en
Feedback
EAA/Ethiopian Agricultural Authority/

EAA/Ethiopian Agricultural Authority/

Open in Telegram
1 497
Subscribers
+224 hours
-17 days
+2830 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን በሸገር ከተማ ለሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ አዲስ አበባ- ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን  በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ፣ ደንበል ጣፎ ወረዳ፣ ወበሪ ቁጥር 1 ቡኡራ ቦሩ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚማሩ ተማሪዎች የማስጀመሪያ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። ​ይህ ድጋፍ በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆችና ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን ያለ ስጋት እንዲጀምሩና በትምህርታቸው ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። ​ ​በስነ-ስርዓቱ ላይ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መሰሉ ዋጋው እንደገለጹት፤ ግብርናን ማዘመን የሚቻለው በትምህርት የበለጸገ ትውልድ ሲፈጠር በመሆኑ፣ ተቋሙ ከሙያዊ ስራው ጎን ለጎን የነገ ሀገር ተረካቢ ህጻናትን መደገፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ​የትምህርት ቤቱ አስተዳደር ወ/ሮ ነጢ ኢቲቻ በበኩላቸው የተደረገውን በጎ አድራጎት አድንቀው፣ ለተደረገው ድጋፍ ሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዘጋቢ:- ብርቱካን አዲሱ ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል  መረጃዎችን ያግኙ   ➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et ➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk ➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (I
+2
በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል። ‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል። ‎ ‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው። ‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።

ከማኑዋል ወደ ዲጂታል፤ ከጊዜና ወጪ ብክነት ወደ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተጠያቂ አገልግሎት! ********************************************************** (አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27/2018 የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን) የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር ላይ ሲሆን፣ አገልግሎቶቹን በዲጂታል መድረኮች ማለትም እንደ eService እና Single Window እንዲሁም በራሱ ባለማቸው ኦንላይን ፕላትፎርሞች በማቅረብ የዜጎችን እና የንግድ ተቋማትን አገልግሎት ለማሻሻል ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ባለሥልጣኑ በአጠቃላይ 462 የተለዩ አገልግሎቶች ካሉት ውስጥ 259 አገልግሎቶችን ዲጂታል አድርጓል። ከእነዚህም 130 በeService እና 26 በESW፣ በአጠቃላይ 156 አገልግሎቶች በቀጥታ ኦንላይን እየተሰጡ ሲሆን፣ 68 አገልግሎቶች ወደ መሶብ ማዕከል ገብተዋል። 19 አገልግሎቶችን ወደ ዪኒፋይድ መሶብ ለማስገባት ተለይተዋል፡፡ ይህ ሽግግር ተገልጋዮች ከማንኛውም ቦታ ሆነው በኢንተርኔት ማመልከት፣ የአገልግሎታቸውን ሂደት መከታተል እና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማግኘት እንዲችሉ አስችሏል። በተጨማሪም የዲጂታል አሰራሩ የአመልካቾችን አካላዊ ተገኝቶ መገልገልና የወረቀት ወጪን በመቀነስ ጊዜና ወጪ ለመቆጠብ አስችሏል፤ እያንዳንዱ የማመልከቻ ደረጃ በሲስተሙ መመዝገቡም ግልጽነትና ተጠያቂነትን አጠናክሯል። ከዚህ ባለፈ፣ የኢ-ፋይቶ (e-Phyto) ስርዓት ከዓለም አቀፉ IPPC Hub ጋር በመቀናጀቱ ባለሥልጣኑ ከ186 አገሮች ጋር የኤሌክትሮኒክ ፋይቶሳኒተሪ ሰርተፍኬት ልውውጥ ማድረግ ችሏል። በመንበረ ሀይሉ ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ ➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et ➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk ➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234

