎቱ ወበረከቱ የሀሉ ምስለ ኵልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም አሜን። ቅዱስ ያዕቆብ የተናገረው የቍርባን ምስጋና ይህ ነው። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✍️ በመፈተት እና በሐዳፌ ነፍስ ጸሎቱ ካህኑ ይህንን ይጸልያል
➢ አቤቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናመሰግንሃለን የኃይላት ጌታ የሥልጣናትም ጌታ የይቅርታም ጌታ ንጹሕ ክቡር ምሥጢርህን አድለኸናልና እናመሰግንህ እንወድስህ ዘንድ በቅዱሳን ላይ የምትኖር ነህ።
➢ በልዑላን የተመሰገንህ ትሑታንም የሚያመሰግኑህ ፈጽመን እናመሰግንሃለን።
ይኽን የተቀበልነውን ቅዱስ ቍርባንን አንተ አድለኸናልና።
#ማብራሪያ :- ልዑላን ያላቸው መላእክት ናቸው። ትሑታን ያላቸው ደቂቀ አዳም ናቸው።
✍️ በመጨረሻም ካህኑ በአንብሮ እድ ይህንን ይጸልያል
➢ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባርከን ቀድሰንም ያለ ኃጢአትና ያለ ነውር በደስታ ወደ ቤታችን እንሄድ ዘንድ የበቃን አድርገን።
➢ ከክብርት ማዕድህ የተቀበልነው ሥጋህና ደምህ የሚያድነን ይሁን።
➢ አቤቱ ወደ ሕይወት መንገድ ይመራን ዘንድ መንፈስህንም ላክልን።
➢ ጸሎትን በሚያሳርጉ በካህናት እጅ የተቀበልነው ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ለሕይወትና ለኃጢአት ማስተሥረያ ከሙታንም ተለይቶ ለመነሣት ለመንግሥተ ሰማይ ስርት ይሁነን ለዘላለሙ አሜን።
#ተፈጸመ_መጽሐፈ_ቅዳሴ_ማብራሪያ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።
ወለወላዲቱ ድንግል።
ወለመስቀሉ ክቡር።
#አሜን!!!
➜ ሐምሌ / 10 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
አንድ ታላቅ ካቴድራልን ከገነባ ይልቅ ፡
አንድ ደሃን ያጠገ ሰው የበለጠ መልካም አደረገ።
ከሕንፃ ሰው ይቅደም።
የድዮስቆሮስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰማንያ_ሁለት
💎 ፍጥረታትን ሳይፈጥር በመንግሥቱ ነበረ
✍️ መግቢያ
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ለኦሬንታል ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አባት ነው። በጉባኤ ኬልቄዶን ተገኝቶ ጉባኤውን አውግዞ ትምህርታቸውን ነቅፎ በሃይማኖት እርሱን የመሰሉት ይዞ በመውጣት የሠለስቱ ምእትን አስተምህሮ አጽንቷል።
እርሱን መስለው እርሱን ተከትለው ጉባኤውን የነቀፉትም የአምስቱ አኃት አብያተክርስቲያናት አባቶች ናቸው።
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ የኬልቄዶን ጉባኤ ውሳኔን በማውገዙና የጉባኤው አስተባባሪዎች የሆኑቱን የሮም ነገሥታትን ትእዛዝ በመቃወሙ በንግሥቲቱ ብርክልያ በባሏ በንጉሡ መርቃን ትእዛዝ የዲዮስቆሮስን ጺሙን አስነጭታ ጥርሱን አስወልቃ አስጋዘችው እርሱም በግዞት እያለ መስከረም ሰባት ቀን አረፈ።
ካህኑ :- አኰቴተ ቍርባን ዲዮስቆሮስ ጸሎቱ ወበረከቱ የሀሉ ምስለ ኵልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም አሜን። ቅዱስ ያዕቆብ የተናገረው የቍርባን ምስጋና ይህ ነው። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✍️ የእግዚአብሔርን ቀዳማዊነት የሚናገር የጸሎት ክፍል
➢ እግዚአብሔር ከዓለም በፊት እስከዘላለም ድረስ እግዚአብሔር በመንግሥቱ አለ እግዚአብሔር በሦስትነቱ አለ። እግዚአብሔር በመለኮቱ አለ።
