🔹قَناةُ أبي جُلَيبيب الأثري
Open in Telegram
789
Subscribers
+224 hours
+697 days
+12230 days
Posts Archive
النجاة والمصلحة والخيرات في الكلام بعلم ، والسكوت بحلم ، ورد كل أمر إلى أهله ، فليس السكوت دائما محمودا ، فقد يكون في السكوت انتشار الباطل أو إظهاره أو غش العامة أو التدليس عليهم فيكون الكلام محمودا ولكن بعلم , وقد يكون في الكلام تقوية للفتنة أو نشر لها ، أو نشر لما لا يحصل به صلاح ولا يدفع به فساد ، ونحو ذلك فيكون السكوت محمودا ولكن بحلم ، فلو لم يتكلم إلا عالم حيث يحسن الكلام أو يجب ، وسكت من لم يعلم بحلم ، وعَرف فضل من علم وتكلم بعلم ، ورُدَّ كل أمر إلى أهله ، وأمسك كل إنسان عن الخوض فيما لايعنيه أو فيما لم يحط بعلمه ، لظهر الصلاح في البر والبحر ، وقل الشر واندحر ، وانطفأت الفتن ، وكثر الخير ، واستراح الناس ، وصلحت الأحوال .
✍الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله ورعاه
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
وَقَدْ ذَكَرَ اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ فِي غَيْرِ مَوْضِعٍ مِنْ كِتَابهِ اليَدَ وَالسَّمْعَ وَالبَصَرَ، فَتَأَوَّلَتِ الجَهْمِيَّةُ هَذِهِ الآيَاتِ فَفَسَّرُوهَا عَلَى غَيْرِ مَا فَسَّرَ أَهْلُ العِلْمِ، وَقَالُوا: إِنَّ اللَّهَ لَمْ يَخْلُقْ آدَمَ بِيَدِهِ، وَقَالُوا: إِنَّ مَعْنَى اليَدِ هَاهُنَا القُوَّةُ.
وقَالَ إِسْحَاقُ بْنُ إِبْرَاهِيمَ: إِنَّمَا يَكُونُ التَّشْبِيهُ إِذَا قَالَ: يَدٌ كَيَدٍ، أَوْ مِثْلُ يَدٍ، أَوْ سَمْعٌ كَسَمْعٍ، أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ، فَإِذَا قَالَ: سَمْعٌ كَسَمْعٍ، أَوْ مِثْلُ سَمْعٍ، فَهَذَا التَّشْبِيهُ. وَأَمَّا إِذَا قَالَ كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى يَدٌ، وَسَمْعٌ، وَبَصَرٌ، وَلَا يَقُولُ كَيْفَ، وَلَا يَقُولُ مِثْلُ سَمْعٍ، وَلَا كَسَمْعٍ، فَهَذَا لَا يَكُونُ تَشْبِيهًا، وَهُوَ كَمَا قَالَ اللَّهُ تَعَالَى فِي كِتَابهِ: {لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ وَهُوَ السَّمِيعُ البَصِيرُ}
