1 497
Subscribers
+224 hours
-17 days
+2830 days
Posts Archive
ባለስልጣኑ ጳጉሜን 4 የኅብር ቀንን በድምቀት አከበረ
**************************************************************
(አዲስ አበባ፡ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም) — የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ጳጉሜን 4 ታስቦ የዋለውን የኅብር ቀን አመራሩና ሠራተኞቹ በተገኙበት በድምቀት አከበረ።
ባለስልጣኑ ብዝኃነትን እንደ ጸጋና የጋራ ዐቅም በመጠቀም፣ የተመዘገቡ ተቋማዊ ስኬቶችን በማጽናት የግብርናውን ዘርፍ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመድረኩ ተመላክቷል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የኅብር ቀን ዋና ዓላማ የተለያዩ ማንነቶችን በማክበር የጋራ ሀገራዊ እሴቶችን ማጠናከር መሆኑን ገልጸው፣ ተቋሙ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ጥቅም ከሚያረጋግጡ ቁልፍ ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ባለሥልጣኑ በወጪና ገቢ የግብርና ምርቶች ላይ ጥራትና ደህንነትን በማረጋገጥ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገት ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር ባሻገር፣ የዲጂታል ሽግግር ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠሉን ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በዚህም መሠረት ከሚሰጣቸው 462 አጠቃላይ አገልግሎቶች ውስጥ 259 አገልግሎቶች ወደ ዲጂታል ሥርዓት መሸጋገራቸውን ገልጸው፤ ከእነዚህም 156 አገልግሎቶች በቀጥታ ኦንላይን እየተሰጡ መሆናቸውንና 68 አገልግሎቶችን ወደ መሶብ ማዕከል በማስገባት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን በመግለጽ ሌሎች አገልግሎቶችን ዲጂታል ለማድረግ ስራዎች እየተሰሩ መሆንን አስገንዝበዋል፡፡
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን የእጽዋት ሬጉላቶሪ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን በማጽናትና በትብብር አሠራር ላይ በመመሥረት የግብርናውን ዘርፍ የበለጠ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ሁሉም ሠራተኛ ብዝኃነትን በማክበር በሀገር ግንባታ ዙሪያ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል።
ዘጋቢ :-መንበረ ሀይሉ
ፎቶ ግራፍ :- ብርቱካን አዲሱ
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
ዌብሳይት:- http:www.eaa.gov.et
ፌስቡክ:-https:www.facebook.comprofile.phpid=61561829814
ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
ባለስልጣኑ ጳጉሜን 4 የኅብር ቀንን በድምቀት አከበረ
**************************************************************
(አዲስ አበባ፡ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም) — የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ጳጉሜን 4 ታስቦ የዋለውን የኅብር ቀን አመራሩና ሠራተኞቹ በተገኙበት በድምቀት አከበረ።
ባለስልጣኑ ብዝኃነትን እንደ ጸጋና የጋራ ዐቅም በመጠቀም፣ የተመዘገቡ ተቋማዊ ስኬቶችን በማጽናት የግብርናውን ዘርፍ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመድረኩ ተመላክቷል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የኅብር ቀን ዋና ዓላማ የተለያዩ ማንነቶችን በማክበር የጋራ ሀገራዊ እሴቶችን ማጠናከር መሆኑን ገልጸው፣ ተቋሙ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ጥቅም ከሚያረጋግጡ ቁልፍ ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ባለሥልጣኑ በወጪና ገቢ የግብርና ምርቶች ላይ ጥራትና ደህንነትን በማረጋገጥ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገት ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር ባሻገር፣ የዲጂታል ሽግግር ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠሉን ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በዚህም መሠረት ከሚሰጣቸው 462 አጠቃላይ አገልግሎቶች ውስጥ 259 አገልግሎቶች ወደ ዲጂታል ሥርዓት መሸጋገራቸውን ገልጸው፤ ከእነዚህም 156 አገልግሎቶች በቀጥታ ኦንላይን እየተሰጡ መሆናቸውንና 68 አገልግሎቶችን ወደ መሶብ ማዕከል በማስገባት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን በመግለጽ ሌሎች አገልግሎቶችን ዲጂታል ለማድረግ ስራዎች እየተሰሩ መሆንን አስገንዝበዋል፡፡
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን የእጽዋት ሬጉላቶሪ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ወንዳለ ሀብታሙ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን በማጽናትና በትብብር አሠራር ላይ በመመሥረት የግብርናውን ዘርፍ የበለጠ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ሁሉም ሠራተኛ ብዝኃነትን በማክበር በሀገር ግንባታ ዙሪያ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል።
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_12
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
የኅብር ቀን
ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች!
በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል።
እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን።
አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!
#EthiopiaPrevails
+1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 3 ለጽናት ቀን ያስተላለፉት መልዕክት
የጽናት ቀን
ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡
ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን!
#EthiopiaPrevails
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
+1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 3 ለጽናት ቀን ያስተላለፉት መልዕክት
የጽናት ቀን
ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡
ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን!
#EthiopiaPrevails
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ለሁለት ችግረኛ ህፃናት የበዓል የገንዘብ ድጋፍ አደረገ!!
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
አዲስ አበባ -ጳጉሜ 2/2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ውስጥ ለሚገኙና በቋሚነት ሲደግፋቸው ለነበሩ ሁለት ችግረኛ ህፃናት መጪውን በዓል አስመልክቶ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ትግስት ወ/አገኘሁ እንደገለፁት፣ ባለስልጣኑ የጀመረውን በጎ ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል በቀጣይም ድጋፉን አሳድጎ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በወረዳው የህ/መ/ድ/የቀ/ል/እድገት ቡድን መሪ አቶ አለሙ ሀ/ስላሴ በበኩላቸው፣ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለህፃናቱ ላደረገው በጎ ተግባርና ላሳየው አጋርነት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘጋቢ:- ብርቱካን አዲሱ
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
ጳጉሜን 2
የማንሠራራት ቀን
ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!
ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።
#EthiopiaDelivers
ምንጭ :-ጠቅላይ ሚኒስትር ፌስ ቡክ ፔጅ
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
Repost from Ministry of Agriculture-Ethiopia
+9
በበጋ ስንዴ፣ በምግብ ሉዓላዊነትና በሌማት ትሩፋት የተመዘገቡት አኩሪ ውጤቶች የሀገራዊ ነጻነታችንና የጽናታችን ማረጋገጫዎች ናቸው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1/2018 (ግብርና ሚኒስቴር) የጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን “እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ ሃሳብ ሀገራዊ መድረክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ተከፍቷል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከተረጂነት ደግሞ ወደ አምራችነት ተሸጋግራለች።
በሁለንተናዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በፋይናንስ ሥርዓት ዘመናዊነት ያስመዘገበችው መዋቅራዊ ስኬት ለኢንቨስትመንት እና ሀገር በቀል ሀብት ማሰባሰብ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን አመላክተዋል።
ሙሉ ዜናወን ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/1BvsmpzsMv/
#ከማምረትበላይ
#BeyondProduction
---------
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለግብርና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇
📌ድረ-ገጽ፦ www.moa.gov.et
****
📌ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/MoAEthiopia
****
📌ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/@moa-ethiopia
****
📌ቴሌግራም፦ https://t.me/MoAEthiopianews
****
📌ቲዊተር፦ https://x.com/MoA_Ethiopia
****
📌ሊንክድኢን፡- https://shorturl.at/7O6cs
****
📌ቲክቶክ፦ http://www.tiktok.com/@moaethiopia
****
📌ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/moa_ethiopia/
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
የእመርታ ቀን
አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!