➢ ከጎሕና ከጽባሕ በፊት ከመዓልትና ከሌሊት በፊት መላእክት ሳይፈጠሩ እግዚአብሔር በመንግሥቱ አለ።
➢ ሰማያት ሳይዘረጉ የየብስም ፊት ሳይታይ ሐመልማላት ሳይበቅሉ እግዚአብሔር በመንግሥቱ ነበረ።
➢ እግዚአብሔር ከፀሐይና ከጨረቃ ከከዋክብትም በፊት ከብርሃናትም መመላለስ በፊት እግዚአብሔር በመንግሥቱ ነበረ።
➢ እንስሳት ፣ አዕዋፋት ፣ የባሕር አራዊት ሳይፈጠሩ እግዚአብሔር በመንግሥቱ ነበረ።
➢ አዳምን በእርሱ አምሳልና አርኣያ ሳይፈጥረው ትእዛዙንም ሳያፈርስ እግዚአብሔር በመንግሥቱ ነበረ።
➢ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል ዛሬ ዘወትርም ለዘላለም።
✍️ የቀደመ በደላችንን አታስብብን
ካህኑ በሐዳፌ ነፍስ ጸሎቱ ይህንን ይጸልያል
➢ አዎን አቤቱ የሁሉ ጌታ ነህ።
አዎን አቤቱ የሁሉ አምላክ ነህ።
አዎን አቤቱ የሁሉ ንጉሥ ነህ።
አዎን አቤቱ ሁሉን የያዝህ ነህ።
አዎን አቤቱ ሁሉን የምትገዛ ነህ።
አዎን አቤቱ ሁሉን የምታድን ነህ።
አዎን አቤቱ የሁሉ መድኃኒት ነህ።
አዎን አቤቱ ሁሉን የምትጠብቅ ነህ።
አዎን አቤቱ ሁሉን የምትመግብ ነህ።
አዎን አቤቱ በእውነት የሁሉ ገዥ ነህ።
➢ ሥጋውያን የምንሆን እኛ ግን የሥጋን ሕግ እናስባለን የሥጋንም ሥራ እንሠራለን በሥጋ መንግድም እንሄዳለን። አንተ ግን የመንፈስን ሕግ አስተምረን አስተምረን የመንፈስንም ሥራ አስረዳን የመንፈስንም መንገድ ምራን።
➢ እኛን ኃጥአንን ብትምረን ያን ጊዜ መሐሪ ትባላለህና። ጻድቃንን ግን ከሥራቸው የተነሣ ትምራቸዋለህ እንደ ጼቃቸውም ትሰጣቸዋለህ።
➢ አቤቱ ይቅርታህ ፈጥኖ ይደረግልን። ወደ አንተ እንጮሃለን ወደ አንተ እናለቅሳለን ወደ አንተ እንማለላለን ለዘላለሙ። አሜን።
#ተፈጸመ_ቅዳሴ_ጎርጎርዮስ
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰማንያ_ሦስት
የጎርጎርዮስ ካልዕ ቅዳሴ
➜ ሐምሌ / 9 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
+1
እኛ የረሳነውን አርሲ ገዳዮቹ ግን አረሱትም።
ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ነው
በምሥራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ 3 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተገለጸ።
EOTCMK TV ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት አሰኮ ወረዳ ባሕሩ አሊ በተባለ ቦታ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም 2 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገልጸዋል።
በዕለቱ ከምሽቱ 5ሰዓት እስከ 6ሰዓት በተከፈተባቸው የተኩስ እሩምታ ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ለማዳን ከቦታው የሸሹ ሲሆን ወ/ሮ አልማዝ የሻነህ እና ወንድ ልጃቸው በግፍ መገደላቸውንና በአሰኮ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መቀበራቸውን ገልጸዋል።
ሐምሌ 5ም ዳኛም የለው በሚባል አካባቢ የ90 ዓመት አዛውንት በግፍ መገደላቸውን የገለጹት ምንጫችን አካባቢው አሁንም ሥጋት ውስጥ እንደሚገኝና ነዋሪዎቹም ቦታውን ለቅቀው እየሸሹ መሆናቸውን አሳውቀዋል።
የያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰማንያ_አንድ
💎 የሙታን ትንሣኤ አዋጅ
✍️ መግቢያ