ከማኑዋል ወደ ዲጂታል፤ ከጊዜና ወጪ ብክነት ወደ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተጠያቂ አገልግሎት! ********************************************************** (አዲስ አበባ፣ ነ
ከማኑዋል ወደ ዲጂታል፤ ከጊዜና ወጪ ብክነት ወደ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተጠያቂ አገልግሎት! ********************************************************** (አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27/2018 የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን) የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር ላይ ሲሆን፣ አገልግሎቶቹን በዲጂታል መድረኮች ማለትም እንደ eService እና Single Window እንዲሁም በራሱ ባለማቸው ኦንላይን ፕላትፎርሞች በማቅረብ የዜጎችን እና የንግድ ተቋማትን አገልግሎት ለማሻሻል ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ባለሥልጣኑ በአጠቃላይ 462 የተለዩ አገልግሎቶች ካሉት ውስጥ 259 አገልግሎቶችን ዲጂታል አድርጓል። ከእነዚህም 130 በeService እና 26 በESW፣ በአጠቃላይ 156 አገልግሎቶች በቀጥታ ኦንላይን እየተሰጡ ሲሆን፣ 68 አገልግሎቶች ወደ መሶብ ማዕከል ገብተዋል። 19 አገልግሎቶችን ወደ ዪኒፋይድ መሶብ ለማስገባት ተለይተዋል፡፡ ይህ ሽግግር ተገልጋዮች ከማንኛውም ቦታ ሆነው በኢንተርኔት ማመልከት፣ የአገልግሎታቸውን ሂደት መከታተል እና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማግኘት እንዲችሉ አስችሏል። በተጨማሪም የዲጂታል አሰራሩ የአመልካቾችን አካላዊ ተገኝቶ መገልገልና የወረቀት ወጪን በመቀነስ ጊዜና ወጪ ለመቆጠብ አስችሏል፤ እያንዳንዱ የማመልከቻ ደረጃ በሲስተሙ መመዝገቡም ግልጽነትና ተጠያቂነትን አጠናክሯል። ከዚህ ባለፈ፣ የኢ-ፋይቶ (e-Phyto) ስርዓት ከዓለም አቀፉ IPPC Hub ጋር በመቀናጀቱ ባለሥልጣኑ ከ186 አገሮች ጋር የኤሌክትሮኒክ ፋይቶሳኒተሪ ሰርተፍኬት ልውውጥ ማድረግ ችሏል። በመንበረ ሀይሉ ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ

የባለሥልጣኑ የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተሞክሮ ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆኑ ተገለጸ:: አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26/2018 (የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን) — የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን አመራሮች የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥና የዲጂታል ሽግግር ተሞክሮ በመጎብኘት ልምድ ተለዋውጠዋል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ድሪባ ኩማ፣ ዲጂታል ሽግግሩ የሥራ ሂደቶችን ለማቀላጠፍ፣ የአገልግሎት ፈላጊዎችን ጊዜና ወጪ ለመቀነስ፣ ብልሹ አሠራርን ለማስቀረት፣ ግልጽነትንና የአገልግሎት ጥራትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ባለሥልጣኑ በአሁኑ ወቅት 259 አገልግሎቶችን ዲጂታል ማድረጉን፣ 156 አገልግሎቶችን በኦንላይን እየሰጠ መሆኑን እና 68 አገልግሎቶችን በመሶብ አንድ ማዕከል እየሰጠ መሆኑን አብራርተዋል ። የውስጥ አገልግሎቶችን ዲጂታል ማድረግ የሥራ ሂደቶችን ከማቀላጠፍ ባለፈ ተቋሙ በዘመናዊ አሠራር እንዲመራ፣ ግልጽነትን እንዲያሳድግና ተወዳዳሪነቱን እንዲያጎለብት እያገዘ መሆኑንም ጠቁመዋል። ባለሥልጣኑ አገልግሎቶቹን ከወረቀት አሠራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር ያጋጠሙ በርካታ ተግዳሮቶችን በመቋቋም ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ለዚህ ውጤት ማብቃት መቻሉን አብራርተዋል ። የህብረት ሥራ ኮሚሽነር ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፣ የግብርና ባለሥልጣኑ በአጭር ጊዜ ያከናወነው የዲጂታል ሽግግር ሥራ አበረታችና አርአያነት ያለው መሆኑን ገልጸው፣ ሌሎች የመንግሥት ተቋማትም ከተሞክሮው ሊማሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ጉብኝቱ በተቋማት መካከል የዲጂታል ልምድ ልውውጥን በማጠናከር፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎትን በማስፋፋት እና ቀልጣፋ፣ ግልጽና ዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎትን ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል:: በመንበረ ሀይሉ

የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ሰራተኞች ደም በመለገስ ሰብአዊ አለኝታነታቸውን አረጋገጡ ++++++++++++++++++++++++++++++++++ አዲስ አበባ — ነሀሴ 26/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች «ደም ይለግሱ ህይዎት ያድኑ» በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የደም ልገሳ መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ ደም በመለገስ አርአያነታቸውን አሳይተዋል። በባለስልጣኑ የሴቶች ጉዳይ ማህበራዊ አካቶ ትግብራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ትግስት ወ/አገኘሁ እንደተናገሩት ሰራተኞች ደም መለገስ  የህይወት አዳኝነቱንና አስፈላጊነቱ በመገንዘብ በየዓመቱ የሚያካሂዱትን ይህን መልካም ተግባር ዘንድሮም በተጠናከረ መልኩ የፈፀሙ ሲሆን፣ በርካታ ሰራተኞች በበጎ ፈቃደኝነት ተሳትፈዋል ብለዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት ሰራተኞች እንደገለፁት፣ ደም መለገስ የሰዎችን ህይወት ከመታደግ ባሻገር የህሊና እርካታን የሚያስገኝ ከፍተኛ ሰብአዊ ተግባር በመሆኑ ይህንን በጎ ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ዘጋቢ:- ብርቱካን አዲሱ ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል  መረጃዎችን ያግኙ   ➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et ➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk ➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234

ጥራት ያለው የስንዴ ዘር ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ነው አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22/2018 (የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ) የአየር ንብረት የሚቋቋም የስንዴ እሴት ሰንሰለት ልማት ፕሮጀክት የዘር ቤተ-ሙከራ መሳሪያዎች ለኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን እና ፕሮጀክቱ ከሚተገበርባቸው ክልሎች ውስጥ ለአማራ፣ ኦሮሚያና አፋር ለ12 ቤተ-ሙከራዎች የሚሆኑ ቁሳቁሶች ርክክብ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ ለቀሪ ክልሎች የሚሰጥ ይሆናል። የአየር ንብረት የሚቋቋም የስንዴ እሴት ሰንሰለት ልማት ፕሮጀክት ብሔራዊ አስተባባሪ አብዱልሰመድ አብዶ ከኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ጋር የስንዴ ዘር ጥራትን ለማሻሻል በርካታ ሥራዎችን እያከናወንን ነው ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት ርክክብ የተደረገባቸው የቤተ-ሙከራ መሳሪያዎች በክልሎች በስንዴ ጥራትና ፍተሻ ላይ ለሚሰሩት ስራዎች አጋዥ እንደሚሆኑ ጠቅሰው ርክክብ በተደረገባቸው እቃዎች ውስጥ አጉሊ ምንጽሮች (microscope)፣ ናሙና መውሰጃ መሳሪያዎች፣ መመዘኛና የእርጥበት መፈተሻ እንዲሁም ሎሎች መካተታቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም የመሳሪያዎቹ አጠቃላይ ወጪ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነም በርክክብ ወቅት ተጠቅሷል፡፡ በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የዕፅዋት ዝርያና ዘር ሬጉላቶሪ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍሰሃ ተሾመ በበኩላቸው የአየር ንብረት የሚቋቋም የስንዴ እሴት ሰንሰለት ልማት ፕሮጀክት ከስንዴ ጋር የተያያዙ ስራዎችን ለመስራት በሚያስችል ሁኔታ ለባለስልጣኑ እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዛሬው እለት ለባለስልጣኑ እና ለክልሎች የተበረከቱት የቤተ ሙከራ መሳሪያዎች በዘር ጥራትና ፈተሻ ላይ ለሚሰራው ስራ ትልቅ አስተዋጾአ ያበረክታሉ ብለዋል፡፡ #ዘገባውን ያደረሰን MOA ነው ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ ➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et ➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk ➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234