“በርግጥም አላህ - ዐዘ ወጀል- በቁርኣኑ ብዙ ቦታዎች ላይ እጁን፣ መስማትና ማየቱን ጠቅሷል። ጀህሚያዎች ግን እነዚህን አንቀፆች ቆልምመው (‘ተእዊል’ አድርገው) ዑለማዎች ባልፈሰሩት መልኩ ፈሰሯቸው። ‘አላህ ኣደምን በእጁ አልፈጠረም’ አሉ። ‘እዚህ ላይ የእጅ ትርጓሜ ሃይል (ቁዋ) ነው’ አሉ።
ኢስሓቅ ብኑ ኢብራሂም እንዲህ ብለዋል፦ ‘ማመሳሰል የሚሆነው ‘እጁ እንደ እጄ ወይም የእጅ አምሳያ ነው፤ መስሚያው እንደ መስሚያዬ ወይም የመስሚያ አምሳያ ነው’ ሲል ነው። ‘መስሚያው እንደ (ፍጡር) መስሚያ ወይም አምሳያ ነው’ ካለ፣ ይሄ ነው ማመሳሰል። ያለ አኳኋን (ከይፍያ)፣ ያለ አምሳያ አላህ እንዳለው ብቻ ‘እጅ’፣ ‘መስሚያ’፣ ‘መመልከቻ’ አልለው’ ካለ ግን ይሄ ማመሳሰል አይሆንም። ይህም ከፍ ያለው አላህ በቁርኣኑ እንዲህ እንዳለው ነው፦ {የሚመስለው ምንም ነገር የለም። እርሱ ሁሉን ሰሚና ሁሉን ተመልካች ነው።}” [ሱነኑ ቲርሚዚይ፡ ሐዲሥ ቁ. 662]
እውነታው በዚህ ልክ እንደ ፀሐይ ፍንትው ብሎ ሳለ የሚጨናበሱ ሰዎች መኖራቸው የቢድዐ ዳፍንት ምን ያክል ከባድ እንደሆነ ነው የሚያሳየው። “አሽዐሪዮች እና ወራሾቻቸው አሕ-ባሾችስ ለአቋማቸው ማጠናከሪያ ምን ይጠቅሳሉ?” ካላችሁ “እጅ የለውም” የሚል ቀጥተኛ ማስረጃ ከቁርኣንም፣ ከሐዲሥም፣ ከሰለፎች ንግግርም አንዲትም መረጃ መቼም አያመጡም። ሐቅ ፈላጊ ሆናችሁ በነሱ ማምታቻ የተሸወዳችሁ ሁሉ! “እጅ የለውም” የሚል ቀጥተኛ ማስረጃ አምጡ ብላችሁ አፋጧቸው። የራሳቸውን ከንቱ ትንታኔ እንጂ አንድም አያቀርቡላችሁም። ይልቁንም የሚጠቅሱት እንዲሁ ማምታቻ ነው።
[ማምታቻ አንድ]፡-
“የሚመስለው የለም” የሚለውንና መሰል አንቀፆችን በመጥቀስ ከሶሐቦች ያልተገኘ የራሳቸውን ትርጉም መስጠት። “ምን አገናኘው?” ካላችሁ እነሱ ዘንድ “እጅ አለው” ማለት በፍጡር ማመሳሰል ነው። በቃ! “እንዲያ ከሆነ ቁርኣኑ የማመሳሰልና የሺርክ ሰነድ ነው ማለት ነው” ብትሏቸው ምንም ሳያፍሩ “አዎ ዟሂሩ ኩ^ f ^ር ነው” ይላሉ። እንዲያ ከሆነ የመጀመሪያ አመሳሳዮች አላህና መልእክተኛው ናቸው ማለት ነው! አዑዙ ቢላህ! ሐቂቃው ግን አላህን እራሱን በገለፀበት፣ ነብዩም ﷺ አላህን በገለፁበት መግለፅ ፈፅሞ ማመሳሰል አለመሆኑ ነው። የቡኻሪ ሸይኽ የሆኑት ኑዐይም ብኑ ሐማድ አልኹዛዒይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡-
مَنْ شَبَّهَ اللَّهَ بِشَيْءٍ مِنْ خَلْقِهِ فَقَدْ كَفَ-رَ وَمَنْ أَنْكَرَ مَا وَصَفَ اللَّهُ بِهِ نَفْسَهُ فَقَدْ كَفَ-رَ فَلَيْسَ مَا وَصَفَ اللَّهُ بِهِ نَفْسَهُ وَرَسُولُهُ تَشْبِيهٌ