ቅዱስ ያዕቆብ አባቱ የሶርያ ሊቀ ካህናት ነው ሌላ ልጀሸ የለውም። እናቱ በሦስት ዓመቱ ወደ ቤተክርስቲያን ይዛው ገባች ፤ ቍርባን በሆነ ጊዜ ከእናቱ ጭን ወርዶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ። ሊቀ ጳጳሱ ጸጋ እግዚአብሔር እንጠራው አውቆ ሦስት ጊዜ በጽዋው ደሙን ጋተው። በዚህ ጊዜ ምሥጢር ተገልጾለት ሥጋህን ደምህን የሰጠኸኝ እያለ አመሰገነ።
ከዚህ በኋላ እኔስ ሦስት ነገሮችን እፈራለሁ አለ።
1, የነፍስን ከሥጋ መለየት።
2, በእግዚአብሔር ፊት መቆም።
2, በእኔ ላይ የሚፈረደውን ፍርድ እያለ ያለቅስ ጀመር።
በዚህ ጊዜ ሕዝቡም ካህናቱም እግዚአብሔር እንጂ በዚህ ሕፃን አድሮ ዘለፈን ብለው አልቅሰዋል።
በ7 ዓመቱ ብሉይ ሐዲስ አጠና። በ12 ዓመቱ ድርሰት ይደርስ ጀመር። ከዕለታትም በአንድ ቀን አምስት ያክል ጳጳሳት መጥተው ከፊታችን ቁመህ እኛ እየሰማንህ እንግዳ ድርሰት ድረስልን አሉት።
በዚህን ጊዜ አባቶቼ ከእናንተ ፊትስ እንኳን እንግዳ ድርሰት ልደርስ ያጠናውትን ቀለምም አከናውኖ መናገር አይቻለኝም አለ። ይህንን ማለቱ ስለ ትሕትና ነው።
ከዚህ በኋላ እሱ ካለበት ቤተክርስቲያን ያለውን ሥዕለ ኪሩብ ተርጎሙ አብራርቶ አስረድቷቸዋል።
ሥሩግ በተባለች ሀገር ሊቀ ጵጵስና የተሾመው ቅዱስ ያዕቆብ ብዙ ድርሰት ደርሷል ብዙ ተግሣጽ ጽፏል። ከብዙውም አንዱ ይህ ቅዳሴው ነው።
ካህኑ :- አኰቴተ ቍርባን ዘቅዱስ ያዕቆብ ኤጲስቆጶስ ዘሥሩግ ጸሎቱ ወበረከቱ የሀሉ ምስለ ኵልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም አሜን። የሥሩግ ኤጲስቆጶስ ቅዱስ ያዕቆብ የተናገረው የቍርባን ምስጋና ይህ ነው። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✍️ በፍርሃት ተነሡ
ካህኑ :- እግዚአብሔርን በመፍራት ተነሡትሰሙ ዘንድ ጀሯችሁን ክፈቱ እግዚአብሔር ያያል ይመረምራል።
✍️ የሙታን ትንሣኤ አዋጅ
ጌታ ዓለምን ለማሳለፍ በሚመጣ ጊዜ መላእክት መለከትን ይነፋሉ ሦስት አዋጅም ይታወጃል።
➢ በመጀመሪያው አዋጅ :- በዓለም ዳርቻ ሁሉ የተበተነ የሥጋ ትቢያ በባህር በየብስ በአራዊት ሆድ ያለው ሁሉ ይሰበሰባል።
➢ በሁለተኛው አዋጅ :- አጥንቶች ከሥጋና ከደም ጋራ ይያያዛሉ ያለ መናወጽም ያለ መንቀሳቀ ፍጹም በድን ይሆናል።
➢ በሦስተኛው አዋጅ :- ሙታን እንደ ዓይን ጥቅሻ ፈጥነው ይነሣሉ። ጻድቃንና ኃጥአን በምድር ሳሉ የሠሩትን ሥራ ይዘው የነሣሉ። ጻድቃንን በቀኝ ኃጥአንን በግራ ታቆማለህ።
➢ ለጻድቃን እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና ፤ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና። ትላቸዋለህ።
➢ በግራህ ያሉትን ደግሞ እንዲህ ትላቸዋለህ። እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
#ማጠቃለያ :- የያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ዕለተ ምጽአትን የሚመለከት ቅዳሴ ስለሆነ በዕለተ ምጽአት የሚደረገውን በመላ ይጠቅሳል።
#ተፈጸመ_ቅዳሴ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰማንያ_ሁለት
የዲዮስቆርዮስ ቅዳሴ
➜ ሐምሌ / 8 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
+3
ደብረ ብርሃን ሥላሴ ጎንደር
እንኳን ለቅድስት ሥላሴ አደረሳችሁ።
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
የቄርሎስ ቅዳሴ
መጽሐፈ ቅዳሴ ማብራሪያ
#ክፍል_ሰማንያ