#EthiopiaDelivers
ተቋማዊ ስኬት በላቀ አገልግሎት ይገነባል ተባለ፡፡
******************************************************
አዲስ አበባ- ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ሙያዊ ስነ-ምግባር ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጠ።
የግብርና ባለሥልጣን የብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ስራ አስፈጻሚ አሰተባባሪነት ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ተቋማዊ ገጽታ ግንባታ ፣ የአገልግሎት ጥራት፣ ደህንነትና የሥራ ቦታ ንጽህና ለማጠናከር ስልጠና የሰጠ ሲሆን ፤ በስልጠናው ሙያዊ ስነ-ምግባር፣ የደንበኛ አያያዝና አቀባበል፣ የግንኙነት ክህሎት፣ የሥራ ቦታ የደህንነትና ጥንቃቄ፣ በዋናነት ተነስተዋል።
ሠራተኞች የተቋሙን እሴትና ገጽታ በየዕለቱ በተግባር የሚያሳዩ የተቋሙ አምባሳደሮች በመሆናቸው፣ በሚሰጡት አገልግሎት ሙያዊነትን፣ ትህትናንና ተጠያቂነትን እንዲያሳዩ በስልጠናው አቅጣጫ ሰጥቷል።
የስልጠናው ዋና ዓላማም የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን የሥራ ብቃትና ግንዛቤ በማሳደግ፣ ቀልጣፋ፣ ጥራት ያለውና ተገልጋይን ያማከለ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ነው ተብሏል።
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
ተቋማዊ ስኬት በላቀ አገልግሎት ይገነባል ተባለ!
*************************************************************
አዲስ አበባ- ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ሙያዊ ስነ-ምግባር ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጠ።
የግብርና ባለሥልጣን የብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ስራ አስፈጻሚ አሰተባባሪነት ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ተቋማዊ ገጽታ ግንባታ ፣ የአገልግሎት ጥራት፣ ደህንነትና የሥራ ቦታ ንጽህና ለማጠናከር ስልጠና የሰጠ ሲሆን ፤ በስልጠናው ሙያዊ ስነ-ምግባር፣ የደንበኛ አያያዝና አቀባበል፣ የግንኙነት ክህሎት፣ የሥራ ቦታ የደህንነትና ጥንቃቄ፣ በዋናነት ተነስተዋል።
ሠራተኞች የተቋሙን እሴትና ገጽታ በየዕለቱ በተግባር የሚያሳዩ የተቋሙ አምባሳደሮች በመሆናቸው፣ በሚሰጡት አገልግሎት ሙያዊነትን፣ ትህትናንና ተጠያቂነትን እንዲያሳዩ በስልጠናው አቅጣጫ ሰጥቷል።
የስልጠናው ዋና ዓላማም የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን የሥራ ብቃትና ግንዛቤ በማሳደግ፣ ቀልጣፋ፣ ጥራት ያለውና ተገልጋይን ያማከለ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ነው ተብሏል።
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን በሸገር ከተማ ለሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
አዲስ አበባ- ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ፣ ደንበል ጣፎ ወረዳ፣ ወበሪ ቁጥር 1 ቡኡራ ቦሩ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚማሩ ተማሪዎች የማስጀመሪያ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
ይህ ድጋፍ በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆችና ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን ያለ ስጋት እንዲጀምሩና በትምህርታቸው ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መሰሉ ዋጋው እንደገለጹት፤ ግብርናን ማዘመን የሚቻለው በትምህርት የበለጸገ ትውልድ ሲፈጠር በመሆኑ፣ ተቋሙ ከሙያዊ ስራው ጎን ለጎን የነገ ሀገር ተረካቢ ህጻናትን መደገፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የትምህርት ቤቱ አስተዳደር ወ/ሮ ነጢ ኢቲቻ በበኩላቸው የተደረገውን በጎ አድራጎት አድንቀው፣ ለተደረገው ድጋፍ ሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዘጋቢ:- ብርቱካን አዲሱ
ጠንካራ የሬጉላቶሪ ስርዓት ለዘላቂ ዕድገት
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል መረጃዎችን ያግኙ
➜ዌብሳይት:-http:www.eaa.gov.et
➜ፌስቡክ:-https://web.facebook.com/profile.php?id=61561829817494&sk
➜ቴሌግራም:-https:t.meeaapr_1234