“አላህን ከፍጡሩ በየትኛውም ያመሳሰለ በርግጥም ከኢስላም ወጥቷል። አላህ እራሱን የገለፀበትን የካደም ከኢስላም ወጥቷል። አላህ እራሱን የገለፀበት እና መልእክተኛው (እሱን የገለፁበት) ማመሳሰል አደለም።” [ላለካኢይ፡ ቁ. 936]
ይሄ የኑዐይም ንግግር በአላህ መገለጫዎች ዙሪያ ቁልፍ የሆነ ቀመር ነው። ከውስጡ ሶስት ወሳኝ ህጎችን እናገኝበታለን። እነሱም፡-
1ኛ፡- አላህን በፍጡር ማመሳሰል ክህ -ደት ስለሆነ መጠንቀቅ እንደሚገባ፣
2ኛ፡- አላህ እራሱን የገለፀበትን ማስተባበል ክህ^ደት እንደሆነ፣
3ኛ፡- በቁርኣንና በሐዲሥ ውስጥ ፈፅሞ ማመሳሰል የሚባል ነገር እንደሌለ። (በርካታ አሽዐሪዮች ግን ቁርኣንና ሐዲሥ በማመሳሰል የታጨቀ ነው ብለው ነው የሚያምኑት።)
[ማምታቻ ሁለት]፡-
ሌላኛው የሚጠቅሱት “ማስረጃቸው” በታዋቂ ዑለማዎች ማስፈራራት ነው። ቁርኣንና ሐዲሥ ስትጠቅሱላቸው እነሱ “ነወዊይ፣ ኢብኑ ሐጀር፣…” ይላሉ። ከቁርኣንና ሐዲሥ በተቃራኒ ፍፁም ያልሆኑ ሰዎችን ማጣቀስ ነውር ነው። “እናንተ ቁርኣኑንና ሐዲሡን ከነሱ በላይ ልታውቁት ነወይ?” ይላሉ። መልካም! እነሱስ ቁርኣኑንና ሐዲሡን ከሰለፎች በላይ ሊያውቁት ነውን? እስኪ የሰለፎቹን ተፍሲር መርምሩና አደብ ይኑራችሁ።
የአሕ-ባሽ አቋም ሌላው ቀርቶ “እንከተላቸዋለን” ከሚሏቸው የአቡል ሐሰን አልአሽዐሪ አቋም ጋር እንኳን አይገጥምም፡፡ አቡል ሐሰን የአህሉ ሱና፞ን ዐቂዳ ሲዘረዝሩ እንዲህ ብለዋል፡-
وأن الله سبحانه على عرشه كما قال: الرحمن على العرش استوى وأن له يدين بلا كيف كما قال: خلقت بيدي وكما قال: بل يداه مبسوطتان
“የጠራው አላህ ‘አረ፞ሕማን በዐርሹ ላይ ከፍ አለ’ እንዳለው በዐርሹ ላይ ነው። ሁለት እጆች እንዳሉትም እንዲሁ ያለ አኳኋን መስጠት (ያፀድቃሉ)። ‘በሁለት እጆቼ ፈጠርኩ’ እንዳለው፤ ‘ይልቁንም ሁለት እጆቹ የተዘረጉ ናቸው’ እንዳለውም (እንዲሁ ያፀድቃሉ)።” [መቃላቱል ኢስላሚዪ፞ን፡ 290]
ከዚያም የአህሉ ሱና፞ን አቋም በሰፊው ከዘረዘሩ በኋላ “እነዚህ ባጠቃላይ (የሱና፞ ሰዎች) የሚያዝዙባቸው፣ የሚተገብሯቸውና የሚያምኑባቸው ናቸው። በዘረዘረነው አቋማቸው ሁሉ እናምናለን። እንጓዝበታለንም” ብለው ቋጭተዋል። [መቃላት፡ 297]
ሲጠቃለል "አላህ እጅ አለው" ማለት ፈጣሪን በፍጡር ማመሳሰል ነው የሚል አካል ነብዩም ﷺ በሐዲሣቸው፣ ሰለፎቹም፣ ኢማማችን የሚሏቸው አቡል ሐሰን አልአሽዐሪም አመሳሳይ ሙጀሲማ ናቸው እያለ ነው። ቁርኣን ራሱ ዟሂሩ ተጅሲም የሆነ መልእክት ስለያዘ አሳሳች ነው እያሉ ነው። ሙግታቸው ከኛ ጋር ሳይሆን ከአላህ፣ ከነብዩ ﷺ፣ ከሰለፎቹ እና ኢማማችን ከሚሏቸው አቡል ሐሰን አልአሽዐሪ ጋር ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ህዳር፡ 12/2012)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
እውን አላህ እጅ የለውም?