💎 በሰማይ እናት በምድር አባት የለውም
✍️ መግቢያ
ቅዱስ ቄርሎስ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን በጉባኤ ኤፌሶን ከሀዲ ንስጥሮስን በአፈ ጉባኤነት ተከራክሮ ረትቶታል።
ቅዱስ ቄርሎስ ብዙ ድረሰት ደርሷል ብዙ ተግሣጽ ጽፏል ከእነዚህም አንዱ ይህ ቅዳሴው ነው።
አኰቴተ ቍርባን ዘቅዱስ ቄርሎስ ጸሎቱ ወበረከቱ የሀሉ ምስለ ኵልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም አሜን። የቅዱስ ቄርሎስ የቍርባን ምስጋና ይህ ነው። ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✍️ ካህኑም ይህንን ይጸልያል
➢ ልዑል እግዚአብሔር አነዋወሩ የማይገኝ ነው።
➢ የጌታ ዙፋኑ ከሰማያት በላይ ነው። ምድርም የእግሩ መመላለሻ ነው።
➢ እሳታውያን የሚሆኑ ኪሩቤል እና ሱራፌል በየሠራዊቶቻቸው ያመሰግኑታል።
✍️ ወልድ የአብ ብቸኛ ልጁ ነው
ካህኑ በዚህ ጸሎቱ የአብ ብቸኛ ልጁ ወልድ እንደሆነ ይናገራል።
➢ አብ ሆይ ወልድ ብቸኛው ልጅህ ነው። አንተም ብቻህን በእውነት አባቱ ነህ። ከአንተ መወለዱ አይገኝም (አይመረመርም ማለት ነው)። ለአነዋወርህ ጥንት እንደሌለው ለርሱም ለልጅህ ጥንት የለውም ፍጻሜም የለውም ለዘመንህ ጥንት እንደ ሌለው።
➢ ከአንተ ከተወለደ ከልጅህ በቀር በቀኝህ የሚቀመጥ የለም በዙፋኑም ላይ እንደሱ የሚቀመጥ የለም አርአያውና አባቱ እንደሱ የሆነ ወላጁ ነው እንጂ።
ይኸውም ልጅህ ምክርህም ነው ከአንተ የተገኘ ወዳጅህ አምሳልህና መልክህ ሕሊናህና ቃልህ ጥበብህና ምክርህ ቀኝህና ክንድህ። ከእውነተኛ ባሕርይህ የተወለደ እውነተኛ አምላክ ወልድ ዋሕድ ነው።
#ማብራሪያ :- ከአንተ ከተወለደ ከልጅህ በቀር በቀኝህ የሚቀመጥ የለም ማለት በክብር የሚተካከልህ ማለት ነው። ቀኝ ማለት ክብር ማለት ነውና። "እስመ ብሂለ የማን ይመርኅ ኀበ ተዋሕዶቶሙ በክብር ፤ ቀኝ ማለት ወደ አንድነታቸው ይመራል።" እንዳለ።
✍️ ለወልድ በሰማይ እናት በምድር አባት የለውም
➢ አብ ከልጁ ጋራ ከመንፈስ ቅዱስም ጋራ ከሰዓትና ከዕለት ከአውራኅና ከዓመታት አስቀድሞ የነበረ ነው።
➢ በአነዋወር ለአንዱ ከሁለተኛው ለሁለተኛውም ከሦስተኛው መቅደም የለም።
➢ አብ ልጁን ዓለም ሳይፈጠር የወለደው በሥራ ሊረዳው አይደለም። የመንፈስ ቅዱስም ባሕርይ የተገኘ ብልሀትና ሥራ ለማወጣጣት አይደለም።
➢ ከእግዚአብሔር አብ ብቻ መወለዱን እንናገር ያን ጊዜ እናት አልነበረችውም። ዳግመኛም ምድራዊ አባት ሳይኖረው የአምላክ ልጅ ብቻውን ከዳዊት ልጅ ከድንግል ብቻ መወለዱን እንናገር እናውራ።
➢ በዘር ለመወለድ አባት ስላልነበረው የሰውነት ሥራ አልጎደለበትም ከብቸኛዋ ሴት ብቻ ፈጽሞ ሰው ሆነ እንጂ።
#ማብራሪያ :- የሰውነት ሥራ አልጎደለበትም ማለት ለሰው የተሰጠው አካል ዘየአክልን ገንዘብ አደረገ ማለት ነው።
➢ ከአዳም ጎን አጥንት በተፈጠረች ጊዜ እናት ስላልነበረቻት ሔዋን የሴቶች ባሕርይ እንዳልጎደለባት። አዳምም የጎኑ አጥንት ስለ ተነቀለ ከቀደመው የሥጋው ፍጥረት እንዳልጎደለበት እንደዚሁ የአዳምን አባት በሥጋ በወለደችው ጊዜ የማርያም ማኅተመ ድንግልናዋ አልጎደለም።
➢ አዳምን የጎኑ አጥንት በተነቀለ ጊዜ እንዳላሳመመው እንደዚሁ የገሊላ ወገን የምትሆን የአምላክን እናት ሕማመ ወሊድ አላገኛትም።
#ተፈጸመ_ቅዳሴ_ቄርሎስ
➢➢ የቀጣይ ትምህርት
#ክፍል_ሰማንያ_አንድ
የያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ
➜ ሐምሌ / 6 / 2018 ዓ.ም
© ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