~
ህሊና ላለው ሰው “አላህ እጅ የለውም” የሚል እምነት አስቀያሚና እጅጉን የሚያሳፍር ነው። ግና አእምሯቸው በእምነት የለሾች ፍልስፍና በመበከሉ የተነሳ ይህንን አጉል እምነት ተውሒድ ያደረጉ፣ ይባስ ብሎም ጥፋታቸውን የማይጋራቸውን በሙሽ^ ሪክነት የሚወነጅሉ አንጃዎች ተፈልፍለዋል። በዘመናችን ይህንን ብልሹ አመለካከት ከሚያራምዱ አንጃዎች ውስጥ “አሕ-ባሽ” ፊታውራሪ ነው። ይህ የአሕ-ባሽ አመለካከት ከሙዕተዚላ የተኮረጀ እምነት ነው። ለዚህም ሁለት አይነት መረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል።
1ኛ፡- የሙዕተዚላዎችን ስራዎች። ለምሳሌ የቃዲ ዐብዱልጀባር አልሙዕተዚሊን ስራዎች። [ሸርሑ ኡሱሊል ኸምሳ፡ 228] [ሙተሻቢሁል ቁርኣን፡ 231]
2ኛ፡- አሕ-ባሾች እንከተላቸዋለን የሚሏቸው ኢማሞች ምስክርነት። ለምሳሌ አቡል ሐሰን አልአሽዐሪና አቡ መንሱር አልበግዳዲይ ይህ እምነት የሙዕተዚላ ዐቂዳ እንደሆነ መስክረዋል። [መቃላቱል ኢስላሚዪ፞ን፡ 157፣ 167] [ኡሱሉዲን፡ 228]
ስለ ራሱም ይሁን ስለሌሎች ከማንም በላይ አዋቂ የሆነው ጌታ ግን እጅ እንዳለው በግልፅ ቋንቋ ተናግሯል። መልእክተኛውም ﷺ እንዲሁ። ጥቂት ማስረጃዎችን እንመልከት፡-
#ማስረጃ_አንድ፦
(قَالَ یَـٰۤإِبۡلِیسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسۡجُدَ لِمَا خَلَقۡتُ بِیَدَیَّۖ )
{ኢብሊስ ሆይ! በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት ከመስገድ ምን ከለከለህ?} [ሷድ፡ 75]
ከዚች አንቀፅ አባታችን ኣደም በአላህ እጆች የተፈጠሩ ክቡር ፍጡር እንደሆኑ ማንም ይርረዳል፡፡ አሕ -ባሽ ሲቀር። እነሱ ግን “እጅ”/ “የድ” የሚለውን “ችሎታ፣ ፀጋ ማለት ነው” ይላሉ።
- ለችሎታማ ሁሉም የተፈጠረው በአላህ ችሎታ ነው። ኣደምን በልዩ ሁኔታ አክብሮ እንደፈጠራቸው ሲናገርኮ ነው “በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት” ያለው። የ“እጅ” ትርጓሜው “ችሎታ” ቢሆን ኖሮ ኣደም ከኢብሊስ ልዩነት ባልነበራቸው ነበር። ኢብሊስም በአላህ ችሎታ የተፈጠረ ነውና።
- እጅ ማለት ችሎታ ቢሆን ኖሮ {በሁለት እጆቼ ለፈጠርኩት} ሲለው ኢብሊስ “እኔስ በችሎታህ አይደል የተፈጠርኩት?” ይል ነበር። ግን አላለም። ይህም በዚህ ነጥብ ላይ ኢብሊስ ከነዚህ ሰዎች የተሻለ እምነትና መገንዘብ እንዳለው ያሳየናል። አዎ የጥፋት ቁንጮው ኢብሊስ በአላህ እጆች አልካደም። “የለም! በእጆችህ አልፈጠርከውም። ሲጀመር አንተ እጅ የት አለህና?!” አላለም! “ከኛ ወዲያ ተውሒድ አዋቂ ላሳር” የሚሉ አሕ -ባሾች ግን “አላህ እጅ የለውም” ሲሉ ኢብሊስ እንኳን ያልደፈረውን ጥፋት እየፈፀሙ ነው ያሉት።
#ማስረጃ_ሁለት፡-
(وَقَالَتِ ٱلۡیَهُودُ یَدُ ٱللَّهِ مَغۡلُولَةٌۚ غُلَّتۡ أَیۡدِیهِمۡ وَلُعِنُوا۟ بِمَا قَالُوا۟ۘ بَلۡ یَدَاهُ مَبۡسُوطَتَانِ یُنفِقُ كَیۡفَ یَشَاۤءُۚ)
{የሁ^ዶችም “የአላህ እጅ የተጠፈረች ናት” አሉ። እጆቻቸው ይጠፈሩ! ይልቅ ሁለቱም እጆቹ የተዘረጉ ናቸው። እንደሚሻ ይለግሳል፡፡} [ማኢዳህ፡ 64]
አስተውሉ! የሁ^ዶቹ የተረ-ገሙት “የአላህ እጅ የተጠፈረች ናት” በማለታቸው እንጂ ከነ ጭራሹ “አላህ እጅ የለውም” ብለው አይደለም። አሕ-ባሾችስ? የሁዶች እንኳን ያልተዳፈሩትን በመዳፈር ጭራሽ ለአላህ እጅ መኖሩን አስተባብለዋል። በዚህ ነጥብ ላይ ጥፋታቸው ከየሁ/ዶቹ የከፋ ነው።
#ማስረጃ_ሶስት፡-
ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
يُجْمَعُ المُؤْمِنُونَ يَوْمَ القِيَامَةِ فَيَقُولُونَ: لَوِ اسْتَشْفَعْنَا إِلَى رَبِّنَا فَيُرِيحُنَا مِنْ مَكَانِنَا هَذَا، فَيَأْتُونَ آدَمَ فَيَقُولُونَ لَهُ: أَنْتَ آدَمُ أَبُو البَشَرِ، خَلَقَكَ اللَّهُ بِيَدِهِ، وَأَسْجَدَ لَكَ المَلاَئِكَةَ، وَعَلَّمَكَ أَسْمَاءَ كُلِّ شَيْءٍ فَاشْفَعْ لَنَا إِلَى رَبِّنَا حَتَّى يُرِيحَنَا
{በቂያማ ቀን አማኞች ይሰበሰቡና ‘ወደ ጌታችን አማላጅ ብንልክና ከዚህ ቦታችን ቢያሳርፈን’ ይላሉ። ከዚያም ኣደም ዘንድ ይመጡና፡ ‘አንተ የሰው ዘር ሁሉ አባት የሆንከው ኣደም ነህ። አላህ #በእጁ ፈጥሮሃል። መላእክትን አሰግዶልሃል። የሁሉን ነገር ስሞችም አስተምሮሃል። ያሳርፈን ዘንድ ጌታችን ዘንድ አማልደን’ ይላሉ። … } [አልቡኻሪይ፡ 7516]
#ማስረጃ_አራት፡-
ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
يَأْخُذُ اللهُ عَزَّ وَجَلَّ سَمَاوَاتِهِ وَأَرَضِيهِ بِيَدَيْهِ، فَيَقُولُ: أَنَا اللهُ - وَيَقْبِضُ أَصَابِعَهُ وَيَبْسُطُهَا - أَنَا الْمَلِكُ " …
{አላህ - ዐዘ ወጀል - ሰማያቱንና ምድሮቹን #በሁለት_እጆቹ ይይዝና ‘እኔ ነኝ አላህ!’ - ጣቶቻቸውን እየጨበጡና እየዘረጉ - ‘እኔ ነኝ ንጉሱ’ ይላል።} … [ሙስሊም፡ 2788]
#ማስረጃ_አምስት:- የሰለፎች_አቋም
ለማሳጠር ስል ከሰለፎች ንግግር ውስጥ ቀንጨብ ብቻ ላድርግ። አልኢማም አቲርሚዚይ (279 ሂ.) ረሒመሁላህ {አላህ ሶደቃን ተቀብሎ በቀኙ ይይዛታል…} የሚለውን ሐዲሥ “ሐሰኑን ሶሒሕ” በማለት ደረጃውን ከገለፁ በኋላ እንዲህ ብለዋል፦
وَقَدْ قَالَ غَيْرُ وَاحِدٍ مِنْ أَهْلِ العِلْمِ فِي هَذَا الحَدِيثِ وَمَا يُشْبِهُ هَذَا مِنَ الرِّوَايَاتِ مِنَ الصِّفَاتِ: وَنُزُولِ الرَّبِّ تَبَارَكَ وَتَعَالَى كُلَّ لَيْلَةٍ إِلَى السَّمَاءِ الدُّنْيَا، قَالُوا: قَدْ تَثْبُتُ الرِّوَايَاتُ فِي هَذَا وَيُؤْمَنُ بِهَا وَلَا يُتَوَهَّمُ وَلَا يُقَالُ: كَيْفَ؟ هَكَذَا رُوِيَ عَنْ مَالِكٍ، وَسُفْيَانَ بْنِ عُيَيْنَةَ، وَعَبْدِ اللهِ بْنِ الْمُبَارَكِ أَنَّهُمْ قَالُوا فِي هَذِهِ الأَحَادِيثِ: أَمِرُّوهَا بِلَا كَيْفٍ، وَهَكَذَا قَوْلُ أَهْلِ العِلْمِ مِنْ أَهْلِ السُّنَّةِ وَالجَمَاعَةِ، وَأَمَّا الجَهْمِيَّةُ فَأَنْكَرَتْ هَذِهِ الرِّوَايَاتِ وَقَالُوا: هَذَا تَشْبِيهٌ.
“በርካታ የእውቀት ባለቤቶች በዚህና መሰል የአላህን መገለጫዎችና የጌታችንን -ተባረከ ወተዓላ - በየሌሊቱ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ መውረድ በሚጠቁሙ ሐዲሦች ላይ ‘ዘገባዎቹን በዚህ ላይ ማፅደቅ ይገባል፣ ይታመንባቸዋል እንጂ ግመታ (ወህም) ውስጥ አይገባም፤ እንዴት አይባልም’ ብለዋል። ከማሊክ፣ ከሱፍያን ብን ዑየይናና ከዐብዲላህ ብኒል ሙባረክ፣ ... በዚሁ መልኩ የተዘገበ ሲሆን በነዚህ ሐዲሦች ላይ ‘ያለ እንዴት አሳልፏቸው’ ብለዋል። ከአህለ ሱና ወልጀማዐ የሆኑ የሌሎች የእውቀት ባለቤቶች አቋምም እንዲሁ ነው። ጀህሚያዎች ግን እነዚህን ዘገባዎች የተቃወሙ ሲሆን ‘ይሄ ማመሳሰል ነው’ ብለዋል።
❁⁞ - قيام الليل "ميزان" الدين - ⁞❁⁞
- به تعرف قدر محبتك لله، وقيامك من أجله.
- به تعرف مبلغ خشوعك وتضرعك بين يدي الله.
- به تعرف معنى "حلاوة الإيمان" و"لذة العبادة"
- به تعرف "جمال المناجاة" و"سكينة الدعاء"
- به تعرف "الافتقار إلى الله" و"الوقوف بين يدي الملك"
- قيام الليل "ميزان" الذين "يعلمون" حقاً وصدقاً والذين "لا يعلمون"
من عظُمَ انكسارُهُ لله، أدناهُ ربُّه من مقامِ رضاه، وقد يُبتلى العبدُ فيجدُ مرارةَ الألم؛ ليُذيقَهُ اللهُ من الإيمانِ حلاوةَ الطَّعم.
٩ صفر ١٤٤٨
📝 الشيخ صالح العصيمي
🎬 የ ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ዐብዲል ወሓብ«ዑዝር ቢል ጀህል» በግልፅ የሚሰጡባቸው ንግግሮች ስብስብ ።
ከዚህ በታች ያሉትን ክፍሎች በመጫን ቀጥታ ቪዲዮዎቹን መመልከት ትችላላችሁ፦
📌 ▶️ ክፍል 1 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 2 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 3 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 4 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 5 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 6 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 7 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 8 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 9 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 10 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 11 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
📌 ▶️ ክፍል 12 - ቪዲዮውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
